en
Feedback
የትምህርትና ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን

የትምህርትና ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን

Open in Telegram
5 357
Subscribers
No data24 hours
-97 days
+730 days
Posts Archive
3ኛውየአዲስ አበባ ከተማ ምክር ቤት አምስተኛ ዓመት የስራ ዘመን 1ኛ መደበኛ ጉባዔውን ማካሄድ ጀምሯል፡፡ ምክር ቤቱ የአዲስ አበባ ከተማ ምክር ቤት 3ኛ ዙር አራተኛ ዓመት የስራ ዘመን 4ኛ መደበኛ
3ኛውየአዲስ አበባ ከተማ ምክር ቤት አምስተኛ ዓመት የስራ ዘመን 1ኛ መደበኛ ጉባዔውን ማካሄድ ጀምሯል፡፡ ምክር ቤቱ የአዲስ አበባ ከተማ ምክር ቤት 3ኛ ዙር አራተኛ ዓመት የስራ ዘመን 4ኛ መደበኛ ጉባዔ ቃለ ጉባኤ በማጽደቅ በተለያዩ አጀንዳዎች ላይ በመወያየት ውሳኔዎችን ያስተላልፋል:: ምክር ቤቱ የአዲስ አበባ ከተማ ምክር ተመራጭ አባላት ከመራጩ ህዝብ ጋር ባደረጉት ውይይት ላይ በተነሱ ጥያቄዎች ላይ ምላሽ ይሰጣል፡፡ በተመሳሳይ ምክር ቤቱ የተለያዩ ሹመቶችን በማጽደቅ ይጠናቃል ተብሎ ይጠበቃል፡፡

“ሰንደቅ አላማችን ለኢትዮጵያ ታላቅ የከፍታ ዘመን ብስራት፣ለብሔራዊ አንድነታችን፣ ለሉዓላዊነታችንና ለኢትዮጵያ ህዳሴ” (ጥቅምት 3 ቀን 2018 ዓ.ም)በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የትምህርትና ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን 18ኛው ብሔራዊ የሰንደቅ አላማ ቀንን የባለስልጣኑ አመራሮችና ሰራተኞች በተገኙበት በታላቅ ድምቀት አከበረ፡፡ ወ/ሮ ታጋይቱ አባቡ የባለስልጣኑ ምክትል ስራ አስኪያጅና የጥራት ዘርፍ ሀላፊ በመክፈቻ ንግግራቸው ባስተላለፉት መልዕክት የአንድ ሀገር መገለጫ ሉአላዊነት ነው፡፡ሰንደቅ አላማችን የሉአላዊነታችን የአንድነታችን የጋራ አሻራችን ነው፡፡ኢትዮጵያ ችላ ያሳየች ወደፊትም የምትችል ሉአላዊት ሀገር ናት መጭው ትውልድ ሀገሩን የሚወድ ውስጣዊ ፍቅር ያለው ትውልድ መፍጠር እንድንችል እንዲሁም ምቹ ሀገር እንድትሆን የበኩላችንን አሻራ ማስቀመጥ ያስፈልጋል ብለዋል፡፡ አቶ ሰለሞን አለማየሁ የባለስልጣኑ አማካሪ “ሰንደቅ አላማችን ለኢትዮጵያ ታላቅ የከፍታ ዘመን ብስራት፣ለብሄራዊ አንድነትችን፣ለሉዓላዊነታችንና ለኢትዮጵያ ህዳሴ!” በሚል መሪ ቃል የብሄራዊ የሰንደቅ አላማ ቀንን አስመልክቶ ሰነድ አቅርበዋል፡፡ አቶ አለልኝ ወንዴ የባለስልጣኑ ምክትል ስራ አስኪያጅና የምዘና ዘርፍ ሀላፊ እንደገለጹት ሰንደቅ ዓላማ የአንድ ሀገር መለያ፣ የሀገር ፍቅር ማሳያና የህዝቦች ማንነት መገለጫ ነው።ኢትዮጵያ አባቶቻችን ያስረከቡንን መልካም ሀገር ልታሳካው የምትፈልገውን ራዕይ እንድታሳካ እንዲሁም ሀገሩን የሚወድ ትውልድ እንዲተካ መልካሙን በማድርግና በማስቀጠል እየተሳኩ ያሉትን በመደገፍ የተሻለች ሀገር መገንባትና ማስረከብ ያስፈልጋል ብለዋል፡፡ በመጨረሻም ከቤቱ አስተያየትና ሀሳብ የተነሳ ሲሆን ውይይትም ተደርጎበታል፡፡ #ፌስቡክ;https://www.facebook.com/AA-Educational-Training-Quality-Occ-Competency-Assurance-Authority-100864428091362/?__tn__=-UC*F #ድረ_ገጽ; educoc.gov.et #ቴሌግራም https://t.me/AAEQOCAA #ቲክቶክ https://www.tiktok.com/@educationtraning2?_t=ZM-8u2f6smztvr&_r=1 #ነጻ_የጥቆማ_የስልክ_መስመር_9302 #ዩቲዩብ https://www.youtube.com/channel/UCzbsHLZjub9c7uVPjc

