en
Feedback
የትምህርትና ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን

የትምህርትና ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን

Open in Telegram
5 357
Subscribers
No data24 hours
-97 days
+730 days
Posts Archive
“ለኢትዮጵያ የብሩህ ተስፋ ቀንዲል ለሆነው የሕዳሴ ግድብ በድል መጠናቀቅ እንኳን አደረሳችሁ” ከንቲባ አዳነች አቤቤ ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ግንባታ ተጠናቅቆ መመረቁን አስመልክቶ “ኢትዮጵያ ችላለች!” በሚል መሪ በአዲስ አበባ ሕዝባዊ የድጋፍ ሰልፍ ተካሂዷል። በድጋፍ ሰልፉ ላይ ንግግር ያደረጉት ከንቲባ አዳነች አቤቤ፣ “ለኢትዮጵያ የብሩህ ተስፋ ቀንዲል፣ የታሪካችን እውነተኛ እጥፋት፣ የማንሰራራት ድንቅ መሠረት ለሆነው ለታላቁ ሕዳሴ ግድብ መጠናቀቅ ታሪካዊ እና ሕዝባዊ ድል እንኳን አደረሰን፣ እንኳን አደረሳችሁ! ሲሉ የደስታ መልዕክት አስተላልፈዋል። የአዲስ አበባ ሕዝብ ከሕፃን እስከ አዋቂ፣ ከደሃ እስከ ሀብታም፣ ከተማሪ እስከ ምሁር፣ ከሕዝብ እስከ መሪ በአንድ ድምፅ፣ በአንድ አቋም፣ በኅብረብሔራዊ አንድነት በደማቁ ለተጻፈው እና ለማይደበዝዘው ደማቅ አሻራ መቀነታችንን እና ቀበቶአችንን አጥብቀን ከእለት ጉርሳችን በላባችን፣ በደማችን ጭምር የገነባነው የወል ስኬታችን፣ የድል ብስራታችን ለሆነው ሕዳሴ ግድብ መጠናቀቅ በአብሮነት ደስታችንን ለመግለጽ እና ለጀግናው እና ለማይበገረው ሕዝባችን ምስጋና ለማቅረብ በመስቀል አደባባይ ተገናኝተናል ብለዋል። #ኢትዮጵያ ችላለች #GERD #Ethiopia #addisababa

“ገነባነው! ጨረስነው! አስመረቅነው”!! ከንቲባ አዳነች አቤቤ #Ethiopia #GERD
+5
“ገነባነው! ጨረስነው! አስመረቅነው”!! ከንቲባ አዳነች አቤቤ #Ethiopia #GERD

ከንቲባ አዳነች አቤቤ የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ እውን እንዲሆን ከ6 ቢሊዮን ብር በላይ በማዋጣት ለተሳተፉ ሁሉ ምስጋና አቀረቡ AMN-መስከረም 04/2018 ዓ.ም የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አዳነች አቤቤ “ታላቁ የህዳሴ ግድብ ተጠናቆ ደስታችንን ለመግለጽ በመገናኘታችን እንኳን ደስ አላችሁ” ብለዋል። ከንቲባዋ ይህን ያሉት “በህብረት ችለናል” በሚል መሪ ሀሳብ በመስቀል አደባባይ እየተከናወነ በሚገኝው ህዝባዊ ድጋፍ ላይ ነው። በዚሁ ወቅት ግድቡ ተጀምሮ እስከተጠናቀቀበት ጊዜ ድረስ በተለያየ ዘርፎች ድጋፍ ላደረጉ ኢትዮጵያውን እና ትውልደ ኢትዮጵያውያን ምስጋናቸውን አቅርበዋል። ግድቡ ከመምህር ፣ እስከ ሾፌር ፣ ከእንጨት ለቃሚ እስከ ሊስትሮ ሁሉም ከጉያው ቀንሶ እውን ያደረገው የሁሉም ኢትዮጵያውያን ኩራት ምንጭ የሆነ ሀብት ነው ብለዋል። የለውጡ መንግስት ወደ ስልጣን በመጣበት ጊዜ ግድቡ በውስብስብ ችግሮች ተተብትቦ እንደነበር ያስታወሱት ከንቲባዋ፤ ግድቡ ዛሬ ላይ ለበቃበት ስኬት ይደርስ ዘንድ ግድቡን ከገባበት ቅርቃር ለማውጣት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የሰጡት አመራር ምስጋና እንደሚገባው አንስተዋል። በዛ ፈታኝ በሆነው ሀሩር ወጣትነታቸውን ለኢትዮጵያ ብልጽግና ሰውተው በግድቡ ግንባታ ለተሳተፉ ፣ የግድቡን ደህንነት በመጠበቅ የተሳተፉ የጸጥታ አካላት፣ በአለም አቀፍ መድረክ ስለ ግድቡ ሲከራከሩ የነበሩ አምባሳደሮች ፣ ዲፕሎማቶች እና የዲያስፖራ አባላት በከንቲባዋ ንግግር ተመስግነዋል። ለግድቡ እውን መሆን ሳይሰስቱ ያላቸውን በሙሉ ለሰጡ እንዲሁም ከ6 ቢሊዮን ብር በላይ ለታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ላዋጣው የአዲስ አበባ ነዋሪ ከንቲባዋ ምስጋናቸውን አቅርበው ፤ አለም አቀፍ ጫና በበረታበት ጊዜ ለሀገራቸው ድምጽ ለሆኑ የማህበረሰብ አንቂዎች እና የሚዲያ ሰዎችንም አመስግነዋል። ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ በላባችን በደማችን የገነባነው የወል ስኬታችን ነው ያሉት ከንቲባ አዳነች፤ “በራሳችን ወጪ በላብ እና የደም ዋጋ ጨምር ገነባነው ፣ ጨረስነው ፣ አስመረቅነው” ሲሉ ደስታቸውን ገልጸዋል። ከዚህ ባለፈ የግድቡ መጠናቀቅ በቀጣይ ለምንጀምራቸው ፕሮጀክቶች የአንድነት ሀይል ውጤት ምን ያህል ሀያል እንደሆነ አመላክቷል ብለዋል።

