Mereja TV
前往频道在 Telegram
Please send us photos, videos and information to our Telegram account: @realmerejatv
显示更多📈 Telegram 频道 Mereja TV 的分析概览
频道 Mereja TV (@merejamedia) 阿姆哈拉语 语言赛道中的 是活跃参与者。目前社区聚集了 17 985 名订阅者,在 新闻与媒体 类别中位列第 12 390,并在 埃塞俄比亚 地区排名第 1 871 位。
📊 受众指标与增长动态
自 невідомо 创建以来,项目保持高速增长,吸引了 17 985 名订阅者。
根据 08 七月, 2026 的最新数据,频道保持稳定运转。过去 30 天订阅人数变化为 -186,过去 24 小时变化为 -7,整体触达仍然可观。
- 认证状态: 未认证
- 互动率 (ER): 平均受众互动率为 26.66%。内容发布后 24 小时内通常能获得 8.50% 的反应,占订阅者总量。
- 帖子覆盖: 每篇帖子平均可获得 4 796 次浏览,首日通常累积 1 529 次浏览。
- 互动与反馈: 受众积极参与,单帖平均反应数为 42。
📝 描述与内容策略
作者将该频道定位为表达主观观点的平台:
“Please send us photos, videos and information to our Telegram account: @realmerejatv”
凭借高频更新(最新数据采集于 09 七月, 2026),频道始终保持新鲜度与高覆盖。分析显示受众积极互动,使其成为 新闻与媒体 类别中的关键影响点。
17 985
订阅者
-724 小时
-717 天
-18630 天
帖子存档
17 985
ብልሆች ህይወታቸውን እያተረፉ ነው በዛሬው እለት የፓራ ኮማንዶ አባላቱ እና ዲሽቃ ምድብተኛው ፋኖን ተቀላቅለዋል። ከጠላት ወደ 201ኛ ኮር 74ኛ ክ/ጦር የተቀላቀሉ የአብይ አህመድ ሰራዊት አባላት
ብልሆች የመሪያችን የምረት አወጅ በመጠቀም በዚህ ወር ከሰኔ 1--30/2018 ዓ.ም ከጠላት በመውጣት ወደ 201ኛ ኮር 74ኛ ክ/ጦርን የተቀላቀሉ የጠላት ኃይል ፦
1.ይልቃል አባየሁ ...... ፓራ ኮማንዶ
2.ጥጋቡ የሺ .............ፓራ ኮማን
3.ሐብቴ ቁሜ.............ፓራ ኮማንዶ
4.አበበ ጌታሁን...........ፖሊስ
5.ተመስገን ደመቀ.......ፖሊስ
6.አለማየሁ ጨመር......ፓራ ኮማንዶ
7.ደረጀው ተረፈ.......... ሚሊሻ
8.ይርጋ ደርጀው..........ሚሊሻ
9.አበበ አንላይ........... ፓራ ኮማንዶ
10.አብርሐም አየልኝ ....ፖሊስ
11.የሽዋስ ታድሎ........አድማ ብተና
12.አየነውመንግስት....አድማ ብተና
13.ምኒችል ገደፋው.....ሚሊሻ
14.ደግዋለ አይተነው....ሚሊሻ
15.ዘለቀ ጸሐይ.......... አድማ ብተና
16.ሞላ ዋለ.............. አድማ ብተና
17.በላቸው አባተ....... አድማ ብተና
18.ገበያው ሞላ..........ፓራ ኮማንዶ.
