uz
Feedback
Mereja TV

Mereja TV

Kanalga Telegram’da o‘tish

Please send us photos, videos and information to our Telegram account: @realmerejatv

Ko'proq ko'rsatish

📈 Telegram kanali Mereja TV analitikasi

Mereja TV (@merejamedia) Amxar til segmentidagi kanali faol ishtirokchi. Hozirda hamjamiyat 17 806 obunachidan iborat bo'lib, Yangiliklar & Media toifasida 12 666-o'rinni va Efiopiya mintaqasida 1 914-o'rinni egallagan.

📊 Auditoriya ko‘rsatkichlari va dinamika

невідомо sanasidan buyon loyiha tez o‘sib, 17 806 obunachiga ega bo‘ldi.

01 Avgust, 2026 dagi oxirgi ma’lumotlarga ko‘ra kanal barqaror faollikka ega. Oxirgi 30 kunda obunachilar soni -248 ga, so‘nggi 24 soatda esa -1 ga o‘zgardi va umumiy qamrov yuqori darajada qolmoqda.

  • Tasdiqlash holati: Tasdiqlanmagan
  • Jalb etish (ER): Auditoriya o‘rtacha 10.83% darajada jalb etiladi. Nashrdan keyingi dastlabki 24 soatda kontent odatda umumiy obunachilar sonining 6.69% ini tashkil etuvchi reaksiyalarni to‘playdi.
  • Post qamrovi: Har bir post o‘rtacha 1 928 marta ko‘riladi; birinchi sutkada odatda 1 191 ta ko‘rish yig‘iladi.
  • Reaksiyalar va o‘zaro ta’sir: Auditoriya faol: har bir postga o‘rtacha 6 ta reaksiya keladi.

📝 Tavsif va kontent siyosati

Muallif resursni shaxsiy fikrni ifoda etish maydoni sifatida ta’riflaydi:
Please send us photos, videos and information to our Telegram account: @realmerejatv

Yuqori yangilanish chastotasi (oxirgi ma’lumot 02 Avgust, 2026 da olingan) sababli kanal doimo dolzarb va katta qamrovli bo‘lib qoladi. Analitika auditoriya kontent bilan faol hamkorlik qilishini, uni Yangiliklar & Media toifasidagi muhim ta’sir nuqtasiga aylantirishini ko‘rsatadi.

17 806
Obunachilar
-124 soatlar
-307 kunlar
-24830 kunlar
Postlar arxiv
Mereja TV
17 808
በአፋብን ወለጋ ቢዛሞ ቀጠና አይሻ ሰይድ ዕዝ ይበልጣል መኮነን አዲስ አለም ክ/ጦር ባደረገው የተጠና ኦፕሬሽን በኪረሙ ወረዳ ስር ቦቃ፣ ነጭሎ፣ ወዴሳ ዲማ የተባሉ ሦስት ቀበሌዎችን ጨምሮ ሃሮ አዲስ አለም ከተማን መቆጣጠሩን አስታወቀ። ትናንት ሃምሌ 23/2018 ዓ/ም በተካሄደው በዚህ አውደ ውጊያ፡ የብልፅግና መከላከያ ሠራዊት ከክልሉ ጥምር ኃይል በጋራ ሆኖ የተሰለፈ ቢሆንም ከወደ ፋኖ የተሰነዘረበትን ጥቃት መቋቋም አቅቶ ተሽመድምዷል። በዚህ ተጋድሎ 36 የጠላት ወታደሮች ሲገደሉ፡  42 ወታደሮች ደግሞ ሲቆስሉ በድምሩ 78 የአገዛዙ ወታደሮችን ከስምሪት ውጭ ማድረግ ተችሏል። በተጋድሎው፡ ጀግኖቹ የይበልጣል መኮነን አዲስ አለም ክ/ጦር አርበኞች ጠላትን አይቀጡ ቅጣት በመቅጣት አዲስ አለም ከተማን ጨምሮ በጊዳ ኪረሙ ወረዳ ስር ቦቃ፣ ነጭሎ፣ ወዴሳ ዲማ የተባሉ ሦስት ቀበሌዎችን በቁጥጥራቸው ስር አስገብተዋል። በተያያዘ! ከሆሮ ጉዱሩ ወለጋ ዞን አቤ ዶንጎሮ ወረዳ መነሻውን ያደረገ የጠላት ጦር ወደ ምስራቅ ወለጋ ዞን ጊዳ ኪረሙ ወረዳ እገዛ ለማረግ እየተንቀሳቀሰ እንዳለ በአይሻ ሰይድ ዕዝ ስር የጌጤ ግርማ መብረቁ ክ/ጦር አርበኞች መንደር 21 ቀበሌ ልዩ ቦታው አንገር መድሃኒያለም ላይ በፈፀሙት የደፈጣ ጥቃት፡ በርካታ የጠላት ወታደሮች ሙትና ቁስለኛ ሲደረጉ፡ ጠላት የእንቅስቃሴ እቅዱ መክኖበት ብትንትኑ ወጥቷል። በተመሣሣይ ከይበልጣል መኮነን አዲስ አለም ክ/ጦር እና ከአንገር ጉትን ክ/ጦር የተወጣጡ አሃዶች በቅንጅት በወሰዱት እርምጃ በርካታ የጠላትን ጦር ደምስሰው በኪረሙ ወረዳ የጎላ ወታደራዊ ጠቀሜታ ያላት ቆፍቆፌ ከተማን በቁጥጥራቸው ስር አስገብተዋል። በዚህ ስፍራ ከመደምሰስ የተረፈው የጠላት ኃይል ሙትና ቁስለኛውን እያዝረከረከ የጊዳ አያና ወረዳ መቀመጫ ወደሆነችው ጊዳ ከተማ ፈርጥጧል። ከወደፋኖ የተወሰደበትን እርምጃ መቋቋም ያልቻለው የአገዛዙ ሰራዊት እንደለመደው ንፁኋንን ኢላማ ያደረገ የከባድ መሳሪያ ድብደባ በማድረግ ወደሳ ዳማ በተባለ ቀበሌ ላይ የ13፣ የ15ና የ16 ዓመት ታዳጊ ልጆችን በአሰቃቂ ሁኔታ መግደሉ ነው የተሰማው።

Mereja TV
17 808
በጊዳ ኪረሙ ወረዳ በተደረገ ውጊያ የጎላ ወታደራዊ ጠቀሜታ ያላት ቆፍቆፌና አከባቢዋ በፋኖ ቁጥጥር ስር ዋለ! በአፋብን ወለጋ ቢዛሞ ቀጠና የአይሻ ሰይድ ዕዝ አርበኞች በቅንጅት በወሰዱት እርምጃ በርካ
በጊዳ ኪረሙ ወረዳ በተደረገ ውጊያ የጎላ ወታደራዊ ጠቀሜታ ያላት ቆፍቆፌና አከባቢዋ በፋኖ ቁጥጥር ስር ዋለ! በአፋብን ወለጋ ቢዛሞ ቀጠና የአይሻ ሰይድ ዕዝ አርበኞች በቅንጅት በወሰዱት እርምጃ በርካታ የጠላትን ጦር ደምስሰው በኪረሙ ወረዳ የጎላ ወታደራዊ ስትራቴጂካዊ ጠቀሜታ ያላት ቆፍቆፌ ከተማን በቁጥጥራቸው ስር አስገብተዋል። በዚህ ስፍራ ከመደምሰስ የተረፈው የጠላት ኃይል ሙትና ቁስለኛውን እያዝረከረከ የጊዳ አያና ወረዳ መቀመጫ ወደሆነችው ጊዳ ከተማ ፈርጥጧል።

