የትምህርትና ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን
Open in Telegram
5 357
Subscribers
No data24 hours
-97 days
+730 days
Posts Archive
+6
የአፋር ክልል የሙያ ብቃት ምዘና ኤጀንሲ የልምድ ልውውጥ አደረገ፡፡
(መስከረም 15 ቀን 2018 ዓ.ም)በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የትምህርትና ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን የሙያ ብቃት ምዘና ዘርፍ ከአፋር ክልል የሙያ ብቃት ምዘና ኤጀንሲ ከመጡ የስራ ሃላፊዎች ጋር የልምድ ልውውጥ አደረጉ፡፡
ለልምድ ልውውጡ የመጡት አመራሮች የባለስልጣኑ በተለይም የሙያ ብቃት ምዘና ዘርፍ አወቃቀሩን፣አደረጃጀቱን፣የአሰራር ሂደቱን እንዲሁም በስራ ክፍሉ ማየትና በግልጽ እንዲብራራላቸው የፈለጉትን ዝርዝር ተግባራት የጠየቁ ሲሆን አቶ አለልኝ ወንዴ የባለስልጣኑ ምክትል ስራ አስኪያጅና የምዘና ዘርፍ ሃላፊ የባለስልጠኑ የምዘና ዘርፍ የሚያከናውነውን ተግባር፣ ከባለድርሻ አካላት ጋር በቅንጅት የሚሰራውን ተግባር፣ማሕበራዊ ሃላፊነቱን ከመወጣት አንጻር፣የተለያዩ መመሪያዎችን አስመልክቶ በምን መልኩ አገልግሎት ላይ እየዋለ እንደሆነ አብራርተዋል፡፡
ወ/ሮ ታጋይቱ አባቡ የባለስልጣኑ ምክትል ስራ አስኪያጅና የጥራት ዘርፍ ሃላፊ በበኩላቸው በጥራት ዘርፍ የሚከናወኑ ተግባራትን በተለይ ለቴክኒክና ሙያ ተቋማት እውቅና ፍቃድ አሰጣጥን በዝርዝር ለልምድ ልውውጡ አባላት አስረድተዋል፡፡
አቶ አለልኝ ወንዴ የባለስልጣኑ ምክትል ስራ አስኪያጅ በበኩላቸው ፈተናው የተዘጋጀው ከባለድርሻ አካላት ጋር በጋራ መሆኑንና አላማውም ባለሙያው በሚችለው መስክ ተፈትኖ እንዲመደብ ለማስቻል በመሆኑ የስነልቦና ዝግጅት ማድረግ ስለሚያስችል የቀረበው ሰነድ ራሳችንን እንድናዘጋጅና ውጤታማ ለመሆን የሚያግዝ መሆኑን ገልጸው ከስራ ባህሪያችን አንጻር ዝግጅት እናድርግ የሚል መልዕክት አስተላልፈዋል፡፡
#ፌስቡክ;https://www.facebook.com/AA-Educational-Training-Quality-Occ-Competency-Assurance-Authority-100864428091362/?__tn__=-UC*F
#ድረ_ገጽ; educoc.gov.et
#ቴሌግራም https://t.me/AAEQOCAA
#ቲክቶክ https://www.tiktok.com/@educationtraning2?_t=ZM-8u2f6smztvr&_r=1
#ነጻ_የጥቆማ_የስልክ_መስመር_9302
#ዩቲዩብ https://www.youtube.com/channel/UCzbsHLZjub9c7uVPjc
+4
የባለስልጣኑ የወርቃማ ሰኞ ማለዳ የማነቃቂያና የእውቀት ሽግግር መርሃ-ግብር ተካሄደ፡፡
(መስከረም 12 ቀን 2018 ዓ.ም)በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የትምህርትና ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን የወርቃማ ሰኞ የማነቃቂያና የእውቀት ሽግግር መርሃ-ግብር "ውጤታማ የፈተና ዝግጅት" በሚል ርዕስ ተካሂዷል፡፡
