መካነ ቅዱሳን አቡነ አረጋዊ ወ አቡነ በትረማርያም ፍሬ ኃይማኖት ሰ/ት/ቤት
Open in Telegram
* መዝሙሮችን ❖ ትምህርቶችን ❖ መንፈሳዊ ምስሎችን ❖ መንፈሳዊ ፅሁፎችን ያገኛሉ :: Join በማለት ይ🀄️ላ🀄️ሉን Group- https://t.me/+5YBXXnHzFK01Nzk0 Channal- https://t.me/@aqlecia tube ይቀላቀሉን
Show more336
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days
Data loading in progress...
Similar Channels
No data
Any problems? Please refresh the page or contact our support manager.
Tags Cloud
No data
Any problems? Please refresh the page or contact our support manager.
Incoming and Outgoing Mentions
---
---
---
---
---
---
Attracting Subscribers
October '23
October '23
+3
in 0 channels
September '23
+7
in 0 channels
Get PRO
August '23
+5
in 0 channels
Get PRO
July '23
+16
in 0 channels
Get PRO
June '23
+15
in 0 channels
Get PRO
May '23
+25
in 0 channels
Get PRO
April '23
+18
in 0 channels
Get PRO
March '23
+47
in 0 channels
Get PRO
February '23
+43
in 0 channels
Get PRO
January '23
+21
in 0 channels
Get PRO
December '22
+29
in 0 channels
Get PRO
November '22
+38
in 0 channels
Get PRO
October '22
+15
in 0 channels
Get PRO
September '22
+13
in 0 channels
Get PRO
August '22
+231
in 0 channels
| Date | Subscriber Growth | Mentions | Channels | |
| 12 October | 0 | |||
| 11 October | 0 | |||
| 10 October | +1 | |||
| 09 October | +1 | |||
| 08 October | 0 | |||
| 07 October | 0 | |||
| 06 October | +1 | |||
| 05 October | 0 | |||
| 04 October | 0 | |||
| 03 October | 0 | |||
| 02 October | 0 | |||
| 01 October | 0 |
Channel Posts
#የብፁዓን_አባቶች_የአዲስ_ዓመት_መልዕክት
የጥፋት መሳሪያችሁንም አስቀምጣችሁ ወደ ሰላም ማድ ቀርባችሁ በወንድማማችነት መንፈስ ችግራችሁን በክብ ጠረጴዛ በውይይት በመፍታት የሀገሪቱንና የሕዝቡን አንድነት እንድታስቀጥሉ ሁሉን በሚያይ እግዚአብሔር ስም እንማጸናችኋለን፡፡"
(ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ፓትርያርክ)
"ትናንት የነበረው ችግር እንዳይደገም ሁሉም በየአለበት ለአብሮነትና ለሰላም ቅድሚያ በመስጠት ችግሮቻችንን ሁሉ በመደማመጥና በመግባባት በመፍታት ለሀገራዊ አንድነት ትኩረት መስጠት አለብን"
(ብፁዕ አቡነ ቀሌምንጦስ ሊቀ ጳጳስ)
"ዘመኑን መልካም የምናደርገው በዘመኑ መካከል ራሳችንን ለበጎ ነገር ዝግጁ ስናደርግ እና ከኃጢአት ተመልሰን አዲስ ለመሆን ዝግጁ ስንሆን ነው"
(ብፁዕ አቡነ ሄኖክ ሊቀ ጳጳስ)
"ባለፈው ዘመን ተለያይተን እርስ በእርስ የተጋጨንባቸውና ያለያዩንን ጉዳዮች በአዲሱ ዘመን በእርቅና በአንድነት ካልተካናቸው አዲስ ዘመን ብለን ማክበራችን ትርጉም አይኖረውም"
(ብፁዕ አቡነ ዮሴፍ ሊቀ ጳጳስ)
"ይህን ክፉ ዘመን በሚገባ አውቀንና ተረድተን ከክፉው ዘመን ጋር ተጠቅልለን ሳንጠፋ ዛሬን ለንስሐ ፤ ነገን ለአዲስ ሕይወት እንድንዘጋጅ ጥላቻውን በፍቅር ለውጠን ይህን አዲስ ዘመን ተቀብለን ልናከብረውም ልንከብርበትም ይገባል"
(ብፁዕ አቡነ ናትናኤል ሊቀ ጳጳስ)
| 2 | ✝ቅዱስ ሩፋኤል✝
እንኳን ለርኅወተ ሰማይ፣ ለቅዱስ ሩፋኤል፣ መልከ ጼዴቅ፣ ዘርዓ ያዕቆብና ሰራጵዮን ዓመታዊ በዓል በሰላም አደረሳችሁ፤ አደረሰን።
†††በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!