Mereja TV
17 808
የ303ኛ አሳምነው ኮር አርበኞች በአገዛዙ ወታደር ላይ የማያዳግም እርምጃ በመውሰድ ድል ተቀዳጁ! በአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ አፋብን ወሎ ቤተ -አማራ ምኒልክ ዕዝ 303ኛ አሳምነው ኮር አካል የሆነ
የ303ኛ አሳምነው ኮር አርበኞች በአገዛዙ ወታደር ላይ የማያዳግም እርምጃ በመውሰድ ድል ተቀዳጁ! በአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ አፋብን ወሎ ቤተ -አማራ ምኒልክ ዕዝ 303ኛ አሳምነው ኮር አካል የሆነው 14ኛ (ጀኔራል ሃይሉ ከበደ) ክፍለ ጦር በዋግህምራ ዞን ጋዝጊብላ ወረዳ  09 ቀበሌ ላልኪው የ አፓርታይዱ አብይ አህመድ ወንበር አስጠባቂ  ወታደር ላይ በተሰላና በታቀደ የተጠናከረ ሽምቅ ውጊያ እና ተስቦ በመግባት ከተኛበት ምሽግ ላይ የማያዳግም እርምጃ በመውሰድ ከፍተኛ ድል ተቀዳጅተዋል። የሽምቅ ውጊው ሐምሌ 23ለ24  ሃሙስ ለአርብ  ከሌሊቱ 6:00 ሰዓት እስከ ንጋት 11:00 ሰዓት የተጠናከረ ሲሆን ልዩ ቦታው ገበያው ሰፈር ወይም በተለምዶ ጊወርጊስ ትኩ ተብሎ ከሚጠራው ተራራ ላይ መሽጎ የነበረውን የጥላት ሃይል በሽምቅ ከማጥቃት ሙሉ በሙሉ ምሽጉን በማስለቀቅ በአገዛዙ ላይ ሰብአዊ እና ቁሳዊ ኪሳራ አድርሰውበታል ። በተጠናከረው የሽምቅ ውጊያ ከ17በላይ የጥላት ሃይል ሲደመሰስ 4 ምርኮኛ፣9ጥቁር ክላሽ ፣1500 የብሬን ተተኳሽ፣725 የክላሽ ተተኴሽ ፣2 ኤፍዋን የእጅ ቦንብ ፣አንድ የወገብና አንድ የደረት ትጥቅ ተማርኳል ሲል የ303ኛ አሳምነው ኮር ህዝብ ግንኙነት መረጃውን አድርሷል። ምንጭ፦በአፋብን ምኒልክ ዕዝ ሚዲያና ኮሙኒኬሽን መምሪያ!

Mereja TV
17 808
WCC condemns deadly drone strike on monastery in Ethiopia’s Amhara Region World Council of Churches general secretary Rev. Prof. Dr Jerry Pillay strongly condemned the reported drone strike on the Abbay Giyorgis St Arsema Unity Monastery in Ethiopia’s Amhara Region on 22 July. The strike reportedly killed two civilians and injured several others, including women who had gathered to prepare food for a religious commemoration. “The reported attack on a place of worship and the killing and wounding of civilians is deeply disturbing and utterly unacceptable,” said Pillay. “Religious institutions and civilians must never be targeted or placed in the path of military operations.” He called for an end to the continued violence and reported attacks on civilian communities and religious sites in the Amhara Region. “The World Council of Churches calls for an immediate, credible, transparent, and impartial investigation into this incident and for those responsible to be held accountable,” Pillay said. “All parties to the conflict must respect international humanitarian law and their responsibility to protect civilians and religious institutions.” Pillay urged the government of Ethiopia and all parties to the conflict to end the cycle of violence, stop attacks that cause suffering of innocent people, and pursue a peaceful resolution to the ongoing conflict. “We extend our deepest condolences to the families of those killed, pray for the healing of the injured, and stand in Christian solidarity with the Ethiopian Orthodox Tewahedo Church and the people of Ethiopia,” he concluded. “May the God of peace comfort those who mourn, protect the innocent, and guide Ethiopia towards justice, reconciliation, and sustainable peace.” https://www.oikoumene.org/resources/documents/wcc-general-secretary-condemns-deadly-drone-strike-on-monastery-in-ethiopias-amhara-region

Mereja TV
17 808

Mereja TV
17 808
Having been defeated on the battlefield, the Abiy Ahmed government continues its inhumane actions.
Having been defeated on the battlefield, the Abiy Ahmed government continues its inhumane actions.