አቶ መስፍን ኃይሉ የአጠቃላይ ትምህርት ጥራት ማረጋገጥ ባለሙያ ውጤታማ የፈተና ዝግጅት በሚል ርዕስ ስለ ውጤታማ የፈተና ዝግጅት ሰነድ በማቅረብ አብራተዋል፡፡ በዚህም ለፈተና በምንዘጋጅበት ጊዜ ውጤታማ ለመሆን በራስ መተማመን፣ፈተና ላይ ለመቀመጥ ምን ነገር ያስፈልገናል፣የሰዓት አጠቃቀምን መለየት፣በምን ዓይነት መንገድ ብናጠና ውጤታማ እንሆናለን፣የምንፈተነው ፈተና ምን ሊሆን ይችላል የሚሉ ሃቦችን በማንሳት ዝርዝር መረጃዎችን አስቀምጠዋል፡፡
ወ/ሮ ታጋይቱ አባቡ የባለስልጣኑ ምክትል ስራ አስኪያጅ በመርሃ-ግብሩ ላይ እንደገለጹት ባለስልጣኑ እየሠራ ባለው ሪፎርም ወቅት ይህ ሃሳብ መነሳቱ ሰራተኛው ተረጋግቶ የሚሠጠውን ፈተና በአግባቡ መስራት እንዲያስችለው የሚያግዝ መሆኑን ጠቅሰው ሁሉም ሰራተኛ በልበ ሙሉነት የሚሠጠውን ፈተና በማስተዋል እንዲሰራ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል፡፡
"በእመርታና ማንሰራራት የታጀበ ህዝባዊ በዓላትን በጋራ እናክብር"
(መስከረም 9 ቀን 2018 ዓ.ም)በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የትምህርትና ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን ሰራተኞች አመራሮች የአደባባይ በዓል የሆኑትን የመስቀልና የኢሬቻ በዓል አከባበር አስመልክቶ ውይይት አደረጉ፡፡
አቶ አለልኝ ወንዴ የትምህርትና ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን ምክትል ስራ አስኪያጅ የመወያያ ሰነድ ያቀረቡ ሲሆን የሰነዱን አላማ ኢትዩጵያ በአያሌ ቅርሶችና እሴቶች የበለፀገች ሀገር መሆኗን ሀገራዊ እና ዓለም አቀፋዊ ግንዛቤ ማሳደግ፣የመስቀልና የኢሬቻ በዓላትን ባህላቸዉንና እሴታቸውን ጠብቀው እንዲከበሩ በማድረግ እሴቶቹን ለሀገር ግንባታ ማዋል፣በዓላቱ ለከተማችንና ለሀገራችን የኢኮኖሚና ቱሪዝም ዕድገት ምንጭ ማድረግ መሆኑን ሰነዱ የሚያመላክት ሲሆን የዘንድሮውን መስቀልና ኢሬቻ በዓላትን ስናከብር እንደ ሀገር እና አዲስ አበባም የትላልቅ ድሎች ባለቤቶች በሆንበት ወቅት ላይ በመሆኑ ልዩ ያደርገዋል ብልዋል፡፡
ዶክተር ደሳለኝ ጴጥሮስ የባለስልጣኑ አማካሪ በመርሃ-ግብሩ ላይ እንደገለጹት ሁለቱ በዓላት የኢትዩጵያውያን የአደባባይ በዓላት እንደመሆናቸው በደመቀና ሰላማዊ በሆነ መልኩ ማክበር እንድንችል ሁላችንም በኢትዮጵያዊነት ስሜት በዓላቱ ተጀምረው እስኪጠናቀቁ ያላቸውን ሀይማኖታዊ እና ባህላዊ እሴት ጠብቀው በሰላም ተጀምረው በሰላም እንዲጠናቀቁ ማድረግ ይጠበቅብናል ብለዋል፡፡
በመርሃግብሩ ላይ የተገኙት ሰራተኞች ሃሳባቸውን ሲገልጹ እኛ ኢትዮጵያውያን እንግዳ ተቀባይ ባህላችንን ይበልጥ ማጠናከር፣ በዓላቱ ባማረ እና በደመቀ መልኩ እንዲከበረ ማድረግ፣ ወንድማማችነትን እህትማማችነትን እና ኢትዮጵያዊ አብሮነት ማጠናከር፣ ለሠላም ልዩ ትኩረት ስጥቶ በተባበረ ክንድ መስራት፣በዓላቱ እሴቶቻቸውን ብቻ ተከትለው እንዲከበሩ ማድረግ ከኛ ከኢትዮጵያውያን የሚጠበቅ ተግባር ነው ብለዋል፡፡
