EOTC Books ⛪️
📚 በዚህ ቻናል/ኦ/ተ/ቤ/ክ የምትቀበላቸውን ቅዱሳት መጻሕፍትን ለምዕመናን ተደራሽ ማድረግ ነው ይኸውም ከሀገራችን እንዲሁም ከውጪ ሀገር (ቤ/ክ የምትቀበለውን) ናቸው ። 💬 contact us @Jared2080 buy Ads? https://telega.io/c/EOTCBooks1 YouTube 👇 https://www.youtube.com/@zeEthiop
Show more📈 Analytical overview of Telegram channel EOTC Books ⛪️
Channel EOTC Books ⛪️ (@eotcbooks1) in the Amharic language segment is an active participant. Currently, the community unites 20 322 subscribers, ranking 3 848 in the Religion & Spirituality category and 1 700 in the Ethiopia region.
📊 Audience metrics and dynamics
Since its creation on невідомо, the project has demonstrated rapid growth, gathering an audience of 20 322 subscribers.
According to the latest data from 06 September, 2026, the channel demonstrates stable activity. Although there has been a change in the number of participants by 535 over the last 30 days and by 24 over the last 24 hours, overall reach remains high.
- Verification status: Not verified
- Engagement rate (ER): The average audience engagement rate is 13.44%. Within the first 24 hours after publication, content typically collects 6.78% reactions from the total number of subscribers.
- Post reach: On average, each post receives 2 732 views. Within the first day, a publication typically gains 1 377 views.
- Reactions and interaction: The audience actively supports content: the average number of reactions per post is 8.
📝 Description and content policy
The author describes the resource as a platform for expressing subjective opinions:
“📚
በዚህ ቻናል/ኦ/ተ/ቤ/ክ የምትቀበላቸውን ቅዱሳት መጻሕፍትን ለምዕመናን ተደራሽ ማድረግ ነው ይኸውም ከሀገራችን እንዲሁም ከውጪ ሀገር (ቤ/ክ የምትቀበለውን) ናቸው ።
💬 contact us
@Jared2080
buy Ads?
https://telega.io/c/EOTCBooks1
YouTube 👇
https://www.youtube.com/@zeEthiop”
Thanks to the high frequency of updates (latest data received on 07 September, 2026), the channel maintains relevance and a high level of publication reach. Analytics show that the audience actively interacts with content, making it an important point of influence in the Religion & Spirituality category.
Data loading in progress...
| Date | Subscriber Growth | Mentions | Channels | |
| 07 September | +1 | |||
| 06 September | +26 | |||
| 05 September | +5 | |||
| 04 September | +12 | |||
| 03 September | +7 | |||
| 02 September | +25 | |||
| 01 September | +19 |
| 2 | 🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹
ጳጕሜን እንዴት ተገኘች?
🐲🐲🐲🐲🐲🐲🐲🐲
5 : 6 : 7 የመሆኗ ምሥጢር
🔤በኹለት አሠራር ወይም ሒሳባዊ ስሌት እናያለን።
ሀገራችን ኢትዮጵያ ብቸኛዋ ባለ 13 ወር ናት።
✅ጳጕሜን ማለት ተረፍ ንዑስ (ትርፍ ፣ ታናሽ) ማለት ነው።
ጳጕሜን የተገኘችው በየቀኑ ከሚተርፉት ሽርፍራፊ ሴኮንዶች ነው።
🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼
🔤የመጀመሪያው የጳጕሜን ማግኛ መንገድ በሴኮንድና በደቂቃ አሠራር ነው።
፩ : በሴኮንድና በደቂቃ
መሠረታዊ የቀናት ስሌቶችን መሠረት በማድረግ በአንድ ቀን ውስጥ የሚተርፉ ደቂቃዎችና ሴኮንዶች ተጠራቅመው ጳጕሜን ያስገኙልናል።
➤1ቀን = 24 ሰዓት = 60 ኬክሮስ
➤ 1ቀን = 24 ሰዓት ከ52 ካልዒት ከ31 ሣልሲት ነው። በ1ቀን ውስጥ 52 ካልዒት 31 ሣልሲት ትርፍ አለ።
✦1ካልዒት = 0.4 ደቂቃ = 24 ሴኮንድ ነው።
✦ 1ሣልሲት = 0.4 ሴኮንድ ነው።
💥 በአንድ ቀን ውስጥ ያለውን 52 ካልዒት ወደ ሴኮንድ ስንቀይረው።
1ካልዒት 24 ሴኮንድ ከሆነ
52 ካልዒት ስንት ሴኮንድ ይሆናል?
52 × 24 ሴኮንድ = 1248 ሴኮንድ 48 ቱን ትተን 1200 ሴኮንድ ወደ ደቂቃ ስንቀይረው
20 ደቂቃ ይሆናል።
1248 ሴኮንድ = 20 ደቂቃ ከ48 ሴኮንድ
💥በአንድ ቀን ውስጥ ያለውን 31 ሣልሲት ወደ ሴኮንድ ስንቀይረው።
1ሣልሲት 0.4 ሴኮንድ ከሆነ
31 ሣልሲት ስንት ሴኮንድ ይሆናል?
31× 0.4 ሴኮንድ = 12.4 ሴኮንድ ይሆናል 12 ቱን ሴኮንድ ከላይ ካገኘነው ከ48 ቱ ሴኮንድ እንደምረዋለን።
💥 ቀሪዋ 0.4 ሴኮንድ ግን ትቆየን። ይህችንን የምንጠቀማት በኋላ ነው።
💎 በአንድ ቀን ውስጥ ያለው 52 ካልዒትና 31 ሣልሲት በጠቅላላው ወደ ደቂቃ ሲቀየሩ ድምር ውጤታቸው ይህ ነው።
▶52 ካልዒት = 20 ደቂቃ ከ48 ሴኮንድ
▶31 ሣልሲት = 12 ሴኮንድ
✍️ 25 ካልዒት + 31 ሣልሲት
= 20 ደቂቃ ከ48 ሴኮንድ + 12 ሴኮንድ
= 20 ደቂቃ ከ60 ሴኮንድ (60 ሴኮንድ = 1ደቂቃ)
= 21ደቂቃ ይሆናል።
💥ስለዚህም በአንድ ቀን ውስጥ የሚገኘው ትርፍ 21 ደቂቃ እና ከላይ የተውናት 0.4 ሴኮንድ ናት።
ይህ ማለት አንድ ቀን 24 ሰዓት ሆኖ 21 ደቂቃ ከ0.4 ሴኮንድ ትርፍ አለው።
በየቀኑ የምናገኛቸው ትርፎቹ ጳጕሜን ያስገኙልናል።
ይህንን መሠረት በማድረግ በአንድ ዓመት ውስጥ የሚተርፈውን ማወቅ እንችላለን።
➤አንድ ወር 30 ቀን ነው
➤12 ወራት ደግሞ 360 ቀናት ናቸው
ጳጕሜን የተገኘች ደግሞ ከ12 ወራት 13ኛ ወር ሁና ከ360 ቀናት 365 እና 366 ቀን ሁና ነው።
💥መጀመሪያ በየቀኑ የተረፈውን ደቂቃ መሠረት አድርገን እንሥራ።
በአንድ ቀን የተረፈው 21 ደቂቃ በዓመት ስንት ይሆናል?
✤ 21 × 360 = 7560 ደቂቃ ይሆናል
✤ 7560÷ 60 = 126 ሰዓት ይሆናል
✤ 126 ÷ 24 = 5ቀን ከ6 ሰዓት ይሆናል ወይም 120ው ሰአት 5 ቀን ነው ትርፍ 6 አለ።
➤ በአንድ ዓመት ውስጥ 5 ቀን ከ6 ሰዓት ትርፍ አለ። ይኼውም የጳጕሜን ቀናት ናቸው። ይህም የዓመቱን ቀን 365 ቀን ያደርገዋል። 6 ሰዓት ግን ትርፍ አለ።
በየዓመቱ የተረፈው 6 ሰዓት ደግሞ ምን እንደሚያስገኝ እንሥራ።
✦ በ1ኛው ዓመት 365ቀን ከ6 ሰዓት
✦ በ2ኛው ዓመት 365ቀን ከ12 ሰዓት
✦ በ3ኛው ዓመት 365ቀን ከ18 ሰዓት
✦ በ4ኛው ዓመት 365ቀን ከ24 ሰዓት ሲሆን ይህም 24ቱ ሰዓት 1ቀን በመሆኑ ዓመቱን 366 ቀን ያደርገዋል። በየአራት ዓመቱ ጳጕሜን 6 የምትሆን ከዚህ የተነሣ ነው።
🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼
☝ ወደ ኋላ ልመልሳችሁና ትተናት የመጣን 0.4 ሴኮንድ አለች ይህችም በየቀኑ የምትተርፍ ናት። ከዚች ተነስተን ጳጕሜን 7 የምትሆንበትን እናገኛለን።
➤ በ12 ወር በ360 ቀናት ስንሠራት
0.4×360 = 144 ሴኮንድ ይህም በአንድ አመት የሚገኘው ትርፍ ሴኮንድ ነው።
➤ በ100 ዓመት ውስጥ ስንት ትሆናለች?
✦144 × 100 = 14400 ሴኮንድ = 240 ደቂቃ = 4 ሰዓት ።
✦በ200 ዓመት 8 ሰዓት
✦በ300 ዓመት 12 ሰዓት
✦በ400 ዓመት 16 ሰዓት
✦በ500 ዓመት 20 ሰዓት
✦በ600 ዓመት 24 ሰዓት (አንድ ቀን) ይሆናል። ጳጕሜን በ600 መቶ ዓመት 7 ቀን ትሆናለች።
🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼
ሁለተኛው የጳጕሜን ማግኛ መንገድ በካልዒትና በሣልሲት አሠራር ነው።
፪: በካልዒትና በሣልሲት
መሠረታዊ የቀናት ስሌቶችን መሠረት በማድረግ በአንድ ቀን ውስጥ የሚተርፉ ካልዒትና ሣልሲት ተጠራቅመው ጳጕሜን ያስገኙልናል።
➤1ቀን = 24 ሰዓት = 60 ኬክሮስ
➤ 1ቀን = 60 ኬክሮስ ከ52 ካልዒት ከ31 ሣልሲት ነው። በ1ቀን ውስጥ 52 ካልዒት 31 ሣልሲት ትርፍ አለ።
✔️ በየቀኑ የሚተርፈውን ካልዒት መሠረት በማድረግ በዓመት ምን ያክል ኬክሮስ እናገኛለን
☸️ በ1 ቀን 52 ካልዒት ከተረፈ በ30 ቀን ስንት ይሆናል?
30×52 = 1560 ካልዒት
ወደ ኬክሮስ ስንቀይረው በ60 እንገድፈዋለን ወይም ለ60 እናካፍለዋለን።
👉1 ኬክሮስ = 60 ካልዒት ነው።
1560 ካልዒት ስንት ኬክሮስ ይሆናል ?
1560÷60 = 26 ኬክሮስ።
☸️ በአንድ ወር ውስጥ 26 ኬክሮስ ከተገኘ በዓመት (በ12 ወር) ስንት ኬክሮስ ይገኛል ?
12×26 = 312 ኬክሮስ።
✔️ በየቀኑ የሚተርፈውን ሣልሲት መሠረት በማድረግ በዓመት ምን ያክል ኬክሮስ እናገኛለን
☸️ በ1 ቀን 31 ሣልሲት ከተረፈ በ30 ቀን ስንት ይሆናል?
30×31 = 930 ሣልሲት
☸️ በ1 ወር 930 ሣልሲት ከተረፈ በአንድ ዓመት (12 ወር) ስንት ይሆናል?
12×930 = 11160 ሣልሲት
ወደ ካልዒት ስንቀይረው በ60 እንገድፈዋለን ወይም ለ60 እናካፍለዋለን።
👉1 ካልዒት = 60 ሣልሲት ነው።
11160 ሣልሲት ስንት ካልዒት ይሆናል ?
11160÷60= 186 ካልዒት
ይህንን ወደ ኬክሮስ መቀየር እንችላለን
👉1 ኬክሮስ = 60 ካልዒት
186 ካልዒት ስንት ኬክሮስ ይሆናል ?
186 ካልዒትን በ 60 መግደፍ ወይም ለ 60 ማካፈል።
186 ÷ 60 = 3.1
ይህም ማለት 3 ኬክሮስ ቀሪ 6 ካልዒት ማለት ነው።
✔️ አሁን ሰርተን ያገኘነውን 3 ኬክሮስ ከ 6 ካልዒት መጀመሪያ ካገኘነው 312 ኬክሮስ ጋር እንደምረዋለን።
☸️ በአንድ ዓመት ውስጥ የተገኘ ኬክሮስ
በካልዒት እና በሣልሲት ሰርተን ያገኘነውን ኬክሮስ በመደመር የዓመቱን ኬክሮስ እናገኛለን
312 ኬክሮስ + 3 ኬክሮስ ከ6 ካልዒት = 315 ኬክሮስ ከ6 ካልዒት
በዓመት ውስጥ (በ12 ወር)
315 ኬክሮስ ከ6 ካልዒት ትርፍ አለ
6 ካልዒትን በማቆየት
315 ኬክሮስን ወደ ቀን ስንቀይረው
👉1ቀን = 60 ኬክሮስ
315 ኬክሮስ ስንት ቀን ይሆናል?
