en
Feedback
Ye ortodox tewahido mezmurat

Ye ortodox tewahido mezmurat

Open in Telegram

@✞✟✞

Show more
6 733
Subscribers
+1124 hours
+817 days
+25730 days
Posts Archive
​​እንኳን ለእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም የልደት በዓል በሰላም አደረሳችሁ #መዝ. 86፥1 “መሠረታቲሃ á‹áˆľá‰° áŠ á‹ľá‰Łáˆ­ á‰…á‹ąáˆłáŠ•áĄ- መሠረቶቿ á‹¨á‰°á‰€á‹°áˆą á‰°áˆŤáˆŽá‰˝áŠ“á‰¸á‹â€ ዮም ááˆĽáˆ áŠŽáŠ á‰ áŠĽáŠ•á‰° áˆá‹°á‰ł áˆˆáˆ›áˆ­á‹Ťáˆ በእመቤታችን áˆá‹°á‰ľ áˆáŠ­áŠ•á‹Ťá‰ľá‹›áˆŹ á‹°áˆľ ሆነ፡፡ በግንቦት 1 á‰€áŠ• 5ሺ áЍ5መቶ á‹¨áˆ˜áŠ¨áˆŤá‹ á‹˜áˆ˜áŠ• áˆŠá‹Ťáˆá‰… 15 á‹“áˆ˜á‰łá‰ľ ሲቀሩት/ ሊባኖስ á‰ áˆšá‰Łáˆ ተራራ ከፀሐይ  የምታበራ áˆ´á‰ľ áˆáŒ… á‰°á‹ˆáˆˆá‹°á‰˝áĄáĄ ይህቺውም ááŒĽáˆ¨á‰ľ áˆáˆ‰ á‹°á‰‚ቀ አዳም ሁላቸው ተስፋ ሲያደርጓትና ሲጠባበቋት á‹¨áŠá‰ áˆ¨á‰˝ የድኅነታቸው ምልክት áŠĽáˆ˜á‰¤á‰łá‰˝áŠ• áŠ“á‰ľáĄáĄ ሶሪያዊው áˆŠá‰… á‰…á‹ąáˆľ áŠ¤ááˆŹáˆáˆ  “አክሊለ áˆáŠ­áˆ•áŠ á‹ˆá‰€á‹łáˆšá‰° መድኀኒትነ፡፡ወመሠረተ áŠ•áŒ˝áˆ•áŠ áŠŽáŠ á‰ áˆ›áˆ­á‹Ťáˆ á‹ľáŠ•áŒáˆ:- የመመኪያችን ዘውድ የደኅንነታችን መጀመሪያ የንጽሕናችንም መሠረት በድንግል ማርያም áˆ†áŠáˆáŠ•â€ በማለት መናገሩ ስለዚህ áŠá‹áĄáĄ አክሊል áˆáŠ­áˆáŠ አላት á‹­áˆ…ም áŠ áŠ­áˆŠáˆ የወዲህኛው፣ áˆáŠ­áˆ• á‹¨á‹ˆá‹˛á‹ŤáŠ›á‹ ነው። ከነገሥታት áˆ˜áŠŤáŠ¨áˆ áŠĽáŠ•á‹° á‹łá‹Šá‰ľ á‹¨áŠ¨á‰ áˆ¨ á‹¨áˆˆáˆá˘ ምንም áŠĽáŠ•áŠłáŠ• ቅዱስ ዳዊት á‹¨áŠ¨á‰ áˆ¨ ቢሆን የመመኪያችንን á‹˜á‹á‹ľ ማምጣት አልተቻለውም፡፡ ወቀዳሚተ áˆ˜á‹ľáŠ€áŠ’á‰ľáŠ áŠ áˆ‹á‰ľáĄ- ቀዳሚተ የወዲህኛው áˆ˜á‹ľáŠ€áŠ’á‰ľ የወዲያኛው ነው፡፡ከመሳፍንት á‹ˆáŒˆáŠ• á‹¨áˆšáˆ†áŠ• ኢያሱ áˆáŠ•áˆ á‹¨áˆľáˆ™ ትርጓሜ መድኃኒት ቢሆን á‹¨á‹°áŠ…áŠ•áŠá‰ł መሆን አልተቻለውም፡፡ ወመሠረተ áŠ•áŒ˝áˆ•áŠ áŠ áˆ‹á‰ľ:- መሠረት á‹¨á‹ˆá‹˛áˆ…ኛው፤ áŠ•áŒ˝áˆ• የወዲያኛው ከነቢያተ እግዚአብሔር ወገን የሚሆን áŠ¤áˆá‹Ťáˆľ á‰ á‹ľáŠ•áŒáˆáŠ“ በንጽሕና áˆ˜áŠ–áˆŠ የሚታወቅ áŠá‹áĄáĄ  ነገር áŒáŠ• áˆáŠ•áˆ áŠ•áŒšáˆ• á‹ľáŠ•áŒáˆ á‰˘á‰Łáˆ á‹¨áŠ•áŒ˝áˆ•áŠ“á‰˝áŠ•áˆ˜áˆ áˆ¨á‰ľ áˆ˜áˆ†áŠ• áŠ áˆá‰°á‰ťáˆˆá‹á˘ የመመኪያችን á‹˜á‹á‹ľáŁ á‹¨á‹°áŠ…áŠ•áŠá‰łá‰˝áŠ• መጀመሪያ፤ á‹¨áŠ•áŒ˝áˆ•áŠ“á‰˝áŠ• áˆ˜áˆ áˆ¨á‰ľ á‰…á‹ľáˆľá‰ľ á‹ľáŠ•áŒáˆ áˆ›áˆ­á‹Ťáˆ áŠ“á‰ľá¤â€ á‰ áˆ›áˆˆá‰ľ ተናግሯል። በእርሷ áˆáŠ­áŠ•á‹Ťá‰ľáŠá‰ľ áˆ˜á‹ľáŠ€áŠ’á‹“áˆˆáˆ  የሚፈጽምልንን áŠŤáˆłáŠá‰˘á‹Ťá‰ľáŠ“ á‹¨á‰€á‹°áˆ™ áŠ á‰ á‹ áˆáˆ‰  የእርሷን áˆ˜á‹ˆáˆˆá‹ľ á‰ áŠ“áá‰†á‰ľ áˆ˛áŒ á‰Łá‰ á‰ ነበር። ከነቢያት áŠ áŠ•á‹ą á‹¨áˆ†áА  ኢሳይያስም “የሠራዊት áŒŒá‰ł áŠĽáŒá‹šáŠ á‰Ľáˆ”áˆ­á‹˜áˆ­áŠ• á‰Łá‹Ťáˆľá‰€áˆ­áˆáŠ•  ኖሮ እንደ ሰዶም á‰ áˆ†áŠ•áŠ  እንደ áŒŽáˆžáˆŤáˆ á‰ áˆ˜áˆ°áˆáА ነበር፡፡” በማለት áˆ˜áŠ“áŒˆáˆŠ á‰ áŠĽáˆ­áˆˇ áˆ˜áŒˆáŠ˜á‰ľ  ከጥፋት áˆ˜á‹łáŠ“á‰˝áŠ•áŠ• áˆ˛áŒˆáˆáŒ˝ áŠá‹áĄáĄ  #ኢሳ 1፥9 #ሟር 💚 @ortodoxmezmur 💚 💛 @ortodoxmezmur 💛 ❤️ @ortodoxmezmur ❤️

