en
Feedback
Mereja TV

Mereja TV

Open in Telegram

Please send us photos, videos and information to our Telegram account: @realmerejatv

Show more

📈 Analytical overview of Telegram channel Mereja TV

Channel Mereja TV (@merejamedia) in the Amharic language segment is an active participant. Currently, the community unites 18 134 subscribers, ranking 12 459 in the News & Media category and 1 852 in the Ethiopia region.

📊 Audience metrics and dynamics

Since its creation on невідомо, the project has demonstrated rapid growth, gathering an audience of 18 134 subscribers.

According to the latest data from 14 June, 2026, the channel demonstrates stable activity. Although there has been a change in the number of participants by -385 over the last 30 days and by -2 over the last 24 hours, overall reach remains high.

  • Verification status: Not verified
  • Engagement rate (ER): The average audience engagement rate is 19.12%. Within the first 24 hours after publication, content typically collects 8.42% reactions from the total number of subscribers.
  • Post reach: On average, each post receives 3 468 views. Within the first day, a publication typically gains 1 527 views.
  • Reactions and interaction: The audience actively supports content: the average number of reactions per post is 18.

📝 Description and content policy

The author describes the resource as a platform for expressing subjective opinions:
Please send us photos, videos and information to our Telegram account: @realmerejatv

Thanks to the high frequency of updates (latest data received on 15 June, 2026), the channel maintains relevance and a high level of publication reach. Analytics show that the audience actively interacts with content, making it an important point of influence in the News & Media category.

18 134
Subscribers
-224 hours
-397 days
-38530 days
Posts Archive
Mereja TV
18 134
በአሜሪካን; የፔንሴሌቪያ ምክር ቤት ለአድዋ ድል በሰጠው ታሪካዊ እውቅና ላይ የተሰጠ ምስጋና እና የአቋም መግለጫ
+3
በአሜሪካን; የፔንሴሌቪያ ምክር ቤት ለአድዋ ድል በሰጠው ታሪካዊ እውቅና ላይ የተሰጠ ምስጋና እና የአቋም መግለጫ

Mereja TV
18 134
በአምሃራ ሳይንት በለጩማ ግንባር በጠላት ከፍተኛ አመራሮች ላይ  አስደናቂ የደፈጣ ጥቃት ተፈጸመ! ​በመካነ ሰላም ከተማ ለቀናት የሴራ ስብሰባ ሲያካሂዱ የነበሩት የአገዛዙ ከፍተኛ ወታደራዊ አመራሮች፣ ወደ አምሃራ ሳይንት ወረዳ ለመግባት ሲሞክሩ በንሥሮች በተደገሰላቸው ጥብቅ ደፈጣ ክፉኛ ተመትተዋል። የአገዛዙ የጦር አመራሮች በመካነ ሰላም የነበራቸውን የግምገማ ስብሰባ ጨርሰው፣ የተለመደ የጥፋት ተልዕኮአቸውን ለመፈጸም በከፍተኛ መኪናዎች ታጅበው እየተንቀሳቀሱ በነበረበት ቅፅበት ጀግኖቹ  "በለጩማ" በተባለው ስልታዊ ቦታ ላይ መንገዱን ዘግተው በመጠባበቅ፣ ጠላት ጨርሶ ባልገመተው ሁኔታ መብረቃዊ የደፈጣ ጥቃት  ዶግ አመድ አድርገዉታል። ደፈጣዉም በጀብደኛዉ ምኒልክ ዕዝ ስር በ105ኛ ኮር የ71ኛ ክፍለ ጦር አናብስቶች ሲሆን የተሰራዉ  በጥቃቱም የጠላት ዋና ዋና ወታደራዊ መሪዎች ጭምር ሙት እና ቁስለኛ ሁነዋል።  በጀግኖቹ ክንድ የደረሰባቸውን ከባድ ጉዳት መቋቋም ያልቻለው የጠላት ጦር፣ አመራሮቹን ለማዳን በከፍተኛ መደናገጥ ውስጥ ሆኖ ሲያነሳ የዋለ ሲሆን  ከፍተኛ ጉዳት የደረሰባቸው የጦር መኮንኖች በአስቸኳይ ወደ ደሴ  ሆስፒታል በሪፈር የተሸኙ ሲሆን ቀሪወቹ  በአምሃራ ሳይንት ወረዳ በሚገኘው አጅባር ሆስፒታል ገብተዋል። በጉዳቱ የተደናገጠዉ ስርዓት ሽንፈቱን ለመደበቅ ከትናንት ምሽት ጀምሮ በአጅባር ሆስፒታል ዙሪያ ጥብቅ ወታደራዊ ከበባ ያደረገ ሲሆን  የቆሰሉት አመራሮች ማህበረሰቡ እንዳያያቸዉ  በሚል ስጋት፣ ከሕክምና ባለሙያዎች ውጭ ማንም ሲቪል ታካሚ ወደ ሆስፒታሉ ግቢ እንዳይገባ ሙሉ በሙሉ እስካሁን ድረስ አግደው ይገኛሉ። ምንጭ፦ የምኒልክ ዕዝ ሚዲያ እና ኮሚዩኒኬሽን  መምሪያ!