315 ÷ 60 = 5.25 = 5ቀን ከ15 ኬክሮስ
➤ በአንድ ዓመት ውስጥ 5 ቀን ከ15 ኬክሮስ ትርፍ አለ። ይኼውም የጳጕሜን ቀናት ናቸው። ይህም የዓመቱን ቀን 365 ቀን ያደርገዋል። 15 ኬክሮስ ግን ትርፍ አለ።
✦ በ1ኛው ዓመት 365ቀን ከ15 ኬክሮስ
✦ በ2ኛው ዓመት 365ቀን ከ30 ኬክሮስ
✦ በ3ኛው ዓመት 365ቀን ከ45 ኬክሮስ
✦ በ4ኛው ዓመት 365ቀን ከ60 ኬክሮስ ሲሆን ይህም 60ው ኬክሮስ 1ቀን በመሆኑ ዓመቱን 366 ቀን ያደርገዋል። በየአራት ዓመቱ ጳጕሜን 6 የምትሆን ከዚህ የተነሣ ነው።
🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼
☝ ወደ ኋላ ልመልሳችሁና ትተናት የመጣን 6 ካልዒት አለች ይህችም በየዓመቱ የምትተርፍ ናት። ከዚች ተነስተን ጳጕሜን 7 የምትሆንበትን እናገኛለን።
በየዓመቱ 6 ካልዒት የምትገኘውን ትርፍ በ100 ዓመታት ልዩነቶች ስንት ልትሆን ትችላለች? በዚህም መሠረት ጳጕሜን 7 ስትሆን እናገኛለን።
➤ በ100 ዓመት ውስጥ ስንት ካልዒት ይገኛል?
✦6 × 100 = 600 ካልዒት ይሆናል
👉 600 ካልዒት ስንት ኬክሮስ ይሆናል?
60 ካልዒት = 1 ኬክሮስ
600 ÷60 = 10 ኬክሮስ
✦በ100 ዓመት 10 ኬክሮስ ይገኛል
✦በ200 ዓመት 20 ኬክሮስ
✦በ300 ዓመት 30 ኬክሮስ
✦በ400 ዓመት 40 ኬክሮስ
✦በ500 ዓመት 50 ኬክሮስ
✦በ600 ዓመት 60 ኬክሮስ ይሆናል።
60 ኬክሮስ = 1 ቀን
ስለዚህ በ600 መቶ ዓመት ጳጕሜን 7 ቀን ትሆናለች።
➤የሰአት ፣ የኬክሮስ ፣ የደቂቃ ፣ የካልኢት ፣ የሴኮንድ ፣ የሣልሲት ፣ የራብዒት ፣ የኃምሲት ፣ የሳድሲትን ዝምድና እንደሚከተለው ነው።
✤ 1 ቀን = 24 ሰዓት = 60 ኬክሮስ
✤ 1 ኬክሮስ = 60 ካልኢት
✤ 1 ካልኢት = 60 ሣልሲት
✤ 1 ሣልሲት = 60 ራብዒት
✤ 1 ራብዒት = 60 ኃምሲት
✤ 1 ኃምሲት = 60 ሳድሲት
✤ 1 ሰአት = 2.5 ኬክሮስ or
1 ኬክሮስ = 0.4 ሰአት
✤ 1 ደቂቃ = 2.5 ካልኢት or
1 ካልኢት = 0.4 ደቂቃ
✤ 1 ሴኮንድ = 2.5 ሣልሲት or
1 ሣልሲት = 0.4 ሴኮንድ
✤ 1 ሴኮንድ = 150 ራብዒት
✤ 1 ሴኮንድ = 9000 ኃምሲት
✤ 1 ሴኮንድ = 540000 ሣድሲት
©መ/ር ማኅቶት እሸቴ 📱
ጳጕሜን 1 / 2018 ዓ.ም
🐲🐲🐲🐲🐲🐲🐲🐲 | 1 941 |
| 3 | ✝እንኳን አደረሳችሁ !
☞ሠረቀ ወርኀ ጳጉሜን ቡሩክ፤ በሰላመ እግዚአብሔር፤ ዘሎቱ ስብሐት ወአኮቴት። አሜን፡፡
ወአመ ፩፦
✝ቅድስት ጾመ ጳጉሜን (ጾመ ዮዲት)
✝አብ ዐቢይ ወክቡር፥ ጻድቅ ወንጹሕ ወድንግል፥ ማር ዮሐንስ ወልደ ዘካርያስ፥ መጥምቀ መለኮት፥ ወጸያሔ ፍኖት፥ ወነቢየ ልዑል፥ ሐዋርያ ወካህን ወሰማዕት፥ ወባሕታዊ መምህር ወመገሥጽ፥ ዘኢያደሉ ለገጽ፥ ወዘየዐቢ እምትውልደ አንስት (ተዝካረ ሙቃኄሁ)
✝አብ ዐቢይ ወክቡር፥ ጻድቅ ወንጹሕ፥ ብእሲ ሔር፥ ብእሴ እግዚአብሔር፥ ወትሩፈ ምግባር፥ ኢዮብ ተአጋሢ፥ ወልደ ዛራ ወራጉኤል፥ ወነቢየ አምላክ ልዑል፥ ዘኢነበበ ከንቶ በጊዜ ተጽናስ ወደዌ፥ ወዘተመዝገነ በኀበ እግዚኡ (ተዝካረ ደዌሁ ወሕማሙ)
❖ ወበዓለ ቅዱሳን አበው፦
✝አብ ዐቢይ ወክቡር፥ ጻድቅ ወንጹሕ ወድንግል፥ ኃያል ወመስተጋድል፥ ማር ዑቲኮስ ቡሩክ፥ ሐዋርያሁ ወሰማዕቱ ለእግዚእነ ኢየሱስ ክርስቶስ፥ ዘሎቱ ስብሐት ወአኮቴት፥ ፩ዱ እም፸ወ፪ቱ እርድእት (ረድኡ ለቅዱስ ዮሐንስ ወንጌላዊ)
✝አብ ዐቢይ ወክቡር፥ ጻድቅ ወንጹሕ ወድንግል፥ ኃያል ወመስተጋድል፥ ማር አባ ብሶይ ቀሲስ፥ ሰማዕት ቡሩክ፥ ወመናኔ ዝንቱ ዓለም፥ እኁሁ ለአባ ሖር ሰማዕት፥ ዘሀገረ አንጾኪያ (ዘፈጸመ ገድሎ በምድረ ግብጽ)