🙏ይህች ዕለት የሰዎች ሁሉ ጸሎት የሚያርግባት፣ አራተኛው መጋቢ ኮከብ የሚያልፍባት፣ ለሰው ልጆች ከፈጣሪያቸው ጸጋ በረከት የሚሰጥባት ዕለት ስለሆነች "ርኅወተ ሰማይ - ሰማይ የሚከፈትባት ቀን።" ትባላለች።
🙏አሁን በሰማይ መዘጋት መከፈት ኑሮበት አይደለም። የሰው ልጆችን ልመና ቅዱሳን መላእክት ያለ ከልካይ የሚያሳርጉበት አንድም ቅዱስ ሩፋኤል የዓመቱን የጸሎት መዝገብ የሚከፍትበት ቀን ስለሆነ እንዲህ ተባለ እንጂ።
🙏እመቤታችን ድንግል ማርያም ለአጼ ናዖድ እንደ ነገረቻቸው በዚህች ዕለት ሁሉም ቅዱሳን ስለሚታሰቡ የእግዚአብሔር የምሕረት መዝገቡ ስለሚከፈት ዕለቷን ክብርት ያሰኛታል። በቅዱስ ሩፋኤል አበጋዝነት (መሪነት) በዚህች ዕለት ለዓመት የሚበቃ ምሕረት ይገኛል።
🙏ስለዚህም አባቶቻችን በዚህች ሌሊት ሦስት መቶ ስልሳ አምስት አቡነ ዘበሰማያትን ሲጸልዩ ያድራሉ። በሌላ ወገን ደግሞ የጌታ ዳግም ምጽዓቱ መታሰቢያ እንደ መሆኗ ትልቅ ትኩረትም ይሰጣታል።
ቸሩ ጌታችን ከተከፈተች ገነት ከተነጠፈች ዕረፍት ሁላችንንም ያድርሰን።
✝ ቅዱስ ሩፋኤል ሊቀ መላእክት
🙏ቅዱስ ሩፋኤል በቤተ ክርስቲያን አስተምሕሮ ከሰባቱ ሊቃነ መላእክት በደረጃው ሦስተኛ ነው። በመጀመሪያዋ ዕለተ ፍጥረት እግዚአብሔር መቶ ነገደ መላእክትን ፈጥሮ በአሥር ከተማ ሲያኖራቸው የቅዱስ ሩፋኤል ዕድል ፈንታው ራማ ሆነች።
🙏በዚያም "መናብርት" ተብለው ለሚጠሩ አሥሩ ነገድ አለቃ (መሪ) ሆኖ በፈጣሪው ተሹሟል። በኋላም "መጋብያን" በሚባሉ በሃያ ሦስቱ ነገድ ላይ ሹሞታል። ይህች ዕለትም በዓለ ሲመቱ ናት።
🙏አንድ ቀን ጌታችን ክርስቶስ በደብረ ዘይት ተቀምጦ ሳለ ሐዋርያቱ ቅዱስ ሩፋኤልን እንዲያስተዋውቃቸው ለመኑት። ጌታም ሦስቱን ሊቃናት (ሚካኤል፣ ገብርኤልና ሩፋኤል) ይመጡ ዘንድ አዘዛቸው።
🙏ቀጥሎም ቅዱስ ሩፋኤልን "ክብርህን ንገራቸው።" አለው። እርሱም ለጌታ ሰግዶ ለሐዋርያት ብዙ ምሥጢር ነገራቸው። በተለይ ስሙን ለሚጠሩ መታሰቢያውን ለሚያከብሩ የሚደረገውን ጸጋ አብራርቶላቸው ዐረገ።
🙏በመጽሐፈ ጦቢት ላይ ተጽፎ እንደምናገኘው ቅዱሱ መልአክ ሰው (አዛርያን) መስሎ ጦብያን ለትዳር አብቅቶ፣ ሣራን አስማንድዮስ ከሚባል ሰይጣን አድኖ የጦቢትን ዓይን አብርቷል። በገድላተ ቅዱሳን እንደምናየውም ለብዙ ቅዱሳን ረዳታቸው ሆኖ ገድላቸውን አስፈጽሟል።