በግምገማው ላይ የባለስልጠኑ የጠቅላላ ካውንስል አባላት የየስራ ክፍላቸውን ክንውን ለውይይት በማቅረብ ውይይት ተደርጎበታል፡፡ #ፌስቡክ;https://www.facebook.com/AA-Educational-Training-Quality-Occ-Competency-Assurance-Authority-100864428091362/?__tn__=-UC*F #ድረ_ገጽ; educoc.gov.et #ቴሌግራም https://t.me/AAEQOCAA #ቲክቶክ https://www.tiktok.com/@educationtraning2?_t=ZM-8u2f6smztvr&_r=1 #ነጻ_የጥቆማ_የስልክ_መስመር_9302 #ዩቲዩብ https://www.youtube.com/channel/UCzbsHLZjub9c7uVPjc

የባለስልጣኑ ጠቅላላ ካውንስል የ2018 የመጀመሪያ ሩብ ዓመት እቅድ ክንውን ገመገመ፡፡ (መስከረም 30 ቀን 2018 ዓ.ም)በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የትምህርትና ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን
+5
የባለስልጣኑ ጠቅላላ ካውንስል የ2018 የመጀመሪያ ሩብ ዓመት እቅድ ክንውን ገመገመ፡፡ (መስከረም 30 ቀን 2018 ዓ.ም)በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የትምህርትና ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን የ2018 የመጀመሪያ ሩብ ዓመት እቅድ ክንውኑንና የመልካም አስተዳደርና አገልግሎት አሰጣጥ ክንውኑን የባለስልጣኑ ጠቅላላ ካውንስል በተገኙበት ገመገመ፡፡ አቶ ሰለሞን አለማየሁ የባለስልጣኑ አማካሪ ሪፖርቶቹን በዝርዝር ያቀረቡ ሲሆን በሪፖርቱ የዝግጅት ምዕራፍ ተግባራት፣ቁልፍ ተግባራት፣አበይት ተግባራት ያጋጠሙ ችግርች ፣የነበሩ ጠንካራ ጎኖች፣እንዲሁም የቀጣይ የትኩረት አቀጣጫ ተካቶ በዝርዝር አቅርበዋል፡፡ ከዚህም ሌላ ከመልካም አስተዳደር ችግሮች እንደ ተቋም የተፈቱ የመልካም አስተዳደር ችግሮች፣ምላሽ ሰጪነት፣ የተጠያቂነት ስርዓት ማስፈን፣ ግልጽነት መፍጠርና ሌሎችም ዝርዝር ሃሳቦች በሪፖርቱ ተገልጸዋል፡፡ ወ/ሮ ታጋይቱ አባቡ የባለስልጣኑ ምክትል ስራ አስኪያጅና የጥራት ዘርፍ ሃላፊ እንደገለጹት በዝግጅት ምዕራፍ እቅድ ክንውን በርካታ ስራዎች እንደ ተቋም የተከናወኑ ቢሆንም በቀጣይ በተግባር ምዕራፍ ተግባራትን ከቁጥር በዘለለ በጥራት ሙሉ በሙሉ ማከናወንና ውጤታማ አገልግሎትን አጠናክሮ ማስቀጠል፣ ተገልጋይንም ሙሉ በሙሉ ማርካት ይጠበቅብናል ብለዋል፡፡ አቶ ኢዘዲን ሙስባህ የባለስልጣኑ ዋና ስራ አስኪያጅ በመድረኩ ማጠቃለያ ላይ እንደገለጹት ይህ የመጀመሪያው ሩብ ዓመት የዝግጅት ምዕራፍ ወቅት በመሆኑ እቅዳችንን በአግባቡ አቅደን ወደ ተግባር ምዕራፍ የምንገባበት ጊዜ በመሆኑ ስራዎችን በሃላፊነት ማከናወን፣መረጃዎችን በአግባቡ ማደራጀት፣ በቴክኖሎጂ በአግባቡ መጠቀም፣በያለንበት መስክ አገልግሎት አሰጣጣችንን ለማህበረሰቡ አጠናክረን በሃላፊነት መስጠት ያስፈልጋል የሚል መልዕክት አስተላልፈዋል፡፡