✝ክቡራን ወዐቢያን፥ ጻድቃን ንጹሐን፥ ወሰማዕታት መስተጋድላን (ሰብአ ቤቱ ለአባ ብሶይ)
✝አብ ዐቢይ ወክቡር፥ ጻድቅ ወንጹሕ ወድንግል፥ አባ ጳኩሚስ ገዳማዊ፥ አበ ድርገተ መንፈስ፥ ወሱታፌ መንፈሳውያን ሐዋርያት፥ ጽሙድ ወመስተጋድል፥ አበ መነኮሳት ጻድቃን፥ ብእሲ ሔር፥ ወትሩፈ ምግባር፥ ወወላዴ አእላፍ ቅዱሳን (ዘሠርዓ ሥርዓታተ ሠናያተ ለመነኮሳት)
°ቅድስት ገዳሙ ዳውናስ/ቲቤይድ፥ ወቅዱሳን ውሉዱ መነኮሳት (አእላፋት)
✝አብ ዐቢይ ወክቡር፥ ጻድቅ ወንጹሕ ወድንግል፥ ጽሙድ ወመስተጋድል፥ ወብእሴ እግዚአብሔር፥ ማር አባ ሰራብዮን ገዳማዊ፥ ብእሲ ሔር፥ ወትሩፈ ምግባር፥ ወሊቀ ምኔት በላዕለ ፼ መነኮሳት ጻድቃን (ረድኡ ለማር እንጦንዮስ)
°ቅድስት ገዳሙ፥ ወቅዱሳን ውሉዱ መነኮሳት ጻድቃን
❖ ወስብሐት ለእግዚአብሔር፤
ኪያነኒ ይምሐረነ በጸሎቶሙ።
ወበረከቶሙ ይብጽሐነ፤ ለዓለመ ዓለም አሜን፡፡ | 1 785 |
| 4 | ✨ በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን። ✨
🕊️ እንዴት ናችሁ የልዑል እግዚአብሔር ቤተሰቦች? 🕊️ በቅድሚያ ወደ መንፈሳዊ ቻናላችን በሰላም መጣችሁ!
ይህ ቻናል በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን መጽሐፍ ቅዱስ መሠረት፣ ለሕይወታችን ስንቅና መመሪያ የሚሆኑ አጫጭር የመጽሐፍ ቅዱስ ጥቅሶችን በየዕለቱ የምናደርስበት መንፈሳዊ ማዕድ ነው።
╔═══════════════════════╗ 📜 የዕለቱ የወንጌል ቃል 📜 ╚═══════════════════════╝
"እግዚአብሔር ብርሃኔና መድኃኒቴ ነው፤ የሚያስፈራኝ ማን ነው? እግዚአብሔር የሕይወቴ መታመኛዋ ነው፤ የሚያስደነግጠኝ ማን ነው?" — መዝሙረ ዳዊት ፳፮፥፩ (26:1)
https://t.me/Yewongel_Birhan
🔔 ቃሉን ለሌሎችም በማጋራት (Share) የበረከቱ ተሳታፊ ይሁኑ!
➾Join አድርጉ 👇
https://t.me/Yewongel_Birhan | 1 665 |
| 5 | ✨✨✨✨✨✨✨✨
የዓመቱ የመጨረሻ መዝሙር እና ግጻዌ
✨✨✨✨✨✨✨✨
🎓🎓
[ጳጒሜን ለእመ ኮነ በእሑድ...]
🎓መዝሙር፦
ከመ አንተ መብረቅ ዘይወጽእ እምጽባሕ፤ ወያስተርኢ እስከ ዓረብ፤ ከማሁ ምጽአቱ ለወልደ እግዚአብሔር፤ ምስለ ኃይለ ሰማያት፤ በንጥረ መባርቅት፤ ከማሁ ምጽአቱ ለወልደ እግዚአብሔር፤ ምስለ አዕላፍ መላእክት፤ ወኵሎሙ ሊቃነ መላእክት፤ ከማሁ ምጽአቱ ለወልደ እግዚአብሔር፤ አክሊለ አክሊላት፤ ዲበ ርእሶሙ ለካህናት።
🎓 የዕለቱ መልእክታት፣ ምስባክና ወንጌል፦🎓
🎓መልእክታት:-
➊. ፩ኛ ቆሮንቶስ ፩ : ፩ - ፲ (1:1-10)
➋. ፪ኛ ጴጥሮስ ፫ : ፲ - ፍጻሜ (3:10-ፍጻሜ)
➌. የሐዋ/ሥራ ፱ : ፩ - ፲ (9:1-10)
🎓+ ምስባክ ዘቅዳሴ
እግዚአብሔርሰ ገሐደ ይመጽእ።
ወአምላክነሂ ኢያረምም።
እሳት ይነድድ ቅድሜሁ።
ትርጉም:-
እግዚአብሔር ግልጽ ሆኖ ይመጣል። ዝምም አይልም።
እሳት በፊቱ ይነድዳል።
(መዝ ፵፱ : ፪ /49 : 2)
🎓 ወንጌል ዘቅዳሴ
የሉቃስ ወንጌል ፲፯ : ፲፩ - ፍጻሜ /17:11-ፍጻሜ
፲፩
ወደ ኢየሩሳሌምም ሲሔድ በገሊላና በሠማርያ መካከል አለፈ።
፲፪
ወደ አንዲት መንደርም ሲገባ በሩቅ የቆሙት አሥር ለምጻሞች ተገናኙት፤
፲፫
እነርሱም እየጮኹ። ኢየሱስ ሆይ፥ አቤቱ፥ ማረን አሉ።
፲፬
ዐይቶም። ሒዱ፥ ራሳችሁን ለካህናት ዐሳዩ አላቸው።
፲፭
እነሆም፥ ሲሔዱ ነጹ። ከእነርሱም አንዱ እንደ ተፈወሰ ባየ ጊዜ በታላቅ ድምጽ እግዚአብሔርን እያከበረ ተመለሰ፥
፲፮
እያመሰገነውም በእግሩ ፊት በግንባሩ ወደቀ፤ እርሱም ሣምራዊ ነበረ።
፲፯
ኢየሱስም መልሶ። አሥሩ አልነጹምን? ዘጠኙስ ወዴት አሉ?
