Mereja TV
前往频道在 Telegram
Please send us photos, videos and information to our Telegram account: @realmerejatv
显示更多📈 Telegram 频道 Mereja TV 的分析概览
频道 Mereja TV (@merejamedia) 阿姆哈拉语 语言赛道中的 是活跃参与者。目前社区聚集了 18 136 名订阅者,在 新闻与媒体 类别中位列第 12 476,并在 埃塞俄比亚 地区排名第 1 851 位。
📊 受众指标与增长动态
自 невідомо 创建以来,项目保持高速增长,吸引了 18 136 名订阅者。
根据 13 六月, 2026 的最新数据,频道保持稳定运转。过去 30 天订阅人数变化为 -407,过去 24 小时变化为 -7,整体触达仍然可观。
- 认证状态: 未认证
- 互动率 (ER): 平均受众互动率为 19.66%。内容发布后 24 小时内通常能获得 8.66% 的反应,占订阅者总量。
- 帖子覆盖: 每篇帖子平均可获得 3 566 次浏览,首日通常累积 1 571 次浏览。
- 互动与反馈: 受众积极参与,单帖平均反应数为 18。
📝 描述与内容策略
作者将该频道定位为表达主观观点的平台:
“Please send us photos, videos and information to our Telegram account: @realmerejatv”
凭借高频更新(最新数据采集于 14 六月, 2026),频道始终保持新鲜度与高覆盖。分析显示受众积极互动,使其成为 新闻与媒体 类别中的关键影响点。
18 136
订阅者
-724 小时
-437 天
-40730 天
帖子存档
18 136
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን የቴክሳስ፣ ኦክላሆማ፣ ሉዊዚያና፣ አርካንሳና ሐዋዪ አካባቢ ሀገረ ስብከት በምሥራቅ አርሲ የጅምላ ፍጅት ለደረሰባቸው ወገኖቻችን ጸሎተ ፍትሐት እንዲደረግ መመሪያ አስተላልፏል። እንዲሁም ለእሑድ ሰኔ 8 ቀን 2018 ዓ.ም (June 14, 2026) ደግሞ ልዩ ጉባዔ ጠርቷል። ዝርዝሩ ከደብዳቤው ላይ ይገኛል።
18 136
+1
በአርሲ ሀገረ ስብከት በኦርቶዶክስ ምእመናን እና በአብያተ ክርስቲያናት ላይ በደረሰው አሰቃቂ ጥቃት የሊባኖስ፣ የተባበሩት ዓረብ ኢምሬትስ እና የመካከለኛው ምሥራቅ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ድሜጥሮስ የሐዘን፣ የጸሎተ ፍትሐት እና የጸሎተ ምሕላ መግለጫ
=========
“ቅዱስና እውነተኛ ጌታ ሆይ እስከ መቼ ድረስ አትፈርድም? ስለ ደማችንስ በምድር በሚኖሩት ላይ እስከ መቼ አትበቀልም?”
(ራእይ 6፥10)
18 136
+2
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የዋሽንግተን ዲሲ እና አካባቢው ሀገረ ስብከት በምስራቅ አርሲ ውስጥ በተደጋጋሚ ስለሚከሰተው የክርስቲያኖች ግድያ ስደት እና መከራን አስመልክቶ የወጣ የአቋም መግለጫ
================
«እስመ በእንቲአሁ ይቀትሉነ ኵሎ አሚረ፤ወኮነ ከመ አባግዕ ዘይጠብሑ። ስለ አርሱ ሁልጊዜ ይገድሉናል፥ እንደሚታረዱም በጎች ሆነናል።” (መዝ ፵፫፡፳፪)
