የትምህርትና ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን
Open in Telegram
5 357
Subscribers
No data24 hours
-97 days
+730 days
Posts Archive
+2
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) ታላቁ የኢትዮጵያ ኅዳሴ ግድብን መረቁ
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የኢትዮጵያውያን ሕብረ ብሔራዊነት መገለጫ የሆነውን ታላቁ የኢትዮጵያ ኅዳሴ ግድብ በዛሬው ዕለት መረቁ፡፡
የኢትዮጵያውያን የዘመናት ቁጭት የነበረው ታላቁ ኢትዮጵያ ኅዳሴ ግድብ ግንባታ ተጠናቅቆ የምረቃ ሥነ ሥርዓት በጉባ እየተካሄደ ነው፡፡
በምረቃ ሥነ ሥርዓቱ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)፣ የፌደሬሽን ምክር ቤት አፈ ጉባዔ አገኘሁ ተሻገር፣ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈ ጉባዔ ታገሰ ጫፎ እና ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ተገኝተዋል፡፡
በተጨማሪም በም/ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ማስተባበሪያ ማዕከል ኃላፊ እና የብልጽግና ፓርቲ ም/ፕሬዚዳንት አደም ፋራህ፣ የቀድሞ ጠቅላይ ሚኒስትር ሃይለማሪያም ደሳለኝ፣ የቀድሞ ም/ጠቅላይ ሚኒስትር ደመቀ መኮንን፣ የክልል ርዕሳነ መስተዳድሮች:የከተማ አስተዳደር ከንቲቦች እና ሚኒስትሮች ታድመዋል፡፡
+4
ተመረቀ !!!
እንኳን ደስ አላችሁ፣
እንኳን ደስ አለን፤
ፈጣሪ የተመሰገነ ይሁን።
Eebbifameera!
Baga Gammaddan;
Baga Gammadne;
Waaqni Kan Galataa Yaa Tahu.
“የታሪክና ፖለቲካ ብያኔን የለወጥንበት የጋራ ችሎታችን ትዕምርት ነው”
የኢፌዴሪ መንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት
የኢፌዴሪ መንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ታላቁን የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ምረቃ አስመልክቶ መልዕክት አስተላልፏል።
ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ በታላቋ ኢትዮጵያ ልጆች ጥሪት፣ ላብ፣ ዕውቀት እና ደም የተገነባ የመቻል ትዕምርት ነው፡፡ ከእንግዲህ ኢትዮጵያ የተፈጥሮ ሀብቷ ፍትሐዊ ተጠቃሚ እንጅ ተመልካች አይደለችም፤ በአፍሪካ የታላቁ ግድብ ባለቤት እንጅ የረዥሙ ወንዝ ባለቤት የጥቅሙ ግን ተመልካች አይደለችም፡፡
የዓለማችንን ረዥሙንና በፈታኝ መልክአ ምድር ውስጥ የሚያልፈ ወንዝ ተባብረዉ የገሩ ኢትዮጵያውያን ሕልማቸዉን ከማሳካት የሚያስቆማቸዉ አንዳች ምድራዊ ኃይል አልነበረም፤ አይኖርምም፡፡