══●◉ ሆሳዕና ◉●════ ✥ የአብይ ፆም ስምንተኛ ሳምንት ✥ • በመምህር ዶ/ር ዘበነ ለማ • ✥  ክፍል 8 Âś ለመምህራችን ቃለ ህይወት ያሰማልን ╭══•|❀:✧๑♡๑✧❀|: ══╮    @yamazemur_getemoche ╰══•ೋ•✧๑♡๑✧•  ══╯

☞እንኳን ለሰባተኛ የፆም ሳምንት ሰንበተ ኒቆዲሞስ በሰላም አደረሳችሁ፡፡ ☞ኒቆዲሞስ ማለት መዋዔ ሕዝብ ማለት ነው፡፡ ☞ኒቆዲሞስ የአይሁድ መምህርና አለቃ ነው፡፡ ☞ከፈሪሳውያንም ወገን የአይሁድ አለቃ የሆነ ኒቆዲሞስ የሚባል አንድ ሰው ነበረ፡፡ ☞እርሱም በሌሊት ወደ እየሱስ መጥቶ መምህር ሆይ እግዚአብሔር ከእርሱ ጋር ከሆነ በቀር አንተ የምታደርጋቸውን እነዚህ ምልክቶች ሊያደርግ የሚችል የለምና መምህር ሆነህ ከእግዚአብሔር ዘንድ እንደ መጣህ እናውቃለን አለው፡፡ ☞ኢየሱስም መልሶ እውነት እውነት እልሃለሁ ሰው ዳግመኛ ካልተወለደ በቀር የእግዚአብሔርን መንግሥት ሊያይ አይችልም አለው፡፡ ☞ኒቆዲሞስም ሰው ከሸመገለ በኃላ እንዴት ሊወልድ ይችላል? ሁለኛ ወደ እናቱ ማኅፀን ገብቶ ይወለድ ዘንድ ይችላል? አለው ☞ኢየሱስም እንዲህ ሲል መለሰ እውነት እውነት እልሃለሁ ሰው ከውኃና ከመንፈስ ካልተወለደ በቀር ወደ እግዚአብሔር መንግሥት ሊገባ አይችልም፡፡ ከሥጋ የተወለደ ሥጋ ከመንፈስም የተወለደ መንፈስ ነው፡፡ ዳግመኛ ልትወለዱ ያስፈልጋችኃል ሰላልሁ አታድንቅ፡፡ ☞ነፋስ ወደ ሚወደው ይነፍሳል ድምፁንም ትስማለህ ነገር ግን ከወዴት መጣ ወዴትም እንዲሄድ አታውቅም ከመንፈስ የተወለደ ሁሉ እንዲሁ ነው፡፡ ☞ኒቆዲሞስ መልሶ ይህ እንዴት ሊሆን ይችላል አለው? ኢየሱስም መልሶ እንዲህ አለው፡፡ ☞አንተ የእስራኤል መምህር ስትሆን ይህን አታውቅምን?እውነት እውነት እልሃለሀ የምናውቀውን እንናገራን ያየውንም እንመሰክራለን፥ ምክራችንንም አትቀበሉትም፡፡ ☞ ሰለ ምድራዊ ነገር በነገርኀችሁ ጊዜ ካላመናችሁ ሰለ ሰማያዊ ነገር ብነግራችሁ እንዴት ታምናላችሁ? ከሰማይም ከወረደው በቀር ወደ ሰማይ የወጣ ማንም የለም እርሱም በሰማይ የሚኖረው የሰው ልጅ ነው፡፡ ሙሴም በምድረ በዳ እባብን እንደ ሰቀለ እንዲሁ በእርሱ የሚያምን ሁሉ የዘላለም ሕይወት እንዲኖረው እነጂ እንዳይጠፋ የሰው ልጅ ይሰቀል ይገባዋል፡፡ ☞በእርሱ የሚያምን ሁሉ የዘላለም ሕይወት እንዲኖረው እንጂ እንዳይጠፋ እግዚአብሔር አንድያ ልጁን እስኪሰጥ ድረስ ዓለሙን እንዲሁ ወዶአልና፡፡ ☞ዓለም በልጁ እንዲድን ነው እንጂ በዓለም እንዲፈርድ እግዚአብሔር ወደ ዓለም አላከውምና በእርሱ በሚያምን አይፈረድበትም፡፡ በማያ ምን ግን በአንዱ በእግዚአብሔር ልጅ ስም ስላላመነ አሁን ተፈርዶበታል፡፡ ☞ብርሃን ወደ አለም ሰለ መጣ ሰዎችም ሥራቸው ክፈ ነበርና ከብርሃን ይልቅ ጨለማን ሰለ ወደዱ ፍርዱ ይህ ነውና፡፡ ☞ክፍን የሚያደረግ ሁሉ ብርሃንን ይጠላልና ሥራውም እንዳይገለጥ ወደ ብርሃን አይመጣም፡፡ ☞እውነት የሚያደርግ ግን ሥራው በእግዚአብሔር ተደርጎ እንደሆነ ይገለጥ ዘንድ ወደ ብርሃን ይመጣል፡፡(የዮሐንስ ወንጌል ምዕራፍ 3 ከቁጥር 1- 21) ☞ዕድሜ እና ጤና ሰጥቶ ለዚህ ያደረሰን አምላክ ይመስገን፡፡የጭንቅ ደራሿ ድንግል ማርያም በዚህ ሰአት በጭንቅ ላይ ያላችሁ አለሁ ትበላችሁ፡፡ 👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇 @aregawi @aregawi @aregawi