Mereja TV
18 134
ከደብረ ማርቆስ ወደ ስናን ሬሽን ለማቀበል በተንቀሳቀሰው የጠላት ኃይል ላይ 206ኛ ኮር 24ኛ ክ/ጦር ስናን አባ ጅሜ ሻለቃ ባደረገው ማጥቃት 20 የአረመኔው ሰራዊት ሲደመሰሱ 12 የሚደርሱ ከባድ ቁስለኛ ሁነው 3 ክላሽ ፣ 1050 ጥይት ተማርኳል። የአረመኔው ሰራዊት የ6ኛ ዕዝ 602ኛ ኮር 75ኛ ክ/ጦር ከደብረ ማርቆስ ተነስቶ ወደ ስናን ረዕቡ ገበያ ሬሽን ለማቀበል እየተንቀሳቀሰ ባለበት 206ኛ ኮር 24ኛ ክ/ጦር ስናን አባ ጅሜ ሻለቃ ባደረገው ማጥቃት 20 የጠላት ወታደሮች ሲደመሰሱ 12 የሚደርሱት ቁስለኛ ሁነዋል። በተፈፀመው ፈጣን ጥቃት የጠላት መስመራዊ መኮንኖች ህይወታቸውን ያጡ ሲሆን ፻ አለቃ ታሪኩ በቀለ ባቲሳ የሻለቃ አዛዥ ይገኝበታል። ጠላት በአልጠበቀው ስዓት በተከፈተበት ተኩስ አስክሬን ሳያነሳ ፈርጥጦ 3 ክላሽ፣ 1050 ጥይት ትጥቆችና ወታደራዊ ቦርሳዎች ተማርኳል። ምንጭ፦ በአፋብን ቴዎድሮስ ዕዝ 206ኛ ኮር ህዝብ ግንኙነት ክፍል!

Mereja TV
18 134
በሸዋ ጠቅላይ ግዛት ምንጃርና ከረዩ አውራጃ ነበልባል ክፍለ ጦር ድል ተቀዳጀች በአፋብን ሸዋ/ጠ/ግ/አሳምነው ዕዝ ከሠም ፪ኛ ኮር ነበልባል ክፍለ ጦር የብልፅግናውን ጥምር ጦር እንደ ቅጠል አረገፉት። ሁለት የነበልባል ክፍለ ጦር ሻለቆች የተሳተፉበት ውጊያ ማለትም  መብረቅ  ሻለቃ እና መቶ አለቃ አበባው ሻለቃ ፋኖዎች በጥምረት  ባደረጉት ገድል የብልፅግናውን  ግብስብስ  ሠራዊት በ06/10/2018 ከቀኑ 6:00 እስከ ማታ 9:45 ሰዓት በነበረው ፍልሚያ  ፋኖዎቹ  መብረቃዊ ክንዳቸውን በመሰንዘር እንደ እሳት ሲለበልቡት አምሽተዋል። መነሻውን ከባልጪ  አድርጎ  ወደ ኢራንቡቲ ቀበሌ ያቀናውን የሪፐፕሊካን ጥበቃ 5ኛ ክፍለጦር እና በስሩ በጥቅማጥቅም የሰበሰባቸውን ሆድ አደር ሚሊሾች  እንዲሁም አዲስ ተጨማሪ ሰራዊት በመያዝ ኢራንቡቲ ቀበሌን እቆጣጠራለሁ ብሎ በመንጋ ቢመጣም በአይበገሬዎቹ  ነበልባል ክፍለ ጦር  ሠራዊታችን ወደ መጣበት እዲመለስ አድርገውታል።     የሀይል ብልጫ የተወሰደበት የጠላት ሀይል  ከ15 በላይ እንደተገደለበት እና ቁጥሩ በውል  ያልታወቀ ቁስለኛ በአንቡላንስ ከአራት ጊዜ  በላይ ጭኖ እንዳመላለሰ እና የሞተበትን ሀይል በአካባቢው ማህበረሰብ በማስገደድ ለህክምና የምታመላልሰው አንቡላንስ ደርሳ እስክትደርስ 15ቱን እሬሳ እዲያቀብሉት ማስገደዱን  የውስጥ መረጃችን አሳውቆናል። ይህ በእንዲሕ እንዳለ የአፋብን ሸ/ጠ/ግ/አ/ዕዝ ዓፄ አምደ ጽዮን ኮር 7/70 ክፍለጦር  አንድ(1) የአገዛዙ ወታደር =>  አንድ(1) ዘመናዊ ስናይፐር መሳሪያ => አንድ(1) የደረት ትጥቅ =>  አራት(4) ካዝና በመያዝ ወደ ፋኖ ተቀላቅሏል። በሌላ የአውደ ውጊያ ቀጠና በሸዋ ጠቅላይ ግዛት ይፋት አውራጃ  አስገራሚ ጀብዶች ተሠርተዋል የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው እዝ የዓፄ ዘርዓ ያዕቆብ ፩ኛ ኮር  7/ለ70 ክፍለ ጦር ዛሬም እንደ ትላንቱ በጠላት ይዞታዎች ውስጥ ሰርገው በመግባት አስገራሚ ድሎችን ማስመዝገባቸውን ቀጥለውበታል። ​የክፍለ ጦሩ ልዩ የኦፕሬሽን ቃኝዎች የፋሺስት አብይ አህመድ ግብስብስ ሰራዊትን ወደ ሚንቀሳቀስበት ቦታ ሰርገው በመግባት የጠላትን እቅድ በማክሸፍ መብረቃዊ ጥቃቶችን ፈፅመዋል። ​የሰርጎ ገብ ውጊያ ስምሪቱ በቀን 05/10/2018 ዓ.ም ከለሊቱ 5:00 ሰዓት ላይ ከአጣዬ ተነስቶ ወደ በርግቢ አቅጣጫ እየገሰገሰ በነበረው የጠላት መከላከያ ሰራዊት ላይ የ7ለ70 ክፍለ ጦር ጀግኖች በ06/10/2018  በበርግቢ ቀበሌ እና በይምልዎ መካከል ላይ አድፍጠው በመጠበቅ ከባድ ድንገተኛ ጥቃት ፈፅመዋል። በዚህ እልህ አስጨራሽ የለሊት ውጊያ የጠላት ኃይል ድባቅ በመመታቱ ወደ መጣበት ተገዶ ለማፈግፈግ ተገዷል። በዚሕም ከጠላት ሀይል አራት(4) የተገደሉ ሲሆን የተቀሩት ደግሞ በጽኑ ቆስለው በሕክምና ላይ እንደሚገኙ የውስጥ መረጃዎቻችን ገልፀዋል። ​ ​ይህ የድል ጉዞ ሳይቋረጥ በማግስቱ በ07/09/2018 ዓ.ም ከጠዋቱ 12:00 ሰዓት ላይ ከአጣዬ ከተማ ተነስቶ ወደ አላላ በመጓዝ ላይ በነበረው የሆድ አደር ሚሊሻ ኃይል ላይ ሌላ ስልታዊ ጥቃት ተፈጽሟል። የክፍለ ጦሩ የቁርጥ ቀን ልጆች አራዳ በር ላይ ቀድመው ሰርገው በመግባትና ምሽግ በመያዝ፣ በሚሊሻው ላይ የጀግንነት ክንዳቸውን አሳርፈዋል።​በዚህ እልህ አስጨራሽ ውጊያ እንድሪስ የተባለው የጠላት ሚሊሻ መሪ እስከ ግብረ አበሮቹ ሙሉ በሙሉ የተደመሰሰ ሲሆን፣ ካጋጠማቸው ከባድ ሽንፈት የተረፉት 3ቱ (ሦስቱ) ደግሞ በከባድ የመቁሰል አደጋ ምክንያት ሪፈር ተጽፎላቸው በሕይወትና በሞት መካከል ይገኛሉ ሲል መረጃዎቻችን ተናግረዋል። ምንጭ፦በአፋብን አሳምነው ዕዝ ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ!