Mereja TV
17 808
photo content

Mereja TV
17 808
ሐምሌ 19 ቀን 2018 ዓ.ም የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ የቴዎድሮስ ዕዝ የአመራር ሪፎርም መጠናቀቅን አስመልክቶ የተሰጠ መግለጫ የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ የቴዎድሮስ ዕዝ ላለፉት ወራት የአመራር ሪፎርም ለመስራት ከፍተኛ ስራ ሲሰራ የቆየ መሆኑ ይታወቃል። በዚህ ሂደት ዕዙ መዋቅራዊ አንድነቱ ተጠብቆ ጤናማ ሽግግር እንዲያደርግ ሂደቱን በጥንቃቄ እና በትዕግሥት መምራት አስፈላጊ በመሆኑ በሚፈለገው መልኩ በፍጥነት ሳይጠናቀቅ ቆይቷል። የአደረጃጀት ፈተና ከድርጅት ዕድገት ጋር ተያይዞ በየጊዜው የሚፈጠር ቢሆንም ከውጭ ወደ ውስጥ የሚሰነዘሩ ከፋፋይ ጥቃቶችን እየመከቱ ተፈጥሯዊውን ውስጣዊ ትግል ለመዋቅራዊ ዕድገት በሚጠቅም መልኩ ለማዋል በጥበብ የተመራ ትግል ተደርጓል። ድርጅታዊ መስመርን ለማስጠበቅ የተሄደበት ውስጠ ድርጅታዊ አሰራር ተገቢ እና ትክክል መሆኑ የዕዙን መዋቅራዊ አንድነት አስጠብቆ ለላቀ ግዳጅ የሚያበቃ ውጤት ላይ እንዲደረስ አስችሏል። ይህ የዕዝ አመራር ሪፎርም በተለያዬ ደረጃ ውስጥ ያለፈ እና የመዋቅሩ ተዋረዳዊ ተሳትፎ የነበረበት ነው። የዕዙ ስራ አስፈጻሚ የሪፎርም ስራ አፈጻጸም ሂሩት ላይ የዕዙ ተወካይ በሆኑ የፖሊት ቢሮ አባላት አማካኝነት የኮር እና የክፍለ ጦር አመራሮች ጋር ውይይት ተደርጓል። ቀጥሎም ምክትል መምሪያ ሀላፊዎች እና ሌሎች የክፍል ሀላፊዎችን አወያየቷል። በመጨረሻም በነዚህ መድረኮች የተገኘውን ግብአት በመውሰድ የዕዙ ስራ አስፈጻሚ የሪፎርም ኮሚቴ እንዲዋቀር ወስኖ፣ የአወቃቀር ሂደቱ የሚመራበትን መመሪያ አዘጋጅቶ ወደ ስራ ገብቷል። በዚህ መሠረት ከክፍለጦሮች፣ ከኮር እና ከምክትል መምሪያ ሀላፊዎች የተውጣጣ ኮሚቴ በማዋቀር የሪፎርም ኮሚቴው ተመሰርቷል። የዕዝ ስራ አስፈፃሚው በሰጠው መመሪያ እና ስልጣን መሠረት የሪፎርም ኮሚቴው የዕዙን የአመራር ሪፎርም ላይ ሰፊ ውይይት በማድረግ ስራውን ጨርሶ ፕሮፖዛሉን ለዕዙ ስራ አስፈጻሚ አቅርቧል። ስራ አስፈጻሚው የቀረበለት ፕሮፖዛል መነሻ አድርጎ ሰፊ ውይይት ካደረገ በኋላ የኮሚቴው ፕሮፖዛል ላይ መጠነኛ ማሻሻያ አድርጎ የዕዙን የአመራር ሪፎርም የመጨረሻ ዝርዝር አጽድቋል። በዚህም መሠረት የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ - ጎጃም ጠቅላይ ግዛት ቴዎድሮስ ዕዝ የአፋብን መተዳደሪያ ደንብ አንቀፅ 60 ስር በተቀመጠው መዋቅር መሰረት ከዚህ በታች በተዘረዘረው መልኩ ተደራጅቷል። 1) ሰብሳቢ:- አርበኛ ተፈሪ ካሳሁን 2) ም/ሰብሳቢ:- አርበኛ ጎበዜ ጌታቸው 3) ወታደራዊ አዛዥ:- ሻለቃ የኔአለም ዘለቀ 3.1) ምክትል ወታደራዊ አዛዥ:- መቶ አለቃ እሱባለው ዋለ 4)ፖለቲካ መምሪያ ኃላፊ:- አርበኛ ግሩም ምሳሌ 4.1) ምክትል:- አርበኛ አማረ ካሴ 5) ፅህፈት ቤት ኃላፊ:- አርበኛ ናትናኤል ስናማው 5.1)ምክትል:- አርበኛ ብዙነህ እምቢያለ 6) አደረጃጀት መምሪያ ኃላፊ:- አርበኛ እስቲበል አለሙ 6.1) ምክትል:- አርበኛ ደመላሽ አንድነው 7) የሕዝብ ግንኙነት መምሪያ ኃላፊ:- አርበኛ ወግደረስ ጤናው 7.1)ምክትል:- አርበኛ ታደሰ አስማረ 8)ጥናትና ስትራቴጂ ጉዳዮች መምሪያ:- አርበኛ ዳሞት አለኸኝ 8.1)ምክትል:- አርበኛ መንግስቱ አማረ 9)ፋይናንስ እና ግዥ አስተዳደር:- አርበኛ ይትባረክ አንዳርጌ 9.1)ምክትል:- አርበኛ ያሬድ በቀለ 10)የሕዝብ አስተዳደር መምሪያ:- አርበኛ ዘመን ተሻለ 10.1)ምክትል:- አርበኛ በለጠ ልየው 11) ሴቶች ጉዳይ መምሪያ- ፋኒት አትጠገብ አጥናፉ 11.1)ምክትል:- ፋኒት ክብራለም አያልነህ 12) ማሕበራዊ ጉዳይ መምሪያ:- አርበኛ ላይችሉህ ገበየሁ 12.1) ምክትል:- አርበኛ በላይነህ አለምነህ 13) የሰው ሃብት -ዳኛው ሽባባው 13.1) ምክትል:- አርበኛ በረከት አጥናፉ 14)ት/ት እና ስልጠና መምሪያ:- አርበኛ ክንፈመላክ ካሳ 14.1)ምክትል:- አርበኛ ዘውዳለም አዱኛ 15) መካናይዝድ ጦር መምሪያ:- ኮሎኔል አደመ ልጃለም 15.1) ምክትል:- መቶ አለቃ ሳሙኤል አታላይ 16)ህግ እና ስነስርዓት መምሪያ:- አርበኛ ዘማርያም እስከዚያ 16.1) ምክትል:- አርበኛ ቻላቸው ታፈረ 17) ሀብት አፈላላጊ መምሪያ- አርበኛ ሀይለሚካኤል ባዬህ 17.1) ምክትል:- አርበኛ ደሴ ጌታሁን 18) እቅድ ዝግጅትና ግምገማ መምሪያ:- አርበኛ የሻነው መለሰ 18.1) ምክትል:- አርበኛ አታላይ ሞሴ 19) ዘመቻ መምሪያ-አምሳ አለቃ ታደሰ ልንገሬ 19.1) ምክትል:- መቶ አለቃ አጃናው ጥላሁን 20) ሎጀስቲክ መምሪያ:- አርበኛ ይርሳው ደምስ 20.1) ምክትል:- መቶ አለቃ አስረስ ምህረቴ 21) ወ/አስተዳደር መምሪያ- መቶ አለቃ ያሬድ ጫኔ 21.1) ምክትል:- 50 አለቃ ይበልጣል መልካሙ 22)ወ/ስልጠና መምሪያ:- ሻምበል ጌትነት ንጉሴ 22.1) ምክትል:- አምሳ አለቃ ዘላለም ደሴ 23) ልዩ ዘመቻ መምሪያ- መቶ አለቃ ማርቆስ አሞኜ 23.1)/ምክትል:- ሻለቃ በላይ ብዙ አየሁ 24) መረጃ - ---------- 24.1) ምክትል-- -------- 25)ኢንዶክትርኔሽን መምሪያ:- መቶ አለቃ ጊዮን ጀንበሬ 25.1) ምክትል- መቶ አለቃ ገረመው አጋዠ 26) ወታደራዊ እቅድ እና ስትራቴጅ:- ሃምሳ አለቃ ስማቼው ቢሻው 26.1) ምክትል:- መቶ አለቃ ለዓለም ጌታሁን 27) ወታደራዊ መረጃ------ 27.1) ምክትል- ------- 28) ጤና መምሪያ:- ዶክተር እንዳላማው ጤናው 28.1) ምክትል-- ዶክተር ደመቀ አያሌው

Mereja TV
17 808
የበቃና የነቃ የፋኖ ኃይል የብልፅግናውን አገዛዝ የመጨረሻ እስንፋስ ፀጥ ለማድረግ በተጠንቀቅ ቆሟል።

Mereja TV
17 808
photo content

Mereja TV
17 808
የመከላከያ መንገድ መሪ የነበሩ የዞንና የወረዳ ካድሬዎች ተገደሉ/ ተሽከርካሪው ወደመ! በአፋብን ወለጋ/ቢዛሞ ቀጠና አይሻ ሰይድ ዕዝ ስር የሚገኙ ክፍለ ጦሮች በምስራቅ ወለጋ እና በሆሮ ጉዱሩ ወለጋ ዞኖች ባካሄዱት ተከታታይ የተቀናጀ የፀረ-ማጥቃት እርምጃ፡ መንገድ መሪ ካድሬዎችን ጨምሮ በርካታ የጠላት ኃይልን በመደምሰስ የጦር መሣሪያዎችንና ወታደሮችን በመማረክ እንዲሁም ስትራቴጂካዊ አካባቢዎችን በመቆጣጠር አንፀባራቂ ድል ተቀዳጁ። አርበኞቹ ትናንት ሐምሌ 17/2018 ዓ.ም ከማለዳ ጀምሮ ባካሄዱት የተቀናጀ ኦፕሬሽን፡ የቀድሞው የሃሮ ሊሙ ወረዳ አስተዳዳሪና የአሁኑ የምስራቅ ወለጋ ዞን ወጣቶችና ስፖርት ፅህፈት ቤት ኃላፊው አቶ ደቻሳ ገነቲን ጨምሮ ሌሎች የብልፅግና መከላከያ ሰራዊቱን መንገድ ሲመሩ የነበሩ ብዛት ያላቸው የዞን፣ የወረዳና የከተማ አስተዳደር ካድሬዎችን መገደላቸውን መረብ ሚዲያ ለማረጋገጥ ችሏል። መንገድ መሪ ካድሬዎቹ የተገደሉት ከአንገር ጉትን ከተማ በ4km ርቀት ገደማ ላይ ልዩ ስሙ ነጩ መንገድ ተብሎ በሚጠራው አከባቢ ላይ ሲሆን፡ ከከተማዋ በቅርብ ርቀት የምትገኝ ወሳኝ ወታደራዊ ስፍራም በአርበኞቹ ቁጥጥር ስር መዋሏ ታውቋል። በአይሻ ሰይድ ዕዝ ስር የአንገር ጉትን ክፍለ ጦር አርበኞች በዚህ አከባቢ በወሰዱት እርምጃ ከተገደሉ መንገድ መሪ ካድሬዎች በተጨማሪ ተሳፍረውበት የነበረው ወታደራዊ ተሽከርካሪ ሙሉ በሙሉ መውደሙን ነው ጣቢያችን መረብ ሚዲያ ለማረጋገጥ የቻለው። በዕዙ ስር የአበጀ ጥበቡ ነበልባል ክፍለ ጦር አርበኞች ከጉትን ከተማ በቅርብ ርቀት መንደር 4 ቀበሌ በመግባት የጠላትን ኃይል ሙትና ቁስለኛ በማድረግ አካባቢውን ከጠላት ወታደሮች አፅድተው በቁጥጥራቸው ስር አስገብተዋል። በተመሣሣይ፡ በአይሻ ሰይድ ዕዝ ስር የታፈረ አለሙ ሳተናው ክፍለ ጦር አርበኞች በሆሮ ጉዱሩ ወለጋ ዞን አቤ ደንጎሮ ወረዳ ባካሄዱት ልዩ ወታደራዊ ኦፕሬሽን ስትራቴጂካዊቷ ቱሉጋና ከተማን ሙሉ በሙሉ በቁጥጥራቸው ስር ማስገባታቸውን የመረብ ሚዲያ የወለጋ ቢዛሞ ቀጠና ዘጋቢ ለማረጋገጥ ችሏል። ለቀናት በዘለቀው በዚህ የመከላከልና የመልሶ ማጥቃት  አውደ ውጊያ 31 ክላሽንኮቭ መሣሪያዎች በአርበኞቹ ቁጥጥር ስር ሲውል፡አንድ በሲቪል ሲንቀሳቀስ የነበረ የደህንነት አባልን ጨምሮ 5 የገዳ ኮማንዶ አባላት ከነ ሙሉ ትጥቃቸው እጅ ከፈንጅ ተማርከዋል።