🙏 ይህች ጳጉሜ ፫ ቀን ለቅዱስ ሩፋኤል ቅዳሴ ቤቱም ናት። በአራተኛው መቶ ክፍለ ዘመን በቅዱስ ቴዎፍሎስ ዘእስክንድርያ አማካኝነት ቤቱ ታንጿል። የሚገርመው ደግሞ የታነጸው በዓሣ አንበሪ ጀርባ ደሴት ላይ ነው። በመልአኩ አጋዥነትም ለሦስት መቶ ዓመታት አገልግሏል።
✝ቅዱስ ሩፋኤል በእነዚህ የክብር ስሞች ይጠራል:
መስተፍስሒ (ልቡናን ደስ የሚያሰኝ)፣
አቃቤ ሥራይ (ባለ መድኃኒት ፈዋሽ)፣
መዝገበ ጸሎት (የጸሎት መዝገብ መክፈቻ የተሰጠው)፣
ሊቀ መናብርት (በዙፋን ላይ በክብር የሚቀመጡ መላእክት መሪ)፣
ፈታሔ ማኅጸን (የሰውንም ሆነ የእንስሳትን ማኅጸን የሚፈታ)፣
መወልድ (አዋላጅ፣ ምጥን የሚያቀል)
✝ሊቀ መላዕክት ቅዱስ ሩፋኤል ሆይ
እኛን የተዋህዶ ልጆችህን ባርከን ቀድስን በዚህ ዘመን የጸለይነውን የሰገድነው የተማጸነውን የጾምነውን በሙሉ አሳርግልን:: የእናትህ የቅድስት ድንግልንም በረከት አታርቅብን:: እማማ ኢትዮጵያን እና ሕዝቦቿን ጠብቅልን::
✝ ብሩህ ቀን✝
ቻናላችንን ይቀላቀሉ👇👇👇👇👇
@aregawi
@aregawi
@aregawi
#share | 0 |
| 3 | እግዚአብሔር ሰዎችን ኹሉ ሲፈጥራቸው በመንፈሳዊ ማንነታቸው እኩል አድርጎ ነው፡፡ እንዲህም ስለ ኾነ እያንዳንዱ ሰው በጎም ኾነ ክፉ ግብር ለመሥራት እኩል ዝንባሌ አለው፡፡ እግዚአብሔርን ለመታዘዝም ኾነ ላለመታዘዝ እኩል የመምረጥ ዕድል አለው፡፡ ከዚህ ውጪ በኾነ ነገር ግን ሰው ኹሉ እኩል አይደለም፡፡ አንዳንዱ እጅግ አስተዋይ ነው፤ ሌላው ደግሞ ደከም ያለ ነው፡፡ አንዳንዱ በሰውነቱ ብርቱና ጤናማ ነው፤ ሌላው ደግሞ ደካማና ሕመም የሚበዛበት ነው፡፡ አንዳንዱ ሰው መልከ መልካምና ማራኪ ነው፤ ሌላው ደግሞ አይደለም፡፡
ይህ ኹሉ ቢኾንም ግን በኾነ ነገር ስጦታው ያለው ሰው ስጦታው የሌለውን ሌላውን ሰው ሊንቀው አይገባም፡፡ እግዚአብሔር እንዲህ ለእያንዳንዳችን የተለያየ ስጦታን የሰጠን አንዳችን አንዳችንን እንድንጠቅም ነውና፡፡ እግዚአብሔር እያንዳንዳችን ከሌላው ወንድማችን የምንፈልገው ጥቅም እንዲኖር ያደረገው በመካከላችን መጠላላትና መለያየት እንዳይኖር ነው፤ እንድንፋቀርና አንድ እንድንኾን አስቦ ነውና፡፡