Mereja TV
18 134
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን የቴክሳስ፣ ኦክላሆማ፣ ሉዊዚያና፣ አርካንሳና ሐዋዪ አካባቢ ሀገረ ስብከት በምሥራቅ አርሲ የጅምላ ፍጅት ለደረሰባቸው ወገኖቻችን ጸሎተ ፍትሐት እንዲደረግ
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን የቴክሳስ፣ ኦክላሆማ፣ ሉዊዚያና፣ አርካንሳና ሐዋዪ አካባቢ ሀገረ ስብከት በምሥራቅ አርሲ የጅምላ ፍጅት ለደረሰባቸው ወገኖቻችን ጸሎተ ፍትሐት እንዲደረግ መመሪያ አስተላልፏል። እንዲሁም ለእሑድ ሰኔ 8 ቀን 2018 ዓ.ም (June 14, 2026) ደግሞ ልዩ ጉባዔ ጠርቷል። ዝርዝሩ ከደብዳቤው ላይ ይገኛል።

Mereja TV
18 134
በአርሲ ሀገረ ስብከት በኦርቶዶክስ ምእመናን እና በአብያተ ክርስቲያናት ላይ በደረሰው አሰቃቂ ጥቃት የሊባኖስ፣ የተባበሩት ዓረብ ኢምሬትስ እና የመካከለኛው ምሥራቅ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡ
+1
በአርሲ ሀገረ ስብከት በኦርቶዶክስ ምእመናን እና በአብያተ ክርስቲያናት ላይ በደረሰው አሰቃቂ ጥቃት የሊባኖስ፣ የተባበሩት ዓረብ ኢምሬትስ እና የመካከለኛው ምሥራቅ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ድሜጥሮስ የሐዘን፣ የጸሎተ ፍትሐት እና የጸሎተ ምሕላ መግለጫ ========= “ቅዱስና እውነተኛ ጌታ ሆይ እስከ መቼ ድረስ አትፈርድም? ስለ ደማችንስ በምድር በሚኖሩት ላይ እስከ መቼ አትበቀልም?” (ራእይ 6፥10)

Mereja TV
18 134
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የዋሽንግተን ዲሲ እና አካባቢው ሀገረ ስብከት በምስራቅ አርሲ ውስጥ በተደጋጋሚ ስለሚከሰተው የክርስቲያኖች ግድያ ስደት እና መከራን አስመልክቶ የወጣ የአ
+2
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የዋሽንግተን ዲሲ እና አካባቢው ሀገረ ስብከት በምስራቅ አርሲ ውስጥ በተደጋጋሚ ስለሚከሰተው የክርስቲያኖች ግድያ ስደት እና መከራን አስመልክቶ የወጣ የአቋም መግለጫ ================ «እስመ በእንቲአሁ ይቀትሉነ ኵሎ አሚረ፤ወኮነ ከመ አባግዕ ዘይጠብሑ። ስለ አርሱ ሁልጊዜ ይገድሉናል፥ እንደሚታረዱም በጎች ሆነናል።” (መዝ ፵፫፡፳፪)