ባለስልጣኑ ለእጩ መዛኞች ሲሰጥ የነበረውን የምዘና ስነ-ዘዴ ስልጠና አጠናቀቀ፡፡ (ጥቅምት 30 ቀን 2018 ዓ.ም) የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የትምህርትና ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን የቴ/
+6
ባለስልጣኑ ለእጩ መዛኞች ሲሰጥ የነበረውን የምዘና ስነ-ዘዴ ስልጠና አጠናቀቀ፡፡ (ጥቅምት 30 ቀን 2018 ዓ.ም) የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የትምህርትና ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን የቴ/ሙያ ሙያ ብቃት ምዘና ዝግጅትና አሰጣጥ ዳይሬክቶሬት ከተለያዩ ኢንደስትሪዎች ለተውጣጡ አዳዲስ እጩ መዛኞች የምዘና ስነ-ዘዴ ስልጠና ሰጥቶ አጠናቀቀ፡፡ ባለስልጣኑ ከተለያዩ ኢንደስትሪዎች ለተውጣጡ አዳዲስ እጩ መዛኞች የምዘና ስነ-ዘዴ ስልጠና ለአምስት ተከታታይ ቀናት እየሰጠ እንደነበረ ይታወቃል፤በመሆኑም ስልጠናው ላጠናቀቁ 25 እጩ መዛኞች የሙያ ብቃት ምዘናውን በመውሰድ ስልጠናውን አጠናቅቀው በቀጣይ ወደ ምዘናው ስራ እንደሚቀላሉ ታውቋል፡፡ ዶክተር ገነት ኃ/የሱስ የባለስልጣኑ የቴ/ሙያ ብቃት ምዘና ቡድን መሪ የሙያ ብቃት ምዘና እንደ ሀገር ትልቅ ሀላፊነት የሚጠይቅ እንደመሆኑ ብቁ ሆነው ወደ ስራ ከገቡ በኋላ በቅንነት በታማኝነትና በሀላፊነት እንዲሁም በመልካም ስነ-ምግባር ልታገለግሉ ይገባል ብለዋል፡፡ #ፌስቡክ;https://www.facebook.com/AA-Educational-Training-Quality-Occ-Competency-Assurance-Authority-100864428091362/?__tn__=-UC*F #ድረ_ገጽ; educoc.gov.et #ቴሌግራም https://t.me/AAEQOCAA #ቲክቶክ https://www.tiktok.com/@educationtraning2?_t=ZM-8u2f6smztvr&_r=1 #ነጻ_የጥቆማ_የስልክ_መስመር_9302 #ዩቲዩብ https://www.youtube.com/channel/UCzbsHLZjub9c7uVPjc

