en
Feedback
የትምህርትና ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን

የትምህርትና ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን

Open in Telegram
5 357
Subscribers
No data24 hours
-97 days
+730 days
Posts Archive
የሆረ ፊንፊኔ ኢሬቻ ማክበሪያ ቦታ አሁናዊ ገፅታ:- Iddoo Kabaja Ayyaana Irreechaa Hora Finfinnee Yeroo Ammaan Kana.
+4
የሆረ ፊንፊኔ ኢሬቻ ማክበሪያ ቦታ አሁናዊ ገፅታ:- Iddoo Kabaja Ayyaana Irreechaa Hora Finfinnee Yeroo Ammaan Kana.

የባለስልጣኑ የቦሌ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት የእንግዶች አቀባበል በፎቶ
+3
የባለስልጣኑ የቦሌ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት የእንግዶች አቀባበል በፎቶ

እንኳን ለኢሬቻ መልካ በሰላም አደረሳችሁ - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ኢሬቻ የኦሮሞ የምስጋና ስርዓት ነው፡፡ ኦሮሞ የሰው ዘር አፍርቶ የሚባዛው የተዘራው ሞቶ በመነሣት ፍሬ የሚያፈራው በፈጣሪ ድጋፍና እርዳታ ነው ብሎ ያምናል፡፡ ለዚህ ነው ኢሬቻ ሲደርስ ኦሮሞ ልበ ንፁህ የሆነውን ታላቅ ፈጣሪ ላደረገለት ሁሉ በማመስገን ለሚመጣው ጊዜ ደግሞ ምህረትን በመለመን ውዳሴ ያቀርባል፡፡ በጥንት የኦሮሞ ፍልስፍና ውስጥ ኦሮሞ ለውሃ ትልቅ ስፍራ አለው፡፡ ውሃ የንጽህና ምንጭ ፣ የፍጥረትና የህይወት መሠረት ነው ብሎ ያምናል፡፡ ለዚህም ነው ሲፀልይ ፈጣሪ አምላክ ፣ የፍጥረታት አምላክ ፣ የቡርቃ ወላቡ (የላቡ ምንጭ) አምላክ ብሎ ነው የሚፀልየው፡፡ የዘንድሮው ኢሬቻ ኢትዮጵያ የዜጎቿን የኢነርጂ ፍላጎት ለማሟላት የዓባይን ወንዝ በመገደብ ታላቁን የህዳሴ ግድብ ባስመረቀችበት ማግስት የሚከበር መሆኑ ደስታችንን ድርብ ያደርገዋል፡፡ እንኳን ደስ አላችሁ! እንኳን ደስ አለን! ኦሮሞ መልካ የሌለው ህዝብ ራስ እንደሌለው ህዝብ ነው እንደሚል የባህር በር የሌላት አገር ኑሮ የሌላት አገር ናት ብለን ለህዝባችን ብልጽግና ስንል በሰላማዊና ህጋዊ መንገድ የባህር በር ለማግኘት እየሠራን እንገኛለን፡፡ በዚህ ረገድ እያደረግን ያለነው እንቅስቃሴ በዓለም አቀፍ ማህበረሰብ ዘንድ ተቀባይነት በማግኘት ላይ ነው፡፡ ባለፉት ዓመታት አዲስ እሳቤ በሆነው የመደመር ፍልስፍና በመመራት አገር ያላትን ሀብት፣ ልምድና እውቀት ከህዝባችን ጋር በመሆን ቁርጠኛና በሳል አመራር በመስጠት ፣ ፈጣሪም አግዞን በበርካታ ችግሮች ውስጥ ሆነን አስደናቂ ለውጦችን አስመዝግበናል፡፡ በ2018 ዓመተ ምህረትም የኢሬቻ እሴቶች የሆኑትን ሰላም፣ ምህረትና አንድነትን አጥብቀን በመያዝ የአገራችንን ማንሠራራት ለማረጋገጥ በፈተናዎች ሳንበገር ተግተን እንድንሠራ አደራ ለማለት እወዳለሁ፡፡ በድጋሚ የመከናወን ኢሬቻ ይሁልን እላለሁ! መልካው ሰላም ይሁን! ገዳው የጥጋብና የስኬት ይሁን! ኢትዮጵያ በልጆቿ ጥረት ታፍራና ተከብራ፣ በልጽጋ ለዘላለም ትኑር! ፈጣሪ ኢትዮጵያንና ህዝቦቿን ይባርክ! መስከረም 23 ፤ 2018