ስለዚህ ወዳጄ ሆይ! ወንድምህ ከአንተ ይልቅ አስተዋይና ዐዋቂ፥ ብርቱም ቢኾን በዚህ ቅር አይበልህ፡፡ ከዚህ ይልቅ እግዚአብሔርን አመስግን፤ ከወንድምህ አስተዋይነትና ዐዋቂነት ብርታትም ትጠቀማለህና፡፡ በዚህ ብቻ ሳታቆምም ራስህን፡- “ስጦታዬ ምንድን ነው? ወንድሜን እኅቴን በምን ልጠቅም እችላለሁ?” ብለህ ጠይቅ፡፡ ይህን ጥያቄ በትክክል ስትመልስ፥ እንደ መለስከው ምላሽም ስትተገብር በአንድ መልኩ በሚበልጥህ ሰው ቅር መሰኘትህን፥ በሌላ መልኩ ደግሞ የምትበልጠውን ሌላውን ወንድምህን መናቅህን ታቆማለህ፡፡
(#ቅዱስ_ዮሐንስ_አፈወርቅ) | 0 |
| 4 | ✞ ዐረገች በስብሐት ✞
ዐረገች በስብሐት ዐረገች በእልልታ
በስብሐት በእልልታ
ዐረገች ዐረገች በእልልታ
የጻድቃን እመቤት የሀጥዐን ተስፋ
ዐረገች ዐረገች በእልልታ
የማይታበለው እንዲፈጸም ቃሉ
ብታርፍም እመአምላክ ብዛዊተ ኩሉ
ዐረገች ተነስታ ድንግል የእኛ እናት
እልል በሉላት እልል በሉላት
የጻድቃን እመቤት የሀጥዐን ተስፋ
ዐረገች ዐረገች በእልልታ
/አዝ=====
ሰማያት ተደንቀው በአዲሲቷ ሰማይ
ያልቻሉትን ጌታ ወስናው ብትታይ
ሊቀበሏት ወጡ በሐሴት በሙሉ
ንዒ ንዒ እያሉ ንዒ ንዒ እያሉ
የጻድቃን እመቤት የሀጥዐን ተስፋ
ዐረገች ዐረገች በእልልታ
/አዝ=====
ዘመኗን በሙሉ ስለ ልጇ አልቅሳ
የመከራ ሰይፍን አሳልፋ ነፍሷ
በቀኙ ልትቆም ንግስት እየተባለች
ይኸው ዐርጋለች ይኸው ዐርጋለች
የጻድቃን እመቤት የሀጥዐን ተስፋ
ዐረገች ዐረገች በእልልታ
/አዝ=====
በሐዋርያት አበው ትምህርት የጸናችው
የልጇ ምስክር ከዘሯ የቀራችው
ከሞት ተነስታለች ቅድስት እናታችሁ
እንኳን ደስ ያላችሁ እንኳን ደስ ያላችሁ
የጻድቃን እመቤት የሀጥዐን ተስፋ
ዐረገች ዐረገች በእልልታ
/አዝ=====
ልጅሽ በዳሰሰው በነካው ሰበን
እንደባረክሻቸው ሐዋርያቱን
ማርያም ማርያም ስንል ደጅሽ ላይ ቆመን
እኛንም ባርኪን እኛንም ባርኪን
የጻድቃን እመቤት የሀጥዐን ተስፋ
ዐረገች ዐረገች በእልልታ
#Share and #join ያድርጉ፤ ያስደርጉ።
| 0 |
| 5 | + ማርያማዊ ብሶት +
"ልጄ ሆይ ለምን እንዲህ አደረግህብን?"
ድንግል ማርያም በመጽሐፍ ቅዱስ ላይ የተጻፈ የተናገረችው የብሶት ንግግር ይኼ ብቻ ነው:: "ልጄ ሆይ ለምን እንዲህ አደረግህብን?"
ድንግሊቱ እንዲህ ያለችው ምን ቢደርስባት ነው?