ሕዳሴ የኢትዮጵያ የተሰናሰነ ብዝኃነት ዐቅም የታየበት፣ በየክፍለ ዘመኑ የዓለምን ታሪክና ፖለቲካ የሚቀይር ተምሳሌታዊ ጥረትና ድል ከኢትዮጵያ እንደሚመነጭ ያስመሰከረ ነው፡፡ በ19ኛዉ ክፍለ ዘመን መገባደጃ በውስብስ ተፈጥሯዊና ሰው ሠራሽ ችግሮች አልፈዉ የዓድዋ ድልን ለዓለም የነፃነት ትግል ያበሩት ኢትዮጵያውያን ነበሩ፡፡ ያ ድል የፀረ ቅኝ አገዛዝ ትግልን “ከዓድዋ ድል በፊት እና በኋላ” ብሎ የከፈለ ትልቅ የታሪክ አንጓ ነው፡፡
እነሆ በ21ኛዉ ዘመንም ኢትዮጵያውን ዳግማዊ ዓድዋን አሳክተዋል፡፡ የውኃ ፍትሐዊ አጠቃቀምን “ከኅዳሴ ግድብ በፊት እና በኋላ፣ የአፍሪካ ፖለቲካ ከኅዳሴ ግድብ በፊት እና በኋላ፣ ዓለማቀፍ ዲፕሎማሲ ከኅዳሴ ግድብ በፊት እና በኋላ” ብሎ መክፈል የሚችል ታላቅ ድል ተመዝግቧል፡፡ ይህ ድል ደግሞ የመላው ኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵያውያን ነው፡፡
ሕዳሴ የአይችሉም ትርክትን ‘ኢትዮጵያውያን አይቻሉም’ ወደሚል ቀይሯል፡፡ ከእኛው ውስጥ በተገዙ ተላላኪዎች የተፈጠሩ የእርስ በርስ ግጭት እና ዓለማቀፍ የዲፕሎማሲ ጫና፣ የማናውቃቸዉ የቅኝ ግዛት ዘመን ውሎች እና የታሪካዊ ጠላቶች ወጥመድ ተባብረዉ ያላስቀሩት ታላቅ ድል ነው፤ ሕዳሴ፡፡ ሕዳሴ የኢትዮጵያን የመልማት ዐቅም እና የአፍሪካዊያን ራስን የመቻል ብስራትና የእርስ በርስ ትስስር በእጅጉ የሚወስን ነው፡፡ ሕዳሴ ታዳሽ ኃይል በማመንጨት በካይ የኃይል ምንጮችን የሚያስቀር ዓለም ሊደግፈዉ ሲገባ ሲፈትነዉ የኖረ፣ ግን በኢትዮጵያውያን የጋራ ጥረት የተሳካ ልዩ ፕሮጀክታችን ነው፡፡
ሕዳሴ ለኢትዮጵውያን ከመኩሪያ ስኬት ባሻገር የኃይል ምንጭ፣ የዓሣ ሀብት መገኛ፣ የቱሪዝም መዳረሻም ጭምር ነው፡፡ ሕዳሴ ለሌሎች የተፋሰሱ ሀገራት የፍትሐዊ ተጠቃሚነት ምሳሌ ነው፡፡ ሕዳሴ የታችኛው ተፋሰስ ሀገራት ከጎርፍ ተከላካይ ዋስትናቸው፤ በትነት ይባክን የነበረዉን ውኃ ማቆያቸው፤ ዓመቱን ሙሉ የተመጠነ ውኃ ማግኛቸው፤ ግድቦቻቸዉ በደለል እንዳይሞሉ መከላከያቸው ነው፡፡
እንዲህ ያለ ፋይዳ ያለዉን ግድብ መደገፍ የተገባ ነበር፤ ነገር ግን ይህንን ኹሉ ጥቅማቸዉን በመዘንጋት እና ሕዝባቸዉ በተሳሳተ መንገድ እንዲረዳው በማድረግ ታሪካዊ ጠላቶቻችን የኛን ተጠቃሚነት ለማደናቀፍ ሲጥሩ ኖሩ፡፡ ግን አዘገዩን አንጅ አላስቀሩንም፡፡
እኛ ትዮጵያውያን የሰብአዊነትና የሞራል ባለቤት ሕዝቦች ነን፡፡
አይደለም ተፈጥሮ ለጋራ የሰጠንን ወንዝ ለብቻ በመጠቀም ሌሎችን ልንጎዳ፤ ባሕር ተሻግሮ ሊያጠፋን የመጣ ጠላትን አንዳች ዓለማቀፋዊ ሰብአዊ መብቶች ሕግ፣ ድርጅት እና አሠራር ባልነበረበት ማርከን፣ ተንከባክበን የያዝን፣ በክብርም ወደሀገሩ የመለስን የሰብአዊነትና የሞራል ባለቤቶች ነን፡፡
የታችኞቹ የተፋሰስ ሀገራት ሕዝቦች እንዲያውቁልን የምንፈልገውም ይህንኑ ነው፡፡ ይሁን እንጅ በኃይል ከብልጽግና ጉዟችን ሊያደናቅፈን የሚቃጣን፣ ሉዓላዊነታችንን እና ነፃነታችንን ሊገዳደር፣ በተፈጥሯዊና ታሪካዊ ሀብታችን እንዳንጠቀም ሊከለክለን የሚችል ምድራዊ ኃይል አይኖርም፡፡ ኅዳሴ ለዚህ ማሳያ ትዕምርታችን ነው፡፡
በጋራ ችለናል፤ እንችላለንም!