19.ተስፋው አንሙት....ፓራ ኮማንዶ
20.እንድሪስ ሙሉጌታ..........ፖሊስ
21.ፈንታምትኩ..................ፓራ ኮማንዶ
22.ጓዴ ዘሪሁን................. ፓራ ኮማንዶ
23.ይኸነው ተሜ...............ፓራ ኮማንዶ
24.ዘውዱ አብየ.................መከላከያ
25.ብልሐቱ ካሳ................ ሚሊሻ ሲሆኑ ከመቸውም ጊዜ በላይ ድርጅታችን ያቀረበውን የምረት አዋጅ በመጠቀም ሁሉም አማራን እናድን የሚል የተቀመጠ ሲሆን፦ .......... ከፈለገ ብርሀን ከደብረወርቅ ከሞጣ ፣ከግንደወይን እንዲሁም ከድጎፅዮን በመውጣት ከዚህ በሗላ ለስርአቱ መጠቀሚያ መሆን በቃን በማለት 201ኛ ኮር 74ኛ እና 54ኛ ክፍለ ጦርን ተቀላቅለዋል።
1.ገብሬ ሆነ........ፓሊስ ኮሪያ
2.ፈንታሁን ስማቸው.... ዲሽቃ ምድብተኛ
3.ክንድ ግዛ ...........ፓራ ኮማንዶ
4.እባብየ ድረስ..........ሚሊሻ
5.ወለላው ጌጤ.....ሚሊሻ
6.ገበያው አስቻለ ....ፓራኮማንዶ ጓድመሪ
7.አመት የቆየ..........ፓራኮማንዶ
8.ድንበሩ አበበ.........ሚሊሻ
በክፍለ ጦር አመራሮች አቀባበል የተደረገላቸው ሲሆን ሁላቹህም ይኸን የተሻለ አጋጣሚ በመጠቀም ወደ ትክክለኛው ማንነታቹህ እንድትመለሱ ጥሪያችን እናስተላልፋለን።
ምንጭ፦ አፋብን ቴወድሮስ ዕዝ 201ኛ ኮር ህዝብ ግንኙነት ክፍል!
17 985
ብልሆች ህይወታቸውን እያተረፉ ነው በዛሬው እለት የፓራ ኮማንዶ አባላቱ እና ዲሽቃ ምድብተኛው ፋኖን ተቀላቅለዋል። ከጠላት ወደ 201ኛ ኮር 74ኛ ክ/ጦር የተቀላቀሉ የአብይ አህመድ ሰራዊት አባላት
ብልሆች የመሪያችን የምረት አወጅ በመጠቀም በዚህ ወር ከሰኔ 1--30/2018 ዓ.ም ከጠላት በመውጣት ወደ 201ኛ ኮር 74ኛ ክ/ጦርን የተቀላቀሉ የጠላት ኃይል ፦
1.ይልቃል አባየሁ ...... ፓራ ኮማንዶ
2.ጥጋቡ የሺ .............ፓራ ኮማን
3.ሐብቴ ቁሜ.............ፓራ ኮማንዶ
4.አበበ ጌታሁን...........ፖሊስ
5.ተመስገን ደመቀ.......ፖሊስ
6.አለማየሁ ጨመር......ፓራ ኮማንዶ
7.ደረጀው ተረፈ.......... ሚሊሻ
8.ይርጋ ደርጀው..........ሚሊሻ
9.አበበ አንላይ........... ፓራ ኮማንዶ
10.አብርሐም አየልኝ ....ፖሊስ
11.የሽዋስ ታድሎ........አድማ ብተና
12.አየነውመንግስት....አድማ ብተና
13.ምኒችል ገደፋው.....ሚሊሻ
14.ደግዋለ አይተነው....ሚሊሻ
15.ዘለቀ ጸሐይ.......... አድማ ብተና
16.ሞላ ዋለ.............. አድማ ብተና
17.በላቸው አባተ....... አድማ ብተና
18.ገበያው ሞላ..........ፓራ ኮማንዶ.
19.ተስፋው አንሙት....ፓራ ኮማንዶ
20.እንድሪስ ሙሉጌታ..........ፖሊስ
21.ፈንታምትኩ..................ፓራ ኮማንዶ
22.ጓዴ ዘሪሁን................. ፓራ ኮማንዶ
23.ይኸነው ተሜ...............ፓራ ኮማንዶ
24.ዘውዱ አብየ.................መከላከያ
25.ብልሐቱ ካሳ................ ሚሊሻ ሲሆኑ ከመቸውም ጊዜ በላይ ድርጅታችን ያቀረበውን የምረት አዋጅ በመጠቀም ሁሉም አማራን እናድን የሚል
17 985
በጎንደር ጠቅላይ ግዛት በሊቦ ከምከም አምቦ ሜዳ እና ጨብጪባ ግንባሮች በተካሄደው ተጋድሎ የአገዛዙ ሰራዊት በበላይ ዕዝ አርበኞች ቀለበት ውስጥ ገብቶ ከባድ የሽምቅ እርምጃ ተወስዶበት መሽመድመዱ ታወቀ!