Mereja TV
18 134
በአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ  ሽዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ዓፄ ዘርያዕቆብ ፩ኛ ኮር በፍቃዱ በላይ ክፍለ ጦር  የበረሀው ጀግኖች ትናንት ከማለዳ አንድ(1:00) ሰዓት ከ30 ደቂቃ ጀምረው እስከ ምሽቱ አንድ(1:00) ሰዓት ድረስ በተደረገ እልሕ አስጨራሽ ውጊያ  በሰረርኩላ እና በቱቲ ከተሞች መሽጎ በነበረው የአገዛዙ ኃይል ላይ እንደ እሳት እያቃጠሉ  ጠንካራ ምት አድርገውበታል።  ሆኖም  የሥርዓቱ  ጅምላ ተጋላቢ ኃይል በመሬት ላይ ሊቀበለው የሚገባውን ታሪካዊ ቅጣት ከጀግኖቹ   ክንድ ተመግቧል። የበረሀው ትንታግ  በፍቃዱ በላይ ክፍለጦር አንዲት እሳት የለበሰች ሻለቃ ወደ ሰረርኩላ ከተማ በረገጠችበት ቅጽበት  በአገዛዙ ጥርቅም ኃይል ላይ የወሰደችው ፈጣንና መብረቃዊ የማጥቃት ስልት ጠላትን ሙሉ በሙሉ ግራ አጋብቶታል።  ከዚሕም  የተነሳ  ጭንቅ ውስጥ የገባውና መውጫ ያጣው የአገዛዙ ኃይል  ጫካ ውስጥ ያደራጀውን ዘራፊውን የ"ሸኔ" ስብስብ ለአጋዥነትና ለሕይወት ማዳኛ  የጋበዘ  ሲሆን  የአናብስቶቹ  ክንድ  የማይነካ  በመሆኑ  ነገሩ   እዳሠበው  ሳይሳካ ቀርርቶበታል። ​በመጨረሻም  ጠላት የሚያስማርከውን አስማርኮ  የጓዶቹን አስከሬን እንኳን ሳይሰበስብ ከተማዋን ጥሎ ወደ ጫካ ፈርጥጧል። ጀግኖቹ የሰረርኩላን ከተማ እስከ ምሽቱ  ሁለት(2:00)  ሰዓት ሙሉ በሙሉ በቁጥጥራቸው ስር አውለዋታል። በሌላ በኩል  በቱቲ ከተማ  በተደረገው አውደ ውጊያ   እጅ በአፍ የሚያስጭን  ነበር።  የቱቲ  ከተማ  በተናዳፊዎቹ ሻለቆች የባሩድ ጢስ ስትታጠን፣ ባሩዱም ሲቆላ በዋለበት በዚያ አስፈሪ ሰዓት   ጠላት ምሽጉን  በመነጠቁ  ከተማዋን  ጥሎ  ለመውጣት ተገዷል። የወገን ኃይል ከተማዋን ሙሉ በሙሉ በመቆጣጠር ድላቸውን አጣጥመዋል። ​ይሕ በእንዲሕ እንዳለ  ጠላት በእውር ድንብርና በፍርሃት ተውጦ ዙ-23 እና ሞርተሮችን እያጮኸ ቢውልም  በጀግኖቹ የቦታ ቁጥጥርና በማይበገረው የስነ-ልቦና የበላይነት ግንባሩን  ተመትቶ እንደ ቅጠል ሲረግፍ አምሽቶ ፣ በዚህ ደማቅ አውደ ውጊያ የተረጋገጠውና በጀግኖቹ እጅ የገባው የምርኮ ዝርዝር እንደሚከተለው ይፋ ሆኗል፦ ​➾3  ከፋኖ ከድተው ወደ አገዛዙ ገብተው የነበሩ ባንዳዎች ​➾1  የአገዛዙ ካድሬ ​➾3  የሚሊሻ አባላት ​➾የተማረከ ንብረት ዝርዝር ፦ ​➾8  ክላሽንኮቭ ጠመንጃዎች ​➾4  የወገብ ትጥቅ ​➾1   የደረት ትጥቅ ​➾6    የእጅ ቦንቦች ​እና... በርካታ ተተኳሽ ጥይቶች በጀግኖቹ እጅ ገቢ ተደርገዋል። ​ምንጭ፦ በአፋብን አሳምነው ዕዝ ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ!

Mereja TV
18 134
ከቅ/ሥላሴ ዩኒቨርሲቲ ደቀ መዛሙርት ለብፁዓን አባቶቻችን የቀረበ ጥያቄ!

