የትምህርትና ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን
Open in Telegram
5 357
Subscribers
No data24 hours
-97 days
+730 days
Posts Archive
የባለስልጣኑ አመራሮች እየተገነቡ ያሉትን የአቅመ ዳካማ ወገኖች ቤት ግንባታ ክትትል አደረጉ፡፡
(መስከረም 2 ቀን 2018 ዓ.ም)በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የትምህርትና ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን የትምህርት ማህብረሰብ አካላትን በማስተባበር እያሰራ ያለውን የአቅመ ደካማ ወገኖች ቤት የደረሰበትን የግንባታ ሂደት የባለስልጣኑ አመራሮች ክትትል አደረጉ፡፡
በመሆኑም የግንባታው ሂደት ያለበትን ደረጃ ተመልክተው የግንባታው ቀሪ ስራ በጥቂት ቀናት ውስጥ መጠናቀቅ እንዳለበት ግንባታውን ለሚያከናውነው አካል አሳስበዋል፡፡
#ፌስቡክ;https://www.facebook.com/AA-Educational-Training-Quality-Occ-Competency-Assurance-Authority-100864428091362/?__tn__=-UC*F
#ድረ_ገጽ; educoc.gov.et
#ቴሌግራም https://t.me/AAEQOCAA
#ቲክቶክ https://www.tiktok.com/@educationtraning2?_t=ZM-8u2f6smztvr&_r=1
#ነጻ_የጥቆማ_የስልክ_መስመር_9302
#ዩቲዩብ https://www.youtube.com/channel/UCzbsHLZjub9c7uVPjc
#በህብረት_ችለናል!!
የታላቁን የህዳሴ ግድብ መጠናቀቁን ምክንያት ማድረግ በተዘጋጀው የብዙሃን የአካል ብቃት እንቅስቃሴ በርካታ የመዲናዋ ነዋሪዎች ከንጋቱ 11:00 ጀምሮ በመስቀል አደባባይ ተገኝተዋል።
ነዋሪዎች የአባይ ግድብ መጠናቀቁ የሚያበስሩ፤ ለኢትዮጵያውያን የሚሰጠውን ዘርፈ ብዙ ጥቅም የሚገልፁና አንድነትን፣ አብሮነትን እና ድል አድራጊነትን የሚያሳዩ የተለያዩ መልዕክቶችን እያሰሙ በጋራ የአካል ብቃት እንቅስቃሴ እየሰሩ ይገኛሉ።
በህብረት ችለናል በሚል መሪ ቃል በተዘጋጀው የአካል ብቃት እንቅስቃሴ የከተማው ከፍተኛ አመራርችን ጨምሮ በላይ የህብረተሰብ ክፍሎች ይሳተፋሉ ተብሎ ይጠበቃል።
+3
ከሕዳሴ ግድብ ምረቃ በኋላ የተካሄደ የመሪዎች ስብሰባ።
Post GERD inauguration leaders’ meeting.
#PMOEthiopia
+1
የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) መልዕክት
የነገው ቀን
ዲጂታል ኢትዮጵያን እውን ማድረግ
ትናንትን በመጠቀምና በማረም፣ ዛሬ ላይ ተግተን በመሥራት፣ ነገን እጅግ የተሻለ ለማድረግ ተነሥተናል፡፡
በአናሎግ ዘመን የነበሩ ችግሮች በዲጂታል ዘመን አይደገሙም፡፡
ነገ “ዲጂታል ኢትዮጵያ” ፕሮጀክት ከመሆን አልፎ ባህል ይሆናል፡፡
ንግድ እና አገልግሎታችንን በማቀላጠፍ፣ መረጃዎቻችንን ተደራሽ በማድረግ፣ አንድ ሰው አንድ እንዲሆን በማስቻል፣ የፋይናንስ ሥርዓታችንን ይበልጥ ተደራሽ ቀልጣፋ እንዲሆን በማድረግ፣ የትምህርትና የጤና አገልግሎቶችን በየአቅጣጫው በማስፋፋት፣ ዲጂታል ኢትዮጵያ እንዲሳካ የሁላችንን ጥረትና ትኩረት ይፈልጋል፡፡
+1
የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) መልዕክት
የነገው ቀን
ዲጂታል ኢትዮጵያን እውን ማድረግ
ትናንትን በመጠቀምና በማረም፣ ዛሬ ላይ ተግተን በመሥራት፣ ነገን እጅግ የተሻለ ለማድረግ ተነሥተናል፡፡