ጌዴዎን እስራኤል መከራ ሲጸናባቸው "ጌታዬ ሆይ፥ እግዚአብሔር ከእኛ ጋር ከሆነ ይህ ነገር ሁሉ ለምን ደረሰብን?" ብሎ ነበር:: መሳ. 6:13
ኢያሱም በጠላት እጅ በወደቁ ጊዜ :- ዋይ! ጌታ እግዚአብሔር ሆይ፥ በአሞራውያን እጅ አሳልፈህ ትሰጠን ታጠፋንም ዘንድ ይህን ሕዝብ ዮርዳኖስን ለምን አሻገርኸው? ብሎ በብሶት አልቅሶ ነበር:: ኢያሱ 7:7
ሙሴም የሕዝቡ አመፅ ሲያስጨንቀው ሙሴም እግዚአብሔርን አለው፦ ለምን በባሪያህ ላይ ክፉ አደረግህ? ለምንስ የዚህን ሕዝብ ሁሉ ሸክም በእኔ ላይ አደረግህ? ብሎ ተማርሮ ነበር:: ዘኍ. 11:11
ድንግል ማርያም "ልጄ ሆይ ለምን እንዲህ አደረግህብን?" ብላ የብሶት ቃል የተናገረችው ግን መከራ ሲደርስባት አልነበረም::
ወደ ግብፅ ስደት እንድትወጣ ሲነገራት "ልጄ ሆይ ለምን እንዲህ አደረግህብን?" አላለችም:: ግርፋቱንና ሕማሙን ስታይም ኀዘንዋን ዋጥ አድርጋ ቆመች እንጂ "ልጄ ሆይ ለምን እንዲህ አደረግህብን?" አላለችም::
ድንግል ማርያም "ልጄ ሆይ ለምን እንዲህ አደረግህብን?" ያለችው ልጅዋ ለሦስት ቀናት ከዓይንዋ በራቀበት ወቅት ነበረ:: "እናቱም፦ ልጄ ሆይ፥ ለምን እንዲህ አደረግህብን? እነሆ፥ አባትህና እኔ እየተጨነቅን ስንፈልግህ ነበርን፡ አለችው" ሉቃ. 2:48
ድንግሊቱ ለምን እንዲህ አደረግህብኝ ያለችው ስለ ሌላው መከራዋ ጊዜ ሳይሆን ክርስቶስ ከእርስዋ ዘንድ ስላልነበረባቸው ቀናት ነበር:: እንደርስዋ መንፈሳዊ ስትሆን "ጌታ ሆይ ለምን አስጨነቅኸኝ?" የምትለው እርሱ ከአንተ የራቀ መሆኑ ሲሰማህ ብቻ ነው:: "አምላኬ አምላኬ ለምን ተውኸኝ? እኔን ከማዳንና ከጩኸቴ ቃል ሩቅ ነህ" "አቤቱ፥ ለምን ርቀህ ቆምህ?" እያልክ የምትጮኸው እግዚአብሔር ከአንተ የራቀ ሲመስልህና የተቀደሰው ማርያማዊ ብሶት ሲሰማህ ነው:: መዝ. 21:1፤10:1
እርሱ ከአንተ ጋር ከሆነ "በሞት ጥላ መካከል እንኩዋን ብትሔድ ክፉውን አትፈራም" ከአንተ የተለየ ሲመስልህ ግን "ጌታ ሆይ ምን አደረግህብኝ" ብለህ በማርያማዊ ብሶት ትጮኻለህ::
ከእርሱ ጋር ሆነህ መከራን መቀበል አይከብድህም:: መሰደድም አያስጨንቅህም:: እርሱ ከአንተ ዘንድ ከጠፋ ግን ብርሃንህ ምርኩዝህ ኃይልህ ጉልበትህ ሁሉ ከአንተ ዘንድ የሉምና ልትጸና አትችልም::
ዝምተኛዋን ድንግል ማርያም በብሶት ማናገር የቻለ አንዳች መከራ አልነበረም:: በበረሃ ከልጅዋ ጋር ከተንከራተተችበት ጊዜ ይልቅ ግን ያለ ልጅዋ ያሳለፈቻቸው ሦስት ቀናት "ልጄ ሆይ ለምን ይሄን አደረግህብኝ" ብላ እንድትጮህ አደረጓት::
ድንግል ሆይ ከአንቺ ዘንድ ለሦስት ቀን የተሰወረው ጌታ ከእኔ ሕይወት ከራቀ ዓመታት እንዳለፉ እያየሽ ይሆን? "ልጄ ሆይ ለምን እንዲህ አደረግህበት? ነፍሱ ተጨንቃ እየፈለገችህ አይደለምን?" የማትይው ስለምንድን ነው?