18 136
በአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ ሽዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ዓፄ ዘርያዕቆብ ፩ኛ ኮር በፍቃዱ በላይ ክፍለ ጦር የበረሀው ጀግኖች ትናንት ከማለዳ አንድ(1:00) ሰዓት ከ30 ደቂቃ ጀምረው እስከ ምሽቱ አንድ(1:00) ሰዓት ድረስ በተደረገ እልሕ አስጨራሽ ውጊያ በሰረርኩላ እና በቱቲ ከተሞች መሽጎ በነበረው የአገዛዙ ኃይል ላይ እንደ እሳት እያቃጠሉ ጠንካራ ምት አድርገውበታል። ሆኖም የሥርዓቱ ጅምላ ተጋላቢ ኃይል በመሬት ላይ ሊቀበለው የሚገባውን ታሪካዊ ቅጣት ከጀግኖቹ ክንድ ተመግቧል።
የበረሀው ትንታግ በፍቃዱ በላይ ክፍለጦር አንዲት እሳት የለበሰች ሻለቃ ወደ ሰረርኩላ ከተማ በረገጠችበት ቅጽበት በአገዛዙ ጥርቅም ኃይል ላይ የወሰደችው ፈጣንና መብረቃዊ የማጥቃት ስልት ጠላትን ሙሉ በሙሉ ግራ አጋብቶታል። ከዚሕም የተነሳ ጭንቅ ውስጥ የገባውና መውጫ ያጣው የአገዛዙ ኃይል ጫካ ውስጥ ያደራጀውን ዘራፊውን የ"ሸኔ" ስብስብ ለአጋዥነትና ለሕይወት ማዳኛ የጋበዘ ሲሆን የአናብስቶቹ ክንድ የማይነካ በመሆኑ ነገሩ እዳሠበው ሳይሳካ ቀርርቶበታል።
በመጨረሻም ጠላት የሚያስማርከውን አስማርኮ የጓዶቹን አስከሬን እንኳን ሳይሰበስብ ከተማዋን ጥሎ ወደ ጫካ ፈርጥጧል። ጀግኖቹ የሰረርኩላን ከተማ እስከ ምሽቱ ሁለት(2:00) ሰዓት ሙሉ በሙሉ በቁጥጥራቸው ስር አውለዋታል።
በሌላ በኩል በቱቲ ከተማ በተደረገው አውደ ውጊያ እጅ በአፍ የሚያስጭን ነበር። የቱቲ ከተማ በተናዳፊዎቹ ሻለቆች የባሩድ ጢስ ስትታጠን፣ ባሩዱም ሲቆላ በዋለበት በዚያ አስፈሪ ሰዓት ጠላት ምሽጉን በመነጠቁ ከተማዋን ጥሎ ለመውጣት ተገዷል። የወገን ኃይል ከተማዋን ሙሉ በሙሉ በመቆጣጠር ድላቸውን አጣጥመዋል።
ይሕ በእንዲሕ እንዳለ ጠላት በእውር ድንብርና በፍርሃት ተውጦ ዙ-23 እና ሞርተሮችን እያጮኸ ቢውልም በጀግኖቹ የቦታ ቁጥጥርና በማይበገረው የስነ-ልቦና የበላይነት ግንባሩን ተመትቶ እንደ ቅጠል ሲረግፍ አምሽቶ ፣ በዚህ ደማቅ አውደ ውጊያ የተረጋገጠውና በጀግኖቹ እጅ የገባው የምርኮ ዝርዝር እንደሚከተለው ይፋ ሆኗል፦
➾3 ከፋኖ ከድተው ወደ አገዛዙ ገብተው የነበሩ ባንዳዎች
➾1 የአገዛዙ ካድሬ
➾3 የሚሊሻ አባላት
➾የተማረከ ንብረት ዝርዝር ፦
➾8 ክላሽንኮቭ ጠመንጃዎች
➾4 የወገብ ትጥቅ
➾1 የደረት ትጥቅ
➾6 የእጅ ቦንቦች እና... በርካታ ተተኳሽ ጥይቶች በጀግኖቹ እጅ ገቢ ተደርገዋል።
ምንጭ፦ በአፋብን አሳምነው ዕዝ ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ!
18 136
ከ"ዘመቻ ህፃን አንሻ ሰይድ" ማግስት የብልፅግና ሰራዊት መፍረሱን ቀጥሏል!