ጳጉምን 4/2017 ዓ/ም
የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት
ጳጉሜ 4:-የማንሠራራት ቀን
ዘላቂ ልማት ለሀገራዊ ማንሠራራት
"ኢትዮጵያ ተነሥታለች፡፡ ከእንግዲህ ወደኋላ አትመለስም፡፡ ይሄ የማንሠራራት ጉዞዋ በዘላቂ ኢኮኖሚያዊ ዕድገት የታገዘ መሆን አለበት፡፡
በተለይም በማዕድን፣ በቱሪዝም፣ በግብርና፣ በአምራችነት እና በአይሲቲ ዘርፎች የላቁ ውጤቶችን እያስመዘገብን መቀጠል አለብን፡፡ ለዕድገታችን አጋዥ የሚሆን ሀብት መፍጠር እና ገቢ መሰብሰብ ይገባናል፡፡ ዕድገታችን የሚያመነጨውን ገቢና ሀብትም በሚገባ ሰብስበንና ቆጥበን ለብልጽግና ግባችን መጠቀም አለብን፡፡
የጀመርነውን የማክሮ ኢኮኖሚ ሪፎርም በማሣለጥና በማሳካት የኢትዮጵያ ማንሠራራት ወደ ዘላቂ የኢትዮጵያ ብልጽግና እንዲለወጥ እናደርጋለን"፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትር ዓብይ አህመድ(ዶ/ር)
አፍሪካ በዓለም ፊት በራሷ አቅም ለውጥ የማምጣት አቅም ይዛ መቅረብ አለባት - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር)
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) አፍሪካ በዓለም ፊት ተደራዳሪ አካል ሳትሆን በራሷ አቅም ለውጥ የማምጣት አቅም ይዛ መቅረብ አለባት አሉ፡፡
ሁለተኛው የአፍሪካ የአየር ንብረት ጉባኤ ‘ዓለም አቀፍ የአየር ንብረት መፍትሄዎችን ማሳለጥ፣ የአፍሪካን አረንጓዴ ልማት በፋይናንስ መደገፍ’ በሚል መሪ ሀሳብ ዛሬ በአዲስ አበባ እየተካሄደ ይገኛል።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ በጉባኤው ላይ ባስተላለፉት መልዕክት፤ የኬንያ መንግስት የመጀመሪያውን ጉባኤ ባለፈው ዓመት ባስተናገደበት ወቅት በርካታ ፈር ቀዳጅ ተግባራት እንዲጀመሩ በማድረጉ ምስጋና አቅርበዋል፡፡
የቴክኖሎጂ፣ የጊዜ እና የፋይናንስ ተግዳሮቶችን ለመቀልበስ ባለን አቅም በራሳችን ጥረት አሁን መጀመር አለብን ብለዋል።
አፍሪካ አህጉሪቱን እና ዓለምን መመገብ የሚችል ጥቅም ላይ ያልዋለ ለም የእርሻ መሬት መገኛ፣ የበርካታ ታዳሽ ኃይል ምንጭ ምድር መሆኗን ጠቅሰዋል።
እኛ አፍሪካውያን እዚህ የተሰባሰብነው በአየር ንብረት ጉዳይ ስለ ህልውናችን ለመደራደር ሳይሆን በራሳችን አቅም ለአየር ንብረት ተፅዕኖ ምላሽ ለመሥጠት ነው ሲሉ ተናግረዋል።
ከሰባት ዓመታት በፊት በተጀመረው የአረንጓዴ ዐሻራ መርሀ ግብር አማካኝነት እስካሁን ከ48 ቢሊየን በላይ ችግኞች መተከላቸውን ገልጸው፤ ኢትዮጵያ በምግብ ስርዓት ራስን ከመቻል አልፎ ወደ ውጭ ለመላክ ያስቻላትን ውጤት ማስመዝገቧን አብራርተዋል፡፡
የምግብ ስርዓትን በተመለከተ አፍሪካ ራሷን ከመመገብ አልፋ ባላት ፀጋ ወደ ተቀረው ዓለም የመላክ አቅም እንዳላት ጠቅሰው፤ ይህን እውን ለማድረግ ተገቢውን ጥረት ማድረግ እንደሚገባ ተናግረዋል፡፡
አፍሪካ በዓለም ፊት ተደራዳሪ አካል ሳትሆን በራሷ አቅም ለውጥ የማምጣት አቅም ይዛ መቅረብ እንዳለባት ገልጸዋል፡፡
አሁን ላይ ያለነው ትውልዶች የታለሙ ግቦችን በማሳካት የመጀመሪያዎቹ የመሆን እድል አለን ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ ይህን ማድረግ ካቃተን በታሪክ የመጀመሪያው ተወቃሽ እንሆናለን ብለዋል፡፡
ኢትዮጵያ 32ኛውን የተባበሩት መንግስታት የአየር ንብረት ጉባኤ በፈረንጆቹ 2027 ለማስተናገድ እጩ በመሆኗ መላው ዓለም ወደ አዲስ አበባ በመምጣት ጉባኤውን እንዲታደም ከወዲሁ ጋብዘዋል።
እንኳን ደህና መጣችሁ!