ገብርሔር_ማለት_ምን ማለት_ነው ? ➬ ገብርሔር ማለት ታማኝ አገልጋይ ማለት ነው። ገብርሄር የዓብይ ጾም ሥድስተኛ ሳምንት መጠሪያ ሲሆን ትርጉሙም ታማኝ አገለጋይ ማለት ነው። በዚህ ሳምንት ስለ ገብርሄር( ታማኝ አገለጋይ) እና ገብር—ሃካይ ( ክፉ አገለጋይ) ባርያ : መክሊት ማለትም ስለ፦ ~ባለ አምሥት መክሊት፤የተሰጠው ~ ባለ ሁለት መልክት፤ የተሰጠው እና ~ አንድ መክሊት፤ ሥለተሰጠው ባለ መክሊቶች ከነ ምስጢራቸው በሰፊው ይነገራል። ማቴ፡፳፭፦ "ወደ ሌላ አገር የሚሄድ ሰው ባሮቹን ጠርቶ እንደሰጣቸው እንዲሁ ይሆናልና፤ ለእያንዳንዱ እንደ አቅሙ ለአንዱ አምሥት መክሊት፣ለአንዱም ሁለት ለአንዱም አንድ ሰጠና ወደ ሌላ አገር ወዲያው ኼደ። አምሥት መክሊት የተቀበለው ሄዶ ነገደበት ሌላ አምሥት መክሊትም አተረፈ፣ እንዲሁ ሁለት የተቀበለውም ሌላ ሁለት አተረፈ፤ አንድ የተቀበለው ግን ሄዶ ምድርን ቆፈረና የጌታውን ገንዘብ ቀበረው። ከብዙ ዘመንም በሁዋላ የእነዚያ ባሪዎች ጌታ መጣና ተቆጣጠራቸው ፤ [፩] አምሥት መክሊትየተቀበለውም ቀረበና ሌላ አምሥት መክሊት አስረክቦ ጌታ ሆይ አምሥት መክሊት ሰጥተኸኝ ነበር እንሆ ሌላ አምሥት መክሊት አተረፍኹበት አለው። ጌታውም መልካም አንተ በጎ ታማኝም ባሪያ፡ በጥቂቱ ታምነኻልና በብዙ እሾምኻለሁ ወደ ጌታህ ደስታ ግባ አለው። [፪] ሁለት መክሊት የተቀበለው ደግሞ ቀርቦ ጌታ ሆይ ሁለት መክሊት ሰጥተኸኝ ነበር፤ እንሆ ሌላ ሁለት መክሊት አተረፍኹበት አለው ። ጌታውም መልካም አንተ በጎ ታማኝም ባሪያ፡ በጥቂቱ ታምነኻልና በብዙ እሾምኻለሁ ወደ ጌታህ ደስታ ግባ አለው። [፫] አንድ መክሊትም የተቀበለው ደግሞ ቀርቦ ጌታ ሆይ: ካልዘራህባት የምታጭድ ካልበተንኽባትም የምትሰበስብ ክፋ ሰው መሆንህን አውቃለሁ። ፈራሁም ኼጀም መክሊትህን በምድር ላይ ቀበርኩት። እንሆ መክሊትህ አለህ አለው። ጌታውም መልሶ እንዲህ አለው << አንተ ክፋ እና ሀኬተኛ ባሪያ >> ካልዘራሁባት እንዳጭድ ካልበተንኹባትም እንድሰበስብ ታውቃልህን? ሥለዚህ ገንዘቤን ለለዋጮች አደራ ልትሰጠው በተገባህ ነበር። እኔም መጥቼ ያለኝን ከትርፉ ጋር እወስድ ነበር። ሥለዚህ መክሊቱን ውሰዱበት አሥር መክሊትም ላለው ስጡት ላለው ሁሉ ይሰጠዋልና ይበዛለትማል ከሌለው ግን ያው ያለው እንኳን ይወሰድበታል። የማይጠቅመውንም ባሪያ በውጭ ወዳለው ጨለማ አውጡት በዚያ ልቅሶና ጥርስ ማፋጨት ይሆናል " ማቴ ፳፭፦፲፬-፴ => ውድ ክርስቲያኖች የጨዋይቱ የሳራ የቅድሥት ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ልጆች መክሊታችንን እንወቅ በተሰጠን ጸጋ ቤተክርስቲያንን እናገልግል ፤ ሁላችንም የየድርሻች እንወጣ መክሊቱን ቆፍሮ እንደቀበረው ክፉ አገልጋይ ባርያ በውጭ እንዳንጣል እንትጋ። "እግዚአብሔር በደስታ የሚሰጠውን ይወዳልና እያንዳንዱ በልቡ እንዳሰበ ይስጥ፥ በኀዘን ወይም በግድ አይደለም" ፪ኛ ቆሮ ፱፦፯ "ክፉ ሰው በከንፈሩ ኃጢአት ይጠመዳል ፤ ጻድቅ ግን ከመከራ ያመልጣል። የሰው ነፍስ ከአፉ ፍሬ መልካም ነገርን ትጠግባለች፥ ሰውም እንደ እጁ ሥራ ዋጋውን ይቀበላል። የሰነፍ መንገድ በዓይኑ የቀናች ናት ፤ ጠቢብ ግን ምክርን ይሰማል ። የሰነፍ ቍጣ ቶሎ ይታወቃል ፤ ብልህ ሰው ግን ነውርን ይሰውራል። እውነተኛን ነገር የሚናገር ቅን ነገርን ያወራል ፤ የሐሰት ምስክር ግን ተንኰልን ያወራል። " ምሳ ፲፪፦ ፲፫ " ከሁሉ በሚያንስ የታመነ በብዙ ደግሞ የታመነ ነው ፥ ከሁሉ በሚያንስም የሚያምፅ በብዙ ደግሞ ዓመፀኛ ነው። "ሉቃ ፲፮፦፲ " እንግዲያስ በዓመፃ ገንዘብ ካልታመናችሁ፥ እውነተኛውን ገንዘብ ማን አደራ ይሰጣችኋል?" ሉቃ፲፮፦፲ 👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇 @aregawi @aregawi @aregawi @aregawi