በሁለቱም ግንባሮች በጠላት ላይ ከፍተኛ የሰብዓዊና የቁሳዊ ኪሳራ በማድረስ አከርካሪውን የሰበሩት የበላይ ዕዝ አርበኞች፡ ጠላት የኃይል መዛባትና መፍረክረክ ገጥሞት ሙትና ቁስለኛውን እያዝረከረከ ለመፍረጠጥ እንዲገደድ በማድረግ አውደ ውጊያውን በበላይነት እየመሩት ይገኛሉ።
17 985
በአፋብን ቴዎድሮስ ዕዝ 201ኛ ኮር 54ኛ ክ/ጦር ከአውደ ዉጊያ ጎን ለጎን በቢቡኝ ወረዳ ኮረብታ ንዑስ ከተማ ወይም ከደብረ ማርቆስ ዋብር ኮረብታ ንዑስ ከተማ የሚወስደዉን መንገድ ገረገንቲ በመድፋት መንገዱን በማስጠገን የህዝብን መሰረተ ልማት ጥያቄ እየፈታ ይገኛል።
አምባገነኑ የአብይ አህመድ ስርዓት ለአማራ ህዝብ እንደ መሰረተ ልማት ያቀረበለት በምድር ሞርተርና መድፍ በሰማይ ደግሞ ድሮን መሆኑ ይታወቃል። ነገር ግን የአማራ የቁርጥ ቀን ልጅ የሆነዉ ፋኖ በአማራ ህዝብ ላይ በይፋ የታወጀዉን ህገ_መንግስታዊ፣መዋቅራዊና መንግስታዊ የዘር ማጥፋት(genocide)፣የዘር ማፅዳት(Ethnic cleaning)፣ፊት ለፊት ከመመከትና ከመቀልበስ ባሻገር ቀጥሮ የተረከባቸዉን የአማራ ህዝብ ተያቄዎች በተገቢዉ መንገድ የህዝብ መሰረተ ልማት ስራዎችን እየፈታና ስራ ላይ እያዋለ ሲሆን በቢቡኝ ወረዳ ከድጓ_ፅዮን ኮረብታ ንዑስ ከተማ ወይም ከደብረ ማርቆስ ዋብር ኮረብታ ንዑስ ከተማ የሚወስደዉን መንገድ በቢቡኝ ወረዳ ጊዚያዊ መንግስት አስተዳደርና አስፈፃሚ ኮሚቴዎች አስተባባሪነት ከአዉደ ዉጊያዉ ጎን ለጎን የህዝብ መሰረተ ልማት ስራ የሆነዉን የመንገድ ጥገና ስራዎችን እያስጠገነ ነዉ።
የኮረብታና ዋብር አካባቢ ኗሪ ማህበረሰብ ለዘመናት ሲጠይቅ የነበረዉ የመንገድ ጥገና ስራ ማህበረሰባችን በሚፈልገዉ መልኩ መንቀሳቀስ እንዳልቻለና በዚህ ሰዓት በበጎ አድራጎት ስራ እንዲሰራላቸዉ ለቢቡኝ ወረዳ ጊዚያዊ መንግሰት ባቀረቡት የትብብር ጥያቄ መሰረት መመለስ ተችሏል።
ይሁንና የአካባቢዊ ማህበረሰብ ትብብራችሁ ተጠናክሮ ይቀጥልልን በማለት ከዚህ በኋላ አንዳንድ የንግድ ስራዎችን ለመስራት የመኪና እንቅስቃሴ ገትቶባቸዉ እንደነበር ገልፀዉ የንግድ እቃዎችም ኮረብታ ከተማ ድረስ በቀጥታ እንደሚደርስና መንገዶች እንደተስተካከሉ እዉቅና ፍ
17 985
በአርሲ ዞን አሰኮ ወረዳ ዳግም በተቀሰቀሰ ጥቃት በሰውና ንብረት ላይ ጉዳት እየደረሰ መሆኑ ተገለጠ፤ መረጃ እንዳይወጣ የኔትወርክ አገልግሎት ተቋርጧል
በአርሲ ዞን አሰኮ ወረዳ ከትናንት ጀምሮ ዳግም በተቀሰቀሰ ጥቃት በሰው ሕይወትና በንብረት ላይ ከፍተኛ ጉዳት እየደረሰ መሆኑ ተገልጿል።
ከአካባቢው የተገኙ መረጃዎች እንደሚያመለክቱት፣ ጥቃቱ ከተቀሰቀሰበት ካለፉት ጥቂት ቀናት ጀምሮ በአካባቢው የነበረው አንጻራዊ ሰላም መናጋቱ ታውቋል።