፲፰
ከዚህ ከልዩ ወገን በቀር እግዚአብሔርን ሊያከብሩ የተመለሱ አልተገኙም አለ።
፲፱
እርሱንም። ተነሣና ሒድ፤ እምነትህ አድኖሃል አለው።
፳
ፈሪሳውያንም። የእግዚአብሔር መንግሥት መቼ ትመጣለች ብለው ቢጠይቁት፥ መልሶ። የእግዚአብሔር መንግሥት በመጠባበቅ አትመጣም፤
፳፩
ደግሞም። እነኋት በዚህ ወይም። እነኋት በዚያ አይሉአትም። እነሆ፥ የእግዚአብሔር መንግሥት በመካከላችሁ ናትና አላቸው።
፳፪
ለደቀ መዛሙርቱም እንዲህ አለ። ከሰው ልጅ ቀኖች አንዱን ልታዩ የምትመኙበት ወራት ይመጣል አታዩትምም።
፳፫
እነርሱም። እነሆ በዚህ፥ ወይም። እነሆ በዚያ ይሉአችኋል፤ አትሒዱ አትከተሉአቸውም።
፳፬
መብረቅ በርቆ ከሰማይ በታች ካለ ከአንድ አገር ከሰማይ በታች ወዳለው ወደ ሌላ አገር እንደሚያበራ፥ የሰው ልጅ በቀኑ እንዲህ
ይሆናል።
፳፭
አስቀድሞ ግን ብዙ መከራ እንዲቀበል ከዚህም ትውልድ እንዲጣል ይገባዋል።
፳፮
በኖኅ ዘመንም እንደ ሆነ፥ በሰው ልጅ ዘመን ደግሞ እንዲሁ ይሆናል።
፳፯
ኖኅ ወደ መርከብ እስከ ገባበት ቀን ድረስ፥ ይበሉና ይጠጡ ያገቡና ይጋቡም ነበር፥ የጥፋት ውኃም መጣ ሁሉንም አጠፋ።
፳፰
እንዲሁ በሎጥ ዘመን እንደ ሆነ፤ ይበሉ ይጠጡም ይገዙም ይሸጡም ይተክሉም ቤትም ይሠሩ ነበር፤
፳፱
ሎጥ ከሰዶም በወጣበት ቀን ግን ከሰማይ እሳትና ዲን ዘነበ ሁሉንም አጠፋ።
፴
የሰው ልጅ በሚገለጥበት ቀን እንዲሁ ይሆናል።
፴፩
በዚያም ቀን በሰገነት ያለ በቤቱ ያለውን ዕቃ ሊወስድ አይውረድ፥ እንዲሁም በእርሻ ያለ ወደ ኋላው አይመለስ።
፴፪
የሎጥን ሚስት አስቡአት።
፴፫
ነፍሱን ሊያድን የሚፈልግ ሁሉ ያጠፋታል፥ ነፍሱንም የሚያጠፋ ሁሉ በሕይወት ይጠብቃታል።
፴፬
እላችኋለሁ፥ በዚያች ሌሊት ሁለት ሰዎች በአንድ አልጋ ይሆናሉ፤ አንዱ ይወሰዳል ሁለተኛውም ይቀራል።
፴፭
ሁለት ሴቶች በአንድ ወፍጮ ይፈጫሉ፤ አንዲቱ ትወሰዳለች ሁለተኛይቱም ትቀራለች።
፴፮
ሁለት ሰዎች በእርሻ ይሆናሉ፤ አንዱ ይወሰዳል ሁለተኛውም ይቀራል።
፴፯
መልሰውም። ጌታ ሆይ፥ ወዴት ነው? አሉት። እርሱም። ሥጋ ወዳለበት በዚያ አሞራዎች ይሰበሰባሉ አላቸው።
+ ቅዳሴ ~ ያዕቆብ ዘሥሩግ (ተንሥኡ) በግዕዝ ዜማ
https://t.me/EOTCBooks1
🐲🐲🐲🐲🐲🐲🐲🐲 | 1 687 |
| 6 | No text... | 1 462 |
| 7 | ✍ Deacon Yordanos Abebe:
፨፨፨ በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን በዚችም ዕለት የእናታችን የቅድስት ዜና ማርያም አመታዊ የዕረፍት በዓሏ መታሰቢያ ነው ፨፨፨
✝✞✝ ቅድስት ዜና ማርያም ✝✞✝
፨ በ11መቶ ክፍለ ዘመን በቅዱስ ላሊበላ ዘመነ መንግሥት ግንቦት 30 ቀን በጎጃም ክፍለ ሀገር ተወለደች። የአባቷ ስም ገብረ ክርስቶስ የእናቷ ስም አመተ ማርያም ይባላሉ። እጅግ እግዚአብሔርን የሚፈሩ፡ ቅዲስ ጋብቻቸውን በንጽሕና የሚጠብቁ፡ ለሰው የሚራሩ ደጋግ ሰዎች ነበሩ። እንዲህ ባለ መልካም ግብር ከኖሩ በኀላ በፈቃደ እግዚአብሔር 3 ወንዶች ልጆች እናት አንዲት ሴት ልጅ ወለዱ። ይህችም ሴት ልጅ ተወዳጇ እናታችን ቅድስት ዜና ማርያም ናት።
፨ ቅድስት ዜና ማርያም እናት እና አባቷን እያገለገለች፡ ፈርሐ እግዚአብሔን፡ በጎ ምግባርን ከወለጆቿ እየተማረች አደገች። ለአቅመ ሔዋንም በደረሰች ጊዜ ወላጆቿ ለአንድ ወጣት አጯት። ታላቅ ግብዣ ተደረጎ በተክሊል ተዳረች። በዚያው ወራት ግን የዜና ማርያም እናት አመተ ማርያም አምስተኛ ልጅ ወልዳ ተኝታ ሳለች በአካባቢው ሕማመ ብድብድ (ተላላፊ በሽታ) በመነሳቱ የዜና ማርያም እናት ታማ ነበር፡ በመጨረሻም ከዚህ ኃላፊ ዓለም አረፈች።