ለሌላው መከራዬ የምጮኸውን ያህል ከልጅሽ መለየቴ ተሰምቶኝ በማርያማዊ ብሶት እንዳልጮህ በኃጢአት ብርድ ተይዤ መንፈሳዊ ሙቀት በእኔ ዘንድ የለም:: የምበላው የምለብሰው ሲጎድል እንጂ አምላኬን ሳጣ የሚሰማኝ ሰው አይደለሁም:: እኔ ባልጠይቅሽ እንኳን እንደ ቃና ሙሽሮች ጉድለቴን አይተሽ የማትለምኚልኝ ለምንድን ነው? ልጅሽ ወደ ወይን እንዲለውጠው ከእኔ ሕይወት በላይ ውኃ ውኃ ያለ ነገር ከወዴት ሊመጣ? ከልቤስ በላይ የድንጋይ ጋን ከየት ይገኛል?
"ንዒ ማርያም ለዕውር ብርሃኑ
ወንዒ ድንግል ለጽሙዕ አንቅዕተ ወይኑ
ኦ ኦ ትኃድግኒኑ ኦ ኦ ትመንንኒኑ
ኀዘነ ልብየ እነግር ለመኑ"
"የዕውር ብርሃኑ ማርያም ሆይ ነይ
ለተጠማው ወይን የምታፈልቂለት ማርያም ሆይ ነይ
ወዮ ትተዪኝ ይሆንን? ወዮ ትንቂኝ ይሆንን?
የልቤን ኀዘን ለማን እነግራለሁ? (መልክአ ኤዶም)
ወተዘከርኒ ለኃጥእ ገብርኪ ተክለ ማርያም
ዲያቆን ሄኖክ ኃይሌ
ነሐሴ 7 2015 ዓ.ም. | 0 |
| 6 | 🔴ድንቅ የሆነ ታዳጊ ድንቅ ዝማሬ🔴ዲ/አቤል መክብብ🔴
https://youtube.com/watch?v=lA-N6_ZUIv4&feature=share | 0 |
| 7 | https://youtu.be/lA-N6_ZUIv4 | 0 |
| 8 | 🔴ድንቅ የሆነ የሐምሌ ፲፯ የአቡነ በትረማርያም የንግስ መዝሙር ስብስብ🔴ባሕርዳር
https://youtube.com/watch?v=HkAOauY4rgI&feature=share | 0 |
| 9 | ✝ #ታላቅ_የምሥራች።
#ነገ ጠዋት 3:00 ላይ ይጠብቁን በመካነ ቅዱሳን አየር ሀይል አቡነ አረጋዊ ቤተክርስቲያን ሰንበት ት/ቤት የተዘጋጀው የህፃን ዘማሪ ሱራፌል ዝማሬ በልዑል እግዚአብሔር ስም ሼር ሼር ሼር በማድረግ ይተባበሩ
የዩቲዩብ ገጻችንን ሰብስክራይብ ሼር እና ላይክ ያድርጉ።
https://youtube.com/@ferahaymanottube
ነገ በ3:00 ላይ በዩቲብ ገፅአችን ላይ ይጠብቁን🙏🙏🙏 | 0 |
| 10 | 📚''ከእግዚአብሔር ቤት መረቅናችሁ መዝ 118: 26 '' የምርቃት ጥሪ
✝️የባሕር ዳር ሀገረ ስብከት ሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት በ2015 በጀት ዓመት በአዲሱ የሰንበት ትምህርት ቤቶች ሥርዓተ ትምህርት መሠረት ትግበራ ሲያካሂዱ የነበሩ ሰንበት ትምህርት ቤቶች
👉የአንደኛ ክፍል
👉ሁለተኛ ክፍል
👉አራተኛ ክፍል
👉ሰባተኛ ክፍል ትምህርታቸውን ሲከታተሉ የነበሩ 3100 በላይ ተማሪዎችን ብፁዕ አቡነ አብርሃም የጠቅላይ ቤተ ክህነት ዋና ስራ አስኪያጅ እና የባሕር ዳር ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ በተገኙበት ያስመርቃል።
👉የሀገረ ስብከቱ ዋና ሥራ አስኪያጅ እና፣
👉 የየመምሪያ ኃላፊዎች፣
👉የገዳማት እና የአድባራት አስተዳዳሪዎች ፣
👉 የሰበካ ጉባኤ አባላት ፣
👉የማኅበረ ቅዱሳን ባሕር ዳር ማዕከል