በጥቃቱ ሳቢያ የሰዎች ሕይወት መጥፋቱንና በንብረት ላይም ከባድ ውድመት እየደረሰ መሆኑ የተረጋገጠ ቢሆንም፣ በቁጥር የተደገፈ ሙሉ መረጃ ለማግኘት ግን አዳጋች ሆኗል።
ለዚህም ዋነኛው ምክንያት ከትናንት ምሽት ጀምሮ በአካባቢው ያለው የኔትወርክና የኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሙሉ በሙሉ እንዲቋረጥ መደረጉ እንደሆነ ተገልጿል።
የኔትወርክ መቋረጡ ነዋሪዎች ያሉበትን አስቸጋሪ ሁኔታ ለቀሪው ማህበረሰብና ለሚዲያ ተቋማት እንዳያሳውቁ ትልቅ እንቅፋት ፈጥሯል።
ከዚህም በተጨማሪ የወረዳው ካድሬዎችና አመራሮች በየቀበሌው እየዞሩ የነዋሪዎችን የግል ስልኮች በመንጠቅና የተለያዩ ማስፈራሪያዎችን በመጠቀም፣ በአካባቢው እየተፈጸመ ያለው ጥቃትና ወቅታዊ መረጃ ወደ ውጭ እንዳይወጣ ለማድረግ ከፍተኛ ጥረት እያደረጉ መሆኑ ተሰምቷል።
በአሁኑ ወቅት በአሰኮ ወረዳ ያለው የጸጥታ ሁኔታ አሳሳቢ መሆኑ የተገለጸ ሲሆን፣ በአካባቢው የተፈጠረውን የደህንነት ስጋት ለመግታትና የመረጃ ነጻነትን ለማስከበር የሚመለከታቸው አካላት አስቸኳይ ጣልቃ ገብነት እንደሚያስፈልግ ነዋሪዎችና የሰብአዊ መብት ተሟጋቾች እየገለጹ ይገኛሉ።
መረጃው የመሠረት ሚዲያ ነው።
17 985
ዶ/ር ደሳለኝ ጫኔ የፓርላማ ቆይታቸውን ማጠናቀቃቸውን ተከትሎ ባስተላለፉት መልዕክት ከፖለቲካው ዓለም ለመውጣት መወሰናቸውን ይፋ አደረጉ!
ባለፉት አምስት ዓመታት በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የሕዝብ ድምፅ በመሆን ሲያገለግሉ የቆዩት ዶ/ር ደሳለኝ ጫኔ፡ የፓርላማ አባልነታቸው መጠናቀቁን ተከትሎ ከማንኛውም ቀጥተኛ የፖለቲካ እንቅስቃሴ ራሳቸውን ማግለላቸውን አስታወቁ።
የባሕር ዳር ከተማ መራጮችን ወክለው በምክር ቤቱ የቆዩት ዶ/ር ደሳለኝ፡ የሕዝብ አገልጋይነት ጉዟቸውን በኩራት ማጠናቀቃቸውን ገልጸዋል።
ዶ/ር ደሳለኝ ጫኔ በባለፉት አምስት ዓመታት ማለትም ከ2014 ጀምሮ እስከ 2018 ዓ.ም በምክር ቤቱ ያሳለፉትን ቆይታ በይፋ ማጠናቀቃቸውን ተከትሎ ባስተላለፉት መልዕክት፣ የሕዝብ አደራን በመወጣታቸው የተሰማቸውን ክብር ገልጸዋል።
ከፖለቲካ ሕይወታቸው በፊት በነበረው የ10 ዓመታት የማህበረሰብ አገልግሎት፡ በተለይም በጣና ሐይቅ እንቦጭ አረም ዙሪያ በአክቲቪስትነት ሲያከናውኑት የነበረውን እንቅስቃሴ በማስታወስ፡ የሕዝብ ድምፅ መሆን መቻላቸውን ስለመጠቀሳቸው መረብ ሚዲያ ዶክተሩ በማህበራዊ ትስስር ገፃቸው ካስተላለፉት መልዕክት ተመልክቷል።
በዚህ ወቅት ለገጠማቸው ፈተናና ጫና ሁሉ ለፈጣሪ ምስጋና ያቀረቡት ዶ/ር ደሳለኝ፡ በተለይም ከሁለት ዓመት ተኩል በፊት በነበረው እስራት ጊዜ ከጎናቸው የቆሙ ወገኖቻቸውን እና የባሕር ዳር መራጮቻቸውን አመስግነዋል።