☞#ሱባዔ_ምንድን_ነው⁉ 👉 አንብቡት አጭር ነው📍🙏 ☞ሱባኤ በሰዋሰው ትርጉሙ "ሰባት"ማለት ሲሆን በመንፈስ አተረጋጎም አንድ ሰው ከዚህ ቀን እስከ ዚህ ቀን በጸሎት ከፈጣሪየ ጋር እገናኛለሁ ብሎ የሚያቅደው መንፈሳዊ ዕቅድ ነው ፡፡ ሰባት ቁጥር በእስራኤላውያን ዘንድ በሥራም በቃልም የሚገለጥ ፍጹም ቁጥር ነው፡፡ ለምሳሌ ፦ ፈጣሪ አለማት እግዚአብሔር በሰባተኛው ቀን ሥነ ፋጥረትን ከመፋጠር ማረፋ ፥ለጸሎት የሚተጉ ምዕመናን በቀን ለሰባት ጊዜ ማመስገናቸው የሰባት ቁጥር ፋጹምነት ያመለክታል ፡፡ [ዘፍ 2*2 , መዝ 118*164 ] አንድ ሰው 7 ቀናት ቢጾም "አንድ ሱባኤ ጾመ" ይባላል ፡፡ ☞ #ሱባኤ_መቼ_ተጀመረ ? የተጀመረው ከውድቀት በሓላ በመጀመርያው ሰው በአዳም ነው፡፡ ቅዱሳን መላእክት አዳምን ጸሎት እንዳስተማሩት የቤተ ክርስቲያናችን መዛግብት ያስረዳሉ በምላሹም ከልጅ ልጅህ ተወልጄ ስጋን ለብሼ ከ 5 ቀን ተኩል በኋላ አድንሃለሁ የሚለውን ቃል ኪዳን የሰማው ሱባኤ በመግባቱ ነው፡ ☞ #ሱባዔ_ለምን? የሰው ልጅ ሓጢአት በሚስማማው የሥጋ ሰውነቱ ዘወትር ፈጣሪውን ይበድላል ፡፡ በፈፀመው በደል ኀሊናው ይወቅሰዋል ይጸጸታል ፡፡በመጀመርያ ደፋሮ በሰራው ሀጥያት በኋላ ይደነግጣል ይህ በማንኛውም ሰብአዊ ፋጥረት ኀሊና ውስጥ የሚፈራረቅ ክስተት ነው ፡፡ በዚህ ግዜ የፈጣሪውን ይቅርታ ለማግኝት ያስባል ይተክዛል፡፡ ሰው በደፋርነቱ የኃያሉን አምላክ ትእዛዝ ተላልፎ አለም ሲያስጨንቀው ሸክሙን የሚያቃልልበትና የሚያስወግድበት መንፈሳዊ ጥበብ ከቸሩ ፈጣሪ ተሰጥቶታል፡፡ ይህውም በጥቂት ድካም ሥጋ ያልተወሰነ ጸጋ እግዚአብሔር የሚያገኝበት ሥርዓት ሱባኤ ነው፡፡ ➊ #እግዚአብሔርን_ለመማጸን ፦ ማንኛውም ሰው ሱባኤ ሲገባ በቁርጥ ወደ ፈጣሪው የሚያቀርበው ተማፅኖ ሊኖረው ይገባል ፡፡ ምንም የምንጠይቀው ( የምንማፀነው) ነገር ሳይኖር ሱባዔ ብንገባ የምናገኝው መልስ አይኖርም ፡፡ ስለዚህ ሱባኤ ከመግባታችን በፊት ፦ሱባዔ የምንገባው ለምንድን ነው ? በማለት እራሳችንን መጠየቅ ይኖርብናል ፡፡ ➋ #የቅዱሳንን_በረከት_ለመሳተፍ ቅዱሳን አባቶችና እናቶች የተጋደሉትን ተጋድሎ በማዘከር ቃል ኪዳን በተሰጣቸው ገዳማትና አድባራት የሚገባ ሱባኤ የቅዱሳን በረከት ተካፋይ ያደርጋል፡፡ በጾመ ነብያት የነብያትን ፤ በጾመ ሀዋርያት የሀዋርያትን ፤በጾመ ፋልሰታ የእመቤታችንን በረከት ለመሳተፋ ሱባኤ መግባት የነበረ ነው፡፡ ☞ #የሱባኤ_አይነቶች 1 የግል ሱባኤ ( ዝግ ሱባኤ) ፦ አንድ ሰው ብቻውን አመች ቦታ ማንም ሳያየው በግሉ የጸሎት በአቱን ዘግቶ በሰቂለ ኀሊና ሆኖ ፈጣሪው ብቻ እንዲያየው በኀቡዕ የሚፈፅመው ሱባኤ ነው ፡፡ 2 ,የማህበር ሱባኤ ፦ ካህናት ምዕመናን ወንዶች ሴቶች ሽማግሌወች ፤ወጣቶች ፤በአንድ ሆነው በቤተ ክርስትያንና አመች በሆኑ ቦታወች ሁሉ ተሰብስበው የሚገብት ሱባዔ ነው፡፡ 3 , የአዋጅ ሱባዔ ፦ በሀገር ላይ ድንገተኛ አደጋ ፤ አባር ቸነፈር ጦርነት ሲነሳ እንዲሁም በማህበረ ምዕመናን ላይ አስጊ የሆነ መቅሰፋት ሲከሰት እግዚአብሔር መዓቱን በምህረት ቁጣውን በትዕግስት እንዲመልስ የሚያዝ የሱባዔ አይነት ነው፡፡ ☞ቅድመ_ዝግጅት ሱባኤ ከመግባታችንም ሆነ ከገባን ግዜ እንዲሁም ከጨረስን በኋላ ምእመናን ቅድመ ዝግጅት ማድረግ ይገባናል ፡፡ ➊ #ሱባኤ_ከመግባት_አስቀድሞ ፩ በመጀመርያ ሱባዔ የምንገባበትን ምክንያት ለይቶ ማወቅ ያስፈልጋል ፡፡ ፪ ሱባኤ ለመግባት የወሰንበትን ምክንያት ከለየን በኋላ ምክንያታችንን ይዘን የንስሃ አባታችንን ማማከር ያስፈልጋል፡፡ ፫ ለምን ያህል ቀናት መቆየት እንዳለብን መወሰን ያስፈልጋል ፡፡ሱባኤ ከዚህ እስከዚህ እቆያለሁ ብለን ዕቅድ የምንይዝበት ነው፡፡ ፬ ወቅትና ቦታ መምረጥ ተገቢ ነው፡፡በቤተ ክርስቲያናችን በአብዛሀኛው ግዜ ሱባኤ የሚገባው በአጽዋማት ወቅት በመሆኑ ይህንን መለየት ነው ፡፡ምክንያቱም በጾም ወቅት ብዙ አባቶች ጸሎት የሚይዙበት ስለሆነ ፀሎታችን ከእነርሱ ጋር አብሮ ያርግልናልና ነው፡፡ እዚህ ላይ በማንኛውም ግዜ ሱባኤ አይያዝም ለማለት አይደለም በማንኛውም ግዜ ፈተና ያጋጠመው ሰው ሱባዔ ሊይዝ ይችላል፡፡ ➋ #በሱባኤ_ግዜ ሀ. በጸሎት ሰአት ዓምድና ግድግዳ ሳይደገፉ መቋሚያ ሳይዙ በሁለት እግር ቀጥ ብሎ በመቆም መጸለይ ይኖርብናል፡፡ እንዲሁም ፊትን ወደ ምስራቅ መልሶ መቆም ወደ ግራ ወደ ቀኝ አለመዟዟር በሰቂለ ህሊና ኾኖ መጸለይ ይገባል፡፡ ለ . በቅደም ተከተል መፀለይ ይገባል በመጀመርያ አአተብ ከሚለው ተጀምሮ አቡነ ዘበሰማያትን ጠቅሶ ጸሎተ ሀይማኖትን መጨረስ ፡፡ሰግዱ እና ስለ መስቀል በሚያነሳው ላይ እየሰገዱና እያማተቡ መጸለይ ፡፡ በማስቀጠል አቡነ ዘበሰማያት ፤መዝሙረ ዳዊት ውዳሴ ማርያም ሌሎችንም ማስከተል ከዚያ 41 ግዜ ኪራላይሶ ይባላል ፡፡ ሐ. በሱባዔ ግዜ ከተሐራሚው የሚጠበቀው ነገር ሐጢአቱን እያሰበ ማዘን ማልቀስ ለእያንዳንዱ በደል ማልቀስ ማዘን ይገባዋል ፡፡ መ. በመጨረሻም ሱባዔ የገባው ሰው ሱበዔውን ሳይጨርስ ወይም አቋርጦ ከማንኛውም ሰው ጋር ፈፅሞ መገናኝት የለበትም ፡፡ ➌ #ከሱባዔ_በኋላ ላቀረብነው ተማፅኖ እግዚአብሔር የሚያደርግልንን ነገር መጠበቅ ይኖርብናል ፡፡ "ሱባዔ" የገባ ሰው ሁሉ ራዕይ ላያይ ይችላል፡፡ምክንያቱም የእግዚአብሔር መልስ አሰጣጥ ለማንም ግልጽ አይደለም ፡፡ ከሱባዔ በኋላ መጀመሪያ የምናገኝው የህሊና ሰላም ነው ፡፡ ይህ ትልቅ የአምላክ ስጦታ ነው ፡፡ ከዚህ ባሻገር ሱባኤ ገብተን ያሰብነውን ካላገኝን ዳግመኛ ተዘጋጅተን እስከ መጨረሻው ሰዓት በመማፀን መጽናት ይኖርብናል፡፡፡ ወስብሐት ለእግዚአብሔር ወለወላዲቱ ድንግል ወለመስቀሉ ክብር አሜን ይቆየን 🙏 ተቀላቀሉ ቴሌግራም 👉@aregawi 👉@aregawi 👉@aregawi 👉@aregawi

☞እመቤታች ድንግል ማርያም ሆይ ☞መልካሚቱ ምድር ድንግል ሆይ ከጤነኞችም ይልቅ እኛ ሕሙማን እንሻሸለን፡፡ አንቺ የሕሙማን መድኃኒት ነሽና፡፡፡ ☞እመቤታችን ድንግል ማርያም ሆይ ከጻድቃን ይልቅ እኛ ኃጢኣን እንወድሻለን፡፡ ንሥሓ ለሚገቡ ኹሉ አንቺ አማላጃቸው ነሽና፡፡ ☞እመቤታችን ድንግል ማርያም ሆይ ከብዑላን ይልቅ እኛ ነዳያን እንወድሻለን፡፡ አንቺ የተቸገሩ መነሻ ነሽና፡፡ ☞እመቤታችን ሆይ ከፍሡሓን ይልቅ እኛ ኅዙናን እንወድሻለን የተከዙት ደስ የምታሰኚ ነሽና፡፡ ☞እመቤታችን ሆይ ከክቡራኑም ይልቅ እኛ የተናቅን እንወድሻለን አንቺ ለተናቁ ሞገሳቸው ነሽና፡፡ ☞እመቤታችን ድንግል ማርያም ሆይ ዓለም የሚጠላን እኛ ክርስቲያን እንወድሻላን አንቺ የተጠሉትንና የተናቁትን የምትወጂ ነሽና፡፡ ☞እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ሆይ ንጹሓን የአይደለን እኛ ኃጢአትን የፈጸምን በደለኞች ልጆችሽ እንወድሻለን በኃጢአት ለተዳደፋ አንቺ በአማላጅነትሽ የሚነጹ ብሽ ነሽና፡፡ ☞ጠቢባን የእይደለን ሰነፎች እኛ እንወድሻለን የሰነፎች ጥበባቸው አንቺ ነሽና፡፡ ☞ብርቱዎች የአይደለን እና ደካሞች እንወድሻለን የደካሞች ኃይላቸው አንቺ ነሽና፡፡ ☞የአልጠገብን እኛ ርኁባን ልጆችሽ እንወድሻለን የርኁባን ጥጋብ በረከታቸው አንቺ ነሽና፡፡ ☞እመቤታችን ድንግል ማርያም በመታመን ለለመነሽ ጩኹቱን የምትሰሚ የማዳን ደጃፋ የይቅርታ በር አንቺ ነሽ፡፡ አሁንም በአማላጅነትሽ አምነው ለሚጠሩሽ ለሚማጸኑሽ ፈጥነሽ ድረሺ፡፡ ☞(ከእመቤታችን ወዳጅ ከአባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ ድርሰት ከሆነው"ዕንዚራ ስብሐት"ድረሰት የተወሰደው፡፡ ☞@aregawi 👉@aregawi 👉@aregawi 👉@aregawi