እንኳን ለ2018 ለኢሬቻ በአል አደረሳችሁ! ኢሬቻ በኦሮሞ ሕዝብ ዘንድ ለፈጣሪ አምላክ ምስጋና የሚቀርብበት፤ ከሰው ጋር ሰላም፣ ፍቅር እና አብሮነት የሚከናወንበት፤ አዲስ ተስፋና ብሩህ ዘመን የሚበሰርበት በዓል ነው። በዩኔስኮ የተመዘገው የኦሮሞ ገዳ ሥርአት አካል የሆነው የኢሬቻ በዓል የሀገራችንን መልከ-ብዝሃነት፤ ጥልቅ ዉበት ለመላዉ ዓለም ካሳዩ እና ካስተዋወቁ በዓላት መካከል አንዱ ነው። የኦሮሞ ህዝብ ከሌሎች ወንድም እህት ህዝቦች ጋር በመሆን ባካሄደዉ መራር ትግል ከተቀዳጃቸው ድሎች መካከል አንዱ የኢሬቻ ሆረ ፊንፊኔን ክብረ በዓል በጥንታዊ ስፍራው ማክበር መቻል ሲሆን ይህም ባለፉት 7 አመታት በከፍተኛ ድምቀት ባህላዊ እሴቱን እና ቱፊቱን ጠብቆ በመዲናችን አዲስ አበባ እየተከበረ ይገኛል። የመዲናችን አጠቃላይ ህዝብም ከወንድም እህቱ የኦሮሞ ህዝብ ጋር በአብሮነት በሚያከብረው በዚህ ታላቅ በዓል ላይ እንደወትሮው ሌሎች የአደባባይ በዓላት ሲከበሩ ለበዓላቱ ድምቀት እና ባማረ መልኩ መጠናቀቅ እንደሚያደርገው ሁሉ አብሮነትን፣ ወንድማማችነትን፣ እህትማማችነትን በሚያጸና መልኩ፤ በከተማው ውስጥ ከሚኖሩ የኦሮሞ ሕዝቦችም ሆነ በእንግድነት ከሚመጡት ወገኖቹ ጋር በመሆን በዓሉ እሴቱን ጠብቆ እንዲከበር ለማድረግ በመንገድ ጽዳት፣ በአደባባይ ማስዋብ እና በሌሎችም በርካታ በጎ ፈቃድ ስራዎች ከምንጊዜውም በላቀ መልኩ ለአገር ገጽታ ግንባታ፣ ለዘላቂ ቱሪዝም መስህብነት፣ ለከፍተኛ የኢኮኖሚ እንቅስቃሴ በሚያመች መልኩ በሕብረ ብሄራዊ አንድነት መንፈስ ቅድመ ዝግጅቱን አጠናቅቋል። መላው የከተማችን ነዋሪዎች በከተማችን የአደባባይ በዓላት ሲከበሩ በዓላቱ ከዋዜማዉ አንስቶ እስኪጠናቀቁ ድረስ በተለያዩ የበጎ ፈቃድ ተግባራት በመሳተፍ እያበረከታችሁ ላለዉ እጅግ የላቀ ሚና እያመሰገንኩ፣ ይህ ተግባር ውብ እና ድንቅ ባህሎቻችን ከእኛ አልፈው ለመላዉ ዓለም የምናበረክታቸው፤ የእኛነታችን መለያ ጌጥ በመሆናቸው እንደወትሮው ሁሉ የዘንድሮውን የኢሬቻ በዓል በድምቀት ባህላዊ እሴቱን ጠብቆ ባማረ መልኩ ለማክበር ያደረግነውን ቅድመ ዝግጅት ከዋዜማው ጀምሮ በጋራ በምናከናውነው ተግባር የከተማችንን የሰላም ተምሳሌትነት፣ የህዝባችንን የሰላም ዘብነት እና እንግዳ ተቀባይነት በማረጋገጥ ይሆናል። በድጋሚ እንኳን ለ 2018 ኢሬቻ ክብረ በዓል አደረሳችሁ! ፈጣሪ ኢትዮጵያንና ሕዝቦቿን ይባርክ Baga Kabaja Ayyaana Irreechaa bara 2018tin Isin gahe, nuun gahe! Ayyanni Irreecha Ummanni Oromoo sirana waaqa umaa umaatiif galata ittin dhiyessudha. Jaarmiyaalee Sirna Gadaa; kan Yuuneeskon Galmaahe, keessaa tokko kan ta'ee Ayyaanni Irreechaa calaqqeewwan bifa danuu, Bareedinaa fi Hawwata Addaa, Adunyaaf agarsiisan keessaa isa tokko yoo ta'u, mallattoo Nageenyaa, Kan jaalalaa, Kan waloominaa, Araara fi sirna Injifannoowwan Uummatni Oromoo, Uummattoota