ዶክተር ብሩክ ከድር የፌዴራል ቴክኒክና ሙያ ኢንስቲቲዩት ዋና ዳይሬክተር በበኩላቸው እንደገለጹት በህብረተሰቡ ውስጥ በልምድ ከሚሰሩ ሙያተኞች መካከል የብየዳ ሙያ ዋናው በመሆኑ ይህን ቁልፍ የሆነ ሙያ በልምድ የሙያ ባለቤት ለሆኑ ሙያተኞች እውቅና እንዲያገኙ ለማድረግ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የትምህርትና ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን በጋራ ለመስራት ያደረግነው ምክክር ሀገራዊ የሆነ ሃላፊነትን ከዳር ማድረስ እንደሆነ ገልጸው ከባለስልጣኑ ጋር በቀጣይ የመግባቢያ ስምምነት በማድረግ በጋራ እንሰራለን ብለዋል፡፡ #ፌስቡክ;https://www.facebook.com/AA-Educational-Training-Quality-Occ-Competency-Assurance-Authority-100864428091362/?__tn__=-UC*F #ድረ_ገጽ; educoc.gov.et #ቴሌግራም https://t.me/AAEQOCAA #ቲክቶክ https://www.tiktok.com/@educationtraning2?_t=ZM-8u2f6smztvr&_r=1 #ነጻ_የጥቆማ_የስልክ_መስመር_9302 #ዩቲዩብ https://www.youtube.com/channel/UCzbsHLZjub9c7uVPjc

ባለስልጣኑ በልምድ የተገኘን የሙያ ብቃት እውቀትና ክህሎት እውቅና ለመስጠት እንዲያስችለው የምዘና ጣቢያዎችን ለመመልመል ምልከታ አደረገ፡፡ (መስከረም 29 ቀን 2018 ዓ.ም) የአዲስ አበባ ከተማ አ
+4
ባለስልጣኑ በልምድ የተገኘን የሙያ ብቃት እውቀትና ክህሎት እውቅና ለመስጠት እንዲያስችለው የምዘና ጣቢያዎችን ለመመልመል ምልከታ አደረገ፡፡ (መስከረም 29 ቀን 2018 ዓ.ም) የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የትምህርትና ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን የቴ/ሙያ ብቃት ምዘና ዝግጅትና አሰጣጥ ዳይሬክቶሬት በብየዳ ሙያ በልምድ የተገኘን የሙያ ክህሎት እውቅና ለመስጠት እንዲቻል በትብብር ከባለስልጠኑ ጋር ለመስራት ከፌዴራል ቴክኒክና ሙያ ኢንስቲቲዩት ጋር የሾፕ ምልከታ በማድረግ ምክክር ተደረገ፡፡ አቶ አለልኝ ወንዴ በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የትምህርት ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን ምክትል ስራ አስኪያጅና የምዘና ዘርፍ ሃላፊ እንደገለጹት ባለስልጣኑ በተለያየ መስክ የሰለጠኑ የሙያ ባለቤቶች በሙያ ብቃት ምዘና እያረጋገጠ የምስክር ወረቀት እየሰጠ መሆኑን ጠቅሰው በልምድ የተገኘን እውቀትና ክህሎት እውቅና መስጠት እንዲቻል በትብብር ለመስራት ከፌዴራል ቴክኒክና ሙያ ኢንስቲቲዩት ጋር በተለይ በብየዳ ሙያ የቴክኖሎጂ ማምረት እና ብየዳ ልህቀት ማእከልን በምዘና ጣቢያነት ስናየው በሙያው በልምድ ክህሎቱ እና እውቀቱ ያላቸው ባለሙያዎችን በምዘና ለማረጋገጥ ምቹ በመሆኑ እንደ ባለስልጣን ወስደን በቀጣይ የጋራ ስምምነት የምናደርግ ሲሆን ሁሉም በድርሻው ማድረግ የሚገባውን ሀገራዊ ሃላፊነት መወጣት ይገባዋል ብለዋል፡፡

በተጨማሪም ስልጠናውን የሚወስዱት በተለያዩ የሙያ ዘርፎች ከተለያዩ ኢንደስትሪዎች የተውጣጡ የመጀመሪያ ዲግሪ እና ከዛ በላይ ያላቸው እና ሶስት ዓመት በላይ በኢንደስትሪ ያገለገሉ እና የሙያ ብቃት ምዘና ወስደው ብቃታቸውን ያረጋገጡና መስፈርቱን የሚያሟሉ መሆናቸውን በማጣራት የተመለመሉ መሆኑን የገለፁልን ሲሆን ስልጠናው ለተከታታይ 5 ቀናት የሚቆይ መሆኑን አስረድተዋል፡፡ #ፌስቡክ;https://www.facebook.com/AA-Educational-Training-Quality-Occ-Competency-Assurance-Authority-100864428091362/?__tn__=-UC*F #ድረ_ገጽ; educoc.gov.et #ቴሌግራም https://t.me/AAEQOCAA #ቲክቶክ https://www.tiktok.com/@educationtraning2?_t=ZM-8u2f6smztvr&_r=1 #ነጻ_የጥቆማ_የስልክ_መስመር_9302 #ዩቲዩብ https://www.youtube.com/channel/UCzbsHLZjub9c7uVPjc