☞የካቲት 16 ቀን ኪዳነ ምህረት እናታችን የምህረት ቃል ኪዳን የተቀበለችበት አመታዊ በዓሏ በሰላም አደረሳችሁ፡፡ ☞"ከመረጥኩት ጋር ቃልኪዳኔን አደርጋለሁ"መዝ 88፥3 ☞እመቤታችን ከጌታ ዕርገት በኃላ በዮሐንስ ቤት የኖረችው 15 ዓመት ነው፡፡ ☞እነዚያን ዓመታት ያሳለፈቻቸው የልጇ መቃብር በነበረው በጎልጎታ መቃብር ላይ በሚገኘው ሥፍራ ላይ ቆማ በመጸለይ ነበር፡፡ ☞ከዕለታት በአንዱ የካቲት 16 ቀን አብርሃም ይሰሃቅ ያዕቆብና ጻድቃን ነቢያት ያሉበትን ቦታ ያሳዩአት ዘንድ መላእክትን እመቤታችንን ወደ ሰማይ ወሰዷት ደጋግ አባቶች እናቶች ያሉበትን የሰላም ሥፍራ አሰጎበኛት፡፡ እጅግም ተደ ሰተች እግዚአብሔር አመሰገነች፡፡ ☞የዲያቡሎስና የኃጥአንን መኖሪያ ቅዱሳን መላእክት ሊስጎበኛት ወሰዷት ነፍሳት በጨለማ በእሳት ውስጦ እጅግ በሚከብድ ሁኔታ ውስጥ ሆነው አየች፡፡ ☞እጅጎም አዘነች አለቀች በመጨረሻም መላአክት ወደ ቦታዋ መለሷት፡፡ ☞ይህን አሰቃቂ የኩነኔ ቦታ እና የኃጥአንን ነፍሳት ወደ ቦታዋ መለሷት፡፡ይህን አሰቃቂ የኩነኔ ቦታ እና የኃጥአን ነፍሳት ስቃይ ካየች በኃላ በጎልጎታ በጌታ መቃብር ላይ ቆማ ስለ ኃጥአን ስታማልድ ኖረች፡፡ ☞"ልጄ ሆይ በባሕርይ አባትህ በእግዚአብሔር በአብ፤ በባሕር ሕይወትህ በመንፈስ ቅዱስ፤ ክርስቶስ በተባለው ስምህ ፤ ዘጠኝ ወር በተሸከመችህ ማኅፀኔ፤በጠባሃቸው ጡቶቼ፤ በሳሙህ ከንፈሮቼ፤ባቀፋህ እጆቼ በተሸከመህ ጀርባዬ፤ ተወልደህ በተኛህበት በረት፤ በተጠቀልልከበት ጨርቅ ከአንተ ጋር በስደት በተመላለሱ እግሮቼ እማጸንሃለሁ እለምንሃለሁ ☞ልመንዬን ሰምተህ የልቦናዬን ፈቃድ ትፈጽምልኝ ዘንድ እለምንሃለሁ፡፡ ☞አሁንም ፍጹም ልመናዬን አድምጥ እኔ እናትህ ባርያህም የምንግርህ የልመናየን ነገር ስማ፡፡ ☞ተዝካሬን የሚያደርግ ቤተ ክርስቲያንም በስሜ የሚሠራ በስሜ የታረዘ የሚያለብስ የታመመ የሚጎበኝ የተራበ የሚያበላ የሚያጠጣ ወይም ያዘነ የሚያረጋጋ ቢሆንም የተከዘን ደስ የሚያሰኝ ወይም ምስጋናዬን የጻፈ፡፡ ☞ሴት ልጁንና ወንድ ልጁን በኔ ስም የጠራውንም እኔም በምከብርበት ቀን ምስጋና ያመሰገነውን አቤቱ ዓይን ያላየውን ፤ጆሮም ያለሰማውን በሰው ልቡና ያልታሰበውን በጎ ዎጋ ስጠው፡፡ ☞አቤቱ በኔ ቃል ኪዳነ ሰላመነ ሁሉ እማልድሃለሁ እለምንሃለሁ መራቤን መጠማቴን ካንተ ጋር እንዳንተ መከራንም ሁሉ አሰበህ አቤቱ ወደ ሲኦል ከመውረድ ነፃ የወጣ አድርገው ☞ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስም የለመንሽው ሁሉ ይደረግልሻል የምትወጂውን ሁሉ እፈጽምልሻለሁ የለመንሽውን ሁሉ ላደርግልሽ ሰው ሁኜ አለሁና፡፡ ☞መሓለየን እንዳላፈርስ አማኑኤል ብዬ በራሴ ማልሁልሽ፡፡ ☞አምላክን የወለደች በድንጋሌ ሥጋ በድንጋሌ ነፍስ የፀናች የክብር እመቤታችን ስጦታ የሚሆን የማኅፀንዋን ፍሬ ኑ እዩ፡፡ ☞ወዳጆቿም የምትሆኑ ደስ የሚያአሰኝ ይህን ድንቆ ኪዳን ቸርነትንና በጎነትን "ያዘ ጌቴ በሰማይና በምድር ያለ ሁሉ ስሟን በመጥራት ይድን ዘንድ የሰጣትንም ድንቅ የሚሆን መሓላን ታዩ ዘንድ ኑ፡፡ ☞በጎ ሥራ ሳይሠሩ ሕግጋቱን ሳይጠብቁ መዳን የሱ ፍርድ ምን ይረቅ? ☞(ድርሳነ ኪዳነ ምህረት) ☞በዚህ ቃል ከዳን ስምዖን (በላየ ሰብዕ) ድኖበታል፡፡ ☞እኛንም የእናታችን የእመቤታችን የቃልኪዳኗ ተከፍይ ያድርን፡፡ 👉የቴሌግራም ቻናላችንን ይቀላቀሉ 👉@aregawi 👉@aregawi 👉@aregawi