በምክር ቤቱ የመጨረሻ ቀናት ከጠቅላይ ሚኒስትር ዓብይ አህመድ ጋር በነበራቸው ቆይታ፡ ጠቅላይ ሚኒስትሩ "አብረን እንስራ" በማለት ጥሪ ማቅረባቸውንና በምክር ቤቱ እንዲቀጥሉ ፍላጎት ማሳየታቸውን ጠቅሰዋል።
ይሁን እንጂ ዶ/ር ደሳለኝ በአሁኑ ወቅት ውሳኔያቸው የተለየ መሆኑን አስታውቀዋል።
ከዚህ የፓርላማ ተሳትፎ በኋላ ራሳቸውን ከማንኛውም ቀጥተኛ የፖለቲካ እንቅስቃሴ በአባልነትም ሆነ በደጋፊነት ማግለላቸውን ይፋ ማድረጋቸውን ነው መረብ ሚዲያ በማህበራዊ ትስስር ገፃቸው ካሰፈሩት ፅሁፍ ለመመልከት የቻለው።
ዶ/ር ደሳለኝ ወደፊት በሙያቸው ሀገራቸውን ለማገልገል፣ በግሉ ሴክተር ላይ ለመሰማራት እና ለቤተሰቦቻቸው ጊዜ ለመስጠት መወሰናቸውን ገልጸዋል።
ምንም እንኳን ከፓርቲ ፖለቲካ ቢወጡም፡ የአማራን ሕዝብ አንድነት የሚያጠነክሩ፣ ብሔራዊ እርቅን የሚደግፉ እና የዜጎችን ኑሮ የሚያሻሽሉ አገራዊ ጉዳዮች ላይ በሙያቸው አስተዋጽኦ ለማድረግ መዘጋጀታቸውን አረጋግጠዋል።
ዶ/ር ደሳለኝ መልዕክታቸውን ሲያጠቃልሉ፡ የ
መጭው 2019 ዓ.ም ለኢትዮጵያ የሰላም፣ የፍቅርና የተስፋ ዘመን እንዲሆን መልካም ምኞታቸውን ገልፀዋል።
17 985
በተጉለት አውራጃ ደረፎ ክላስተር የገዥው ጥምር ጦር በንጹሃን ላይ ዘረፋ ሲፈፅም፡ አድማ ብተና ሀይሎች ፋኖን ተቀላቅለዋል!
ከደብረ ብርሃን ተነስቶ ወደ አንኮበር ቀጠና ደረፎ ቀበሌ ያመራውና ራሱን "ጥምር ጦር" ብሎ የሚጠራው የመከላከያና አድማ ብተና ሰራዊት፣ የፋኖ ኃይላችን በሌሉበት የህዝብ ንብረት መዝረፉ ታወቀ።
ሰራዊቱ ሰኔ 29 ቀን 2018 ዓ.ም በየቀበሌው በመግባት አርሶ አደሮች ለክረምት ዝግጅት ያከማቹትን 10 ኩንታል የአፈር ማዳበሪያ እንዲሁም አቶ ኪዳኔ ከተባለ አርሶ አደር ቤት በመግባት ሥስት(3) ጭነት ባቄላ ዘርፎ መውሰዱ ተረጋግጧል። በዚህ የዘረፋ ተግባር ላይ ለሆዳቸው ያደሩ የአካባቢው ሚሊሻዎችም የተሳተፉበት መሆናቸው ተረጋግጧል።
ድርጊቱ እንደተሰማ የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ፣ መሐመድ ቢሆነኝ ኮር እቴጌ ጣይቱ ክፍለ ጦር በፍጥነት ወደ ስፍራው ቢያመራም፣ የገዥው አካል ጦር የዘረፈውን ንብረት ጭኖ ወደ ደብረ ብርሃን ለመፈርጠጥ ተገዷል።
ይሕ በእንዲሕ እዳለ አገዛዙ በንፁሀን ላይ የሚፈፅመውን ግፍና ዘረፋ የሠሙት የአገዛዙ ደጀን የነበሩት አድማ ብተና ኃይሎች ፋኖን ተቀላቅለዋል። በዚሕም ሁለት የአድማ ብተና አባላት የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ አፄ አምደጽዮን ኮር ራንቦ ክፍለ ጦርን ከነ ሙሉ ትጥቃቸው በቀን 01/11/2018 ዓ.ም ተቀላቅለዋል።
ምንጭ፦ በአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ!