Mereja TV
17 808
ሐምሌ 18 ቀን 2018 ዓ.ም የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ ጎንደር ጠቅላይ ግዛት በላይ ዘለቀ ዕዝ የአመራር ምደባ አድርጓል። የቀድሞወቹ ሁለት እዝ አመራሮች በጋራ በአካል በመገናኘት ባካሄዱት ጉባኤ የተዋሃደው የጎንደር ጠቅላይ ግዛት በላይ ዕዝ አመራር በሚከተለው መልኩ የኃላፊነት ምደባ ተደርጓል። የሰብሳቢውን ቦታ አርበኛ ዮሐንስ ንጉሱ እና አርበኛ ባዬ ቀናው ለ3 ወራት ያክል በጥምር የሚመሩት ይሆናል፡፡ 1ኛ/ ከሁለቱ አርበኞች በተጨማሪ የተመደቡ የስራ አስፈፃሚ አባላት:- ተቀ/ምክ/ሰብሳቢ…………………አርበኛ ሰለሞን አጣናው ም/ሰብሳቢ ለፖለቲካ ጉዳዮች………አርበኛ ኪሩቤል ጎቤ ወታደራዊ አዛዥ…………………….አርበኛ ደረጀ በላይ ምክ/ወታደራዊ አዛዥ………………አርበኛ አሻምበል አምሳሉ ማዘንጊያ ምክ/ወታራዊ አዛዥ ለአስተዳደር ጉዳዮች....አርበኛ ሸጋ ጌታቸው ወታራዊ አማካሪ…………………………ኮ/ል አበራ አዛናው ፖለቲካ መምሪያ…………………..……አርበኛ አንተነህ ድረስ ዘመቻ መምሪያ……………………….አርበኛ ተሾመ አበባው ጽ/ቤት ኃላፊ……………………….አርበኛ በየነ አለማው አደረጃጀት ጉዳይ …..……………..አርበኛ አበበ መልኬ ፋይናንስና ግዥ መምሪያ……….አርበኛ ሐብታሙ ሙላው ሎጅስቲክ መምሪያ…………….………አርበኛ በላዬ ዘለቀ ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ………….…አርበኛ ጋሻው ግዛት ሕዝብ አስተዳደር መምሪያ………….አርበኛ ንጉሴ አዱኛ ልዩ ዘመቻ መምሪያ..……………….አርበኛ አስፋው ሰርፀ ወታደራዊ ስልጠና መምሪያ…….……አርበኛ ጌታሰው በሬ ወታደራዊ እቅድና ስትራቴጂ መምሪያ…..አርበኛ ተመስገን አብርሃም ምክ/ዘመቻ መምሪያ ኃላፊ……..……አርበኛ ስጦታው ዳኛው/ባሻ ሜካናይዝድ ጦር መምሪያ………..አርበኛ ሲሳይ አሸብር ቴክኖሎጅና ምህንድስና መምሪያ……አርበኛ ያለው አዱኛ ጥናትና ስትራቴጂ መምሪያ………..አርበኛ ዘመነ እረኛው ትምህርትና ስልጠና መምሪያ……….አርበኛ ዘላለም በላይነው ሕግና ስነ-ምግባር ጉዳይ መምሪያ……አርበኛ ማሩ ቢተው ማሕበራዊ ጉዳዮች መምሪያ………..አርበኛ ብዙአየሁ ወንድምነው ሴቶችና ወጣቶች መምሪያ………..አርበኝት አስምሪው መሳፍንት ተስፉ ሰው ሃብት አስተዳር መምሪያ….……አርበኛ አዳነ ፀጋ ሃብት አፈላላጊ መምሪያ….…………..አርበኛ ማሩ በሪሁን ኢንዶክትሪኔሸን መምሪያ…..………አርበኛ ተመስገን ውባንተ የውስጥ ኦዲት መምሪያ……………..አርበኛ ግዛቸው አሌ ጤና መምሪያ……………………………አርበኛ አታለለ ሰጠኝ እቅድ ዝግጅትና ግምገማ መምሪያ ……አርበኛ ታደሰ ወርቁ ቁጥጥርና ኦዲት ኮሚቴ ሰብሳቢ…………አርበኛ ባንቲደር እውነቱ ሕግና ስነ-ስርዓት ኮሚቴ ሰብሳቢ…………አርበኛ ወልደአረጋይ ሸርብ ወታራዊ ፍርድ ቤት ሰብሳቢ……………..አርበኛ ታርቆ ከበደ 2ኛ) ምክትል የስራ አስፈጻሚ መምሪያዎች ምክ/ፖለቲካ መምሪያ………………..…አርበኛ ዳኛው አጣናው ምክ/ጽ/ቤት………………………..አርበኛ መ/አ ገዳም ካሳ ምክ/አደረጃጀት ጉዳይ…………………...አርበኛ ብርሃኑ ነጋ ምክ/ፋይናንስና ግዥ መምሪያ…………..አርበኛ ስጦታው መልኬ ምክ/ሎጅስቲክ መምሪያ…………………አርበኛ ደፋሩ አቤ ምክ/ ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ…………አርበኛ ማንደፍሮ ተሰማ ምክ/ ሕዝብ አስተዳደር መምሪያ……….አርበኛ ዋሴ ታደሰ ምክ/ልዩ ዘመቻ መምሪያ..………………...አርበኛ ሙሉዬ ደሴ ምክ/ወታደራዊ ስልጠና መምሪያ…………ሻምበል መሳፍንት ተስፉ ምክ/ወታደራዊ እቅድና ስትራቴጂ………...አርበኛ እያቸው ብርሃኑ ምክ/ሜካናይዝድ ጦር መምሪያ…….…….አርበኛ ንጋት አየለ ምክ/ቴክኖሎጅና ምህንድስና መምሪያ…….አርበኛ አለሜ ባዬ ምክ/ጥናትና ስትራቴጂ መምሪያ………...አርበኛ ፋሲል ሙሏለም ምክ/ትምህርትና ስልጠና መምሪያ………..አርበኛ አብዩ ማሩ ምክ/ሕግና ስነ-ምግባር መምሪያ………..…አርበኛ ደመቀ አለሙ ምክ/ማሕበራዊ ጉዳዮች መምሪያ…………..አርበኛ ደምሰው ድረስ ምክ/ሴቶችና ወጣቶች መምሪያ……………….አርበኝት ገነት ፀጋው ምክ/ሰው ሃብት አስተዳደር መምሪያ………አርበኛ ወዳጅ አስፋው ምክ/ሃብት አፈላላጊ መምሪያ ….…………..አርበኛ አስማማው ዋለልኝ ምክ/ኢንዶክትሪኔሸን መምሪያ ….…………አርበኛ አዲሱ መሰለ ምክ/የውስጥ ኦዲት መምሪያ………………..አርበኛ መ/አ ቢራራ ምክ/ወታደራዊ መረጃና መገናኛ መምሪያ……አርበኛ ሚናስ አለማየሁ ምክ/ጤና መምሪያ…………………………..አርበኛ ምዕራፍ ሙጨ ምክ/እቅድ ዝግጅና ግምገማ መምሪያ……….አርበኛ መ/አ ኃይለየሱስ ታደሰ 3ኛ) ሌሎች የስራ ክፍል ኃላፊዎች፡- የሕዝብ ሰላምና ደህንነት ከፍል…………አርበኛ መለሰ ተሾመ ምርኮኛ አስተዳደር ከፍል …………….አርበኛ አለማየሁ ሰማ ወታደራዊ ቃል አቀባይ………………..አርበኛ ቢኒያም አለምነህ ቀጠናዊ ትብብር……………………...አርበኛ ዘመኑ ታደሰ ሰማዕታት ቤተሰብ ድጋፍ ክፍል………..አርበኛ አማኑኤል ተፈራ ስንቅ አቅርቦት ክፍል…………………..አርበኛ ክንዱ ግርማ ሒሳብ ሹም…………………………….አርበኛ አያናው አዱኛ መሰረተ-ልማትና ኢኮኖሚ ክፍል……..አርበኛ አበበ አመኑ ኦርዲናንስ……………………………..አርበኛ ዳንኤል አስረስ ፐርሶኔል …………………………….አርበኛ ዮናስ አያልቅበት ግዥ ክፍል ………………………….አርበኝት ትዕግስት ተረፈ ገንዘብ ያዥ……………….…………..አርበኛ መላክ ተስፋ ሕዝብ አገልግሎት ………………….አርበኛ አለባቸው ጌጡ ኪነ-ጥበብና መዝናኛ ክፍል…………..አርበኛ አስተውል አምሳሉ ታሪክና ማሕደር ክፍል ……………..አርበኛ አንዷለም አሰፋ አባት አርበኞች ማደራጃ ክፍል………አርበኛ ጌትነት ስመኝ ማሕበራዊ ፍርድ ሸንጎ………………..አርበኛ ማናለ ገላጋይ ፕሮጀክት ቀረፃና አስተዳደር …………አርበኛ ባንቲ ጌትነት