በአናሎግ ዘመን የነበሩ ችግሮች በዲጂታል ዘመን አይደገሙም፡፡
ነገ “ዲጂታል ኢትዮጵያ” ፕሮጀክት ከመሆን አልፎ ባህል ይሆናል፡፡
ንግድ እና አገልግሎታችንን በማቀላጠፍ፣ መረጃዎቻችንን ተደራሽ በማድረግ፣ አንድ ሰው አንድ እንዲሆን በማስቻል፣ የፋይናንስ ሥርዓታችንን ይበልጥ ተደራሽ ቀልጣፋ እንዲሆን በማድረግ፣ የትምህርትና የጤና አገልግሎቶችን በየአቅጣጫው በማስፋፋት፣ ዲጂታል ኢትዮጵያ እንዲሳካ የሁላችንን ጥረትና ትኩረት ይፈልጋል፡፡
+9
የአራዳ እና ቂርቆስ ቅ/ጽ/ቤት የማዕድ ማጋራት መርሃ-ግብር አከናወነ፡፡
(ጳጉሜ 4 ቀን 2017 ዓ.ም)በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የትምህርትና ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን የአራዳና ቂርቆስ ቅ/ጽ/ቤት በዓሉን ምክንያት በማድረግ ለሰራተኞች እና ቅ/ጽ/ቤቱ በቋሚነት ለሚረዳቸው ህጻናት ማዕድ አጋርቷል፡፡
አቶ ያሬድ ካሳ የአራዳና ቂርቆስ ቅ/ጽ/ቤት ስራ አስኪያጅ አዲስ ዓመትን ምክንያት በማድረግ ለተደረገው ማዕድ ማጋራት ግብአት በማሰባሰብ ለተሳተፉ አካላት ምስጋና ያቀረቡ ሲሆን መጭው አዲስ ዓመት በጋራ ሰርተን የምንቆምበት ውጤት የምናስመዘግብበት በፍቅር በአንድነት የምንቆምበት እና የምንደማመጥበት ዘመን እንዲሆን መልካም ምኞታቸውን በመግለጽ የእንኳን አደረሳችሁ መልእክት አስተላልፈዋል፡፡
#ፌስቡክ;https://www.facebook.com/AA-Educational-Training-Quality-Occ-Competency-Assurance-Authority-100864428091362/?__tn__=-UC*F
#ድረ_ገጽ; educoc.gov.et
#ቴሌግራም https://t.me/AAEQOCAA
#ቲክቶክ https://www.tiktok.com/@educationtraning2?_t=ZM-8u2f6smztvr&_r=1
#ነጻ_የጥቆማ_የስልክ_መስመር_9302
#ዩቲዩብ https://www.youtube.com/channel/UCzbsHLZjub9c7uVPjc
አዲሱ ዓመት የበለጠ ውጤታማ የሆኑ ስራዎችን በመስራት የብልፅግና ዘመን እንዲሆን በትጋት መስራት ይገባል ተባለ፡፡
(ጳጉሜ 4 ቀን 2017 ዓ.ም)በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የትምህርት ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን ለባለስልጣኑ ሠራተኞች የማዕድ ማጋራት መርሃ-ግብር አከናወነ፡፡
በባለስልጣኑ የመሰብሰቢያ አዳራሽ በተከናወነው የማዕድ ማጋራት መርሃ ግብር ላይ የትምህርትና ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን ዋና ስራ አስኪያጅ አቶ ኢዘዲን ሙስባህ ባስተላለፉት መልዕክት እንደገለፁት ቀኑ የህዳሴ ግድብ የተመረቀበት እና ድርብ ድል ይዘን ወደ አዲሱ ዘመን ለመሻገር ዋዜማ ላይ ነን ብለዋል፡፡
አዲሱን አመት የበለጠ አቅም ፈጥረን የተሻለ ስራ ለመስራት ጥረት ማድረግ የሚገባ ሲሆን ስራን በማቀድ መስራት የተሻለ ዘመን በመመኘት መተግበር ይገባል ብለዋል፡፡አገራችን የበለጸገች ሃገር እንድትሆንና ራዕይዋን ለማሳካት ሁሉም ዜጋ የበኩሉን ሊወጣ ይገባል የሚል መልዕክት አስተላልፈዋል፡፡
በማዕድ ማጋራቱ ላይ የባለስልጣኑ አመራሮች የተገኙ ሲሆን ለሠራተኞቹም ማዕዱን አጋርተዋል፡፡
የማዕድ ማጋራቱ መርሃ-ግብር የተከናወነው የአጠቃላይ ትምህርት ተቋማት እና የማሠልጠኛ ተቋማትን በማስተባበር መሆኑም ተገልጿል፡፡