17 985
አስቴጎማ ተራራ ክፍለጦር በመኮይ ከተማ በአገዛዙ ጦር ላይ መብረቃዊ ጥቃት በመሰዘር ታላቅ ገድል ፈፅሟል!
በሸዋ ጠቅላይ ግዛት ይፋትና ጥሙጋ አውራጃ አንፆኪያ ገምዛ ክላስተር መኮይ ከተማ «44ቱ» ተብሎ በሚጠራው ልዩ ቦታ ላይ ሰፍሮ በነበረው የአገዛዙ ጥምር ጦር ላይ የተቀናጀና ስልታዊ ድንገተኛ ጥቃት ተፈጽሟል።
በአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ስር የሚገኘው የሙሀመድ ቢሆነኝ ኮር አስቴጎማ ተራራ ክፍለጦር ይህንን የላቀ ወታደራዊ ኦፕሬሽን አስደማሚ ገድል ፈፅሟል።
የክፍለጦሩ የቁርጥ ቀን ታጋዮች በከፈቱት ፈጣን ማጥቃት የአገዛዙን ዙፋን አስጠባቂ ሠራዊትና ተባባሪ ጥምር ኃይሎች ከጥቅም ውጪ ተደርገዋል።
በጠላት ላይ የደረሰው ወታደራዊ ኪሳራ፦
. 10 የብልፅግና መከላከያ ሠራዊት አባላት የተደመሰሱ ሲሆን
. ከ13 በላይ የሚሆኑት ሲቆስሉት ቀሪዎቹ ሕይወታቸውን ለማትረፍ የዕዝ ሰንሰለታቸው ተበጋጥሶ ተበታትነዋል።
የክፍለ ጦሩ አባላት የተሰጣቸውን ግዳጅ በአስተማማኝ ሁኔታ ከፈጸሙ በኋላ፣ ያለምንም የሰውና የማተርያል ጉዳት ሳይደርስባቸው በሰላም ወደ ምሽጋቸው ተመልሰዋል።
ሽንፈት የገጠመው ጠላት የበቀል በትሩን በንጹኃን ዜጎች መኖሪያ መንደሮች ላይ የ«ዙ-23» ፀረ-አውሮፕላን መሣሪያን በዘፈቀደ ሲተኩስ በነበረው አሸባሪ ኃይል ላይ የተወሰደው እርምጃ፣ የትጥቅ ትግሉን የህልውናና የነጻነት ጉዞ ይበልጥ ያፋጠነ ሆኗል።
የሙሀመድ ቢሆነኝ ኮር ሚዲያና ኮሚኒኬሽን ክፍል፡ የሕዝብን ሙሉ ነጻነትና ደህንነት እስኪረጋገጥ ድረስ የተባበረው የፋኖ ክንድ በአገዛዙ ላይ ማረፉን ይቀጥላል ሲል ገልጿል።
17 985
ትናንት ለዛሬ ሌሊት በምዕራብ ወሎ ግንባር ቢሊ ታዳጊ ከተማን ሙሉ በሙሉ ነጻ ማድረግ ተችሏል!!
የአፋብን ወሎ ቤተ- አማራ ምኒልክ እዝ 105 ኛ ኮር 29ኛ ክፍለ ጦር በሰራው የሌሊት ኦፕሬሽን ቢሊ ታዳጊ ከተማን ነጻ ማውጣት የቻለ ሲሆን ከአመሻሽ 12 ሰዓት ጀምሮ እስከ እኩለ ሌሊት ድረስ ሞት አይፈሬዎቹ የመካነሰላም አናብስት ጠላትን መፈናፈኛ አሳጥተው የጦር ሰፈራቸውን አስለቅቀዋል::
ኦፕሬሽኑ ላይ የተሳተፉት የ29ኛ ክፍለ ጦር ቃኝ አባላት በተለመደው ፈጣን የውጊያ ስልታቸው ጠላትን አናብዘው ሙት እና ቁስለኛ አስታቅፈውታል:: በሌሊቱ ኦፕሬሽን የተደመሰሱ እና የቆሰሉ የጠላት ኃይል አባላትን ትክክለኛ ቁጥር ለማወቅ የሰአቱ ሁኔታ አስቻይ ባይሆንም የውስጥ ወታደራዊ ምንጮች እንደተናገሩት ጠላት ያላሰበው ሽንፈት ገጥሞት አባላቱን ተነጥቋል::
ከሞት ያድነው ይመስል 3 ዲሽቃና 2 ሞርተር ከበርካታ የቡድን መሳሪያዎች ጋር ይዞ የነበረው ጠላት የ29 ክፍለ ጦር ቃኝን ወደ ሌላ ቀጠና መንቀሳቀስ ተከትሎ ወደ ቢሊ ታዳጊ ከተማ ቢገባም ቃኝይቱ በብርሀን ፍጥነት ተመልሳ ከ3ተኛ ሻለቃ ጋር በመናበብ ስትለበልበው የተማመነበትን የሽፋን እና የቡድን መሳሪያ ሁሉ ነቅሎ እግሬ አውጭኝ ብሎ እንደ ልማዱ ወደመጣበት ሊፈረጥጥ ችሏል::
ምንጭ፦በአፋብን ምኒልክ ዕዝ ሚዲያና ኮሚዩኒኬሽን መምሪያ!