ከቁጭት - ወደ ችሎ ማሳየት AMN-መስከረም 04/2018 ዓ.ም የኢትዮጵያን የዘመናት የቁጭት ምንጭ የሆነው የታላቁ ኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ እና የአባይ ወንዝ ተጠቃሚነት ጥያቄ ምላሽ አግኝቷል። ኢትዮጵያ ህዝቧን አስተባብራ ድር ቢያብር አንበሳ ያስር ብሂልን እውን ያደረገችበት፣ ለመጪው ጊዜ ፕሮጀክቶች ጉልበት እና ተስፋ ስንቅ የሰነቀችበት የግድቡ መጠናቀቅ፤ ከቁጭት ወደ ችሎ ማሳየት ተሸጋግሯል። በዛሬው ዕለትም ከአዲስ አበባ ከተማ ከተለያዩ አካባቢዎች የተውጣጡ ነዋሪዎች በመስቀል አደባባይ ተገኝተው በግድቡ መጠናቀቅ የተሰማቸውን ደስታ እየገለጹ ይገኛሉ። በህብረት ችለኛል በሚል መሪ ሀሳብ እየተከናወነ የሚገኝው ህዝባዊ ድጋፍ ግድባችን የአንድነታችና የአብሮነታችን አርማ ነው ፣ ከግድብ ወደ ወደብ ፣ በተባበረ ክንድ የኢትዮጵያ ጉዞ እውን ይሆናል ፣ የጉባ ራዕያችን የቀጣይ ድላችን አይቀሬ ነው እና ሌሎችም መልዕክቶች እየተላለፉበት ነው። የተለያዩ የአፍሪካ ሀገራት መሪዎች በተገኙበት ባሳለፍነው ጷግሜን 4 በተካሄደው የግድቡ ምረቃ ስነስርአት ላይ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) በመጪዎቹ አመታት እንደሚጀመሩ ያበሰሯቸው ፕሮጀክቶች የኢትዮጵያን የእድገት ግስጋሴ ይበልጥ ለማፋጠን እንደሚረዱ ተነግሯል። ከ30 ቢሊየን ዶላር በላይ ወጪ የሚደረግባቸው ፕሮጀክቶች በሀይል አቅርቦት ፣ በመኖሪያ ቤት ፣ የማዳበሪያ ፋብሪካ እና በአፍሪካ ግዙፉ አየር ማረፊያ የመገንባት እቅድ እና ሌሎችም ለበርካታ አመታት የምጣኔ ሀብቱ ማነቆ ሆነው ለሰነበቱ ተግዳሮቶች ምላሽ የሚሰጡ ናቸውም ተብሏል። የአዲስ አበባ ከንቲባ አዳነች አቤቤ ግድቡ በተመረቀበት ወቅት ባስተላለፉት መልዕክት የህዳሴ ግድብን ስላጠናቀቅን እንቆማለን ማለት አይደለም ማለታቸው ይታወሳል። ከንቲባዋ በመጪዎቹ ጊዜዎች ወደብን ጨምሮ ኢኮኖሚው የሚፈልጋቸውን ጉዳዮች እያሳካን እንቀጥላለን ሲሉም ተደምጠዋል። በአሁኑ ወቅት ከመዲናዋ የተለያየ ክፍል ከሌሊት ጀምሮ ወደ መስቀል አደባባይ የተመመው ነዋሪ በኢትዮጵያ ሰንደቅ አላማ ፣ በተለያዩ የባህል አልባሳት እና መፈክሮች ደምቆ ደስታውን እየገለጸ ይገኛል።