#ፌስቡክ;https://www.facebook.com/AA-Educational-Training-Quality-Occ-Competency-Assurance-Authority-100864428091362/?__tn__=-UC*F
#ድረ_ገጽ; educoc.gov.et
#ቴሌግራም https://t.me/AAEQOCAA
#ቲክቶክ https://www.tiktok.com/@educationtraning2?_t=ZM-8u2f6smztvr&_r=1
#ነጻ_የጥቆማ_የስልክ_መስመር_9302
#ዩቲዩብ https://www.youtube.com/channel/UCzbsHLZjub9c7uVPjc
+8
የአዲስ አበባ ከተማ ነዋሪዎች ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ በርካታ ዉጣ ዉረዶችን አልፎ በመመረቁ ደስታቸዉን እየገለጹ ነዉ
የአዲስ አበባ ከተማ ነዋሪዎች የታላቁ ህዳሴ ግድብ ምረቃን አስመልክቶ ደስታቸውን እየገለጹ ይገኛሉ፡፡
የዛሬዋ እለት ለመላ ኢትዮጵያዊያን የደስታ ቀን ናት፡፡ ብዙ መስዋትነት የተከፈለበት፣ መላ ኢትዮጵያዊያን አሻራቸውን ያስቀመጡበት እና ለፍፃሜው ሲጓጉለት የነበረው ታላቁ የህዳሴ ግድብ ግንባታ ተጠናቆ ለምረቃ በቅቷል፡፡
ዕርስ በዕርስ በመረዳዳት በጎነትን ማጠናከር እንደሚገባ ተገለጸ፡፡
(ጳጉሜ 4 ቀን 2017 ዓ.ም)በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የትምህርት ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን በአራዳ ክፍለ ከተማ በወረዳ 9 ለሚገኙ አቅመ ደካማ የሕብረተሰብ ክፍሎች ማዕድ አጋርቷል፡፡
በወረዳ 9 በተካሄደው የማዕድ ማጋራት መርሃግብር ላይ የትምህርትና ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን ዋና ስራ አስኪያጅ አቶ ኢዘዲን ሙስባህ ባስተላለፉት መልዕክት ቀኑ የህዳሴ ግድብ የሚመረቅበት እና የበዓል መዳረሻ በመሆኑ ልዩ ቀን እንደሆነ አስታውሰው በበዓል ቀን አንድም ሰው መቸገር የሌለበት በመሆኑ በየግዜው ማዕድ በማጋራት የበጎነት ስራ የሚከናወን መሆኑን ተናግረዋል፡፡
ለማዕድ ማጋራቱም የትምህርት ተቋማትን በማስተባበር ስራው መከናወኑን የተናገሩ ሲሆን ተቋማት ሃገር ተረካቢ ዜጎችን ከማፍራት ባሻገር ማህበራዊ ኃላፊነታቸውንም እየተወጡ ያሉበት ሁኔታ መሆኑን ገልጸዋል፡፡
በዕለቱም የተገኙት የአራዳ ክፍለ ከተማ ወረዳ 9 ዋና ስራ አስፈፃሚ የሆኑት ወ/ሮ ፀጋነሽ ታምራት በበኩላቸው ባስተላለፉት መልዕክት ተቋማት መልካም አጋርነታቸውን እየገለፁ ሲሆን ቤት በማደስ ማዕድ በማጋራት የሚያደርጉነት የበጎነት ስራ የሚበረታታ መሆኑን ጠቅሰው በአዲስ ዓመትም በወረዳው ለሚገኙ አቅመ ደካማ የሕብረተሰብ ክፍሎች ለተደረገው የማዕድ ማጋራት መርሃግብር ምስጋናቸውን አቅርበዋል፡፡
በመርሃግብሩ ላይ የባለስልጣኑ የበላይ አመራሮች ተገኝተው ከሀምሳ በላይ ለሚሆኑ አቅመ ደካማ ወገኖች ዘይት እና ዱቀት ተሰጥቷል፡፡
#ፌስቡክ;https://www.facebook.com/AA-Educational-Training-Quality-Occ-Competency-Assurance-Authority-100864428091362/?__tn__=-UC*F
#ድረ_ገጽ; educoc.gov.et
#ቴሌግራም https://t.me/AAEQOCAA
#ቲክቶክ https://www.tiktok.com/@educationtraning2?_t=ZM-8u2f6smztvr&_r=1
#ነጻ_የጥቆማ_የስልክ_መስመር_9302
#ዩቲዩብ https://www.youtube.com/channel/UCzbsHLZjub9c7uVPjc