Obbolaa, Sabaaf sablammoota hunda waliin ta'uun Qabsoo hadhaahaa adeemsiseen goonfate keessaa inni tokko Ayyaana Irreecha Hora Finfinnee iddoo ganamaa isaatti deebihee akka kabajamu gochuu isaati. Kanaanis uummatni Oromoo waggootan 7n darban Magaalaa Finfinnee keessatti Karaa Seenaa, Aadaa, fi Duudhaa isaa eeggateen sadarkaa olaanan Sabaaf Sablammoota hunda waliin kabajaa jira. Aadaa Waloon jiraachuu cimaa, fi waldanda'uun kan beekkaman jiraattotni Magaalaa Finfinnees, Ayyaana Obboleeyyan isaa Uummatni Oromoo Kabaju kana akkuma kana dura ayyaanotni uummataa kanneen biroo bifa hawwataa ta'een karaa nagaahan kabajamii akka xumuramaniif hijjechaa ture, Bifa Obbolummaa, fi Waliin jireenya keenya dagaagsu fi itichuu danda'uun uummata Oromoo Magaalaa keenyaa fi keessummootaa fageenya irraa dhufan waliin ta'uun, Ayyaanichi Duudhaa isaa eeggatee akka kabajamuuf, Hojii qulqullinaan, Adabaabayiiwwan adda addaa Bareechun, kenna tajaajilaani, fi hojiilee gocha gaarii adda addaatin kan kanaan dura ture caalatti bifa Hawwata turizimii walitti fufaa fi Sochii diinagdee olaanaf oolun Afuura Obbolummaa Sabdaneessummaan socho'uun kabajuuf qophii isaa xumuree jira. Jabana kana Jiraattotni Magaalaa Keenyaa hundi Ayyaanotni Uummataa kanneen Adabaabayii irratti kabajaman hunda jala bultii irraa kaasee hanga xumuramanitti hojiilee Gocha gaarii adda addaa irratti hirmaachun nageenya fi miidhagina isaaniif shoora olaanaa waan taphattaniif maqaa koo fi maqaa Bulchiinsa Magaalaa Finfinneetin isin galateeffachuun barbaada.Hanga xummura ayyanichattii gocha fakkenyummaa kana cimsuin akka ittifuftan amantaan qaba. Irra deebihuun, Baga Kabaja Ayyaana Irreechaa Bara 2018tin isin gahe! Waaqayyo Itoophiyaa fi Uummattoota ishee haa eebbisu! Kantiibaa Adaanech Abeebee.

ኢሬቻ ለሀገር ማንሰራራት ! (መስከረም 23 ቀን 2018 ዓ.ም) በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የትምህርትና ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን የሰላም፣የወንድማማችነት እና የእህትማማችነት ተምሳሌት የሆነውን የኢሬቻ በዓል ለማክበር ለሚመጡ እንግዶች ስድስት ኪሎ አደባባይ የእንኳን ደህና መጣችሁ ቅድመ ዝግጅት አድርጎ እንግዶችን እየተጠባበቀ ይገኛል፡፡ #ፌስቡክ;https://www.facebook.com/AA-Educational-Training-Quality-Occ-Competency-Assurance-Authority-100864428091362/?__tn__=-UC*F #ድረ_ገጽ; educoc.gov.et #ቴሌግራም https://t.me/AAEQOCAA #ቲክቶክ https://www.tiktok.com/@educationtraning2?_t=ZM-8u2f6smztvr&_r=1 #ነጻ_የጥቆማ_የስልክ_መስመር_9302 #ዩቲዩብ https://www.youtube.com/channel/UCzbsHLZjub9c7uVPjc

⚡️ በአንዳንድ ቴክኒክ ችግኝ ምክንያት ቻናሉ занew ይፈጠራል። በወደፊት ተመሳሳይ ችግኝ እንዳይከሰት እባኮትን ለመጨመር አዲሱን አገናኝ ለማግኘት ብቻ ቦታችንን @link1301bot ይጠቀሙ። የቀድሞው ቻናል አሁን ንቁ አይደለም እና ሊሰረዝ ይችላል።

ከዚህም ሌላ በተለያዩ አካላት የቀረቡ ርዕሶች የተቋሙን ዓላማ ማሳካቱን ለማረጋገጥ፣ተሳታፊዎች የግንዛቤና ልምድ የቀሰሙ መሆኑን ለማረጋገጥ እና በቀጣይ በምን አግባቡ መመራት እዳለበት አቅጣጫ ለማስቀመጥ አላማ አድርጎ መከናወኑን ተናግረዋል፡፡በተጨማሪም የመረጃ አሰባሰብ ሣይንሳዊ ዘዴን የተከተለና አመራሮች እንዲሁም በየስራ ክፍል ያሉ ባለሙያዎችን አሳታፊ ያደረገ በመጠይቅ እና በቡድን ውይይትም ጭምር መረጃ እንደተሰበሰበ ገልጸው በቀጣይም የጥናቱ ግኝት ለማእከል እና ለቅ/ጽ/ቤቶችም እንደሚቀርብ ጨምረው ተናግረዋል፡፡ #ፌስቡክ;https://www.facebook.com/AA-Educational-Training-Quality-Occ-Competency-Assurance-Authority-100864428091362/?__tn__=-UC*F #ድረ_ገጽ; educoc.gov.et #ቴሌግራም https://t.me/AAEQOCAA #ቲክቶክ https://www.tiktok.com/@educationtraning2?_t=ZM-8u2f6smztvr&_r=1 #ነጻ_የጥቆማ_የስልክ_መስመር_9302 #ዩቲዩብ https://www.youtube.com/channel/UCzbsHLZjub9c7uVPjc

የወርቃማ ሰኞ የማነቃቂና የእውቀት ሽግግር ፕሮግራም አተገባበርን ለማሻሻል ዳሰሳዊ ጥናት ተደረገ፡፡ (መስከረም 21 ቀን 2018 ዓ.ም)የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የትምህርትና ስልጠና ጥራት ቁጥጥ
+3
የወርቃማ ሰኞ የማነቃቂና የእውቀት ሽግግር ፕሮግራም አተገባበርን ለማሻሻል ዳሰሳዊ ጥናት ተደረገ፡፡ (መስከረም 21 ቀን 2018 ዓ.ም)የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የትምህርትና ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን የአሰራር ጥራት ቁጥጥር ቡድን የወርቃማ ሰኞ የማነቃቂና የእውቀት ሽግግር ፕሮግራም አተገባበርን ለማሻሻል ዳሰሳዊ ጥናት ተደረገ ፡፡ አቶ አምላኩ ተበጀ የባለስልጣኑ የአሰራር ጥራት ቁጥጥር ቡድን መሪ እንደገለጹት በወርቃማ ሰኞ የማነቃቂያና የእውቀት ሽግግር መርሃ ግብር አተገባበር ላይ ከዚህ ቀደም ከጥናትና ምርምር ቡድን ጋር በጋራ በመሆን ዳሰሳዊ ጥናት መደረጉን ተናግረው የፕሮግራሙን አፈጻጸም ውጤታማነቱን ለማረጋገጥና ያጋጠሙ ችግሮችን በመፈተሽ በቀጣይ ማስተካከያ ስራዎችን ለመተግበር ታስቦ እንደተሰራ ገልጸዋል፡፡