Mereja TV
17 808
ሐምሌ 18 ቀን 2018 ዓ.ም በብሔራዊ የምክክር ኮሚሽን ስም ዘረ ፈጁ አገዛዝ ያዘጋጀውን የብልጽግና እና ጀሌዎቹ ጉባኤ አስመልክቶ ከአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ የተሰጠ መግለጫ ለልዩነት እና ለጦርነት
+1
ሐምሌ 18 ቀን 2018 ዓ.ም በብሔራዊ የምክክር ኮሚሽን ስም ዘረ ፈጁ አገዛዝ ያዘጋጀውን የብልጽግና እና ጀሌዎቹ ጉባኤ አስመልክቶ ከአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ የተሰጠ መግለጫ ለልዩነት እና ለጦርነት ምክንያት በሆኑ አጀንዳወች ላይ አካታች ብሔራዊ ውይይት እና ምክክር ማድረግን በተመለከተ የኢትዮጵያ ህዝብ ለዘመናት ሲያቀርበው የቆዬ ጥያቄ መሆኑ ይታወቃል። ሀቀኛ ብሔራዊ ምክክር ማድረግ ለሀገር ዘላቂ ሰላም አስፈላጊ የመሆኑን ያህል የብሔራዊ ምክክር ሂደት በተለይም የምክክር ሂደቱ አካታችነት፣ የሚካሄድበት ነባራዊ ሁኔታ፣ ሂደቱን የሚመራው ተቋም አወቃቅር እና ተቋማዊ ገለልተኝነት፣ አሳታፊነት እና ሌሎችም ሁኔታወች በአግባቡ ካልታዩ ነባር ችግሮችን እና ቅራኔወችን ከማስፋት እና ከማወሳሰብ ያለፈ ፋይዳ አይኖረውም። በብልፅግና አገዛዝ ጦረኝነት እና ዘረ-ፈጅ የቀውስ አገዛዝ ምክንያት ዓመታትን የተሻገረ እና የሚሊዮኖችን ሕይወት ያመሰቃቀለ ደም አፋሳሽ ጦርነት ውስጥ ያለችው ሀገራችን፣ ይህን በህዝብ ላይ የተከፈተዉን ጦርነት ያወጀው አገዛዝ ጦርነትን ለማቆም ምንም አይነት ፍላጎት ባላሳየበት ሁኔታ ውስጥ የሚደረግ የምክክር ድግስ በጀት ከማባከን እና ለአገዛዙ የገጽታ ግምባታ ከመስራት ያለፈ ፋይዳ አይኖረውም። ባለፉት አመታት በዳበሳ ከሚታወቁ የሀገሪቱ እውነቶች መካክል ጦርነት ፣ ስደት፣ መፈናቀል ጅምላ ጭፍጨፋና ማንንነት መሰረት ያደረጉ ግልፅ ጥቃቶች በአገዛዝ ስፖንሰርነት እየተፈፀሙ ነው:: በብልፅግና የቀውስ አገዛዙ ምክንያት ሚሊዮኖች ተሰደዋል፣ በርካቶች በአገዛዙ የፀጥታ መዋቅር ንብረታቸዉን ተዘርፈዋል:: አማራ ክልልን ጨምሮ ከፊሉ የሀገሪቱ ክፍል በወታደራዊ አገዛዝ ስር ከወደቀ ሶስት አመታትን አስቆጥሯል። አገዛዙ በቀጥታ የእርስ በእርስ ግጭቶችን እና ጦርነቶችን በማዋለድ እና አለመተማመን እንዲነግስ በማድረጉ አብዛኛው የሀገሪቱ ክፍል ቀውስ ውስጥ ይገኛል። ይኸው ወታደራዊ አገዛዝ ምርጫ ለማድረግ የሚያበቃ የሰላም ሁኔታ ሳይኖር ራሱ ተመራጭ፣ ራሱ ታዛቢ፣ ራሱ መራጭ እና አስመራጭ በመሆን ትልቅ የፖለቲካ እና የዲሞክራሲ ክንዉን በሆነው የምርጫ ሂደት ላይ መቀለዱን ዓለም አቀፍ ማህበረሰቡም የመሰከረው እና የታዘበው ሐቅ ነው። ይህንንም ተከትሎ የ2018 ምርጫ ክንዉን አለመካሄዱን እና ብልፅግናም በምርጫ ያገኘው ቅቡልነት እንደሌለ ተረጋግጧል። አገዛዙ ይህንን በምርጫ ድግስ ያጣውን ቅቡልነት በምክክር ለማግፕት ጥረት እያደረገ ቢሆንም የብሔራዊ ምክክር ሂደቱን ለማሰናዳትም ሆነ በባለቤትነት ለማስኬድ የሚያበቃ የህግ መሰረት ግን የለዉም። ሀቀኛ ብሔራዊ ምክክርን መምራት የሚችል ኮሚሽን በኢትዮጵያ ውስጥ ባሉ ተፋላሚ ኃይሎች ይሁንታ የተሰጠው፤ ስቪክ ማህበራትን ጨምሮ በሁሉም ኃይሎች ተሳትፎ የተቋቋመ እና ገለልተኛነቱም የተረጋገጠ መሆን ይገባዋል። የወቅቱን የብሔራዊ ምክክር ጉዳይ እመራለሁ የሚለው ኮሚሽን ከአገዛዙ በስተቀር በየትኛውም የፖለቲካ ኃይል እውቅና እና ይሁንታ ያልተሰጠው ከመሆኑ ባሻገር የብልፅግናን በተለይም የጠቅላይ ሚኒስትሩን የግል ፍላጎት የብሔራዊ ምክክር ውጤት አድርጎ ይዞ ለመቅረብ የተዘጋጀ፣ ሂደቱ የሚመራበትን አሰራር የሚወስን ህግ እንኳን እንዲወጣ ያላደረገ የጏዳ ወዳጆችና የፖለቲካ ደላሎች ስብስብ ነው። ገለልተኛ ባልሆነ ተቋም የሚመራ ምክክር ደግሞ የብልፅግና ካድሬወች ውይይት እንጅ ብሔራዊ ምክክር አይሆንም። ለሀገሪቱ ችግርም ዘላቂ ሰላምም አያመጣም። ላለፉት በርካታ ዓመታት ሀቀኛ ወኪል ሳይኖረው በመቅረቱ እጣ ፋንታውን ሌሎች የፖለቲካ ኃይሎች ሲወስኑለት የቆዬው የአማራ ህዝብ በዚህ የምክክር ጉባኤም ተመሳሳይ ሂደት ውስጥ ይገኛል። በአብን እና በአማራ ብልፅግና ስም ከየጎሬው ተለቃቅመው በጉባኤው አማራን ወክለን እንሳተፋለን የሚሉትም በአማራው ላይ ይፋዊ ጦርነት ያወጀውን ዘረ ፈጅ አገዛዝ የተቀበሉ የብልፅግና ወኪሎች እንጅ ለአማራ ህዝብ መብት እና ጥቅም ቅንጣት ታክል አስተዋፅኦ ማድረግ የማይችሉ በመሆናቸው ይህ የምክክር ጉባኤ የአማራ ህዝብ ያልተወከለበት እና የማይሳተፍበት መሆኑ በታሪክ ፊት ተመዝግቧል። የአማራን ህዝብ ብቻ ሳይሆን ከብልፅግና አገዛዝ ጋር ይፋዊ ጦርነት ውስጥ ያሉ የፖለቲካ ኃይሎችን ያገለለ የምክክር ጉባኤ በመሆኑም ከአማራ ህዝብ ብቻ ሳይሆን ሌላው ኢትዮጵያዊም ቢሆን በዚህ ጉባኤ በትክክለኛ ወኪሎቹ አማካኝነት እየተሳተፈ ነው ብለን አናምንም። በመሆኑም ድርጅታችን አፋብን ለአማራ ሕዝብ፣ ለኢትዮጵያ ሕዝቦች እና ለዓለም አቀፉ ማህበረሰብ የሚከተለውን ጥሪ ያቀርባል:- 1. ለአማራ ሕዝብ - ይህ ምክክር ተብሎ በአገዛዙ የሚደረገው እንቅስቃስ የአማራ ህዝብ ያልተወከለበት እና ትክክለኛ ወኪሎቹ የህልውና ትግል ላይ በመሆናቸው፣ ትግሉን ጫፍ በማድረስ ስር ነቀል ለውጥ በማምጣት ህልውናውን አረጋግጦ ለወደፉቱ ከሌሎች ህዝቦች ወኪሎች ጋር በግልፅ ተነጋግሮ ሀገራዊ እውነተኛ እርቅና ምክክር ለማምጣት እንዲቻል አሁን ላይ ሁሉንም አቅሞች አሰባስቦ በበለጠ ቁርጠኝነት እንዲታገል ጥሪ እናቀርባለን፤ 2. ለኢትዮጵያ ሕዝብ:- ይህ የምክክር የተባለው ክሹፉና አስመሳይ ሂደት የአማራን ሕዝብ ጨምሮ ሌሎች ጥያቄ ያላቸው የፖለቲካ ኃይሎችም የተሳተፉበት አለመሆኑን፣ የሀገሪቱን አንድነት የበለጠ አደጋ ላይ የሚጥል መሆኑን፣ የእርስ በርስ ጦርነቱን የማያስቆምና የሚያባብስ መሆኑን፣ የአንድ ግለሰብ እና የገዢ ቡድን ፍላጎት ለማሳካት እየተደረገ ያለ መሆኑን በማመን ከአማራ ሕዝብ ጎን ቆሞ ስርዓቱን መታገል ይገባል:: በቀጣይ በጋራ የሽግግር መንግስት መስርተን ሀገራችንን ማፅናት እንችል ዘንድ ብሎ እውንተኛ ምክክርና እርቅ እንፈፅም ዘንድ በተባባረ መልኩ ፀረ አገዛዝ ትግል እንዲደረግ ጥሪ እናቀርባለን፤ 3. ለዓለም አቀፉ ማህበረሰብ:- እንደሚታወቀው በትክክለኛው መንገድ የማይካሄድ ብሄራዊ እርቅና ምክክርን ሂደቱ ካለ መኖሩ የከፋ ሀገራዊ ችግርን ያስከትላል። ብሄራዊ ምክክር ከከሸፈ አንድ ሀገር የምትገባበት ቀውስ እጅግ ከባድና በአዙሪት የተሞላና የማይገመት ይሆናል:: የብዙ ሀገራት ብሄራዊ እርቅና ምክክር የተኮላሸው ገለልተኛነትና አሳታፊነት የሌለውን ሂደት በመከተላቸው እንደሆነ ብዙ ምሳሌና ተሞክሮዎች አሉ:: የአሁኑ የአገዛዙ ብሔራዊ ምክክር የተባለው ሂደትም የህዝብ ቅቡልነት የሌለው፣ እውነተኛ ችግር ፈች ምክክር ሳይሆን ብልጽግና እና ደጋፊዎቹ የአገዛዙ ስልጣን ማጽኛ እንደሆነ እና ሀገሪቱን እንዲሁም የቀጣናውን ሰላም ከድጡ ወደማጡ የሚያስገባ መሆኑን ተገንዝባችሁ ለሀቀኛ ሽግግር እና ዘላቂ ሰላም እንድትሰሩ ጥሪ እናቀርባለን። 4. የአማራ ህዝብ ወኪል ነን ለምትሉ የሂደቱ ተሳታፊወች:- ከዚህ ቀደም እንደሆነው ሁሉ የአገዛዙ ተላላኪ በመሆን እና ተገቢው የአማራ ህዝብ ውክልና ሳይኖራችሁ በሂደቱ የምትሳተፉ ግለሰቦች እና ቡድኖች በብሔራዊ ምክክር ስም በሚካሄድ የብልፅግና ጉባኤ በመሳተፍ ታሪካዊ ስህተት ከመፈፀም እንድትታቀቡ እያሳሰብን ይህን ማሳሰቢያ ችላ በማለት የምታደርጉት ሂደት የአማራን ህዝብ ጥያቄወች ለሌላ ምዕራፍ ለማዳፈን ለምታደርጉት ያልተገባ ተግባር ኃላፊነት የምትወስዱ መሆኑንም በህዝብ እና በታሪክ ፊት እናሳውቃለን። የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ

Mereja TV
17 808
photo content

Mereja TV
17 808
ከጣይቱ እስከ ፋኖ የማይበጠሰው የሴቶች የጽናት ሰንሰለት! በኢትዮጵያ የታሪክ አውድ ውስጥ ሴትነት በቤት ውስጥ ሥራና በልጆች አስተዳደግ ብቻ የሚገደብ "ለስላሳ" ማንነት አይደለም። ይልቁንም፣ አገር ስትደፈርና ህልውና ሲታወክ፣ ያ ለስላሳ እጅ ክላሽንኮቭ የሚጨብጥበት፣ ያ ሩኅሩኅ ልብ የቆራጥነት ማማ የሚሆንበት ጥበብ ነው። የዛሬዎቹ ሴት ፋኖዎችና የዐድዋው ዘመን ሴት አርበኞች የሚገናኙበት መሠረታዊ ነጥብም ይሄው ነው፦ "ህልውናን ለማስከበር የሚከፈል ዋጋ።" የዐድዋ ድል የጥቁር ሕዝቦች ኩራት የሆነው በወንዶች ጥይት ብቻ አይደለም፤ በእቴጌ ጣይቱ ብርሃን የስትራቴጂክ መሪነትም ጭምር ነው። ጣይቱ በመቀሌው ከበባ የጠላትን የውኃ ምንጭ በማስቆረጥ ያሳዩት ብልሃት፣ ዛሬ በጦር ሜዳ ለሚገኙ ሴት ፋኖዎች ትልቅ የታሪክ ስንቅ ነው። በዐድዋ ወቅት የነበሩ ሴት አርበኞች ስንቅ በማቀበል፣ ቁስለኛ በማከም ብቻ ሳይሆን፣ እንደ ወንዶቹ ፊት ለፊት ተፋልመው ለነፃነት ደማቸውን አፍስሰዋል። ያኔ ጠላታቸው የባዕድ ወራሪ ነበር፤ ግባቸውም ብሔራዊ ሉዓላዊነትን ማስከበር። የዛሬዎቹ ሴት ፋኖዎች ደግሞ የታሪክ ድግግሞሾች ናቸው። እነርሱ ወደ ትግሉ የገቡት ለዝና ወይም ለሥልጣን ፍለጋ ሳይሆን፣ የማንነትና የህልውና አደጋ ስላንኳኳባቸው ነው። የዛሬዎቹ ሴት ፋኖ፣ የጣይቱን "እምቢኝ" ባይነትን ወርሰው፣ በፖለቲካዊ መገለልና በማንነት ላይ በተቃጣ ጥቃት ሳቢያ የቤት ውስጥ ምቾታቸውን ትተው ወደ በረሃ ወጥተዋል። ይህ ውሳኔ ከወታደራዊ ግዳጅ በላይ ጥልቅ የሆነ ፖለቲካዊ ትርጉም አለው፤ "እጣ ፈንታዬን በገዛ እጄ እወስናለሁ" የሚል የነፃነት አዋጅ ነው። በዐድዋ ጊዜ ሴቶች ለሃገራቸው አንድነትና ክብር ቆመው ነበር። ዛሬ ደግሞ ሴት ፋኖዎች ለፍትሕ፣ ለእኩልነትና ለተገፋ ማንነት መከበር እየታገሉ ነው። የዐድዋዋ አርበኛ ለሃገሯ ክብርና ሉዓላዊነት መከበር ዋጋ ከፈለች፤ የዛሬዋ ፋኖ ደግሞ የወገኖቿን ደኅንነት ለማረጋገጥ መከራን ትጋፈጣለች። በፖለቲካው ረገድ፣ የሴት ፋኖዎች ተሳትፎ የትግሉን ሕዝባዊነትና ሞራላዊ የበላይነት ያሳያል። አንዲት ሴት ልጅ፣ እናት ወይም እህት መሣሪያ አንግባ ወደ በረሃ ስትወጣ፣ ትግሉ የጥቂቶች ፍላጎት ሳይሆን የሕዝብ የብሶት ድምፅ መሆኑን ያረጋግጣል። ይህ ደግሞ በታሪክ ውስጥ እንደምናየው፣ የሴቶች ተሳትፎ ያለበት ትግል ውጤቱ ድልና አሸናፊነት ነው። የሴት ፋኖዎች ትግል የዐድዋው ድል ቀጣይ ምዕራፍ ነው። ያኔ በጣይቱ የተለኮሰው የነፃነት ችቦ፣ ዛሬ በፋኖ ሴቶች እጅ ደምቆ እየበራ ይገኛል። እነዚህ ሴቶች የትናንቱን ታሪክ በዛሬው ጽናት፣ የትናንቱን ጀግንነት በዛሬው ፖለቲካዊ ንቃት አዋህደው የያዙ የቁርጥ ቀን ልጆች ናቸው። የዐድዋዋ ጣይቱ ዛሬም ፋኖ ናት!

Mereja TV
17 808
ከጣይቱ እስከ ፋኖ የማይበጠሰው የሴቶች የጽናት ሰንሰለት! በኢትዮጵያ የታሪክ አውድ ውስጥ ሴትነት በቤት ውስጥ ሥራና በልጆች አስተዳደግ ብቻ የሚገደብ "ለስላሳ" ማንነት አይደለም። ይልቁንም፣ አገር
ከጣይቱ እስከ ፋኖ የማይበጠሰው የሴቶች የጽናት ሰንሰለት! በኢትዮጵያ የታሪክ አውድ ውስጥ ሴትነት በቤት ውስጥ ሥራና በልጆች አስተዳደግ ብቻ የሚገደብ "ለስላሳ" ማንነት አይደለም። ይልቁንም፣ አገር ስትደፈርና ህልውና ሲታወክ፣ ያ ለስላሳ እጅ ክላሽንኮቭ የሚጨብጥበት፣ ያ ሩኅሩኅ ልብ የቆራጥነት ማማ የሚሆንበት ጥበብ ነው። የዛሬዎቹ ሴት ፋኖዎችና የዐድዋው ዘመን ሴት አርበኞች የሚገናኙበት መሠረታዊ ነጥብም ይሄው ነው፦ "ህልውናን ለማስከበር የሚከፈል ዋጋ።" የዐድዋ ድል የጥቁር ሕዝቦች ኩራት የሆነው በወንዶች ጥይት ብቻ አይደለም፤ በእቴጌ ጣይቱ ብርሃን የስትራቴጂክ መሪነትም ጭምር ነው። ጣይቱ በመቀሌው ከበባ የጠላትን የውኃ ምንጭ በማስቆረጥ ያሳዩት ብልሃት፣ ዛሬ በጦር ሜዳ ለሚገኙ ሴት ፋኖዎች ትልቅ የታሪክ ስንቅ ነው። በዐድዋ ወቅት የነበሩ ሴት አርበኞች ስንቅ በማቀበል፣ ቁስለኛ በማከም ብቻ ሳይሆን፣ እንደ ወንዶቹ ፊት ለፊት ተፋልመው ለነፃነት ደማቸውን አፍስሰዋል። ያኔ ጠላታቸው የባዕድ ወራሪ ነበር፤ ግባቸውም ብሔራዊ ሉዓላዊነትን ማስከበር። የዛሬዎቹ ሴት ፋኖዎች ደግሞ የታሪክ ድግግሞሾች ናቸው። እነርሱ ወደ ትግሉ የገቡት ለዝና ወይም ለሥልጣን ፍለጋ ሳይሆን፣ የማንነትና የህልውና አደጋ ስላንኳኳባቸው ነው። የዛሬዎቹ ሴት ፋኖ፣ የጣይቱን "እምቢኝ" ባይነትን ወርሰው፣ በፖለቲካዊ መገለልና በማንነት ላይ በተቃጣ ጥቃት ሳቢያ የቤት ውስጥ ምቾታቸውን ትተው ወደ በረሃ ወጥተዋል። ይህ ውሳኔ ከወታደራዊ ግዳጅ በላይ ጥልቅ የሆነ ፖለቲካዊ ትርጉም አለው፤ "እጣ ፈንታዬን በገዛ እጄ እወስናለሁ" የሚል የነፃነት አዋጅ ነው። በዐድዋ ጊዜ ሴቶች ለሃገራቸው አንድነትና ክብር ቆመው ነበር። ዛሬ ደግሞ ሴት ፋኖዎች ለፍትሕ፣ ለእኩልነትና ለተገፋ ማንነት መከበር እየታገሉ ነው። የዐድዋዋ አርበኛ ለሃገሯ ክብርና ሉዓላዊነት