👉የጽዋ ማኃበራት እና የሰንበት ትምህርት ቤቶች ሥራ አመራር ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች በተገኙበት
👉ቀን የፊታችን እሑድ ሀምሌ 23/15 ዓ/ም
👉 ሰዓት: ከቀኑ 7:00
👉 ቦታ በደብረ ጽዮን ሰላም አድርጊው ማርያም ሰ/ቤት ስብከተ ወንጌል አዳራሽ ያስመርቃል።
🌐 በባሕረዳር ሀገረ ስብከት ሰንበት ት/ቤቶች አንድነት
SUBSCRIBE @AndnetMedia 👇 https://www.youtube.com/c/AndnetMedia 💠 የማኅበራዊ ሚዲያ ገጾቻችንን @EOTCBDSSU በመቀላቀል መረጃዎችን ይከታተሉ ለሌሎች ኦርቶዶክሳዊያንም ያዳርሱ... #Share | 0 |
| 11 | "በቀትርም ጊዜ እርሱ በድንኳኑ ደጃፍ ተቀምጦ ሳለ እግዚአብሔር በመምሬ የአድባር ዛፍ ተገለጠለት
ዓይኑንም አነሣና እነሆ ሦስት ሰዎች በፊቱ ቆመው አየ ባያቸውም ጊዜ ሊቀበላቸው ከድንኳኑ ደጃፍ ተነሥቶ ሮጠ ወደ ምድርም ሰገደ እንዲህም አለ
አቤቱ በፊትህስ ሞገስ አግኝቼ እንደ ሆነ ባሪያህን አትለፈኝ ብዬ እለምናለሁ
ጥቂት ውኃ ይምጣላችሁ እግራችሁን ታጠቡ ከዚህችም ዛፍ በታች ዕረፉ
ቍራሽ እንጀራም ላምጣላችሁ ልባችሁንም ደግፋ ከዚያም በኋላ ትሄዳላችሁ ስለዚህ ወደ ባሪያችሁ መጥታችኋልና እነርሱም እንዳልህ አድርግ አሉት
አብርሃምም ወደ ድንኳን ወደ ሣራ ዘንድ ፈጥኖ ገባና ሦስት መስፈሪያ የተሰለቀ ዱቄት ፈጥነሽ አዘጋጂ ለውሺውም እንጎቻም አድርጊ አላት"
ዘፍ፲፰፥፩-፮
🎊እንኳን አደረሳችሁ አደረሰን🎊
╭══•|❀:✧๑♡๑✧❀|: ══╮
@aklesya
╰══•ೋ•✧๑♡๑✧• ══╯ | 0 |
| 12 | No text... | 0 |
| 13 | https://youtu.be/Q3062vBdaCc | 0 |
| 14 | #ከዚህ በታች ያሉትን ሊንኮች በመጫን ወደ ግሩፓችን እንድትቀላቀሉን ስንል በልዑል እግዚአብሔር ስም ጥሪ እናቀርባለን።
YouTube link
👉https://youtube.com/channel/UC22dlAupPK0w-6I8cdngvTg 👈
Facebook group link
👉https://facebook.com/groups/833348454676003/
Facebook page link
#https://www.facebook.com/profile.php?id=100070619763251👈
telegram group link
👉https://t.me/+BU1kSKGpT-g5YTZk 👈
telegram page link
👉https://t.me/aregawi 👈
tiktok link
tiktok.com/@ferahaymanot1👈
👆👆👆 | 0 |
| 15 | No text... | 0 |
| 16 | https://youtu.be/hGcFZ0Fy7q8 | 0 |
| 17 | No text... | 0 |
| 18 | https://youtu.be/FEJ3PrmKuo8 | 0 |
| 19 | No text... | 0 |
| 20 | ፆም እንዴት ነው?