ባለስልጣኑ ለአዳዲስ እጩ መዛኞች የምዘና ስነ-ዘዴ ስልጠና መስጠት ጀመረ፡፡ (መስከረም 27 ቀን 2018 ዓ.ም) የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳዳር ትምህርትና ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን የቴ/ሙያ
+3
ባለስልጣኑ ለአዳዲስ እጩ መዛኞች የምዘና ስነ-ዘዴ ስልጠና መስጠት ጀመረ፡፡ (መስከረም 27 ቀን 2018 ዓ.ም) የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳዳር ትምህርትና ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን የቴ/ሙያ ሙያ ብቃት ምዘና ዝግጅትና አሰጣጥ ዳይሬክቶሬት ከተለያዩ ኢንደስትሪዎች ለተውጣጡ አዳዲስ እጩ መዛኞች የምዘና ስነ-ዘዴ ስልጠና መስጠት ጀመረ፡፡ አቶ አለልኝ ወንዴ የባለስልጣኑ ምክትል ስራ አስኪያጅና የምዘና ዘርፍ ሀላፊ በመክፈቻ ንግግራቸው ለምትገቡበት ሀላፊነት ለምታገለግሉት ሙያ በቅንነት፣በታማኝነት እና በስነ-ምግባር ታንፃችሁ ለምትቀበሉት ሃላፊነት በቅንነት በማገልገል ለሀገር እንዲሁም ለዜጋ ትልቅ አስተዋፅኦ ማድረግ ያስፈልጋል ያሉ ሲሆን ስልጠናውንም በጥሩ ስነ-ምግባር መከታተል እንደሚገባ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል፡፡ የባለስልጣኑ የቴ/ሙያ ብቃት ምዘና ቡድን መሪ የሆኑት ዶክተር ገነት ኃ/የሱስ እንደገለጹት አዳዲስ መዛኞችን ማፍራትና በምዘና ስነ-ዘዴው ብቁ የሆኑትን ወደ ምዘና ተግባር ማስገባት የስራ ክፍሉ ኃላፊነት እንደመሆኑ ያንን ተግባራዊ ለማድረግ የተሰጠ እና የመዛኝነት ብቃት የሚያገኙበት ስልጠና ነው ያሉ ሲሆን ስልጠናው አጠቃላይ የምዘና ስነ-ዘዴ እና የምዘና ሂደት በስልጠናው መካታቱን ገልጸው ከስልጠናው ሂደት በኋላም በምዘና ብቁ የሚሆኑት ባለሙያዎች ወደ ምዘና ስራ የሚገቡ መሆናቸውን ገልፀው የሙያ ብቃት ምዘና ትልቅ ሀላፊነት የሚጠይቅ እንደመሆኑ ብቁ ሆነው ወደ ስራ ከገቡ በኋላ በሀላፊነትና በመልካም ስነ-ምግባር ሊያገለግሉ ይገባል ብለዋል፡፡

በቀረበው ሰነድ ላይ ውይይት የተደረገበት ሲሆን ሀገራችን በጂኦ-ስትራቴጂ ለዉጥና በሀገራዊ ህልዉና እንዳትቀጥልና ጥቅሞቿ እንዳይከበሩ ታሪካዊ በሆኑ ጠላቶች እየደረሰባት ያሉ ጫናዎችን ለመቀነስና የሚደረጉ ሴራዎችን በመለየት እንደ ሀገር በአንድነት በመቆም ብሄራዊ ጥቅምን ማስከበር ተገቢነት አለዉ ሲሉ የባለስልጣኑ ሰራተኞች ሃሳባቸውን ገልጸዋል፡፡ #ፌስቡክ;https://www.facebook.com/AA-Educational-Training-Quality-Occ-Competency-Assurance-Authority-100864428091362/?__tn__=-UC*F #ድረ_ገጽ; educoc.gov.et #ቴሌግራም https://t.me/AAEQOCAA #ቲክቶክ https://www.tiktok.com/@educationtraning2?_t=ZM-8u2f6smztvr&_r=1 #ነጻ_የጥቆማ_የስልክ_መስመር_9302 #ዩቲዩብ https://www.youtube.com/channel/UCzbsHLZjub9c7uVPjc