Mereja TV
18 134
ከ"ዘመቻ ህፃን አንሻ ሰይድ" ማግስት የብልፅግና ሰራዊት መፍረሱን ቀጥሏል! ለብልፅግና የዙፋን መንበር በማወቅም ይሁን ባለማወቅ እየታተረና እየተጋ የሚገኘው ብልፅግና መራሹ ጦር በዘመቻ ህፃን አንሻ ሰይድ በከባድ ሚዛን በፋኖ ክንድ የተመታው ሰራዊት ከአሐዱ በመፍረስ ፋኖ ወደሚገኝበት ቦታ ሁሉ እየተቀላቀለ ይገኛል። የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ (አፋብን) ወሎ ቤተ-አማራ ምኒልክ ዕዝ 303ኛ ኮር አካል የሆነውን 19ኛ ክፍለ ጦርን የተቀላቀሉት አስር አለቃ አማረ ተፈራ እና ጓደኛው ከ34ኛ ክፍለ ጦር አራተኛ ሬጅመንት በመውጣት የፋኖን ቤት የተቀላቀሉ ሲሆን መከላከያ አሁን ባለው ቁመና የመዋጋት አቅም እንደሌለውና ሰራዊቱም በፍፁም መሰላቸትና በከባድ የስነ-ልቦና ውድቀት ላይ እንደሚገኝ ገልጿል። በሌላ መረጃ 303ኛ ግዙፉ አሳምነው ኮር አካል የሆነውን 30ኛ ክፍለ ጦርን የተቀላቀሉት የ13ኛ ዕዝ ኦፕሬተር የነበሩት:-    1ኛ. መሰረታዊ ወታደር ማርይሁን ጌታ    2ኛ. መሰረታዊ ወታደር ዮሴፍ አዱኛው    3ኛ. መሰረታዊ ወታደር ቴዎድሮስ ጥላሁን ሁላቸውንም ቤተሰቦቻቸው ልከው ከሚያስተምሯቸው ኮሌጅ ላይ በማፈን ወደ ማሰልጠኛ በማስገባት ተገደው የገቡ እንደሆኑ ገልፀው የአገዛዙን ጓዳ ከፈተሹና ከመረመሩ በኋላ ለቤተሰቦቻችንና ወንድም እህቶቻችን ማጥፊያ ስርዓትና ተቋም አናገለግልም በማለት ፋኖን እንደተቀላቀሉ ተናግረዋል። ስቦ በማስከዳት ስርዓቱን ከማፍረስ ጋር ተያይዞ ከመስከረም 14/2018 ዓ/ም ዘመቻ አደም አሊ (አባ ናደው)ን ጨምሮ ለተከታታይ ስምንት ወራት ከ850 በላይ የአገዛዙ ሰራዊት መከላከያ፣ አድማ ብተና፣ ፖሊስ፣ ሚሊሻና ስርዓቱን አገልጋይ ካቢኔ አባላት 303ኛ ግዙፉ አሳምነው ኮር ፋኖን የተቀላቀሉ ሲሆን አሁንም አልረፈደምና ቀሪው የአገዛዙ ሰራዊት  በፍጥነት ፋኖን  በመቀላቀል ህይዎቱን እንዲታደግ ሲል የኮሩ ፖለቲካ መምሪያ ኃላፊ አርበኛ በሪሁን ደምሌ ጥሪ አቅርቧል። ምንጭ፦ የምኒልክ ዕዝ ሚዲያና ኮሚኒኬሽን መምሪያ!

Mereja TV
18 134
የአርበኛ ሳሙኤል ባለዕድል ቤተሰቦች በፋሽስቱ አገዛዝ ታገቱ! የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ ከፍተኛ አመራር አርበኛ ሳሙኤል ባለዕድል ቤተሰቦች በአገዛዙ ብልፅግና ሰኔ 2/2018 ዓ.ም ታግተዋል:: የአ
የአርበኛ ሳሙኤል ባለዕድል ቤተሰቦች በፋሽስቱ አገዛዝ ታገቱ! የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ ከፍተኛ አመራር አርበኛ ሳሙኤል ባለዕድል ቤተሰቦች በአገዛዙ ብልፅግና ሰኔ 2/2018 ዓ.ም ታግተዋል:: የአፋብን ስልጠና መምሪያ ሃላፊው ቤተሰቦች ማለትም ባለቤቱ እህቱና የእህቱ ባል ከህፃናት ልጆቻቸው ጋር በጅምላ ታፍነው ታስረው ይገኛሉ:: ባለፈው ጊዜ የከፍተኛ አመራሩ አጎትና የአጎቱ ልጅ በአገዛዙ በግፍ እንደተገደሉበት የሚታወቅ ነው:: ፋሽስቱ የብልፅግና አገዛዝ ህዝባቸው ላይ እየተፈፀመ ያለውን ዘር ማጥፋት ለመቀልበስ እየታገሉ ያሉ አርበኞችን ታግሎ ማሸነፍ ሲያቅተው ቤተሰቦቻቸውን በመግደል በማገትና ከሃገር እንዲሰደዱ በማድረግ ግፍ በመፈፀም ከአላማቸው ለማደናቀፍ ቢሞርም ተግባሩ ግን አርበኞችን በከፍተኛ ፅናትና ቁርጠኝነት እንዲታገሉ ከማድረግ የዘለለ ሚና የለውም::

Mereja TV
18 134
በምኒልክ ዕዝ 104ኛ ኮር 23ኛ ክፍለ ጦር አምባሰል ላይ አንፀባራቂ ድል ተቀዳጀ! መነሻዉን ከኩታበር ወደ ተለያዬንና ዚሃ እንዲሁም ከደላንታ በተሬ አድርጎ ወደ ዚሃ በምድር ሞርተር ፣ዙ23 እና መድ
በምኒልክ ዕዝ 104ኛ ኮር 23ኛ ክፍለ ጦር አምባሰል ላይ አንፀባራቂ ድል ተቀዳጀ! መነሻዉን ከኩታበር ወደ ተለያዬንና ዚሃ እንዲሁም ከደላንታ በተሬ አድርጎ ወደ ዚሃ  በምድር ሞርተር ፣ዙ23 እና መድፍ ሲጠቀም በሰማይ በሁለት ድሮን ታግዞ  ፋኖን አጠፋለሁ በሚል የተለምዶ ቅዠቱ የመጣ ቢሆንም ጀግኖቹ ምንም ነገር ሳይበግራቸዉ እንደቃሪያ ሲያራግፉት ዉለዋል። ዉጊያዉም  ከንጋቱ 11:00 እስከ 6:00 የተደረገ ሲሆን በዚህ እልህ አስጨራሽ ውጊያ የ104ኛ ኮር 23ኛ ክ/ጦር ተናዳፊወች  ዚሃ የገባውን ሃይል ሙሉ ለሙሉ የደመሰሱት ሲሆን በዚህ የተበሳጨዉ  አገዛዝ በዘፈቀደ ሶስት ጊዜ ድሮን በመጣል ከጦርነቱ ተሳታፊ ያልሆኑ ንፁሀንን የጥቃቱ ሰለባ አድርጓል። አሁን ላይ በድሮን ሽፋን በመስጠት ሬሳና ቁስለኛ እያነሳ ሲሆን ከግሸን በአባላ ለመቁረጥ ቢቀሳቀስም በንስሮቹ በደፈጣ ተመቶ ሙትና ቁስለኛውን ይዞ ወደ መጣበት ተመልሷል። ምንጭ፦ በአፋብን ምኒልክ ዕዝ 104ኛ ኮር ህዝብ ግንኙነት ክፍል!