 âœž ዘወረደ "በእርሱ ፍቃድ" በእርሱ ፍቃድ በአባቱ ፍቃድ በመንፈስ ቅዱስ ፍቃድ ከሰማያት ወረደ ከድንግል ማርያም ተወለደ ዓለሙን እንዲሁ ወደደና ከሰማያት በላይ ወረደና በአጭር ቁመት በጠባብ ደረት ተወሰነ አምላከ አማልክት ከሰማያት የወረደው ፍቅር ስቦት የመጣዉ ወልደ አብ ወልደ ማርያም ኢየሱስ ፈራጅ ነዉ አዝ ቅድመ ዓለም ተወልዶ ያለ እናት ድህረ ዓለምም ያለ አባት የእግዚአብሔር ልጅ በእርግጥም ሰው ሆነ ሁሉ በእርሱ ይኸው ተከናወነ ከሰማያት የወረደው ፍቅር ስቦት የመጣዉ ወልደ አብ ወልደ ማርያም ክርስቶስ አምላክ ነዉ አዝ የማይታይ ታየ በምድር ረቂቁ ገዘፈ ስለፍቅር ሥጋን ተዋህዶ ሆነልን ፈውስ አማኑኤል የነገስታት ንጉሥ ከሰማያት የወረደው ፍቅር ስቦት የመጣዉ ወልደ አብ ወልደ ማርያም እግዚአብሔር እርሱ ነዉ     ዲ/ን ቀዳሜጸጋ 💚 @ortodoxmezmur 💚 💛 @ortodoxmezmur 💛 ❤️ @ortodoxmezmur ❤️

ዐቢይ_ጾም ዐቢይ ለምን ተባለ ቢሉ ‹‹ዐበየ›› ማለት ከፍ አለ ማለት ሲሆን ከዚህም ግስ ዐቢይ የሚለው ቅጽል ይገኛል፡፡ዐቢይ ማለት ከፍ ያለ ትልቅ ማለት ነው፡፡ ዐቢይ ጾም የተባለበት ምክንያት፡- ሀ. ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የጾመው ጾም       ስለሆነ ለ. በቀኑ ቁጥር ከሌሎች አጽዋማት የሚበልጥ ስለሆነ ሐ. ሦስቱ ታላላቅ የሰይጣን ፈተናዎች ማለትም              ➛ ትዕቢት              ➛  ስስት              ➛  ፍቅረ ነዋይ ድል የተመቱበት ስለሆነ ነው፡፡ በቤተክርስቲያን ስያሜ መሰረት በዐቢይ ጾም ውስጥ የሚውሉ ሰንበታት እያንዳንዳቸው መጠሪያ ስም ሲኖራቸው እነርሱም፡- ዘወረደ የዐቢይ ጾም የመጀመሪያው ሰንበት ሲሆን ይህም ቅድመ ዓለም የነበረ ዓለምን ፈጥሮ የሚኖር አልፋና ኦሜጋ ከሰማየ ሰማያት መውረዱንና ከእመቤታችን ከቅድስተ ቅዱሳን ከንጽሕተ ንጹሐን ከድንግል ማርያም መወለዱን የሚያመለክት ሥያሜ ነው፡፡ ቅድስት ይህ የሁለተኛው ሰንበት ስያሜ ሲሆን የተባለበትም ምክንያት ሾለ ዕለተ ሰንበት ቅድስና ስለሚያወሳ ነው፡፡ እንዲሁም ይህ ዕለት ዕለተ እግዚአብሔር የተባለች የሰንበት ክርስቲያን ቅድስናን ያመለክታል ምክንያቱም የዚች ዕለት ጌታ እርሱ ቅዱስ እግዚአብሔር ነውና ስለዚህም ዕለተ ሰንበት ቅድስት ተብላለች፡፡ ምኩራብ ይህ የሦስተኛው ሰንበት ስያሜ ሲሆን በዚህ ሰንበት ጌታ በመዋዕለ ትምህርቱ በምኩራብ ገብቶ ማስተማሩ ይነገራል፡፡ እንዲሁም ይህች ዕለት መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በምኩራብ ገብቶ እንዳስተማረ የሚታሰብበት ዕለት ነው፡፡ ምኩራብ ማለት የቤተ አይሁዳውያን የጸሎት ቤት ነው፡፡ መጻጉዕ ይህ የአራተኛው ሰንበት መጠሪያ ሲሆን ይህም ዕለት ጌታችን አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ድውያንን መፈወሱ እውራንን ማብራቱ ለምጻምን ማንጻቱ ሽባዎችን መተርተሩ የሚያነሳ መዝሙር የሚዘመርበት እንዲሁም እነዚህ ሁሉ ድንቅ ገቢራተ ታምራቶች የሚዘከሩበት ዕለት ነው፡፡ ደብረ_ዘይት ይህ የአምስተኛው ሰንበት መጠሪያ ሲሆን ይህም ዕለት ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በደብረ ዘይት ተራራ ላይ ሆኖ ነገረ ምጽአቱን እንዳስተማረ የሚወሳበት ሰንበት ነው፡፡ ደብረ ዘይት ማለት ወይራ የበዛበት ተራራ ማለት ነው፡፡ ገብርኄር ይህ የስድስተኛው ሳምንት ሰንበት ስያሜ ሲሆን ይህም ዕለት ለጌታው ታማኝና በጎ የሆነው ባርያ ወደ ጌታህ ደስታ ግባ ተብሎ እንደተመሰገነ የሚነገርበት