በመሆኑ ያለው ለሌለው በመስጠትና በመደጋገፍ ችግርን በጋራ በመተባበር መቅረፍ እንደሚቻል ያሳየ ተግባር መሆኑን ገልጸው በዚህ ስራ ላይ እጃቸውን ላሳረፉ ሁሉ ምስጋናቸውን አቅርበዋል፡፡ ወ/ት ትዕግስት ጌታሁን በባለስልጣኑ የየካ ቅ/ጽ/ቤት ስራ አስኪያጅ እንደገለጹት በጋራ የሚከናወን ስራ ውጤታማ መሆኑን ገልጸው ሁላችንም በጋራ ከተባበርን ለችግሮች መፍትሄ ማግኘት ቀላል እንደሆነ ተናግረዋል፡፡ከዚህም ሌላ በዚህ መልካም ተግባር ላይ ለተሳተፉ አካላት ምስጋናቸውን አቅርበዋል፡፡ በመጨረሻም ስራው ላይ ለተሳተፉ አካላት ላበረከቱት አስተዋጽኦ እውቅናና ሽልማት ተሰጥቷቸዋል፡፡ በመርሃ ግብሩ ላይ የባለስልጣኑ አመራሮች፣የቅ/ጽ/ቤቱ አመራሮች፣የግል ት/ቤት ባለሃብቶች እንዲሁም የትምህርት ቤቱ ማህበረሰብ ተሳታፊ ሆነዋል፡፡ #ፌስቡክ;https://www.facebook.com/AA-Educational-Training-Quality-Occ-Competency-Assurance-Authority-100864428091362/?__tn__=-UC*F #ድረ_ገጽ; educoc.gov.et #ቴሌግራም https://t.me/AAEQOCAA #ቲክቶክ https://www.tiktok.com/@educationtraning2?_t=ZM-8u2f6smztvr&_r=1 #ነጻ_የጥቆማ_የስልክ_መስመር_9302 #ዩቲዩብ https://www.youtube.com/channel/UCzbsHLZjub9c7uVPjc

ችግሮቻችንን ለማቃለል በጋራ መተባበር መስራት ወሳኝ መሆኑ ተጠቆመ፡፡ (መስከረም 20 ቀን 2018 ዓ.ም) በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የትምህርትና ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን የየካ ቅርንጫፍ
+9
ችግሮቻችንን ለማቃለል በጋራ መተባበር መስራት ወሳኝ መሆኑ ተጠቆመ፡፡ (መስከረም 20 ቀን 2018 ዓ.ም) በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የትምህርትና ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን የየካ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ከዘጠና ቀን የበጎ ፈቃድ ስራዎች መካከል በሆነው በትውልድ ለትምህርት ንቅናቄ ፕሮግራም ያስገነባውን የመጸዳጃ ቤት አስረከበ፡፡ የየካ ቅ/ጽ/ቤት የግል ት/ቤት ባለሃብቶችን በማስተባበር በየካ ክፍለ ከተማ ወረዳ 5 ለየካ ቅድመ አንደኛ የመጀመሪያና መካከለኛ ደረጃ ት/ቤት ባለአስር ቀዳዳ መጸዳጃ ቤት በማስገንባት አስረክቧል፡፡ አቶ አለልኝ ወንዴ የትምህርትና ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን ምክትል ስራ አስኪያጅ በመርሃግብሩ ላይ እንደገለጹት ባለስልጣኑ በዘጠና ቀን እቅዱ የተለያየ ትልልቅ ተግባራት ማከናወኑን ገልጸው ዛሬ እዚህ ግንባታው ተጠናቆ ለተማሪዎች አገልግሎት ክፍት የሆነው የመጸዳጃ ቤት ስራ በትውልድ ለትምህርት ንቅናቄ ፕሮግራም ቅ/ጽ/ቤቱ የግል ትምህርት ተቋማትን በማስተባበር ያከናወነው ተግባር ነው፡፡