Mereja TV
17 808
ወደ መዘዞ ከአራት አቅጣጫ ለዘረፋ የተንቀሳቀሰው የጠላት ኃይል ክፉኛ ተመታ! ሐምሌ/17/2018 ዓ.ም የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ 7/ለ70 እና የመሀመድ ቢሆነኝ ኮር አስቻለው ደሴ ክ
ወደ መዘዞ ከአራት አቅጣጫ ለዘረፋ የተንቀሳቀሰው የጠላት ኃይል ክፉኛ ተመታ! ሐምሌ/17/2018 ዓ.ም የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ 7/ለ70 እና የመሀመድ ቢሆነኝ ኮር አስቻለው ደሴ ክፍለጦሮች ወደ መዘዞ በተለያየ አቅጣጫ የተንቀሳቀሰውን የጠላት ኃይል  በጋራ በመሆን፡ በመዘዞ ዙሪያ፣ በባሽና እና በሞፈር ውሃ አካባቢዎች ከፍተኛ ትንቅንቅ እያካሄዱ  ይገኛሉ። መነሻውን ከመንዝ አውራጃ ሞላሌ፣ወገሬ ፣መሀል ሜዳና ዘመሮ ያደረገውን የጠላት ኃይል፡ የመሀመድ ቢሆነኝ ኮር ወንዱ አስቻለው ክፍለጦር ከረፋዱ 4:00 ሰዓት ጀመሮ ከባሽ ከተማ ዙሪያ ከፋተኛ ትንቅንቅ እያደረጉ ይገኛል ከቆብ አስጥል እስከ መዘዞ ከተማ ድረስ ሁለቱም ክፋለጦሮች በቅንጂት ገጥመው ሲያራግፈው፡ የ112ኛ እና የ104 ጥምር ጦር አስካሁን ድረስ በከባድ ትንቅንቅ  ላይ ይገኛሉ።  በሌላ ግንባር ማለትም፦ ከጣርማበር እና ከሰላድንጋይ በሞፈር ውሃ ጅረት ወደ መዘዞ የተንቀሳቀሰውን የጠላት ኃይል 7ለ70 ክፋለጦር እና  መሐመድ ቢሆነኝ ኮር ወንዱ አስቻለው ደሴ ክፍለ ጦር  ጠላትን እዳመጣጡ አያራገፉት ይገኛሉ። በዚሕ ከባድ ትንቅንቅ ጠላት ብዙ ሙትና ቁስለኛ ያስተናገደ ሲሆን ተጨማሪ ኃይል ከደብረ ብርሀን መጠየቁ ተሠምቷል። ምንጭ፦ በአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ የሕዝብ ግንኙነት መምሪያ

Mereja TV
17 808
በምዕራብ ጎንደርና በመተማ ወረዳዎች የአገዛዙ የሚሊሻና የፀረ-ሽምቅ መዋቅር መፍረሱ ተገለጸ! በአፋብን በላይ ዘለቀ ዕዝ መይሣው ካሳ ኮር ፊታውራሪ ገበየሁ ክፍለጦር በምዕራብ ጎንደር አዳኝ አገር ጫቆ
በምዕራብ ጎንደርና በመተማ ወረዳዎች የአገዛዙ የሚሊሻና የፀረ-ሽምቅ መዋቅር መፍረሱ ተገለጸ! በአፋብን በላይ ዘለቀ ዕዝ መይሣው ካሳ ኮር ፊታውራሪ ገበየሁ ክፍለጦር በምዕራብ ጎንደር አዳኝ አገር ጫቆ ወረዳ ነጋዴ ባህር እና በመተማ ወረዳ ኩመር አውላላ ባካሄደው ልዩ ወታደራዊና የማኅበረሰብ ውይይት የአገዛዙ የሚሊሻና የፀረ-ሽምቅ መዋቅር ሙሉ በሙሉ በሚባል ደረጃ መፍረሱ ታወቀ። የኮሩ ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ ይፋ ባደረገው መረጃ መሠረት፡ አገዛዙ በአካባቢው የሚገኙ ነዋሪዎችን "አማራና ቅማንት" በማለት ለዘመናት ሲያጋጭና ለጥፋት ዓላማው ሲጠቀምበት የቆየውን ሴራ፡ ፊታውራሪ ገበየሁ ክፍለጦር ባካሄደው የማኅበረሰብ ውይይትና ከታጠቁ ኃይሎች ጋር ባደረገው ስምምነት ማክሸፍ ተችሏል። በዚህም ሳቢያ አገዛዙ መዋቅሩን ለሌላ ግጭት ለማዘጋጀት ያደርገው የነበረው ጥረት ከንቱ ሆኖ የቀረ ሲሆን፣ ከ50 በላይ የሚሊሻና የፀረ-ሽምቅ አባላት ከነሙሉ ትጥቃቸው መይሣው ካሳ ኮርን ሲቀላቀሉ፡ በርካቶች ደግሞ ትጥቃቸውን ፈትተው ወደ ሰላማዊ ኑሯቸው ተመልሰዋ።

Mereja TV
17 808
የአይሻ ሰይድ ዕዝ አርበኞች በወለጋ ቢዛሞ ቀጠና ስር በሚገኙ በስቡ ስሬ ወረዳ፣ ጉቶ ጊዳ ወረዳ፣ ጊዳ አያና ወረዳ፣ በአቤ ደንጎሮ ወረዳ እንዲሁም በአንገር ጉትን ከተማ ዙሪያ ባሉ አከባቢዎች ላይ ባ
የአይሻ ሰይድ ዕዝ አርበኞች በወለጋ ቢዛሞ ቀጠና ስር በሚገኙ በስቡ ስሬ ወረዳ፣ ጉቶ ጊዳ ወረዳ፣ ጊዳ አያና ወረዳ፣ በአቤ ደንጎሮ ወረዳ እንዲሁም በአንገር ጉትን ከተማ ዙሪያ ባሉ አከባቢዎች ላይ ባካሄዱት የተቀናጀ የፀረ-ማጥቃት እርምጃ በርካታ የጠላት ኃይልን በመደምሰስ 31 ክላሽንኮቭ መሣሪያዎችን ማርከው መታጠቃቸው ታወቀ። አርበኞቹ በሆሮጉድሩ ወለጋ ዞን አቤ ደንጎሮ ወረዳ ስር የምትገኘው ስትራቴጂካዊቷ ቱሉ ጋና ከተማን ጨምሮ በምስራቅ ወለጋ ዞን ከአንገር ጉትን ከተማ በቅርብ ርቀት መንደር 4 ተብሎ የሚጠራውን አከባቢ በቁጥጥራቸው ስር ማስገባታቸውን መረብ ሚዲያ ለማረጋገጥ ችሏል።

Mereja TV
17 808
በሸዋ ጠቅላይ ግዛት መዘዞ ዙሪያ፣ በባሽና፣ በሞፈር ውሃ፣ በከባሽ ከተማ ዙሪያ ደግሞ ከቆብ አስጥል እስከ መዘዞ ከተማ ባሉት ቀጠናዎች እንዲሁም ከጣርማበር እስከ ሰላድንጋይ ባሉ ቀጠናዎች ላይ ከፍተኛ
በሸዋ ጠቅላይ ግዛት መዘዞ ዙሪያ፣ በባሽና፣ በሞፈር ውሃ፣ በከባሽ ከተማ ዙሪያ ደግሞ ከቆብ አስጥል እስከ መዘዞ ከተማ ባሉት ቀጠናዎች እንዲሁም ከጣርማበር እስከ ሰላድንጋይ ባሉ ቀጠናዎች ላይ ከፍተኛ ውጊያ የተካሄደ ሲሆን፡ የአሳምነው ዕዝ አርበኞች በወሰዱት ብርቱ የፀረ-ማጥቃት እርምጃ፡ የጠላት ኃይል ከመስመራዊ አዋጊዎቹ ጀምሮ በርካታ የኮማንዶ ኃይሉ ተደምስሶበት መሽመድመዱ ታወቀ!

Mereja TV - Telegram kanali @merejamedia statistikasi va tahlili