ዕለት ነው፡፡ ኒቆዲሞስ ይህ የሰባተኛው ሰንበት ስያሜ ነው፡፡ ይህም ዕለት ኒቆዲሞስ የተባለው የአይሁድ መምህር በሌሊት ወደ ጌታው ወደ ኢየሱስ ክርስቶስ እየመጣ ይማር እንደነበረ ይታሰብበታል በዚም ዕለት የኒቆዲሞስን ታሪክ የሚያስታውስ መዝሙር ይዘመርበታል፡፡ ሆሳዕና ይህ የስምንተኛው ሳምንት ሰንበት መጠሪያ ሲሆን ይህም ዕለት በነቢዩ በዘካርያስ ላይ የተጻፈው ትንቢት ይፈጸም ዘንድ ጌታችም መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በአህያይቷ እና በውርንጭላይቷ ላይ ተቀምጦ ሆሳዕና በአርያም ሆሳዕና ለዳዊት ልጅ ተብ እየተመሰገነ ወደ ቤተ መቅደስ መግባቱ የሚተሰብበት ዕለት ነው፡፡ ሆሳዕና ማለት ‹‹እባክህ አሁን አድን አሁን ባርከን›› ማለት ነው፡፡በሰሙነ ሕማማት ጸሎተ ፍትሃት ጸሎተ አስተስርዮ ስለማይፈጸም ጸሎተ ፍትሃትና አስተስርዮ የሚደረገው በዚሁ ዕለት ነው::                ጾሙን የበረከት ጾም ያድርግልን፡፡ ለኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ልጆች👇                 •➢ ሟር // SHARE 💚  https://t.me/aregawi

#መከራው_ክርስትናዬን_አጣፈጠው ✞ መከራው ክርስትናዬን አጣፈጠው ስደቱ ማህተቤን አጠበቀው በሞት መንደር በሀዘን ውስጥ በመከራ አየውት እግዚአብሔርን ከኔ ጋራ ክርስትያን ተብለን በክርስቶስ ስም የተጠራነው በጥልቁ ውስጥም በእግዚአብሔር እንድናምን ነው ለጥቂት ግዜ ቢበረታብን ስደት ሀዘኑ አምላክ ግን መውጫ ያዘጋጃል በዚህ ተፅናኑ #አዝ በስደት ሳለን ካፋችን ቢደርቅ የፅዮን ዜማ ከወንዙ አጠገብ ቁጭ ብለን ሰለን ድምፁን ሳንሰማ በእግዚአብሔር ጊዜ ከባቢሎን ምድር እንለቃለን መሰንቆአችንን ከአርያም ዛፍ ላይ እናወርዳለን #አዝ ደካሞች ሲሉን በስሙ ያን ጊዜ እንበረታለን ድሆች ስንባል ባለጠጎች እናደርጋለን በምድር ቅዱስ ህዝብ አድርጎ ለእርሱ ለየን ጨለማው አልፎ በቸርነቱ ብርሀን አሳየን #አዝ ከፀጋ በላይ እንዳንፈተን ይከልለናል በቁስላችን ላይ የፈውስን ዘይት ያፈስልናል በጊዜም ቢሆን ያለ ጊዜውም በእርሱ እንፅና እንኳን ስደቱን ሞቱን ሊገታው ይችላልና ሊቀ-መዘምራን ዲያቆን ቴድሮስ ዮሴፍ 💚 @ortodoxmezmur 💚 💛 @ortodoxmezmur 💛 ❤️ @ortodoxmezmur ❤️

በሻሸመኔ ከተማ ሰማዕትነትን የተቀበሉ ኦርቶዶክሳውያን ቁጥር ሁለት ደረሰ! በሻሸመኔ ከተማ ሰማዕትነትን የተቀበሉ ኦርቶዶክሳውያን ቁጥር ሁለት የደረሰ ሲሆን በአራቱ ላይ ደግሞ ከፍተኛ ጉዳት እንደደረሰባቸው ተገለጸ። አብያተ  ክርስቲያናት ውስጥ ያሉት ምእመናን እስካሁን ድረስ በቅጽር ግቢ ውስጥ እንዳሉ ናቸው። ነገር ግን አሁን ላይ ወደ ቤተ ክርስቲያን የሚመጣውን የጸጥታ ኃይል አባላት በዱላ እያባረሩ ይገኛሉ። የከተማዋ የኦሮሚያ ልዩ ኃይል አካላት ከኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ምእመናን ውጪ ላሉት የከተማዋ ነዋሪዎች ነጠላ በማደል ሻሸመኔ ስታዲዮም ተገኝተው ሕገ ወጡን ቡድን እንዲቀበሉ እያስተባበሩ ያሉ ሲሆን በመኪና ከተማውን እየዞሩ ቅስቀሳ በማድረግ ላይ ይገኛሉ። በዚህ ሰዓት የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ከሻሸመኔ እስከ አርሲ ነገሌ ድረስ ያለውን ቦታ ተቆጣጥሯል። ምንጭ: እውነተኛ የተዋሕዶ ድምፅ ------------------------------------------- ሌሎችን ለማግኘት 👇👇👇👇👇👇👇👇👇 @orthodoxtewahdo14 @orthodoxtewahdo14 @orthodoxtewahdo14 ለተዋህዶ ልጆች መረጃዉን ያጋሩ!!! #share