17 985
በአፋብን ጎንደር ጠቅላይ ግዛት በላይ ዘለቀ ዕዝ 206ኛ ከፊያለው ደሴ ኮር አንበሣው ጋይንት ክፍለጦር ወንዱ አስቻለው ደሴ ብርጌድ ስር ለበርካታ ወራት የኮማንዶ ወታደራዊ ሣይንስን ከፅንሰ-ሃሳብ እስከ ትግበራ ትንቅቅ አድርገው ሰልጥነው ለምርቃት የበቁ የፋኖ ኮማንዶዎች!
17 985
Senay Conversation | Segment 03: Capturing The Truth One Frame at a Time with @JemalCountess | July 4, 2026
https://youtu.be/iiCkkOekaXY
Disclaimer [Senay Conversation]: The views discussed in the show are solely owned by the respective speakers. If you feel like an idea or claim presented needs to be counter argued, please contact us through DM and we will do our best to arrange a #SenayConversation segment with you.
___________________________
X: https://x.com/SenayConverse
FB: https://www.facebook.com/profile.php?id=61591725962050
Telegram: https://t.me/senayconversation
WhatsApp: https://whatsapp.com/channel/0029VbC2Nn4JENxy2FG4Vx1U
https://youtu.be/iiCkkOekaXY?is=fTC-RCYrQprTXAKR
17 985
Senay Conversation | Segment 03: Capturing The Truth One Frame at a Time with @JemalCountess | July 4, 2026
https://youtu.be/iiCkkOekaXY
Disclaimer [Senay Conversation]: The views discussed in the show are solely owned by the respective speakers. If you feel like an idea or claim presented needs to be counter argued, please contact us through DM and we will do our best to arrange a #SenayConversation segment with you.
___________________________
X: https://x.com/SenayConverse
FB: https://www.facebook.com/profile.php?id=61591725962050
Telegram: https://t.me/senayconversation
WhatsApp: https://whatsapp.com/channel/0029VbC2Nn4JENxy2FG4Vx1U
17 985
በአፋብን በላይ ዘለቀ ዕዝ ሜጀር ጄነራል ውብአንተ አባተ ኮር የኮሩ ተወርዋሪ ክፍለ ጦር አርበኞች እና የነበልባሉ 23ኛ ክፍለ ጦር አርበኞች በክቡር ሰማዕቶቹ አርበኛ ሙሉቀን አለኸኝ እና በአርበኛ ሰለሞን ጋሻው ስም ዘመቻ በማወጅ በዓለም በር ከተማና በወረታ ከተማ ዙሪያ ባደረጉት ተጋድሎ የጠላትን አከርካሪ ሰብረው አንፀባራቂ ድል ተቀዳጁ።