#ፌስቡክ;https://www.facebook.com/AA-Educational-Training-Quality-Occ-Competency-Assurance-Authority-100864428091362/?__tn__=-UC*F
#ድረ_ገጽ; educoc.gov.et
#ቴሌግራም https://t.me/AAEQOCAA
#ቲክቶክ https://www.tiktok.com/@educationtraning2?_t=ZM-8u2f6smztvr&_r=1
#ነጻ_የጥቆማ_የስልክ_መስመር_9302
#ዩቲዩብ https://www.youtube.com/channel/UCzbsHLZjub9c7uVPjc
ባለስልጣኑ የ15 አቅመ ደካማ ወገኖችን ቤት መልሶ በመገንባት ርክክብ አደረገ፡፡
(መስከረም 8 ቀን 2018 ዓ.ም)በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የትምህርትና ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን በከተማው ውስጥ ያሉ የግል የትምህርትና ስልጠና ተቋማትን በማስተባበር በአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ ወረዳ 3 ለሚገኙ አቅመ ደካማ ወገኖች 15 ቤቶችን በአዲስ መልክ ገንብቶ በማጠናቀቅ ርክክብ አከናወነ፡፡
አቶ ታረቀኝ ወርቅነህ የአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ ዋና ስራ አስፈጻሚ በመርሃ-ግብሩ ላይ እንደተናገሩት አቅም ላነሰው፣ ለሌለው ማድረግ ደስታ ፣በረከት የምናተርፍበት እና ደስታ የሚፈጥር ስራ ነው ፡፡ ያገዛችሁ ያደረጋችሁ በሙሉ በዚህ በጎ ስራ ልትደስቱ በመልካም ስራችሁ ልትቀጥሉ ይገባል ብለዋል ፡፡
ዶክተር ዘላለም ሙላቱ የአዲስ አበባ ከተማ ትምህርት ቢሮ ሃላፊ እንደገለጹት ያማረች የተመቻቸች ሀገር በማስረከብ ሂደት ውስጥ ተቋማት ካላቸው ከጉድለታቸው ስላደረጉት ነገር ሊመሰገኑ ያስፈልጋል፤ በጋራ በተደመረ ውጤት ሀገርን በማሳደግ ሂደት ውስጥ ማሳያ መሆኑን ገልጸው ትምህርት ሀገር የሚገነባበት ነው ትምህርት ቤቶችም የዚህ አውድ ማሳያ ናቸው ለሀገር እድገት ለትውልድ ግንባት የጋራ ስራና ርብርብ የሚጠይቅ ነው ይህ ውጤት የተደመረ የማህበረሰብ ውጤት ነው ስለዚህ ይህ ሰራ ተጠናክሮ ሊቀጥል ይገባል ብለዋል፡፡
አቶ ኢዘዲን ሙስባህ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የትምህርትና ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን ዋና ስራ አስኪያጅ በመርሃ-ግብሩ ላይ እንደተናገሩት የግል የትምህርትና ስልጠና ተቋማትን በማስተባበር ከ18 ሚሊየን ብር በላይ በሆነ ወጪ የተከናወነ መሆኑን ገልጸው የትምህርትና ስልጠና ተቋማት ባለቤቶች ሚናቸውን ተወጥተዋል፤በዚህም ሊመሰገኑ ይገባል ያሉ ሲሆን መንግስት ሰው ተኮር ሆኑ ስራዎችን እንደሚሰራ ገልጸው ወደፊትም እንዲህ ያለውን የልማት ስራ አጠናክረን እንቀጥላለን ያሉ ሲሆን በጋራ ከተባበርን ችግርን ማለፍ እንችላለን ብለዋል፡፡
በዕለቱ መርሃ-ግብሩ በአባቶችና በአገር ሽማግሌዎች ምርቃት ተጀምሯል፡፡ በመርሃግብሩ ላይ የክፍለ ከተማው አመራሮች፣የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የህብረተሰብ ተሳትፎ በጎ ፈቃድ ም/ኮምሽነር የወረዳው አመራሮች፣የትምህርትና የማሰልጠኛ ተቋማት፣የአካባቢው ማህበረሰብ የተገኙ ሲሆን መርሃ ግብሩ በደማቅ ሁኔታ ተከናውኗል፡፡