🧙♂🙇
ከእለታት አንድ ቀን አንድ ወጣት ወደ ነፍስ አባቱ ይሄድና ሰላም ካላቸው በኃላ
🧙♂ ልጄ መንፈሳዊ ሂይወት እንዴት ነው?
🙎♂ ወጣቱም መልሶ በጣም ጥሩ ነው አባ።
🧙♂ደስ ብሏቸው ጎሽ ልጄ በርታ እና ፆሙስ እንዴት ይዞሃል?
🙇 ወጣቱም አይ አባቴ ፆም እንኳን እየፆምኩ አይደለም።
🧙♂ለምን ልጄ ምን ነካህ?
🙎♂ወጣቱም አይ አባቴ ፆም ከገባ በኋላ ፍርጅ ውስጥ የነበረ ስጋ ወጥ ረሰቸው በላሁት ከዛም ያው አንዴ ሽርያለሁ ብየ አልፆምም።
🧙♂የነፍስ አባቱም በጣም አዘኑና እህህህ ልጄ አንድ ጥያቄ ልጠይቅህ?
🙎♂ወጣቱም እሺ ይጠይቁኝ
🧙♂ 💥እሳት አየሞክ እያለህ ሳታስበው በድንገት እግርህን ወደ እሳቱ ቢገባና እግርህ ቢቃጠል አንዴ ተቃጥያለው ብለህ ሳታወጣው ዝም ትላለህ ወይስ ታወጣዋለህ?
🙍♂ ወጣቱም በድንጋጤ🤷♂ 💥 እንዴ አባቴ ለምን ዝም እላለው ቶሎ ብዬ አውጥቼ በፍጥነት ወደ ህክምና ሄጄ እታከመዋለው።
🧙♂ጥሩ ብለሃል ልጄ ፆምም አንዴ በልቻለው እያልክ መብላትህ ተገቢ አይደለም። ሃጥያትም ነው ልጄ ልክ ከእሳቱ እግርህን ቶሎ ብለህ አውጥተህ ወደ ህክምና እንደ ሄድክ ነፍስም ከቁስሏ ቶሎ ብለህ ከስህተት ተመልሰህ በፆም በጸሎት ማከም ይገባሃል ልጄ።በስህተት የሻርከውን ንስሐ ይሰጥህና የቀረውን መፆም ነው የሚገባህ ልጄ በስህተት ላይ ስህተት እየጨመርክ መንፈሳዊ ህይወትህ ማጥፋት የለብህም በማለት ቀኖና ሰጥተው ፆሙን እንዲፆም ነግረው አሰናበቱት።
፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨
መልዕክት፦አብዛኞቻችን አንዴ ፆሙን ሽርያለው በሃጢአት ወድቅያለው ገና ወጣት ነኝ ነገ እሳሳታለው እያልን ብዙ ምክንያት እየደረደረን መንፈሳዊ ሂይወታችንን ረስተን በዝሙት በመጠጥ በጭፈራ በተለያዩ ወጥመድ ተይን ወጥተን የጠፋን ስንቶቻችን ነን ቤት ይቁጠረን። ቶሎ ብለን ዲያብሎስን ካልነቃንበት ህይወታችንን በማበላሸት ያጠፋናል።አንዴ ተሳስቻለው ብለን ሁሌም መሳሳት የለብንም በንስሃ ተመልሰን መልካሙን መንፈሳዊ ህይወታችንን እናጠናክር እንዲ እያሉ የሚገስጹ ደግ አባቶቻችንን ያብዛልን።
በንስሐ እንመለስ❗
ወስብሐት ለእግዚአብሔር
፨ከተስፋ ሚካኤል ሃይለ ማርያም
✨✨✨✨✨✨✨✨✨
✨✨✨✨✨✨✨✨✨
ቻናላችንን ይቀላቀሉ
👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇
@aregawi
@aregawi
@aregawi
#Share | 0 |