፨ ከዚህ በኋላ የታመመውን ወንድሟንና ሌሎቹንም በመያዝ ከተላላፊው በሽታ ለመትረፍ ሲሉ አካባቢውን ለቀው ወደ በረሃ ወጡ። በዚያም ሌሊት የዱር አራዊት መጥተው ከበቧቸው ሁሉንም ሊበሏቸው ሞከሩ እናታችን ቅድስት ዜና ማርያም ስመ እግዚአብሔርን ስትጠራ አራዊቱ ወደኋላ በመሸሽ ከአካባቢው ራቁ። እርሷም ከክፉ ሁሉ የጠበቃቸውን፡ ከአራዊት መበላት የሰወራቸውን እግዚአብሔርን አመሰገነች። በነጋም ጊዜ የታመመውን ወንድሟን እና ሌሎችን በመያዝ መንገድን ቀጠሉ አንዲት ባዶ ቤት አግኝተው ከእርሷ ተጠጉ። በፀሐዩ ንዳድና ታናሽ ወንድሟን በማዘል እጅግ ስለደከመች ከባድ እንቅልፍ ጣላት። ጠዋት ስትነሳ ግን የታመመው ወንድሟ ከአጠገቧ አላገኘችውም ሌሊት የዱር አራዊት በልተውታልና። አጅም አዘነች የእግዚአብሔር ፈቃድ ነው ብላ አራሷን አፅናናች የወንድሟን ተረፈ ሥጋ አጠራቅሟ ቀበረች። በመቀጠልም በአካባቢው ካለ ገዳም ሔዳ ምንኩስናን ተቀበለች።
፨ ከዚህ በኋላ ባሏ አባቷን ሚስቴን አምጣ እያለ ስለጨቀጨቀው ከብዙ ልፋት እና ድካም ፈልጎ አገኛት ወደ ሀገሯም ወሰዳት። በዚያም ወደ ጉባኤ ቀርባ ለምን ወደ ገዳመ እንደሄደች እና ባሏን አንደከዳች ተጠየቀች። እርሷም እግዚአብሔር ከብዙ መከራ አድኖኛል እና እራሴን ለእግዚአብሔር ሰጥቻለሁ አለች። የጉባኤው ተሰብሳቢ በሏ ሀብቷን ወርሶ እንዲያሰናብታት ፈረዱ። እርሷም በዚህ ነገር በመስማማት የነበራትን ላም እና በሮች አስረከበች።
፨ ከዚህ በኋላ በአባቷ ቤት ለአንድ ዓመት ያህል በመቀመጥ የእናቷን ተዝካር አውጥታ ወደ ገዳሙ ተመለሰች በዛም ለጥቂት አመታት የተለያዩ ገድላትን ስትፈጽም ከቆየች በኋሏ ከነፍስ አባቷ ባሕታዊ አባ ገብረ መስቀል ጋር ወደ ጎንደር ሀገረ ስብከት ልዩ ስሙ እንፍራንዝ (ጣራ ገዳም) አካባቢ ዋሻ እንድርያስ በተባለው ለ25 ዓመት በብሕትውና ኖረች። አሁንም ድረስ በዚያ ዋሻ እናታችን ዜና ማርያም በፀሎት ጊዜዋ እንቅልፍ እንዳይጥላት ስትጠቀምበት የነበረ ዘንግ ፣ የምተቆምበት ዙሪያውን በገመድ የታሰረ የተቦረቦረ ግንድ አሁንም ድረስ ተአምር እየሰሩ ይገኛሉ። ከዚህም በመቀጠል ዛሬ ዜና ማርያም ተብሎ ወደ ሚጠራው ዋሻ ሔደች በዚያም በጾምና በጸሎት በልዩ ልዩ ተጋድሎ እስከ እለተ እረፍቷ ድረስ በዚያ ኖራለች።
+++ የገድል ዓይነቶች +++
፨ በየሰዓቱ ከ 100-300 ትሰግድ ነበር
፨ ሁለት ቀን እየፆመች በሶስተኛ ቀን ጥቂት ጥሬ ቀምሳ ሳምንቱን ታሳልፈው ነበር
፨ 150ን መዝሙረ ዳዊት እና ወንጌል በየቀኑ ትጸልይ ነበር
፨ በብሕትውና ወራት ማር፣ ቅቤን፣ ወተትን ፈጽሞ አትቀምስም ነበር
፨ የጌታችን መከራ መስቀል እና ስትየ ሐሞት በማሰብ በየሳምንቱ ዓርብ ዓርብ ኮሶ የሚባል ቅጠል እየበጠበጠች ከቅል ውስጥ ከሚገኘው መራራ ፍሬ ጋር በማዋሐድ ትጠጣ ነበር
፨ ከጸሎት እና ከስግደት በምታርፍበት ጊዜ አትክልት በመትከል እና በመኮትኮት ጊዜዋን ታሳልፍ ነበር
፨ የጌታችንን ግርፋቱን በማሰብ 100 ጊዜ ጀርባዋን ስለምትገረፍ እና ደም ስለሚፈሳት ጀርባዋ ይቆስል እና ይተላ ነበር።
+++ ተአምራት +++
፨ ዓይናቸውን በተለያየ በሽታ የታመሙ ሰውዎች ሁሉ ከህመማቸው ተፈውሰዋል
፨ የራስ በሽታ ( የራስ ፍልጠት፣ ጭንቀት፣ ማዞር) የታመሙ ጸበሉን በመቀባት ድነዋል፡፡
፨ ጸበሉን በመጠመቅ፤ የጻድቋን ተአምር በማዘል፤ ስዕለት በመሳል መካኖች ወላድ ሆነዋል። ሌሎች በየቀኑ ብዙ ተአምራትን እናታችን ቅድስት ዜና ማርያም ታደርጋለች።
+++ ቃል ኪዳን +++
ቅድስት ዜና ማርያም ከዚህ ዓለም የምታርፍበት ጊዜ እንደደረሰ በመንፈስ ቅዱስ በአወቀች ጊዜ ከታላቅ ዛፍ ወጥታ ስትፀልይ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከእናቱ ከቅድስት ድንግል ማርያምና ከእልፍ አእላፋት ቅዱሳን መላእክት ጋር፣ ከነቢያት፣ ከሐዋርያት፣ ከሰማዕታት፣ ከጻድቃን፣ ከደናግል መነኮሳት ጋር በመሆን ተገልጾ ከአረጋጋት በኋላ ቃል ኪዳንን ሰጧታል።
፨ በፀሎትሽ ያመነውን ኃጢአቱን ይቅር እለዋለሁ
፨ በስምሽ የተራበውን ያበላ በመንግስተ ሰማያት ኅብስተ ሕይወት አበላዋለሁ፤ የተጠማውን ያጠጣ ጽዋዓ ሕይወትን አጠጣዋለሁ
፨ መጽሐፈ ገድልሽን የጻፈውን፡ ያጻፈውን፡ የሰማውን፡ ያሰማውን ስሙን በዓምደ ወርቅ እጽፈዋለሁ
፨ ከሕፃንነትሽ እስከ አሁን ድረስ ስለ እኔ ብለሽ ብዙ መከራ ተቀብለሻል፦ ደጅሽን የረገጠ የሦስት ጭነት ጤፍ ያህል ነፍሳትን እንደሚምርላት፡ እንዲሁም ከሲዖል ነፍሳትን እንደሚያወጣላት ጌታችን በማይታበል ቃሉ ቃልኪዳን ገብቶላታል። እንዲሁም ከሲዖል ነፍሳትን እንደሚያወጣላት፡፡