የቤት ግንባታው የተሰራላቸው ወገኖችም በተደረገላቸው መልካም ነገር አመስግነው ፤ሁላችሁንም እናመሰግናለን የሚል መልዕክት አስተላልፈዋል፡፡
በመጨረሻም በዚህ ተግባር ላይ ለተሳተፉና ስራውን ላስተባበሩ አካላት የምስጋና የምስክር ወረቀት ተሰጥቷል፡፡
#ፌስቡክ;https://www.facebook.com/AA-Educational-Training-Quality-Occ-Competency-Assurance-Authority-100864428091362/?__tn__=-UC*F
#ድረ_ገጽ; educoc.gov.et
#ቴሌግራም https://t.me/AAEQOCAA
#ቲክቶክ https://www.tiktok.com/@educationtraning2?_t=ZM-8u2f6smztvr&_r=1
#ነጻ_የጥቆማ_የስልክ_መስመር_9302
#ዩቲዩብ https://www.youtube.com/channel/UCzbsHLZjub9c7uVPjc
ባለስልጣኑ የ15 አቅመ ደካማ ወገኖችን ቤት መልሶ በመገንባት ርክክብ አደረገ፡፡
(መስከረም 8 ቀን 2018 ዓ.ም)በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የትምህርትና ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን በከተማው ውስጥ ያሉ የግል የትምህርትና ስልጠና ተቋማትን በማስተባበር በአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ ወረዳ 3 ለሚገኙ አቅመ ደካማ ወገኖች 15 ቤቶችን በአዲስ መልክ ገንብቶ በማጠናቀቅ ርክክብ አከናወነ፡፡
አቶ ታረቀኝ ወርቅነህ የአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ ዋና ስራ አስፈጻሚ በመርሃ-ግብሩ ላይ እንደተናገሩት አቅም ላነሰው፣ ለሌለው ማድረግ ደስታ ፣በረከት የምናተርፍበት እና ደስታ የሚፈጥር ስራ ነው ፡፡ ያገዛችሁ ያደረጋችሁ በሙሉ በዚህ በጎ ስራ ልትደስቱ በመልካም ስራችሁ ልትቀጥሉ ይገባል ብለዋል ፡፡
ዶክተር ዘላለም ሙላቱ የአዲስ አበባ ከተማ ትምህርት ቢሮ ሃላፊ እንደገለጹት ያማረች የተመቻቸች ሀገር በማስረከብ ሂደት ውስጥ ተቋማት ካላቸው ከጉድለታቸው ስላደረጉት ነገር ሊመሰገኑ ያስፈልጋል፤ በጋራ በተደመረ ውጤት ሀገርን በማሳደግ ሂደት ውስጥ ማሳያ መሆኑን ገልጸው ትምህርት ሀገር የሚገነባበት ነው ትምህርት ቤቶችም የዚህ አውድ ማሳያ ናቸው ለሀገር እድገት ለትውልድ ግንባት የጋራ ስራና ርብርብ የሚጠይቅ ነው ይህ ውጤት የተደመረ የማህበረሰብ ውጤት ነው ስለዚህ ይህ ሰራ ተጠናክሮ ሊቀጥል ይገባል ብለዋል፡፡
+4
ባለስልጣኑ ድጋፍና ክትትል ተደረገለት፡፡
(መስከረም 6 ቀን 2018 ዓ.ም)በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የትምህርትና ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን ከፐብሊክ ሰርቪስ ቢሮ የመጡ የክትትልና ድጋፍ ቡድን የዝግጅት ምዕራፍ ስራዎች ላይ ድጋፍና ክትትል አድርገዋል፡፡