ለብልፅግና የዙፋን መንበር በማወቅም ይሁን ባለማወቅ እየታተረና እየተጋ የሚገኘው ብልፅግና መራሹ ጦር በዘመቻ ህፃን አንሻ ሰይድ በከባድ ሚዛን በፋኖ ክንድ የተመታው ሰራዊት ከአሐዱ በመፍረስ ፋኖ ወደሚገኝበት ቦታ ሁሉ እየተቀላቀለ ይገኛል።
የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ (አፋብን) ወሎ ቤተ-አማራ ምኒልክ ዕዝ 303ኛ ኮር አካል የሆነውን 19ኛ ክፍለ ጦርን የተቀላቀሉት አስር አለቃ አማረ ተፈራ እና ጓደኛው ከ34ኛ ክፍለ ጦር አራተኛ ሬጅመንት በመውጣት የፋኖን ቤት የተቀላቀሉ ሲሆን መከላከያ አሁን ባለው ቁመና የመዋጋት አቅም እንደሌለውና ሰራዊቱም በፍፁም መሰላቸትና በከባድ የስነ-ልቦና ውድቀት ላይ እንደሚገኝ ገልጿል።
በሌላ መረጃ 303ኛ ግዙፉ አሳምነው ኮር አካል የሆነውን 30ኛ ክፍለ ጦርን የተቀላቀሉት የ13ኛ ዕዝ ኦፕሬተር የነበሩት:-
1ኛ. መሰረታዊ ወታደር ማርይሁን ጌታ
2ኛ. መሰረታዊ ወታደር ዮሴፍ አዱኛው
3ኛ. መሰረታዊ ወታደር ቴዎድሮስ ጥላሁን
ሁላቸውንም ቤተሰቦቻቸው ልከው ከሚያስተምሯቸው ኮሌጅ ላይ በማፈን ወደ ማሰልጠኛ በማስገባት ተገደው የገቡ እንደሆኑ ገልፀው የአገዛዙን ጓዳ ከፈተሹና ከመረመሩ በኋላ ለቤተሰቦቻችንና ወንድም እህቶቻችን ማጥፊያ ስርዓትና ተቋም አናገለግልም በማለት ፋኖን እንደተቀላቀሉ ተናግረዋል።
ስቦ በማስከዳት ስርዓቱን ከማፍረስ ጋር ተያይዞ ከመስከረም 14/2018 ዓ/ም ዘመቻ አደም አሊ (አባ ናደው)ን ጨምሮ ለተከታታይ ስምንት ወራት ከ850 በላይ የአገዛዙ ሰራዊት መከላከያ፣ አድማ ብተና፣ ፖሊስ፣ ሚሊሻና ስርዓቱን አገልጋይ ካቢኔ አባላት 303ኛ ግዙፉ አሳምነው ኮር ፋኖን የተቀላቀሉ ሲሆን አሁንም አልረፈደምና ቀሪው የአገዛዙ ሰራዊት በፍጥነት ፋኖን በመቀላቀል ህይዎቱን እንዲታደግ ሲል የኮሩ ፖለቲካ መምሪያ ኃላፊ አርበኛ በሪሁን ደምሌ ጥሪ አቅርቧል።
ምንጭ፦ የምኒልክ ዕዝ ሚዲያና ኮሚኒኬሽን መምሪያ!
18 136
የአርበኛ ሳሙኤል ባለዕድል ቤተሰቦች በፋሽስቱ አገዛዝ ታገቱ!
የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ ከፍተኛ አመራር አርበኛ ሳሙኤል ባለዕድል ቤተሰቦች በአገዛዙ ብልፅግና ሰኔ 2/2018 ዓ.ም ታግተዋል::
የአፋብን ስልጠና መምሪያ ሃላፊው ቤተሰቦች ማለትም ባለቤቱ እህቱና የእህቱ ባል ከህፃናት ልጆቻቸው ጋር በጅምላ ታፍነው ታስረው ይገኛሉ:: ባለፈው ጊዜ የከፍተኛ አመራሩ አጎትና የአጎቱ ልጅ በአገዛዙ በግፍ እንደተገደሉበት የሚታወቅ ነው::
ፋሽስቱ የብልፅግና አገዛዝ ህዝባቸው ላይ እየተፈፀመ ያለውን ዘር ማጥፋት ለመቀልበስ እየታገሉ ያሉ አርበኞችን ታግሎ ማሸነፍ ሲያቅተው ቤተሰቦቻቸውን በመግደል በማገትና ከሃገር እንዲሰደዱ በማድረግ ግፍ በመፈፀም ከአላማቸው ለማደናቀፍ ቢሞርም ተግባሩ ግን አርበኞችን በከፍተኛ ፅናትና ቁርጠኝነት እንዲታገሉ ከማድረግ የዘለለ ሚና የለውም::
18 136
በምኒልክ ዕዝ 104ኛ ኮር 23ኛ ክፍለ ጦር አምባሰል ላይ አንፀባራቂ ድል ተቀዳጀ!