"ከጂኦ-ስትራቴጅያዊ ኩስመና ወደ ታደሰ ቁመና" በሚል ርዕሰ ጉዳይ ላይ ውይይት ተደረገ፡፡ (መስከረም 27 ቀን 2018 ዓ.ም)በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የትምህርትና ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስል
+6
"ከጂኦ-ስትራቴጅያዊ ኩስመና ወደ ታደሰ ቁመና" በሚል ርዕሰ ጉዳይ ላይ ውይይት ተደረገ፡፡ (መስከረም 27 ቀን 2018 ዓ.ም)በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የትምህርትና ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን አመራሮችና ሰራተኞች "ከጂኦ-ስትራቴጅያዊ ኩስመና ወደ ታደሰ ቁመና" በሚል ርዕስ ጉዳይ ላይ ውይይት አካሂደዋል፡፡ የመወያያ ሰነዱን ያቀረቡት አቶ ኢዘዲን ሙስባህ የባለስልጣኑ ዋና ስራ አስኪያጅ የመወያያ ሰነዱን ያቀረቡ ሲሆን ሀገራችን በፖለቲካና ኢኮኖሚው ዘርፍ፣ዓባይን በመገደብ ቀጠናዊና ጂኦ- ስትራቴጅያዊ ትኩረት ማግኘት መቻላችንና የባህር በር የማግኘት ተፈጥሯዊና ታሪካዊ መብታችንን ዓለም አቀፍ አጀንዳ እንዲሆን በማድረግ ከፍተኛ ለውጥ ተመዝግቧል ብለዋል፡፡ ኢትዮዽያ ጂኦ- ስትራቴጂያዊ ቁመናዋ እንዲኮሰምን ባዳዎችና ባንዳዎች እየሰሩ ቢሆንም የውስጥ አንድነትን በማጠናከርና በህብረት በመቆም ውስጣዊ ሰላምን ማረጋገጥ ለታደሰ ጂኦ- ስትራቴጂያዊ ቁመና ግንባታ ወሳኝ መሆኑን ስራ አስኪያጁ አስረድተዋል፡፡ከዚህም ሌላ እያንዳንዱ ዜጋ በተሠማራበት የስራ መስክ ኃላፊነቱን በቅንነት ሊወጣ እንደሚገባ አስገንዝበዋል፡፡ የትምህርት ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን ምክትል ስራ አስኪያጅና የምዘና ዘርፍ ሃላፊ የሆኑት አቶ አለልኝ ወንዴ እንደተናገሩት ሀገራችን ባላት እድገት እና ለውጥ የውስጥና የውጪ ጠላቶች ቁጭት ላይ ገብተዋል በመሆኑም ውስጣዊ አንድነት ማጠናከር በፍቅር በፅናት አገልግሎትን በአግባቡ መስጠት የጥፋት ስትራቴጂ በመገንዘብ መታገል ይኖርብናል ያሉ ሲሆን ሁሉም ማህበረሰብ በሚሠራበትና በሚኖርበት አካባቢ ግንዛቤ ኖሮት የራሱን ሚና ለመወጣት ለአገር በቁርጠኝነት መስራት ይገባዋል ብለዋል፡፡