የድጋፍና ክትትል ቡድኑ ባለስልጣኑ በ2018 የዝግጅት ምዕራፍ ስራዎች ላይ ትኩረት በማድረግ ድጋፍና ክትትሉን አድርጓል፡፡ከዚህም ሌላ የቁልፍ ተግባራት አፈጻጻም በምን ደረጃ ላይ እንዳሉ ምልከታ አድርገዋል፡፡በድጋፍና ክትትሉ ወቅት የድጋፍና ክትትል ቡድኑ በሰነድ የተደገፉ መረጃዎችን ምልከታ አድርጓል፡፡
የድጋፍና ክትትል ቡድኑ ላነሱት ሃሳብና አስተያየቶች የሚመለከታቸው የስራ ክፍል ሃላፊዎችና ባለሙያዎች ማብራሪያና ምላሽ ሰጥተዋል፡፡
#ፌስቡክ;https://www.facebook.com/AA-Educational-Training-Quality-Occ-Competency-Assurance-Authority-100864428091362/?__tn__=-UC*F
#ድረ_ገጽ; educoc.gov.et
#ቴሌግራም https://t.me/AAEQOCAA
#ቲክቶክ https://www.tiktok.com/@educationtraning2?_t=ZM-8u2f6smztvr&_r=1
#ነጻ_የጥቆማ_የስልክ_መስመር_9302
#ዩቲዩብ https://www.youtube.com/channel/UCzbsHLZjub9c7uVPjc
አቶ አለልኝ ወንዴ የትምህርትና ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን ምክትል ስራ አስኪያጅ እና የምዘና ዘርፍ ሀላፊ በስልጠናው ማጠቃለያ ላይ እንደገለጹት ባለስልጣኑ የምዘና ጣቢያዎችን ከመለየት ድጋፍና ክትትል ከማድረግ አንስቶ በርካታ ስራዎችን መሰራታቸውን ገልጸው RPL ላይ ግንዛቤ በመፍጠር የተሻለ ውጤት ለማስመዝገብ ሁሉም ባለድርሻ አካል የበኩሉን ሚና እንዲወጣ አሳስበዋል፡፡
#ፌስቡክ;https://www.facebook.com/AA-Educational-Training-Quality-Occ-Competency-Assurance-Authority-100864428091362/?__tn__=-UC*F
#ድረ_ገጽ; educoc.gov.et
#ቴሌግራም https://t.me/AAEQOCAA
#ቲክቶክ https://www.tiktok.com/@educationtraning2?_t=ZM-8u2f6smztvr&_r=1
#ነጻ_የጥቆማ_የስልክ_መስመር_9302
#ዩቲዩብ https://www.youtube.com/channel/UCzbsHLZjub9c7uVPjc
+5
ባለስልጣኑ ከ ILO ጋር በጋራ በመሆን በRPL ትግበራ ላይ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ሰጠ፡፡
(መስከረም 6 ቀን 2018 ዓ.ም)የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርትና ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን የቴክኒክና ሙያ ብቃት ምዘና አሰጣጥ ዳይሬክቶሬት ከ ILO ጋር በጋራ በመሆን በኢ-መደበኛ የተገኘን እውቀትና ክህሎት (RPL) ያለውን ብቃት እውቅና መስጠት የሚያስችል ስልጠና ለባለድርሻ አካላት ሰጠ፡፡