+++ ገዳሟ እና መገኛው+++
፨ የቅድስት ዜና ማርያም መካነ መቃብሯ ( ጸበሏ) በደቡብ ጎንደር ሀገረ ስብከት ከም ከም ወረዳ ይገኛል ቦታውም አዲስ ዘመን ከተማ 20 ኪ.ሜ ርቆ የሚገኝ ሲሆን ከከተማው በስተሰሜን በኩል "ደሪጣ" ቀበሌ ገበሬ ማህበር ውስጥ ይገኛል።
"ደሪጣ"
ሸክላ ማርያም ተብላ ትጠራ የነበረችው ቦታ ስያሜው ተቀይሮ ደሪጣ ዜና ማርያም ዋሻ (ገዳም) ተብሎ እስከ አሁን ድረስ እየተጠራ ይገኛል፡፡ ይህን ስያሜ ያገኘውም በቅድስት ዜና ማርያም ገድል ውስጥ " ወትሰቲ ሲካር (ኮሶ) ደሪፃ" የሚል ቃል ይገኛል። ይህም ማለት ኮሶ የተባለውን እንጨት (ቅጠል) ቀጥቅጣ (አልማ) ከቅል ውስጥ ከሚገኘው ፍሬ ጋር በማደባለቅ ትጠጣለች ማለት ነው። ስለዚህ ቦታው "ደሪፃ" ተብሎ ተሰየመ በማለት በአካባቢው የሚገኙ አባቶች ይናገራሉ። በመጨረሻም ተጋድሎዋን በመፈጸም በዚሁ በተቀደሰ ስፍራ ነሐሴ 30 ቀን ከዚህ አለም ድካም ዐርፋለች። የእናታችን የቅድስት ዜና ማርያም በረከቷ ቸርነቷ ይደርብን። አሜንን!!
+++ ወስብሐት ለእግዚአብሔር ኪያነኒ ይምሐረነ በጸሎታ፡፡ ወበረከታ ለቅድስት ዜና ማርያም የሀሉ ምስሌነ ለዓለመ ዓለም አሜን!!! +++
(በዲ/ያዕቆብ ሙሉጌታ / https://t.me/EOTCBooks1 ዝክረ ቅዱሳን) | 1 778 |
| 8 | የታሰሩት 24 ቀበሌ ገቢዎች አካባቢ በሚገኘው ፖሊስ ጣቢያ ነው።
በቀሲስ መንግሥቱ ጎበዜ (ዶ/ር) የተጻፈው "የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የሦስት ሺሕ ዘመናት የታሪክ ጉዞ" የተሰኘው ዐዲስ መጽሐፍ በመሸጣቸው ምክንያት፣ መጽሐፉ በፖሊስ ተወርሶባቸው ያለአግባብ የታሰሩት እነ አብርሃም ኃይሉ ያሉበት ቦታ ፒያሳ የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን ዋና መሥሪያ ቤት በሚገኘው እስር ቤት አይደለም። በአሁኑ ወቅት የታሰሩት 24 ቀበሌ ገቢዎች አካባቢ በሚገኘው ፖሊስ ጣቢያ ስለሆነ፣ እየሄድን እነዚህን የግፍ እስረኞች እንጠይቃቸው።
በአሁኑ ወቅት "ዕውቀትን በዕውቀት መሞገት" የሚለው መርሕ አፈር በልቷል። በመጽሐፉ ውስጥ ባሉ ሐሳቦች ላይ ተገቢውን የጽሑፍ ሒስ በማቅረብ መከራከር ሲገባ፣ መጽሐፉ እንዳይነበብ በፖሊስ ኃይል ማስለቀም፣ ማገድና መጻሕፍት አከፋፋዮችን ማሰር ፈጽሞ የማይገባ ድርጊት ነው። | 1 657 |
| 9 | https://c.org/rLs8kKHvwp | 1 944 |
| 10 | No text... | 2 096 |
| 11 | ጊዜው የዓመት በዓል ዝግጅት ነው። መምህሩ እሥር ላይ ናቸው።
አባታቸው የሞቱባቸው 4ወምንድምና እህቶቻቸውን ያስተዳድራሉ። ባለቤታቸውና ልጃቸውም ሌላ ተስፋ የላቸውም። ይኼን ቤተሰብ ካልረዳን ትብብራችን ወዴት አለ?
ቀሲስ ሞገስን፣ ባለቤታቸውንና ቤተሰባቸውን ለመደገፍ የቀረበ የእርዳታ ጥሪ
መምህር ሞገስ ሁን ያለው ከቅኔ መጸሐፍና አብነት ሙያቸው በተጨማሪ ጥሩ የሥነ ጽሑፍ አዋቂ ናቸው።
ውዳሴ ማርያምን በግጥም መልክ የተረጎሙ ሊቅ ናቸው።
በአሁኑ ወቅት በቁጥጥር ሥር ውለው ከየካ አባዶ ፖሊስ ጣቢያ ወደ ሜክሲኮ ፌደራል ፖሊስ እስር ቤት ተዛውረዋል። በዚህም ምክንያት፣ ሙሉ በሙሉ በእሳቸው ገቢ ይተዳደር የነበረው ቤተሰባቸው ለከፍተኛ ምጣኔ ሀብታዊና ማኅበራዊ ችግር ተጋልጠዋል። ስለሆነም፣ ይህንን የክፉ ቀን የቤተሰብ ችግር በጋራ እንድንወጣው አስቸኳይ ድጋፍ እንድናደርግ ወገናዊ ጥሪያችንን እናቀርባለን።
🔻ፈቃደኛ ለሆናችሁ ወገኖች የገንዘብ ድጋፍ ማድረጊያ መንገዶች፦
የቀሲስ ሞገስ ባለቤታቸው የባንክ ስም እና የሒሳብ ቁጥር
ዓባይ ባንክ፦ 1149112384641023
አዋሽ ባንክ፦ 013470853026400
የባለቤታቸው የአካውንት ስም፦ Huluager Sisay Akele
ዛሬ በችግር ላይ ለወደቁ ወገኖቻችን የምናደርገው ድጋፍ ለካህኑና ለቤተሰባቸው ትልቅ መደገፊያ ነው። እያንዳንዷ የምታደርጓት ድጋፍ ለቤተሰቡ ተስፋ፣ ለሕጋዊ ሂደቱም ትልቅ አቅም ትሆናለች።
እግዚአብሔር በቸርነቱ ይክፈልልን!