ኢትዮዽያ ችላለች ! ኢትዮዽያ የድል አድራጊዎች ፣ የአሸናፊዎች ምድር ! መላዉ አዲስ አበባ ለዳግማዊዉ የአድዋ ታላቅ ድል ክብር ከሌሊት አንስቶ ወደ መስቀል አደባባይ በከፍተኛ የድል አድራጊነት ስሜት በነቂስ እየተመመ ይገኛል። #ሕዳሴ #GERD #Ethiopia #AddisAbaba. ከንቲባ አዳነች አቤቤ

ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ግንባታ ተጠናቅቆ መመረቁን አስመልክቶ “ኢትዮጵያ ችላለች!” በሚል መሪ ቃል ፕሬዚዳንት ታየ አጽቀሥላሴ፣ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ፣ ከንቲባ አዳነች አቤ
+5
ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ግንባታ ተጠናቅቆ መመረቁን አስመልክቶ “ኢትዮጵያ ችላለች!” በሚል መሪ ቃል ፕሬዚዳንት ታየ አጽቀሥላሴ፣ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ፣ ከንቲባ አዳነች አቤቤ እና ሌሎች ከፍተኛ የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች በተገኙበት ታላቅ ሕዝባዊ የድጋፍ ሰልፍ በአዲስ አበባ በመስቀል አደባባይ እየተካሄደ ይገኛል። #GERD #Ethiopia

ግድባችን በራሳችን አቅም የገነባነው የአንድነታችንና የአብሮነታችን ምሰሶ ነው:: በመዲናዋ በመካሄድ ላይ የሚገኘው የህዳሴው ግድብ መጠናቀቅን ምክንያት በማድረግ የህዝባዊ ድጋፍ ሰልፍ:: #ኢትዮጵያ ችላለች!!!

ግድባችን በራሳችን አቅም የገነባነው የአንድነታችንና የአብሮነታችን ምሰሶ ነው:: በመዲናዋ በመካሄድ ላይ የሚገኘው የህዳሴው ግድብ መጠናቀቅን ምክንያት በማድረግ የህዝባዊ ድጋፍ ሰልፍ:: #ኢትዮጵያ ችላለች!!!

"ኢትዮጵያ ችላለች"በሚል መሪ ቃል የህዳሴ ግድብ መጠናቀቁን ምክንያት በማድረግ የአዲስ አበባ ከተማ ህዝብ ድጋፉንና ደስታውን ለመግለፅ በመስቀል አደባባይ የድጋፍ ሰልፍ በማካሄድ ላይ ነው:: #ኢትዮጵያ ችላለች!!!

"ኢትዮጵያ ትችላለች" በሚል መሪ ቃል የታላቁን ህዳሴ ግድብ የ14 ዓመት ጉዞ የሚያስቃኝ የፎቶ እና የስዕል አውደ ርዕይ በአድዋ ድል መታሰቢያ ተከፈተ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የታላቁን የህዳሴ ግድብ መጠናቀቅ አስመልክቶ በከተማ ደረጃ በማዘጋጀት የፎቶ እና የስዕል አውደ ርዕይ በአድዋ ድል መታሰቢያ ለእይታ ክፍት አድረጓል። በዚህ በተዘጋጀዉ የፎቶ እና የስዕል አውደ ርዕይ መክፈቻ ስነስርዓት ላይ አዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ እና የኢንዱስትሪ ልማት ቢሮ ኃላፊ አቶ ጃንጥራር ዓባይ፣የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ብልፅግና ቅርንጫፍ ፅ/ቤት ኃላፊ አቶ ሞገስ ባልቻ ፣ናየታላቁ የኢትዮጽያ ህዳሴ ግድብ ህዝባዊ ማስተባበሪያ ፅ/ቤት ዋና ስራ አስፈፃሚ አረጋዊ በርሔ(ዶ/ር ፣ እና ሌሎች ከፍተኛ የፌደራልና የከተማ ክፍተኛ የመንግስት አመራሮች ተገኝተዋል።