ለአማራ ሕዝብ ዋጋ በከፈሉ ጀግኖች ስም የታወጀው ይህ ስኬታማ ዘመቻ ትናንት ሰኔ 28/2018 ዓ/ም ከጧት ጀምሮ በዓለም በር ከተማና በወረታ ከተማ ዙሪያ የተካሄደ ሲሆን፡ በዚህም የጠላት ጦር የተሽመደመደበት ድል መገኘቱን መረብ ሚዲያ ከሜጀር ጄነራል ውብአንተ አባተ ኮር ሕዝብ ግንኙነት ክፍል ለማረጋገጥ ችሏል።
በቅርቡ ክቡር መስዋዕትነትን በከፈለው የጣና ገላውዴዎስ ክፍለ ጦር ዋና ሰብሳቢ አርበኛ ሙሉቀን አለኸኝ እንዲሁም የነበልባሉ 23ኛ ክፍለ ጦር ዋና ሰብሳቢ በነበረው በክቡር ሰማዕቱ አርበኛ ሰለሞን ጋሻው ስም በተደረገው ዘመቻ ነው በርካታ የጠላት ወታደሮች ተደምስሰው አንፀባራቂ ድል የተገኘው።
በአለም በር አከባቢ ማለትም በቁስቋም፣ በሙሉ ተራራ፣ በአይለብሶ፣ በስንቆ፣ በሁ ርጭ፣ በአባይ መስክ፣ በአሳምነው ካምፕ፣ በዓለም በር ከተማ፣ በአስራት ተራራ እና በመድኃኒዓለም አከባቢ ላይ አርበኞቹ አይመከቴ እርምጃ በመውሰድ የጠላትን ጦር ድባቅ በመምታት አፍረክርከውበታል።
በዚህ ተጋድሎ በርካታ የጠላት ወታደሮች ሲደመሰሱ፡ ጠላት ይተማመንባቸው የነበሩ ምሽጎችም ሰዓታትን ባልፈጀ ተጋድሎ ድርምስምሳቸው ወጥቷል።
በተመሣሣይ፡ በወረታ ከተማ ዙሪያ በኮሩ ስር የነበልባሉ 23ኛ ክፍለ ጦር አሃድ የሆኑት የ3ኛ ሬጅመንት አርበኞች ከትናንት ጧት ጀምሮ በጉበና ሚካኤል አከባቢና እና በቋሃር አቦ አከባቢ በወሰዱት እርምጃ በርካታ ወታደሮችን ደምስሰው የጠላት ኃይልን ከባድ የሆነ የሰብአዊና ቁሣዊ ኪሳራን አከናንበውታል።
በክቡር ሰማዕቶቹ አርበኛ ሙሉቀን አለኸኝ እና አርበኛ ሰለሞን ጋሻው ስም በታወጀው በዚህ ዘመቻ የጠላት ጦር በውርደትና በሽንፈት አንገቱን ሲደፋ፡ በአንፃሩ የወገን ኃይል አንፀባራቂ ድሎችን አስመዝግቦ ዘመቻው በስኬት መጠናቀቁን ነው ጣቢያችን መረብ ሚዲያ ከሜጀር ጄነራል ውብአንተ አባተ ኮር ሕዝብ ግንኙነት ክፍል ለማረጋገጥ የቻለው።
17 985
ለፍኖተ ሰላም ከተማ እና ለአካባቢው የተላለፈ ጥብቅ መልዕክት!
ከአፋብን ምዕራብ አማራ ቀጠና ቴዎድሮስ ዕዝ 109ኛ ኮር 77ኛ ክፍለጦር ለፍኖተ ሰላም እና አካባቢው ላላችሁ ቁማር ቤቶች ማለትም፦ካርቴላ ቤት፣ቢንጎ ቤት እና ካርታ ቤት ፣ተጫዋቾችና አጫዋቾች በሙሉ የተላለፈ ማስጠንቀቂያ!
ቁማር ፍኖተሰላም ላይ እንደ ህጋዊ ስራ ሆኖ ከተጀመረ ሰነባብቷል ይህ አረመኔው ስርዓት የፍኖተሰላምን ህዝብ በኢኮኖሚና በማህበራዊ ለማሽቆልቆል ያመቸው ዘንድ በውስጡ ባደራጃቸው መረጃወቹ ከተማው ውስጥ የቁማር ህጋዊ ፍቃድ ሰጦ እያሰራ እንደሆን ደርሰንበታል።
ይህንን ስራ በዋነኚነት እየሰራችሁ ያላችሁ የዚህ ስርዓት ምስለኔወች እና ቁማር ቤቶች ስማችሁን በዝርዝር ከመጥቀሳችን በፊት ከዚህ እኩይ ተግባራችሁ በአስቸኳይ እንድታቆሙ ስንል መልክታችንን እናስተላልፋለን።
በመጨረሻም ይህንን መልዕክት ተላልፋችሁ የምትገኙ ከሆና አፋብን ምዕ/አማራ ቀጠና ቴዎድሮስ ዕዝ 109ኛ ኮር 77ኛ ክፍለ ጦር ከባድ እርምጃ የሚወስድ መሆኑን እናሳውቃለን።
ምንጭ፦ በአፋብን ቴዎድሮስ ዕዝ 77ኛ ክፍለ ጦር የህዝብ ግንኙነት ክፍል!