Mereja TV
18 134
ከዚህ ቀደም የሰላም ስምምነት ተቀብያለሁ በሚል ለሁለት ዓመታት ያህል ከአገዛዙ ስንቅና ትጥቅ ሲሰፈርለት የቆየው የአገው ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄ (አዴን) ታጣቂ ኃይል በዋግ ኽምራ ዞን አበርገሌ እና ፃግ
ከዚህ ቀደም የሰላም ስምምነት ተቀብያለሁ በሚል ለሁለት ዓመታት ያህል ከአገዛዙ ስንቅና ትጥቅ ሲሰፈርለት የቆየው የአገው ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄ (አዴን) ታጣቂ ኃይል በዋግ ኽምራ ዞን አበርገሌ እና ፃግብጂ ወረዳዎችን ሙሉ በሙሉ መቆጣጠሩን አስታወቀ! ከሁለት ዓመት በፊት በአገዛዙና በታጣቂ ኃይሉ መካከል ተደርሶ የነበረውን የሰላም ስምምነት እራሱ አገዛዙ በመጣስ ትንኮሳ ፈፅሟል በተባለበት በዚህ ቀጠና፡ ታጣቂዎቹ ከሕወሓት ኃይሎች ጋር በመቀናጀት በወሰዱት እርምጃ ነው በሰቆጣ ዙሪያ የሚገኙ ሁለት ትላልቅ ወረዳዎችን ሙሉ በሙሉ የተቆጣጠሩት። የዞኑ ፀጥታ ኃይሎች ከነጌታቸው ረዳ የሓራ መሬት ታጣቂዎች ጋር በመቀናጀት በአዴን ቡድን ወታደሮች ላይ አፀፋዊ  እርምጃ በመውሰድ ወረዳውን ዳግም ለመቆጣጠር ያደረጉት ሙከራ ከሽፎ ከፍተኛ ኪሣራን አከናንቧቸው በውረደት እንዲሸሹ መደረጋቸው ታውቋል። (ምስል፦ በታጣቂዎቹ ቁጥጥር ስር የዋሉ የአገዛዙ ተሽከርካሪዎች)

Mereja TV
18 134
አፋብን በላይ ዕዝ መይሳው ካሳ ኮር 16ኛ ልባርጋቸው ሙጨ ክ/ር ግዙፍ 2ኛ ዙር ኮማንዶ የፋኖ ሰራዊት አስመረቀ! ትናንት ሰኔ 02/2018 ጣና ብርጌድ በመባል የሚታዎቀው አደረጃጀት አሁን ላይ ከቀጠ
አፋብን በላይ ዕዝ መይሳው ካሳ ኮር 16ኛ ልባርጋቸው ሙጨ ክ/ር ግዙፍ 2ኛ ዙር ኮማንዶ የፋኖ ሰራዊት አስመረቀ! ትናንት ሰኔ 02/2018 ጣና ብርጌድ በመባል የሚታዎቀው አደረጃጀት አሁን ላይ ከቀጠናው አቀማመጥ ለግዳጅ በሚያመች መንገድ የመፍትሔ አቅጣጫዎችን በዉል በማጤንና በመምከር ታላቁ አርበኛ ልባርጋቸው ሙጨ ያለመውን ትክክለኛ የመታገያ ሀሳብ ከዳር ለማድረስ ጥልቅ ውይይት በማድረግ የክ/ሩን አደረጃጀት አፋብን በላይ ዕዝ መይሳው ካሳ ኮር 16ኛ ልባርጋቸው ሙጨ በሚል ስያሜና በስሩ አራት ሬጅመንቶችን በማደራጀት ካጠናቀቀ የሰነባበተ ሲሆን ለወራት በአስቸጋሪ ሁኔታ ብዙ መሰናክሎችን በማለፍ በተለይ የታላቁ አርበኛ ልባርጋቸው መስዋትነት ሳይበግራቸው እንደ ታጋይ በቁጭት የተሻለ በመስራት አንድ ልቡ ቢሰዋ እሽ ልቡ ይወለዳል በማለት ስልጠናውን በብቃት ማጠናቀቅ ተችሏል። ምንጭ፦ አፋብን በላይ ዕዝ መይሳው ካሳ ኮር ሕዝብ ግንኙነት ክፍል!