መነሻዉን ከኩታበር ወደ ተለያዬንና ዚሃ እንዲሁም ከደላንታ በተሬ አድርጎ ወደ ዚሃ በምድር ሞርተር ፣ዙ23 እና መድፍ ሲጠቀም በሰማይ በሁለት ድሮን ታግዞ ፋኖን አጠፋለሁ በሚል የተለምዶ ቅዠቱ የመጣ ቢሆንም ጀግኖቹ ምንም ነገር ሳይበግራቸዉ እንደቃሪያ ሲያራግፉት ዉለዋል።
ዉጊያዉም ከንጋቱ 11:00 እስከ 6:00 የተደረገ ሲሆን በዚህ እልህ አስጨራሽ ውጊያ የ104ኛ ኮር 23ኛ ክ/ጦር ተናዳፊወች ዚሃ የገባውን ሃይል ሙሉ ለሙሉ የደመሰሱት ሲሆን በዚህ የተበሳጨዉ አገዛዝ በዘፈቀደ ሶስት ጊዜ ድሮን በመጣል ከጦርነቱ ተሳታፊ ያልሆኑ ንፁሀንን የጥቃቱ ሰለባ አድርጓል።
አሁን ላይ በድሮን ሽፋን በመስጠት ሬሳና ቁስለኛ እያነሳ ሲሆን ከግሸን በአባላ ለመቁረጥ ቢቀሳቀስም በንስሮቹ በደፈጣ ተመቶ ሙትና ቁስለኛውን ይዞ ወደ መጣበት ተመልሷል።
ምንጭ፦ በአፋብን ምኒልክ ዕዝ 104ኛ ኮር ህዝብ ግንኙነት ክፍል!
18 136
ከዚህ ቀደም የሰላም ስምምነት ተቀብያለሁ በሚል ለሁለት ዓመታት ያህል ከአገዛዙ ስንቅና ትጥቅ ሲሰፈርለት የቆየው የአገው ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄ (አዴን) ታጣቂ ኃይል በዋግ ኽምራ ዞን አበርገሌ እና ፃግብጂ ወረዳዎችን ሙሉ በሙሉ መቆጣጠሩን አስታወቀ!
ከሁለት ዓመት በፊት በአገዛዙና በታጣቂ ኃይሉ መካከል ተደርሶ የነበረውን የሰላም ስምምነት እራሱ አገዛዙ በመጣስ ትንኮሳ ፈፅሟል በተባለበት በዚህ ቀጠና፡ ታጣቂዎቹ ከሕወሓት ኃይሎች ጋር በመቀናጀት በወሰዱት እርምጃ ነው በሰቆጣ ዙሪያ የሚገኙ ሁለት ትላልቅ ወረዳዎችን ሙሉ በሙሉ የተቆጣጠሩት።
የዞኑ ፀጥታ ኃይሎች ከነጌታቸው ረዳ የሓራ መሬት ታጣቂዎች ጋር በመቀናጀት በአዴን ቡድን ወታደሮች ላይ አፀፋዊ እርምጃ በመውሰድ ወረዳውን ዳግም ለመቆጣጠር ያደረጉት ሙከራ ከሽፎ ከፍተኛ ኪሣራን አከናንቧቸው በውረደት እንዲሸሹ መደረጋቸው ታውቋል።
(ምስል፦ በታጣቂዎቹ ቁጥጥር ስር የዋሉ የአገዛዙ ተሽከርካሪዎች)
18 136
አፋብን በላይ ዕዝ መይሳው ካሳ ኮር 16ኛ ልባርጋቸው ሙጨ ክ/ር ግዙፍ 2ኛ ዙር ኮማንዶ የፋኖ ሰራዊት አስመረቀ!
ትናንት ሰኔ 02/2018 ጣና ብርጌድ በመባል የሚታዎቀው አደረጃጀት አሁን ላይ ከቀጠናው አቀማመጥ ለግዳጅ በሚያመች መንገድ የመፍትሔ አቅጣጫዎችን በዉል በማጤንና በመምከር ታላቁ አርበኛ ልባርጋቸው ሙጨ ያለመውን ትክክለኛ የመታገያ ሀሳብ ከዳር ለማድረስ ጥልቅ ውይይት በማድረግ የክ/ሩን አደረጃጀት አፋብን በላይ ዕዝ መይሳው ካሳ ኮር 16ኛ ልባርጋቸው ሙጨ በሚል ስያሜና በስሩ አራት ሬጅመንቶችን በማደራጀት ካጠናቀቀ የሰነባበተ ሲሆን ለወራት በአስቸጋሪ ሁኔታ ብዙ መሰናክሎችን በማለፍ በተለይ የታላቁ አርበኛ ልባርጋቸው መስዋትነት ሳይበግራቸው እንደ ታጋይ በቁጭት የተሻለ በመስራት አንድ ልቡ ቢሰዋ እሽ ልቡ ይወለዳል በማለት ስልጠናውን በብቃት ማጠናቀቅ ተችሏል።
ምንጭ፦ አፋብን በላይ ዕዝ መይሳው ካሳ ኮር ሕዝብ ግንኙነት ክፍል!