የትምህርትና ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን ዋና ስራ አስኪያጅ አቶ ኢዘዲን ሙስባህ እንደገለጹት ባለፉት ጊዜያት በልምድ የተገኘ እወቀት በምዘና በማለፍ እውቅና ሲሰጥ እንደነበር ተናግረው አሁን ላይ በከተማ አስተዳደሩ ትኩረት ተሰጦት ከ ILO/የአለም ሰራተኞች ድርጅት፣ ከስራና ክህሎት ሚኒስቴር ጋር በጋራ በመቀናጀት እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ በሀገራችን ብዙ ሰዎች በልምድ ያገኙትን እውቀት ተመዝነው የሙያ ደረጃቸው ታውቆ ገበያው በሚፈልገው ቦታ ላይ ተጠቃሚ መሆን እንዲችሉ ተመዝነው እውቅና መስጠት አስፈላጊ መሆን ተናግረው ለዚህም RPL በልምድ የተገኝ እውቀት የመመዘን ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል እንዲሁም ለተመዛኞች በራስ የመተማመን እንደሚጨምር እና በኢንድስትሪው ላይ ተወዳዳሪ ለመሆን እንደሚያስችላቸውም ተናግረዋል በቀጣይም ትኩረት ተሰጥቶት እና ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ገልጸዋል፡፡
የስራና ክህሎት ሚኒስቴር የምዘና ዴስክ አስተባባሪ አቶ ምህረት ጥጋቤ ስልጠናውን የሰጡ ሲሆን RPL የአንድ ሰው የእድሜ ልክ ትምህርት፣ስራ የህይወት ተሞክሮ ከመመዘኛዎች አንጻር በመመዘን ያገኘውን ብቃት እውቅና መስጠት መሆኑን ተናግረዋል በምዘና የምንሰጠው ሰርትፊኬት በሀገር ውስጥም በአለም አቀፍ ደረጃ መወዳደር የሚያስችለው እውቅና ያለው ሰርትፍኬት መሆኑንም ተናግረዋል፡፡
የባለስልጣኑ ሰራተኞች በውይይቱ ወቅት ታላቁ የህዳሴ ግድብ መመረቁ እንዳስደሰታቸው ገልጸው እኛ ኢትዮጵያውያን አንድነታችንን በማጠናከር ከችግሮቻችን መውጣት እንደምንችል፣ በመቻቻል ተባብረን ሀገራችንን ወደፊት ማራመድ እንደሚገባ አስተያየት ሰጥተዋል፡፡
#ፌስቡክ;https://www.facebook.com/AA-Educational-Training-Quality-Occ-Competency-Assurance-Authority-100864428091362/?__tn__=-UC*F
#ድረ_ገጽ; educoc.gov.et
#ቴሌግራም https://t.me/AAEQOCAA
#ቲክቶክ https://www.tiktok.com/@educationtraning2?_t=ZM-8u2f6smztvr&_r=1
#ነጻ_የጥቆማ_የስልክ_መስመር_9302
#ዩቲዩብ https://www.youtube.com/channel/UCzbsHLZjub9c7uVPjc
+5
የታላቁ ህዳሴ ግድብ ግንባታ ተጠናቆ መመረቁን አስመልክቶ የፓናል ውይይት ተደረገ፡፡
(መስከረም 5 ቀን 2018 ዓ.ም)በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የትምህርትና ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን የሕዳሴ ግድብ ግንባታ ተጠናቅቆ መመረቁን አስመልክቶ የባለስልጣኑ አመራሮችና ሰራተኞች የፓናል ውይይት አካሄዱ፡፡
አቶ አዘዲን ሙስባህ የባለስልጣኑ ዋና ስራ አስኪያጅ አጠቃላይ በግድቡ ዙሪያ፣ ሰለህዝባዊ ተሳትፎ፣ሰለ ሀገራዊ መነቃቃት፣ቀጠናዊ ትስሰር፣የይቻላል አስተሳሰብ እንዲሁም የህዳሴው ግድብ ዘርፈ ብዙ አንድምታዎች እና ሌሎች መሰል ዝርዝር ጉዳዮች በሰነዳቸው ላይ ያካተቱ ሲሆን ህዳሴ ከባዱን ነገር አልፈን አይችሉም የተባልነውን ሰብረን መቻልን አሳይተናል የውሀ ጥማችንን ቀልብሰንና እውን አድርገን አይችሉም የተባለውን ችለን ዛሬ ደርሰናል ለቀጣዩ ተጨማሪ ድል አብረን በጋራ የማይቻለውን መንፈስ ድል እናድርግ በህብረት ችለናል ብለዋል፡፡