የማንሰራራታችን ሂደት ለአፍሪካውያን ወንድሞቻችን የሚተርፍ ፣ለዓለም የሚነገር ምስክርነት ነው !
ዛሬ ለ2ኛው የአፍሪካ የአየር ንብረት ጉባኤ ወደ አዲስ አበባ የመጡ ከ25 ሺህ በላይ እንግዶችን ተቀብለን በጉባኤው ላይ እየተሳተፉ ይገኛሉ ።
ጉባኤው “ዓለም አቀፍ የአየር ንብረት መፍትሄዎችን ማሳለጥ፣ የአፍሪካን አረንጓዴ ልማት በፋይናንስ መደገፍ” በሚል መሪ ሀሳብ ከጳጉሜን 3 እስከ 5፣ 2017 ዓ.ም በአዲስ አበባ ይካሄዳል። በጉባዔው መሪ ሃሳብ መሠረት ኢትዮጵያ ለአየር ንብረት መዛባት መፍትሔ ይሆናሉ ያለቻቸውን ተግባራት ጥንቅቅ አድርጋ እየሰራች መሆኗን በኤግዚቢሽን ተሳትፎአችን ለአፍሪካውያን ወንድሞቻችን አስረድተናል።
እጅ ለእጅ ተያይዞ ለማደግ፤ ለመጪው ትውልድ የሚተርፍ ስራ ለመስራት አዲስ አበባ ማሳያ ተሞክሮዎችን ይዛ ቀርባለች።
ውድ የከተማችን አንግዶች አዲስ አበባ የእናንተ የምቾት ቤታችሁ ናት ። አዲስ አበባ የእናንተ የብልፅግና በር ናት። መምጣታችሁ፣ አብረን መምከራችን ለመጪው የአፍካዊያን መፃኢ ዕድል መሠረት ነው ።
የከተማችን ነዋሪዎችም እስካሁን እያደረገችሁት ያለው አስተዋጽኦ ጉባኤው እስኪጠናቀቅና እንግዶች ወደየመጡበት አገር እስኪመለሱ ድረስ የተለመደ ትብብራችሁንና እንግዳ ተቀባይነታችሁን እንድታጠናክሩ ስል እጠይቃለሁ።
ፈጣሪ ኢትዮጵያን እና አፍሪካን ይባርክ
ከንቲባ አዳነች አቤቤ
+7
የአፍሪካ መዲና አዲስ አበባ 25 ሺህ በላይ ሰዎች ይሳተፉበታል ተብሎ የሚጠበቀዉን 2ኛዉን የአፍሪካ አየር ንብረት ጉባኤ ከጳጉሜን 3 እስከ 5 ቀን 2017 ዓ.ም ድረስ የሚቆይ ሲሆን አዲስ አበባ እንግዶቿን እያስተናገደችም ትገኛለች::
አያይዘውም ሳምንቱ ያማረና የደመቀ እንዲሆን መልካም ምኞታቸውን በመግለፅ መጪው አዲሱ ዓመት አገራችን እያስመዘገበች ያለውን ስኬት በእመርታ ላይ እመርታን በመጨመር ብልጽግና እውን የሚሆንበት ዘመን ይሁንልን በማለት መልካም ምኞታቸውን አስተላልፈዋል፡፡
#ፌስቡክ;https://www.facebook.com/AA-Educational-Training-Quality-Occ-Competency-Assurance-Authority-100864428091362/?__tn__=-UC*F
#ድረ_ገጽ; educoc.gov.et
#ቴሌግራም https://t.me/AAEQOCAA
#ቲክቶክ https://www.tiktok.com/@educationtraning2?_t=ZM-8u2f6smztvr&_r=1
#ነጻ_የጥቆማ_የስልክ_መስመር_9302
#ዩቲዩብ https://www.youtube.com/channel/UCzbsHLZjub9c7uVPjc
+5
የባለስልጣኑ የወርቃማ ሰኞ ማለዳ የማነቃቂያና የእውቀት ሽግግር መርሃ-ግብር ተካሄደ፡፡
(ጳጉሜ 3 ቀን 2017 ዓ.ም)በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የትምህርትና ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን የወርቃማ ሰኞ የማነቃቂያና የእውቀት ሽግግር መርሃ-ግብር "የባህሪ ግንባታና የትግበራ ክህሎት"በሚል ርዕስ ተካሂዷል፡፡