18 136
በአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነዉ ዕዝ ዓፄ ዘርዓያዕቆብ ኮር ነጎድጓድ ክፍለ ጦር 2ኛ ሻለቃ በሰራችው ድንቅ ና ልዩ የከተማ ውስጥ ኦፕሬሽን ካለምንም የተኩስ ልውውጥ የአገዛዙን የሚሊሻ ሻንበል መሪ ከነ ሙሉ ትጥቁ ጋማውን አንጠልጥላ በድል ተመልሳለች።
የነጎድጓድ ክፍለ ጦር 2ኛ ሻለቃ ሰኔ 1/2018 ዓ/ም ከሌሊቱ 10:00 ሰዓት ገደማ ላይ በደብረ ብርሃን ከተማ ዙሪያ በሚገኘው በሲያደብርናዋዩ ወረዳ ስር ልዩ ስሙ አንጨቆረር ከተማ ድረስ ዘልቃ በመግባት በወሰደችው የተጠና ልዩ ኦፕሬሽን የአገዛዙን ወንበር አስጠባቂ ሚሊሻ ሻምበል መሪ የሆነውን መካሻ አግደው በጋሻው የሚባለውን ባንዳ ሚሊሻ ከነሙሉ ትጥቁ ስታወጣ አቶ መካሻ አግደው በበኩላቸው ይሕንን ብለዋ፡ ፋኖ እደመብረቅ ድንገት ከፊቴ ሲበራብኝ የእምነታቸውና የታማኝነታቸው ልክ ገብቶኛል ስለሆነም በአገዛዙ እንደኔ የተታለላችሁ አድማ ብተና ና ሚሊሻወች አገዛዙ አያዋጣም እኔ አረጋግጫለሁ ስለዚሕ እናተም ተረዱና ወደ ፋኖ ተቀላቀሉ ሲሉ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል።
የፋኖ አናብስቶቹም ይሕንን ሲሉ መልዕታቸውን አስተላልፈዋል ፡ ከአገዛዙ ጎን የተሠለፋችሁ ሁሉ እኛ ስራችን ነውና ከዚሕ ብትማሩ ይበጃችኋል ብለዋል ።
ምንጭ፦አፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ!
18 136
ለኢትዮ 251 ሚዲያ ተከታታዮችና ቤተሰቦች ተወዳጁ “ኢትዮ 251 ዛሬ” ዝግጅታችን በአዲስ መልክ በመረጃ ቴሌቪዥን በኩል በቀጥታ ወደ እናንተ መድረስ መጀመሩን በታላቅ ደስታ እንገልጻለን!