Mereja TV
18 134
በአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነዉ ዕዝ ዓፄ ዘርዓያዕቆብ ኮር ነጎድጓድ ክፍለ ጦር 2ኛ ሻለቃ በሰራችው ድንቅ ና ልዩ የከተማ ውስጥ ኦፕሬሽን ካለምንም የተኩስ ልውውጥ የአገዛዙን የሚሊሻ ሻንበል መ
በአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነዉ ዕዝ ዓፄ ዘርዓያዕቆብ ኮር ነጎድጓድ ክፍለ ጦር 2ኛ ሻለቃ በሰራችው ድንቅ ና ልዩ የከተማ ውስጥ ኦፕሬሽን ካለምንም የተኩስ ልውውጥ የአገዛዙን የሚሊሻ ሻንበል መሪ ከነ ሙሉ ትጥቁ ጋማውን አንጠልጥላ በድል ተመልሳለች። የነጎድጓድ ክፍለ ጦር 2ኛ ሻለቃ ሰኔ 1/2018 ዓ/ም ከሌሊቱ 10:00 ሰዓት ገደማ ላይ በደብረ ብርሃን ከተማ ዙሪያ በሚገኘው በሲያደብርናዋዩ ወረዳ ስር ልዩ ስሙ አንጨቆረር ከተማ ድረስ ዘልቃ በመግባት በወሰደችው የተጠና ልዩ ኦፕሬሽን የአገዛዙን ወንበር አስጠባቂ ሚሊሻ ሻምበል መሪ የሆነውን መካሻ አግደው በጋሻው የሚባለውን ባንዳ ሚሊሻ ከነሙሉ ትጥቁ ስታወጣ አቶ መካሻ አግደው በበኩላቸው ይሕንን ብለዋ፡  ፋኖ እደመብረቅ ድንገት ከፊቴ ሲበራብኝ  የእምነታቸውና የታማኝነታቸው ልክ ገብቶኛል ስለሆነም በአገዛዙ እንደኔ የተታለላችሁ አድማ ብተና ና ሚሊሻወች አገዛዙ አያዋጣም እኔ አረጋግጫለሁ ስለዚሕ እናተም ተረዱና ወደ ፋኖ ተቀላቀሉ ሲሉ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል። የፋኖ አናብስቶቹም ይሕንን ሲሉ መልዕታቸውን አስተላልፈዋል ፡ ከአገዛዙ ጎን የተሠለፋችሁ ሁሉ እኛ ስራችን ነውና ከዚሕ ብትማሩ ይበጃችኋል ብለዋል ። ምንጭ፦አፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ!

Mereja TV
18 134
ለኢትዮ 251 ሚዲያ ተከታታዮችና ቤተሰቦች ተወዳጁ “ኢትዮ 251 ዛሬ” ዝግጅታችን በአዲስ መልክ በመረጃ ቴሌቪዥን በኩል በቀጥታ ወደ እናንተ መድረስ መጀመሩን በታላቅ ደስታ እንገልጻለን! ​ዕለታዊና
ለኢትዮ 251 ሚዲያ ተከታታዮችና ቤተሰቦች ተወዳጁ “ኢትዮ 251 ዛሬ” ዝግጅታችን በአዲስ መልክ በመረጃ ቴሌቪዥን በኩል በቀጥታ ወደ እናንተ መድረስ መጀመሩን በታላቅ ደስታ እንገልጻለን! ​ዕለታዊና ወቅታዊ ይዘቶችንና ልዩ ልዩ አጀንዳዎች የሚቀርቡበት “251 ዛሬ” ፕሮግራማችን፣ ዘወትር ከሰኞ እስከ ቅዳሜ በኢትዮጵያ ሰአት አቆጣጠር ምሽት 2:00 ጀምሮ በመረጃ ቴሌቪዥንና በኢትዮ 251 ሚዲያ ሶሻል ሚዲያ አማራጮች ወደ እናንተ ይደርሳል። በመረጃ ቴሌቪዥን ​📡 የሳተላይት ስርጭት መረጃ (Nilesat)፦ ​🛰️ ሳተላይት (Satellite): Nilesat / Eutelsat 8 West B (8°W) ​📡 ፍሪኩዌንሲ (Frequency): 11636 MHz (ወይም 11637) ​↕️ ፖላራይዜሽን (Polarization): Vertical (V) / ቨርቲካል ​🔄 ሲምቦል ሬት (Symbol Rate): 27500 ​🔢 FEC: 5/6 እንዲሁም በቴሌግራም:- https://t.me/ethio251media በዋትስአፕ:- https://whatsapp.com/channel/0029Vb6SADMFy72J1pBscv40 በX (ትዊተር) ፡- https://x.com/251Media ፈጣንና ወቅታዊ መረጃዎችን ወደ እናንተ እንደርሳለን። @ethio251media

Mereja TV
18 134
ውድ የአሻራ ሚዲያ ተከታታዮች: የመረጃ ቲቪ ሳተላይት ስርጭት በአዲስ መልክ ተመልሷል! አሻራ ሚዲያም በዚሁ በመረጃ ቴሌቪዥን መረጃዎቻን ወደ እናንተ ለማድረስ መዘጋጀታችንን የምናሳውቀው በደስታ ነው
ውድ የአሻራ ሚዲያ ተከታታዮች: የመረጃ ቲቪ ሳተላይት ስርጭት በአዲስ መልክ ተመልሷል! አሻራ ሚዲያም በዚሁ በመረጃ ቴሌቪዥን መረጃዎቻን ወደ እናንተ ለማድረስ መዘጋጀታችንን የምናሳውቀው በደስታ ነው ። ዘወትር ከሰኞ እስከ እሁድ ከምሽቱ 1፡00 ሰዓት (የኢትዮጵያ አቆጣጠር) ስለምናስተላልፍ በNailesat /Eutelsat 8°w -11636/11637 frequency -polarization verticsl sybol rate 27500 -5/6 fec እንገኛለ፤ ፈልጉን።