አቶ ኢዘዲን ሙስባህ የባለስልጣኑ ዋና ስራ አስኪያጅ በመርሃ-ግብሩ ላይ እንደጠቀሱት ቀልጣፋ አገልግሎት ለማከናወን ራሳችንን በቴክኖሎጂ ማዘጋጀት እና ስማርት በመሆን በቅንነት፣ በቅልጥፍናና በዝግጁነት አስደሳች አገልግሎት ለተገልጋይ መስጠት ያስፈልጋል ብለዋል፡፡ #ፌስቡክ;https://www.facebook.com/AA-Educational-Training-Quality-Occ-Competency-Assurance-Authority-100864428091362/?__tn__=-UC*F #ድረ_ገጽ; educoc.gov.et #ቴሌግራም https://t.me/AAEQOCAA #ቲክቶክ https://www.tiktok.com/@educationtraning2?_t=ZM-8u2f6smztvr&_r=1 #ነጻ_የጥቆማ_የስልክ_መስመር_9302 #ዩቲዩብ https://www.youtube.com/channel/UCzbsHLZjub9c7uVPjc

የባለስልጣኑ የወርቃማ ሰኞ ማለዳ የማነቃቂያና የእውቀት ሽግግር መርሃ-ግብር ተካሄደ፡፡ (መስከረም 26 ቀን 2018 ዓ.ም)በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የትምህርትና ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን
+6
የባለስልጣኑ የወርቃማ ሰኞ ማለዳ የማነቃቂያና የእውቀት ሽግግር መርሃ-ግብር ተካሄደ፡፡ (መስከረም 26 ቀን 2018 ዓ.ም)በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የትምህርትና ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን የወርቃማ ሰኞ የማነቃቂያና የእውቀት ሽግግር መርሃ-ግብር "ስማርት ሲቲ እና የአንድ መሶብ አገልግሎት" በሚል ርዕስ ተካሂዷል፡፡ ወ/ት ሜሮን ገ/እግዚአብሔር የባለስልጣኑ የኔትወርኪግና ኮምፒውተር ጥገና ቡድን መሪ ስማርት ሲቲ እና የአንድ መሶብ አገልግሎት ሰነድ በማቅረብ ያብራሩ ሲሆን በዚህም የአንድ መሶብ አገልግሎት ምንድን ነው? የአንድ መሶብ አገልግሎት ጥቅሞች? ቴክኖሎጂን መሰረት ያደረገ የአንድ መሶብ አገልግሎት፣አንድ ከተማ ስማርት ሲቲ ለመባል ምን ያስፈልገዋል?ስማርት ሲቲ የሚጠቀማቸው ቴክኖሎጂዎች የስማርት ሲቲ ጥቅሞች በሚሉ ይዘቶች ላይ ዝርዝር ሰነድ ያቀረቡ ሲሆን አገልግሎታችንን በፍጥነት፣በቀላልና በግልጽነት ለማቅረብ የሚያገለግል አስፈላጊ መንገድ ነው ያሉ ሲሆን ስማርት ሀገር እንድትፈጠር ዜጎቿ ራሳችንን ብቁ ማድረግና ስማርት መሆን ይጠበቅብናል ብለዋል፡፡

አባገዳዎች እና ሃደ ሲንቄዎች ከቄሮዎች፤ ቀሬዎች፤ ፎሌዎች እና ከበዓሉ ታዳሚዎች ጋር በመሆን የተለያዩ ባህላዊ ዝማሬዎችንና ጭፈራዎችን በማሰማት ወደ መልካ ወይንም ወደ ሆረ ፊንፊኔ መልካ (ወንዝ) በ
+5
አባገዳዎች እና ሃደ ሲንቄዎች ከቄሮዎች፤ ቀሬዎች፤ ፎሌዎች እና ከበዓሉ ታዳሚዎች ጋር በመሆን የተለያዩ ባህላዊ ዝማሬዎችንና ጭፈራዎችን በማሰማት ወደ መልካ ወይንም ወደ ሆረ ፊንፊኔ መልካ (ወንዝ) በመሄድ መልካዉን (ወንዙን) በመመረቅ በእጥብ ሳር ኢሬፈና ወይንም ምስጋና የማቅረብ ሥነ ሥርዓት አስጀምረዋል፡፡ የኦሮሞ ህዝብ ለረጅም ዓመታት በየአመቱ በሆረ ፊንፊኔ መልካ (ወንዝ) በመገናኘት የኢሬፈና ወይንም ለፈጣሪ ምስጋና የማቅረብ ሥነ ሥርዓት ሲካናዉን ቆይቷል፡፡