ዕለታዊና ወቅታዊ ይዘቶችንና ልዩ ልዩ አጀንዳዎች የሚቀርቡበት “251 ዛሬ” ፕሮግራማችን፣ ዘወትር ከሰኞ እስከ ቅዳሜ በኢትዮጵያ ሰአት አቆጣጠር ምሽት 2:00 ጀምሮ በመረጃ ቴሌቪዥንና በኢትዮ 251 ሚዲያ ሶሻል ሚዲያ አማራጮች ወደ እናንተ ይደርሳል።
በመረጃ ቴሌቪዥን 📡 የሳተላይት ስርጭት መረጃ (Nilesat)፦
🛰️ ሳተላይት (Satellite): Nilesat / Eutelsat 8 West B (8°W)
📡 ፍሪኩዌንሲ (Frequency): 11636 MHz (ወይም 11637)
↕️ ፖላራይዜሽን (Polarization): Vertical (V) / ቨርቲካል
🔄 ሲምቦል ሬት (Symbol Rate): 27500
🔢 FEC: 5/6
እንዲሁም በቴሌግራም:- https://t.me/ethio251media
በዋትስአፕ:- https://whatsapp.com/channel/0029Vb6SADMFy72J1pBscv40
በX (ትዊተር) ፡- https://x.com/251Media
ፈጣንና ወቅታዊ መረጃዎችን ወደ እናንተ እንደርሳለን።
@ethio251media
18 136
Repost from Ashara Media - አሻራ ሚዲያ
ውድ የአሻራ ሚዲያ ተከታታዮች: የመረጃ ቲቪ ሳተላይት ስርጭት በአዲስ መልክ ተመልሷል! አሻራ ሚዲያም በዚሁ በመረጃ ቴሌቪዥን መረጃዎቻን ወደ እናንተ ለማድረስ መዘጋጀታችንን የምናሳውቀው በደስታ ነው ። ዘወትር ከሰኞ እስከ እሁድ ከምሽቱ 1፡00 ሰዓት (የኢትዮጵያ አቆጣጠር) ስለምናስተላልፍ በNailesat /Eutelsat 8°w -11636/11637 frequency -polarization verticsl sybol rate 27500 -5/6 fec እንገኛለ፤ ፈልጉን።
18 136
204ኛ አስቻለው ደሴ ኮር ለወራት ያሰለጠናቸውን የፋኖ ሠራዊት አባላትን አስመረቀ።
አፋብን ጎንደር ጠቅላይ ግዛት በላይ ዕዝ 204ኛ አስቻለው ደሴ ኮር ግዙፉ እቴጌ ጣይቱ ክፍለ ጦር ለወራት ያሰለጠናቸውን የፋኖ ሰራዊት አባላት በዛሬው ዕለት በደማቅ ሥነ-ሥርዓት አስመርቋል።
በምረቃ ሥነ-ሥርዓቱ ላይ የዕዝ፣ የኮር እና የክፍለ ጦር ከፍተኛ አመራሮች፣ ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች፣ የሀይማኖት አባቶች፣ የሀገር ሽማግሌዎች፣ ወጣቶች እና የአካባቢው ማኅበረሰብ አባላት ተገኝተዋል። የኮሩ ዋና አዛዥ አርበኛ ተሾመ አበባውን ጨምሮ ከፍተኛ አመራሮች በመርሃ ግብሩ ላይ ተሳትፈዋል።
በዕለቱ የተገኙት ክቡር እንግዳ ባስተላለፉት መልዕክት፣ “ይህ የኮማንዶ ኃይል የአማራን ህልውና ከማስከበር ባለፈ ለሕዝቡ መከታና ጋሻ በመሆን ትልቅ አቅም የሚፈጥር እና ጠንካራ አሸናፊ ኃይል ነው” ብለዋል።
ተመራቂዎቹ በቆይታቸው ወቅት የወታደራዊ ስልጠና ንድፈ ሐሳብን ከተግባራዊ ልምምድ ጋር በማጣመር በቂ ዝግጅት ማድረጋቸው ተገልጿል። በምረቃው ሥነ-ሥርዓቱም የሰለጠኑበትን ጥበብና ወታደራዊ ዝግጁነታቸውን የሚያሳዩ የማርሽ ትርኢቶችና ሌሎች ልዩ ልዩ ትዕይንቶች ቀርበዋል።
በተጨማሪም በስልጠናቸው ከፍተኛ ውጤትና ዓርአያነት ላሳዩ የኮማንዶ አባላት የዕውቅናና የሽልማት አሰጣጥ ተከናውኗል።
204ኛ አስቻለው ደሴ ኮር የተጣለበትን ታሪካዊ ኃላፊነት ለመወጣትና የሕዝቡን ዘላቂ ሰላም ለማረጋገጥ መሰል የሰው ኃይል ግንባታዎችን አጠናክሮ እንደሚቀጥል በዕለቱ ተገልጿል።
ምንጭ፦ በአፋብን ጎንደር ጠቅላይ ግዛት በላይ ዕዝ 204ኛ አስቻለው ደሴ ኮር ሕዝብ ግንኙነት ክፍል!