Mereja TV
18 134
204ኛ አስቻለው ደሴ ኮር ለወራት ያሰለጠናቸውን የፋኖ ሠራዊት አባላትን አስመረቀ። አፋብን ጎንደር ጠቅላይ ግዛት በላይ ዕዝ 204ኛ አስቻለው ደሴ ኮር ግዙፉ እቴጌ ጣይቱ ክፍለ ጦር ለወራት ያሰለጠና
204ኛ አስቻለው ደሴ ኮር ለወራት ያሰለጠናቸውን የፋኖ ሠራዊት አባላትን አስመረቀ። አፋብን ጎንደር ጠቅላይ ግዛት በላይ ዕዝ 204ኛ አስቻለው ደሴ ኮር ግዙፉ እቴጌ ጣይቱ ክፍለ ጦር ለወራት ያሰለጠናቸውን የፋኖ ሰራዊት አባላት በዛሬው ዕለት በደማቅ ሥነ-ሥርዓት አስመርቋል። በምረቃ ሥነ-ሥርዓቱ ላይ የዕዝ፣ የኮር እና የክፍለ ጦር ከፍተኛ አመራሮች፣ ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች፣ የሀይማኖት አባቶች፣ የሀገር ሽማግሌዎች፣ ወጣቶች እና የአካባቢው ማኅበረሰብ አባላት ተገኝተዋል። የኮሩ ዋና አዛዥ አርበኛ ተሾመ አበባውን ጨምሮ ከፍተኛ አመራሮች በመርሃ ግብሩ ላይ ተሳትፈዋል። በዕለቱ የተገኙት ክቡር እንግዳ ባስተላለፉት መልዕክት፣ “ይህ የኮማንዶ ኃይል የአማራን ህልውና ከማስከበር ባለፈ ለሕዝቡ መከታና ጋሻ በመሆን ትልቅ አቅም የሚፈጥር እና ጠንካራ አሸናፊ ኃይል ነው” ብለዋል። ተመራቂዎቹ በቆይታቸው ወቅት የወታደራዊ ስልጠና ንድፈ ሐሳብን ከተግባራዊ ልምምድ ጋር በማጣመር በቂ ዝግጅት ማድረጋቸው ተገልጿል። በምረቃው ሥነ-ሥርዓቱም የሰለጠኑበትን ጥበብና ወታደራዊ ዝግጁነታቸውን የሚያሳዩ የማርሽ ትርኢቶችና ሌሎች ልዩ ልዩ ትዕይንቶች ቀርበዋል። በተጨማሪም በስልጠናቸው ከፍተኛ ውጤትና ዓርአያነት ላሳዩ የኮማንዶ አባላት የዕውቅናና የሽልማት አሰጣጥ ተከናውኗል። 204ኛ አስቻለው ደሴ ኮር የተጣለበትን ታሪካዊ ኃላፊነት ለመወጣትና የሕዝቡን ዘላቂ ሰላም ለማረጋገጥ መሰል የሰው ኃይል ግንባታዎችን አጠናክሮ እንደሚቀጥል በዕለቱ ተገልጿል። ምንጭ፦ በአፋብን ጎንደር ጠቅላይ ግዛት በላይ ዕዝ 204ኛ አስቻለው ደሴ ኮር ሕዝብ ግንኙነት ክፍል!

Mereja TV
18 134
photo content

Mereja TV
18 134
ዋለ አባተን ጨምሮ የምስራቅ ጎጃም ካድሪን በእንባ ያራጨው የሻለቃ በርይሁን ውዱ ድምሰሳ በተጨማሪ ደግሞ 6 አድማ ብተናዎችን ወደ ጥቁር አንበሳ ተልከዋል። ከታች በምስሉ ላይ የሚታየው የ36ኛ ሻለቃ
ዋለ አባተን ጨምሮ የምስራቅ ጎጃም ካድሪን በእንባ ያራጨው የሻለቃ በርይሁን ውዱ ድምሰሳ በተጨማሪ ደግሞ 6 አድማ ብተናዎችን ወደ ጥቁር አንበሳ ተልከዋል። ከታች በምስሉ ላይ የሚታየው የ36ኛ ሻለቃ የአድማ ብተና አዛዥ ሻለቃ በርይሁን ውዱ በጀብደኛው 206ኛ ኮር 14ኛ ክ/ጦር በጅበላ ሙተራ ሻለቃ የተደመሰሰ ነው። ጠንካራ የሚባሉ አራት አጃቢዎቹን አስከትሎ ከ23 የሰራዊት አባላት ጋር ከደብረ ማርቆስ ወደ ሊባኖስ እየሔደ ባለበት የቦ ማርያም አካባቢ በተደረገበት የደፈጣ ጥቃት ድባቅ ተመቷል። ዋለ አባተ የምስራቅ ጎጃም አስተዳደሪ ስቅስቅ ብሎ ያለቀሰበት ትልቅ ድል ተቀናጅተናል። የደብረ ማርቆስ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ፣ የብልፅግና ሹማምንትና አዛውንት ደረት እየደቁ በሚገኙበት በዚህ ስዓት በደብረ ማርቆስ ሆስፒታል በነፍስ ውጭ ነፍስ ግቢ ማጣጣር ላይ የነበሩት ፦ 1. ግዛት ወርቁ 2. ሰጠኝ አላምነህ 3.ጌታሰው  ታደሰ 4. ማሙሸ አዳነ 5. ፈለቀ ጌታቼው 6. መሀመድ አህመድ ህይወታቸውን በደብረ ማርቆስ ሆስፒታል መታደግ ባለመቻሉ ወደ ጥቁር አንበሳ ተልከዋል። 1. ሁሴን ያሲን-  ደብረ ማርቆስ ሆስፒታል የሚገኝ ከባድ ቁስለኛ 2.ፋሲል ሲሳይ- ቀላል ቁስለኛ። በዚህ ስዓት የደብረ ማርቆስ ከተማ ነዋሪዎች በጀግኖች ልጆቻቸው ጀብድ በሃሴት እየቦረቁ መሆናቸውን ታውቋል። ምንጭ፦ በአፋብን ቴዎድሮስ ዕዝ 206ኛ ኮር ህዝብ ግንኙነት ክፍል!