መምህር ኤፍሬም ተስፋዬ ገጽ የተወሰደ።
https://www.facebook.com/share/1MTyJy3ECe/ | 2 251 |
| 12 | በምስራቅ ወለጋ ዞን ጊዳ አያና ወረዳ ውስጥ ፦
በጣም አዝናለሁ ግን ጥቃቱን ሕዝብ ማወቅ አለበት። እነዚህ ሟቾች የሞቱት የተገደሉት የኛን ሞት ነው። ከቦታዉ ባንኖር እንጂ እኛም ያው ነን። አንድም አባት አንድምን ጳጳስ ኃላፊዎች አስተዳደሮች ባላየ ባልሰማ አልፈውታል። ስለዚህ ከፈጻሚዎቹ ምድብ ናቸው። እስከመቼ ነው ነፍስ ይማር እየተባለ የምንኖረው?
እስከመቸ ነውስ ማንነት ተኮር ግድያ የሚያቆመው?
በመከላከያ የተቃጠሉ ቤተክርስቲያናት
1 ሌሊ ተክለሃይማኖት ቤተክርስትያን
2 ዋጃ አቦ ቤተክርስትያን
3 አንዶዴ ቅድስት ስላሴ ቤተክርስትያን
6 መንደር 22 መድሃኒአለም ቤተክርስትያን
7 መንደር 3 ቅድስት ማርያም ቤተክርስትያን
8 መንደር 3 ግንዳሳው ሚካኤል
ቤተክርስትያን ሙሉበሙሉ ወድመዋል
የተገደሉ
1 ቆሞስ አባሆይ ታደሰ መኮነን
የቅድስት ስላሴ የቤተክርስትያኑ
አስተዳዳሪ ዕድሜ 61
2 ቄስ አድስ
3 ቄስ አማረ ሲሳይ ዕድሜ 58
4 እማሆይ ፅጌ ማርያም ዕድሜ 57
5 ዳቆን ፍስሃ አለሙ ዕድሜ 29
6 እማሆይ ወለተ ስላሴ ዕድሜ 66
7 ቀናው አባተ....54
8 አባበለጠ መኮነን.....71
9 ተስፌ በላይ.......49
10 ተመስጌን አባይ......
11 አባአዳሙ..........75
12 አባበሪሁን ሲሳይ.......68
13 ወጣት መቅደስ አበበ.......21
14 ሸጋው አባተ......
15 አባ አበባው አያሌው...........69
16 ሲሳይ ተመቸው............55
በዚሁ ወረዳ መንደር ሦስት ቀበሌ
17 እማሆይ ወለተ ሰንበት......71
18 አባ አየለ ባዩ.......64
19 ታሪኩ ገንዘብ.......51
20 ንጉስ ከበደ....
21 አለሙ ገረመው.....41
22 ተክለሃይለማርያም......
(ትግራዋይ)
23 ፅጌ ተካ.....(ትግራዋይ)
24 አባጥጋቡ
25 ብርሃን ገብሩ...(ትግራዋይ)
26 ይታይ አለሙ......45
27 ደሳለኝ በላይ......
28 ብርሃን በቀለ......47
29 ሐጎስ ኪዳነ......(ትግራዋይ)
30 በላይ ታደሰ.......
31 ካሰይ ብስራት......(ትግራዋይ) እናቱን ፣ ሚስቱን ፣ ልጆችን ጨምሮ
የተረሸኑ
32 አባ ወልደ ፃድቅ.....(ትግራዋይ)
33 እማሆይ ወለተ መካኤል...59
በዚሁ ወረዳ መደር 22፦
34 አባሆይ አየለ አረጋ......85
35 እማሆይ እስከዳር ገላው..63
36 ብረሃን ገላው.....
37 በላይነሺ ረጋ..........41
38 ካሳይ ስጋት.....
39 ዳቆን ጎራው......31
በዚሁ ወረዳ መንደር22 ቀበሌ ልዩ ቦታው በጭበጭ ላይ፦
40 ጎቶም ነጋ....
41 ሹመት.........29
42 ማናየ ታደሰ.........49
43 እማሆይ አስካለማርያም......
44 አባገበየሁ ታረቀኝ.........74
በዚሁ ወረዳ አንዶዴ ቀበሌ ልዩ ቦታዋ አሊ ላይ፦
45 ሸጋው አወቀ......45
46 የኔሰው ሸጋው........
47 አበረ ገበየሁ.........
48 እሚያምረው አያሌው......
49 ሞሴ በላይ.......... 42
50 መኳንት አንማው......
51 ታመነ ቀሬ.....
52 ጎጃም የኔአለም......38
53 ሞገስ ውለታው.... 49
54 ይደነቅ ባይሌ....25
55 ካሳየ ጌቴ....50
56 ተስፋየ ዋሴ....48
57 ዘመን ጌታነህ....
58 ፈንቴ መንግሥቴ .....58
59 ተስፋዬ ወጋየ.....52
60 መቅደስ ታምሩ.....23
61 ደጀን መሰለ.......48
እነዚህ ኹሉም በሰው እጅ ሕይወታቸወን የተነጠቁ ናቸው።
መንግሥትን አምነው አርሰው ቆፍረው ነግደው ለመንግሥት ግብር እየገበሩ የሚኖሩ ከምንም ጋር ግንኙነት የሌላቸው ነዋሪዎች ናቸው።
ኅሊናችሁ ላይ ተኝታችኋል እንዴ? | 2 124 |
| 13 | ኦርቶዶክሳዊነት_እና_የሰይጣን_መንግስት.pdf | 2 165 |
| 14 | ጥንተ አሚን ዘኢትዮጵያ@beteketinn.pdf | 2 411 |
| 15 | መጻሕፍትን_ለማያነቡ_ኦርቶዶክሳውያን_የተሰጠ_ተግሣፅበቅዱስ_ዮሐንስ_አፈወርቅ_.pdf | 2 397 |
| 16 | https://ye-buna.com/ethioyared?ref=product_detail&product=6a0bf611b1f89_ethioyared | 2 479 |
| 17 | https://ye-buna.com/ethioyared?ref=product_detail&product=6a0b158e110f5_ethioyared | 3 |
| 18 | https://ye-buna.com/ethioyared?ref=product_detail&product=6a0976a96a03f_ethioyared | 2 379 |
| 19 | መዳልወ አልባብ የአቋቋም ምልክት.pdf | 3 192 |
| 20 | No text... | 2 609 |