18 136
ዋለ አባተን ጨምሮ የምስራቅ ጎጃም ካድሪን በእንባ ያራጨው የሻለቃ በርይሁን ውዱ ድምሰሳ በተጨማሪ ደግሞ 6 አድማ ብተናዎችን ወደ ጥቁር አንበሳ ተልከዋል።
ከታች በምስሉ ላይ የሚታየው የ36ኛ ሻለቃ የአድማ ብተና አዛዥ ሻለቃ በርይሁን ውዱ በጀብደኛው 206ኛ ኮር 14ኛ ክ/ጦር በጅበላ ሙተራ ሻለቃ የተደመሰሰ ነው። ጠንካራ የሚባሉ አራት አጃቢዎቹን አስከትሎ ከ23 የሰራዊት አባላት ጋር ከደብረ ማርቆስ ወደ ሊባኖስ እየሔደ ባለበት የቦ ማርያም አካባቢ በተደረገበት የደፈጣ ጥቃት ድባቅ ተመቷል።
ዋለ አባተ የምስራቅ ጎጃም አስተዳደሪ ስቅስቅ ብሎ ያለቀሰበት ትልቅ ድል ተቀናጅተናል። የደብረ ማርቆስ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ፣ የብልፅግና ሹማምንትና አዛውንት ደረት እየደቁ በሚገኙበት በዚህ ስዓት በደብረ ማርቆስ ሆስፒታል በነፍስ ውጭ ነፍስ ግቢ ማጣጣር ላይ የነበሩት ፦
1. ግዛት ወርቁ
2. ሰጠኝ አላምነህ
3.ጌታሰው ታደሰ
4. ማሙሸ አዳነ
5. ፈለቀ ጌታቼው
6. መሀመድ አህመድ ህይወታቸውን በደብረ ማርቆስ ሆስፒታል መታደግ ባለመቻሉ ወደ ጥቁር አንበሳ ተልከዋል።
1. ሁሴን ያሲን- ደብረ ማርቆስ ሆስፒታል የሚገኝ ከባድ ቁስለኛ
2.ፋሲል ሲሳይ- ቀላል ቁስለኛ።
በዚህ ስዓት የደብረ ማርቆስ ከተማ ነዋሪዎች በጀግኖች ልጆቻቸው ጀብድ በሃሴት እየቦረቁ መሆናቸውን ታውቋል።
ምንጭ፦ በአፋብን ቴዎድሮስ ዕዝ 206ኛ ኮር ህዝብ ግንኙነት ክፍል!
18 136
ባሕርዳር ዩኒቨርሲቲ ግሽዓባይ ካምፓስ
ወጣቶቹ በጋራ ካሠሙት መፈክር ውስጥ ጥቂቱ፦
# "የአባቶቻችን የእናቶቻች የወንድሞቻችን ደም መሬት ላይ ፈሶ አይቀርም"
# "እነርሱ በእኛ ላይ ያደረጉብንን እኛም ማድረግ አላቃተንም"
# "የአባቶቻችንን ሃይማኖት (አደራ)አንበላም" ...... የቪዲዮ ምንጭ Abreham Ze Tewahido ገጽ
18 136
በጦር ጠበብቶች የሚመራው ጀብደኛው ምኒልክ ዕዝ ታሪክ በደሙ እየፃፈ ይገኛል!!
አፋብን ወሎ ቤተ አማራ ምኒልክ ዕዝ የ106ኛ ኮር 22ኛ ክፍለጦር ረፋዱን የጠላትን ሰራዊት ሙትና ቁስለኛ በማድረግ አይቀጡ ቅጣት ቀጥተውታል።
ከጋሸና ተነስቶ ወደ ገረገራ ሊሻገር በነበረ የአገዛዙ ሰራዊት ላይ የቀኝአዝማች ተበጀ ወርቁ ትንፋሾች ዶግ አመድ አድርገውታል።
ንስሮቹ የጠላትን እንቅስቃሴ በማፈንፈን ከቋና ሮቢት እንደ አቦ ሸማኔ ተምዘግዝገው ዛሬ ማለትም ግንቦት 29/2018 ከረፋዱ 2:00 ሰዓት ላይ አርቢት ኪዳነ-ምህረት ጋሸና አፍንጫ ስር ላይ የስርዓቱ ወንበር አስጠባቂዎች ከባድ ጥቃት ፈፅመዉበታል።
በዚህ ጥናታዊ ኦፕሬሽን ከ09 በላይ የተደመሰሱ እና ከ17 በላይ ከባድ ቁስለኛ ማድረግ ተችሏል።
የተወሰደበት ጥናታዊ እርምጃ አስከፊ በመሆኑ ወደ መጣበት የፈረጠጠ ሲሆን ባጃጅ በማስገደድ ቁስለኛና ሙቱን ጭኖ ሲፈረጥጥ የአርቢት ኪዳነምህረት ምድር አስከሬናቸው በተገተቱ የጠላት ሰራዊቶች ደም ጨቅይቷል።
በርካታ ቁስለኛውን ወደ ኮን ሆስፒታል እያሳከመ የሲቃ ድምፁን እያሰማ ይገኛል ሲል 106ኛ ኮር ህዝብ ግንኙነት መምሪያ መረጃዉን አድርአድርሷል።
መዳረሻውን ድልና ነፃነት የሆነው የአማራ ሕዝብ የሕልውና ተጋድሎ ይቀጥላል!!
ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን!
አፋብን ወሎ ቤተ አማራ ምኒልክ ዕዝ ህዝብ ግንኙነት መምሪያ!!
ግንቦት 29/2018 ዓ/ም
18 136
+2
አፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ለወራት ያሰለጠናቸውን የኮማንዶ አባላት በደማቅ ሁኔታ አስመረቀ!
የሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ እየተዋጋን እንሰለጥናለን እየሰለጠንን እንዋጋለን በሚል መርህ፤ ለረጅም ወራት በጽናት፣ በልዩ ሁኔታና በከፍተኛ ዲሲፕሊን ሲያሰለጥናቸው የቆያቸውን የኮማንዶ አባላት በዛሬው ዕለት የዕዙ ዋና መሪ ኢንጅነር ደሳለኝ ሲያስብ ሸዋ ና ሌሎች የዕዝና የኮር ከፍተኛ አመራሮች በተገኙበት በደማቅ ሁኔታ አስመርቋል።
ተመራቂዎቹ በቆይታቸው ወታደራዊ ስልጠናው ንድፈ ሀሳብን በተግባር በማጣመር በበቂ ሁኔታ በብቁ አሰልጣኞች ሁሉንም አይነት ውጣውረድ ተቋቁመው በቂ ስልጠና የወሰዱ ሲሆን፣ የተሰጣቸውን ተልዕኮ በአስተማማኝ ሁኔታ ለመወጣት ዝግጁ መሆናቸውን ገልፀዋል።
በምረቃ ሥነ-ሥርዓቱ ላይ የዕዙ ከፍተኛ አመራሮች፣ ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች እና የአካባቢው ማኅበረሰብ አባላት የተገኙ ሲሆን፣ የዕለቱ ክቡር እንግዳ ባስተላለፉት መልዕክት፦
"ይህ የኮማንዶ ኃይል የአማራን ህልውና ከማስከበር ባለፈ፣ ለሕዝባችን መከታና ጋሻ በመሆን ረገድ ትልቅ አቅም የሚፈጥር እና ጠንካራ አሸናፊ ሀይልም ነው" ብለዋል።
በምረቃው ስነ-ስርዓት ላይ ተመራቂዎቹ ወታደራዊ ዝግጁነታቸውን የሚያሳይ ልዩ ልዩ ትዕይንቶችንና የማርሽ ትርኢቶችን ያቀረቡ ሲሆን፣በስልጠናቸው ከፍተኛ ውጤትና አርአያነት ላሳዩ የኮማንዶ አባላትም የዕውቅናና የሽልማት አሰጣጥ ተከናውኗል።
አሳምነው ዕዝ የተጣለበትን ታሪካዊ ኃላፊነት ለመወጣትና የሕዝቡን ዘላቂ ሰላም ለማረጋገጥ መሰል የሰው ኃይል ግንባታዎችን አጠናክሮ እንደሚቀጥልም በዕለቱ ተገልጿል።
ምንጭ፦በአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ!
18 136
+2
አፋብን ግንቦት 24 ተካሂዷል የተባለውን ምርጫ ተከትሎ የምርጫ ታዛቢ ቡድኖች የሰጡትን ግምገማ በተመለከተ ጥልቅ ስጋቱን እንዲሁም ነባራዊ የሀገሪቱን ሁኔታ እና የምርጫውን ሒደት በተመለከተ ሰፊ የግንዛቤ ማስጨበጫ ይዘቶች ያየዘ ደብዳቤ ተፅፏል ፡፡
ደብዳቤው የተፃፈው፦ ለአንቶኒዮ ጉቴሬዝ(ተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሀፊ)፣ ለማህሙድ አሊ የሱፍ (የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር)፣ ለኡሁሩ ኬንያታ (የቀድሞ የኬንያ ፕሬዝዳንት እና የአፍሪካ ህብረት የምርጫ ታዛቢ ቡድን መሪ) ነው።
现已上线!2025 年 Telegram 研究 — 年度关键洞察 