የ2018 ዓ.ም የትምህርት አጀማመር ሂደት ተገመገመ፡፡ (መስከረም 19 ቀን 2018 ዓ.ም) በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የትምህርትና ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን የትምህርት ጥራት ማርጋገጥና
+6
የ2018 ዓ.ም የትምህርት አጀማመር ሂደት ተገመገመ፡፡ (መስከረም 19 ቀን 2018 ዓ.ም) በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የትምህርትና ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን የትምህርት ጥራት ማርጋገጥና ምርምር ዳይሬክቶሬት የማዕከልና የ9ኙ ቅ/ጽ/ቤት የዘርፉ ዳይሬክተሮች በ2018 ዓ.ም የትምህርት አጀማመር ዙሪያ ግምገማ አካሄዱ፡፡ አቶ አንዋር ሙላት የባለስልጣኑ የትምህርት ጥራት ማረጋገጥና ምርምር ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር እንደገለፁት የአዲስ አበባ ከተማ ትምህርት ቢሮ ባወጣው የትምህርት ካላንደር መሰረት የመማር ማስተማር ሂደቱ ጅማሮው ውጤታማ ይሆን ዘንድ በ2018 ዓ.ም አጠቃላይ ትምህርት አጀማመር ዙሪያ ግምገማ ማድረጋቸውን ገልጸዋል፡፡ የትምህርት ተቋማት በ2018 የትምህርት ዘመን የዝግጅት ደረጃቸውን፣በምዝገባ፣ በክፍያ፣በግብዓት እንዲሁም አጠቃላይ በመማር ማስተማር ሂደቱ ዙሪያ ላይ ያለውን ሂደት ባለሙያዎች ምልከታ ያደረጉ መሆናቸውንና ሂደቱን መገምገማቸውን ዳይሬክተሩ አስረድተዋል፡፡ በዚህም በአንዳንድ የትምህርት ተቋማት ላይ የሚገኙ ክፍቶችን ከወዲሁ ለማረም ግምገማው አስፋላጊ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ #ፌስቡክ;https://www.facebook.com/AA-Educational-Training-Quality-Occ-Competency-Assurance-Authority-100864428091362/?__tn__=-UC*F #ድረ_ገጽ; educoc.gov.et #ቴሌግራም https://t.me/AAEQOCAA #ቲክቶክ https://www.tiktok.com/@educationtraning2?_t=ZM-8u2f6smztvr&_r=1 #ነጻ_የጥቆማ_የስልክ_መስመር_9302 #ዩቲዩብ https://www.youtube.com/channel/UCzbsHLZjub9c7uVPjc

የባለስልጣኑ የወርቃማ ሰኞ ማለዳ የማነቃቂያና የእውቀት ሽግግር መርሃ-ግብር ተካሄደ፡፡ (መስከረም 19 ቀን 2018 ዓ.ም)በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የትምህርትና ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን
+6
የባለስልጣኑ የወርቃማ ሰኞ ማለዳ የማነቃቂያና የእውቀት ሽግግር መርሃ-ግብር ተካሄደ፡፡ (መስከረም 19 ቀን 2018 ዓ.ም)በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የትምህርትና ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን የወርቃማ ሰኞ የማነቃቂያና የእውቀት ሽግግር መርሃ-ግብር "Efficient System Design" በሚል ርዕስ ተካሂዷል፡፡ አቶ አየን ደርሰህ የባለስልጣኑ የስልጠና ጥራት ማረጋገጥ ቡድን መሪ ስራዎችን ስንሰራ ብክነት መኖሩን ገልጸው ብክነት መኖሩ የሚታሰብ ሆኖ ብክነትን በመቀነስ ዋጋ ላለው ነገር ትኩረት በመስጠት ስራን ማከናወንና ውጤታማ መሆን ያስፈልጋል ብለዋል፡፡ ከዚህም ሌላ በምርት ሂደት ውስጥ እሴትን የማይጨምሩ ነገሮችን በመቀነስ አገልግሎትን በማስፋት የተሻለ ማድረግ ይቻላል ብለዋል፡፡ ወ/ሮ ታጋይቱ አባቡ የባለስልጣኑ ምክትል ስራ አስኪያጅ በመርሃ-ግብሩ ላይ እንደገለጹት ውጤታማ ለመሆን የስራ ሰዓትን ማክበር፣ባለው የሰው ሃይል በአግባቡ መጠቀም፣እሴትን በመጨመርና ጥራትን በማረጋገጥ አገልግሎትን ለተገልጋይ ማድረስ ተገቢ መሆኑን የገለጹ ሲሆን የሰው ልጅ ችሎታና እውቀትን በመደመር ውጤታማ መሆን ይጠበቅበታል ብለዋል፡፡ #ፌስቡክ;https://www.facebook.com/AA-Educational-Training-Quality-Occ-Competency-Assurance-Authority-100864428091362/?__tn__=-UC*F #ድረ_ገጽ; educoc.gov.et #ቴሌግራም https://t.me/AAEQOCAA #ቲክቶክ https://www.tiktok.com/@educationtraning2?_t=ZM-8u2f6smztvr&_r=1 #ነጻ_የጥቆማ_የስልክ_መስመር_9302 #ዩቲዩብ https://www.youtube.com/channel/UCzbsHLZjub9c7uVPjc

ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች በሙሉ እንኳን ለደመራ በዓል እና ለብርሃነ መስቀሉ አደረሳችሁ፡፡ #ፌስቡክ;https://www.facebook.com/AA-Educational-Training-Qualit
ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች በሙሉ እንኳን ለደመራ በዓል እና ለብርሃነ መስቀሉ አደረሳችሁ፡፡ #ፌስቡክ;https://www.facebook.com/AA-Educational-Training-Quality-Occ-Competency-Assurance-Authority-100864428091362/?__tn__=-UC*F #ድረ_ገጽ; educoc.gov.et #ቴሌግራም https://t.me/AAEQOCAA #ቲክቶክ https://www.tiktok.com/@educationtraning2?_t=ZM-8u2f6smztvr&_r=1 #ነጻ_የጥቆማ_የስልክ_መስመር_9302 #ዩቲዩብ https://www.youtube.com/channel/UCzbsHLZjub9c7uVPjc

አቶ አዘዲን ሙስባህ የባለስልጣኑ ዋና ስራ አስኪያጅ በልምድ ልውውጡ ወቅት እንደገለጹት ባለስልጣኑ በሁሉም ዘርፍ ስራዎችን በትኩረት እያከናወነ እንደሆነ ጠቅሰው የምዘና ዘርፍ ደግሞ እንደ አገር አቀፍ የሚከናወን እንደመሆኑ ዘርፉ በጥብቅ ዲሲፕሊን የሚመራ መሆኑን ገልጸው የአፋር ክልልም የሙያ ብቃት ኤጀንሲ አመራሮች የልምድ ልውውጥ ማድረጋቸው የተለያዩ አሰራሮችን መመልከታ እንደሚያስችላቸው ገልጸዋል፡፡ የልምድ ልውውጡን ለማድረግ የመጡት አመራሮችም የተለያዩ የስራ ክፍሎችን ምልከታ ያደረጉ ሲሆን መረጃዎችን በሶፍት ኮፒ እና በሃርድ ኮፒ ከሚመለከታቸው አካላት ያገኙ ሲሆን ባደረጉት የልምድ ልውውጥም ደስተኞች መሆናቸውን ገልጸዋል፡፡ #ፌስቡክ;https://www.facebook.com/AA-Educational-Training-Quality-Occ-Competency-Assurance-Authority-100864428091362/?__tn__=-UC*F #ድረ_ገጽ; educoc.gov.et #ቴሌግራም https://t.me/AAEQOCAA #ቲክቶክ https://www.tiktok.com/@educationtraning2?_t=ZM-8u2f6smztvr&_r=1 #ነጻ_የጥቆማ_የስልክ_መስመር_9302 #ዩቲዩብ https://www.youtube.com/channel/UCzbsHLZjub9c7uVPjc