ወ/ሮ ታጋይቱ አባቡ የባለስልጣኑ ምክትል ስራ አስኪያጅና የጥራት ዘርፍ ሀላፊ ህዳሴ የኢትዮጵያውያን የዘመናት ቁጭት፣ የመቻላችንን ልክ ያሳየንበት የመቻላችን ማሳያ ዳግም አድዋችን ነው የማንሰራራት ምዕራፍ ትልቅ ድልድይና ድል የሉአላዊነት መገለጫ ነው ኢትዮጵያ ወደፊት ዳግም ህዳሴዎችን ትገነባለች ትችላለች በህበረት ችለናል ብለዋል፡፡
አቶ አለልኝ ወንዴ የባለስልጣኑ ምክትል ስራ አስኪያጅና የምዘና ዘርፍ ሀላፊ ህዳሴ ኢትዮጵያ መቻሏን ያረጋገጥንበት ለትውልዱ ታሪክ የፃፍንበት የኢትዮጵያ የመቻል ማሳያ የማንነት የምንነት ማሳያ ፍሬ ያፈራንበት ቀን የማንሰራራት ዘመን ማሳያ ነው ከዚህም በላይ ታላቅ ድል መስራት የምንችል መሆን ማሳያችን ነው በህብረት ችለናል ብለዋል፡፡
በመርሃ ግብሩ በተነሳው ርዕሰ ጉዳይ ላይ ሃሳብና አስተያየት ተሰጥቶበት ውይይት ተገርጎበታል፡፡
#ፌስቡክ;https://www.facebook.com/AA-Educational-Training-Quality-Occ-Competency-Assurance-Authority-100864428091362/?__tn__=-UC*F
#ድረ_ገጽ; educoc.gov.et
#ቴሌግራም https://t.me/AAEQOCAA
#ቲክቶክ https://www.tiktok.com/@educationtraning2?_t=ZM-8u2f6smztvr&_r=1
#ነጻ_የጥቆማ_የስልክ_መስመር_9302
#ዩቲዩብ https://www.youtube.com/channel/UCzbsHLZjub9c7uVPjc
+5
የባለስልጣኑ የወርቃማ ሰኞ ማለዳ የማነቃቂያና የእውቀት ሽግግር መርሃ-ግብር ተካሄደ፡፡
(መስከረም 5 ቀን 2018 ዓ.ም)በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የትምህርትና ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን የወርቃማ ሰኞ የማነቃቂያና የእውቀት ሽግግር መርሃ-ግብር "የእውቀት አመራር ስትራቴጂ" በሚል ርዕስ ተካሂዷል፡፡
አቶ ዳባ ጉተታ የባለስልጣኑ የትምህርት ምዘናና ምርምር ጥናት ቡድን ባለሙያ የእውቀት አመራር ስትራቴጂ በሚል ርዕሰ ጉዳይ ላይ ሰነድ ያቀረቡ ሲሆን እውቀት ኢኮኖሚያዊ፣ማህበራዊ፣ባህላዊ፣ፖለቲካዊ እንዲሁም ሌሎች ነገሮችን የማጎልበትና የማሻሻል መነሻም መድረሻም ነው ያሉ ሲሆን የሰነዱን አላማ፣ ግቦች፣የእውቀት ዓመራር መርሆዎች፣የስትራቴጅው አስፈላጊነት፣የእውቀት አመራር ፕሮግራም መሰረታዊ ጉዳዮች፣ለተቋሙ አስፈላጊ የሆነ እውቀት፣የእውቀት አመራር ዑደት እንዲሁም የአተገባበር ስልቶች በሚሉት ይዘቶች ላይ ሰነድ ያቀረቡ ሲሆን እውቀት ሀብት ነው የበለጠ ስንሰጥ የበለጠ እንቀበላለን የሚል መልዕከትም አስተላልፈዋል፡፡
አቶ ኢዘዲን ሙስባህ የባለስልጣኑ ዋና ስራ አስኪያጅ እንደገለጹት እውቀት ትልቅ ሃብት ነው ስለዚህ ነገሮችን በእውቀትና በተገቢው መምራት ያስፈልጋል ያሉ ሲሆን የተለያዩ እውቀቶች በግለሰቦች ላይ ያሉ እንደመሆኑ እውቀትን መሰብሰብ እንዲሁም ጠቃሚ ነው ብለን ያመነውን እውቀት በተለያዩ መንገዶች ለሌሎች ሽግግር ማድረግና ማካፈል ያስፈልጋል ብለዋል፡፡