አቶ ስለሺ ታደለ የባለስልጣኑ የሪፎርምና አገ/አሰ/ክ/ድ/ዳ/ዳይሬክተር በርእሱ ላይ የተዘጋጀ የመማማሪያ ሰነድ ያቀረቡ ሲሆን ባህሪ ምንድ ነው፣ የመልካም ባህሪያት መገለጫዎች ምንድናቸው፣የስራ ላይ ስነምግባር፣መልካም ባህሪያትን እንዴት እናዳብራለን፣የስሜት ብልህነት፣የስሜት ብልህነት ብቃቶች፣የስሜት ብልህነቶችን ማጎልበቻ መንገዶች ጽናት፣መለማመድ፣ግብረ-መልስ መየጠቅና ማስተካከል ፣ራስን ማወቅ እንዲሁም ከተለመደው የአስተሳሰብ ገደብ በመውጣት እይታን ማስፋት፣መማር፣ውሎን ማስተካካል፣ማንበብ፣ራስን ማሻሻል፣ገንቢ ባህሪያትን ማደበር በሚል ዝርዝር፣ሰፊና ጥልቅ ሃሳቦችን በማንሳት አብራርተዋል፡፡
አቶ ኢዘዲን ሙስባህ የባለስልጣኑ ዋና ስራ አስኪያጅ በመርሃ-ግብሩ ላይ እንደገለጹት ባህሪ የሰውን ልጅ ትልቅ ቦታ ለመድረስ ወሳኝ መሆኑን ገልጸው መልካም የሆነን ባህሪ ማዳበር ስኬታማ ለመሆን ይጠቅማል ብለዋል፡፡ ስኬት ላይ ላለመድረስ ራስን መጠየቅ አስፈላጊ መሆኑን ጠቅሰው ተስፋ መቁረጥም ስኬት ላይ ላለመድረስ አንዱ ምክንያት መሆኑን አንስተው ተስፋ ከመቁረጥ መራቅ አስፈላጊ እንደሆነ ገልጸዋል፡፡
ለአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የትምህርትና ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን አመራሮችና ሰራተኞች መልካም የሥራ ሳምንት ይሁንላችሁ፡፡
#ፌስቡክ;https://www.facebook.com/AA-Educational-Training-Quality-Occ-Competency-Assurance-Authority-100864428091362/?__tn__=-UC*F
#ድረ_ገጽ; educoc.gov.et
#ቴሌግራም https://t.me/AAEQOCAA
#ቲክቶክ https://www.tiktok.com/@educationtraning2?_t=ZM-8u2f6smztvr&_r=1
#ነጻ_የጥቆማ_የስልክ_መስመር_9302
#ዩቲዩብ https://www.youtube.com/channel/UCzbsHLZjub9c7uVPjc
+1
የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) መልዕክት፡-
የኅብር ቀን
ብዝኃነት የኢትዮጵያ ጌጥ
ኢትዮጵያ በብዙ ጸጋዎች የተሞላች ሀገር ናት፡፡ እነዚህ ጸጋዎቿ የተለያዩ ሳይሆኑ ልዩ ልዩ ናቸው፡፡ የባህል፣ የቋንቋ፣ የታሪክ፣ የሥልጣኔ፣ የእምነት፣ የጾታ፣ የአመለካከት፣ ወዘተ. ብዝኃነት ያለንን የጸጋ ብዛት የሚያመለክት ነው፡፡ ብዝኃነት የኢትዮጵያ ታሪኳ እና መልኳ ነው፡፡
አቶ አለልኝ አያይዘውም የምዘና ስራ የብዙ ባለድርሻ አካላትን ተሳትፎ የሚጠይቅ እንደሆነ ገልጸው ሁሉም ባለድርሻ አካላት የምዘና ስራው የተቃና እንዲሆንና የታለመለትን አላማ እንዲመታ ብቁና ተወዳዳሪ ዜጋን ለማፍራት የበለጸገችና ያደገች ሀገር ለመፍጠር የየራሳችንን ሃላፊነት መወጣት ይገባናል ብለዋል፡፡
#ፌስቡክ;https://www.facebook.com/AA-Educational-Training-Quality-Occ-Competency-Assurance-Authority-100864428091362/?__tn__=-UC*F
#ድረ_ገጽ; educoc.gov.et
#ቴሌግራም https://t.me/AAEQOCAA
#ቲክቶክ https://www.tiktok.com/@educationtraning2?_t=ZM-8u2f6smztvr&_r=1
#ነጻ_የጥቆማ_የስልክ_መስመር_9302
#ዩቲዩብ https://www.youtube.com/channel/UCzbsHLZjub9
