en
Feedback
የጥበብ ማዕድ

የጥበብ ማዕድ

Open in Telegram

ዝም ብለህ ተቀላቀል!

Show more

📈 Analytical overview of Telegram channel የጥበብ ማዕድ

Channel የጥበብ ማዕድ (@yetbebmead_ab) in the Amharic language segment is an active participant. Currently, the community unites 15 890 subscribers, ranking 5 407 in the Religion & Spirituality category and 2 116 in the Ethiopia region.

📊 Audience metrics and dynamics

Since its creation on невідомо, the project has demonstrated rapid growth, gathering an audience of 15 890 subscribers.

According to the latest data from 24 June, 2026, the channel demonstrates stable activity. Although there has been a change in the number of participants by 628 over the last 30 days and by 31 over the last 24 hours, overall reach remains high.

  • Verification status: Not verified
  • Engagement rate (ER): The average audience engagement rate is 2.61%. Within the first 24 hours after publication, content typically collects 2.09% reactions from the total number of subscribers.
  • Post reach: On average, each post receives 415 views. Within the first day, a publication typically gains 332 views.
  • Reactions and interaction: The audience actively supports content: the average number of reactions per post is 9.

📝 Description and content policy

The author describes the resource as a platform for expressing subjective opinions:
ዝም ብለህ ተቀላቀል!

Thanks to the high frequency of updates (latest data received on 25 June, 2026), the channel maintains relevance and a high level of publication reach. Analytics show that the audience actively interacts with content, making it an important point of influence in the Religion & Spirituality category.

15 890
Subscribers
+3124 hours
+1507 days
+62830 days
Posts Archive
🏆 ለ ኦርቶዶክሳዊያን ብቻ የተከፈቱ በኢትዮጵያ የመጀመርያዎቹ ኦርቶዶክሳዊ ቻናሎች ❤️❤️❤️
🏆 ለ ኦርቶዶክሳዊያን ብቻ የተከፈቱ በኢትዮጵያ የመጀመርያዎቹ ኦርቶዶክሳዊ ቻናሎች ❤️❤️❤️

ያስቡኝ ይሆን እያልክ አታስባቸው! መጽዋች በሌለበት መታወስን እየለመንክ እኮ ነው።

እወድሻለሁ  አልኳት <<አሁን ነው ትንሽ ያገገምኩት ፤ መሳቅ የጀመርኩት ፤ ብቻዬን መሆንን የለመድኩት ። አሁን ነው እንቅልፍ ሳልቸገር መተኛት የጀመርኩት ። አሁን ነው ሰበብ እያደ
እወድሻለሁ  አልኳት <<አሁን ነው ትንሽ ያገገምኩት ፤ መሳቅ የጀመርኩት ፤ ብቻዬን መሆንን የለመድኩት ። አሁን ነው እንቅልፍ ሳልቸገር መተኛት የጀመርኩት ። አሁን ነው ሰበብ እያደረግኩ ፣ የሆነውን እያስታወስኩ መነፋረቅ ያቆምኩት ። >> እኔ እኮ.. ..አቋረጠችኝ ለቁምነገር ነው የምፈልግሽ ...አከብርሻለሁ ... እወድሻለሁ ...እታመንሻለሁ... አልከዳሽም ....ልትለኝ ነው አይደል ? ሁሉንም ተብያለሁ ተወኝ ትንሽ ብቻዬን መሆንን ላጣጥመው ፤ ትንሽ ማገገሜ ይታወቀኝ ...ተወኝ >> እሺ ...ግን እውነቴን ነው ብሎ እውነተኛም  አለ ፣ ኋላ ማየት ኋላ ያስቀርሻል ፣ ህይወት ወደፊትም ነው .....አሁንም አቋረጠቺኝ    <እሱንም ተብያለሁ......>>  እሺ ..አልኳት ከትላንቱ ጋ የተጣበቀን ሰው ነገን ማሳየት ከባድ ነው   © Adhanom Mitiku

: ለወደዱት መድከም             ለወደዱን ስንክል የቱን እንከተል         የቱ ነው ትክክል?!      አቡ

<< ሰብሊ ለምንድነው ብቻሽን መቀመጥ የምትወጂ ? ለምን ከሰው አትቀላቀይም ? >> << ተወኝማ አቤላ የኔን ነገር እያወከው ... የትኛው ፈላስፋ ነው ግን " ሰዎችን አልጠላቸውም ግን አጠገቤ ሲርቁ ምቾት ይሰማኛል " ያለው ? የኔም ህይወት ከሱ ጋር ተዛማጅ ነው ። ምናልባት እኔ ያሳለፍኩትን ህይወት አሳልፎ ይሆን ?>> << እንዶም አገኘሁሽ ! ያሳለፍሺውን ህይወት ጥቂቱን አሁን ንገሪኛ,,,,,, ካልሺኝ ፈላስፋው ጋር ህይወትሽ ተዛማጅ መሆኑን እንድነግርሽ >> << ተው ዛሬ አይሆንም >> << ነገሩን ራስሽ ነሽ ያመጣሺው so ቀጥይ ...>> << ኡፍፍፍ አቤላ አንተ ደሞ ድርቅ ካልክ አትመለስም >> << እነግርሃለው ካልሺኝ ስንት ቀኑ ዛሬ ተይዘሻል >> << እሺ ይሁና ግን ለዕንባህ ሶፍት ያዝ " ሰው ጋ ከመኖር ለብቻ መሆን ምቾት ይሰጣል " ያልኩበት ምክኒያት የዛሬ አምስት አመት በ Acounting ትምህርቴን ለመማር አሰብኩና እናቴና አባቴ እኔን ለማስተማር አቅም ስለሌላቸው አብሮ አደግ ጓደኛዬ ቤት የቤት ሰራተኛ ሁኜ በ weekend program ለመማር ወስኜ ተመዘገብኩ ። መማር እና መስራት እንደጀመርኩ ሰሞን ሁሉ ነገር ተመችቶኝ ነበረ ግን ቀስ በቀስ ሁሉ ነገር መስመር እየለቀቀ መጣ ። አሰሪዬም ቅዳሜ ቅዳሜ የታክሲ ብር መከልከል ጀመረች እኔም ከጎረቤቶች ብር ተበድሬ የጀመርኩትን  ትምህርት ከማቋርጥ ብየ ክላስ እሄዳለሁ .... አንዳንዴም የመመለሻ ብር አጥቸ የሶስት ሰዓት መንገድ በእግሬ እመጣለሁ ። " አቤላ እኔ እኮ ሰዎችን እወዳለሁ ግን ባዳና የሩቅ ሰው ቢጎዳኝ ምንም አልልም እኔ ግን የምፈተነው በቅርብ ሰው ፣ በማውቀው ፣ በአብሮ አደጌ ፣ መጎዳቴ ነው የምያበሳጨኝ ። ......ቤት ወልውየ ፣ ምግብ ሰርቸ ፣ ልብስ አጥቤ ቁጭ ከማለቴ ድሮ ለወልወል ጦርነት የተለበሱትን የነተቡ ልብስና ጫማ እንዳጥብ ትሰጠኛለች ። እናቴን ለማየት ሄጄ የእማዬን ፍቅርና ጠረኗን ሳላጣጥም " ቶሎ ነይ " ብላ ትደውላለች ። አሁን ራሱ በህይወት የቆየሁት ለከርታታው አባቴ ነው አቤላዬ አባቴ እኮ እኔ የጠየኩትን ነገር ከማድረግ ወደ ኋላ አይልም። የለምን አያውቅም እና ለዚህ ጀግናው አባቴ የኔ ራስን ማጥፋት ሳይሆን የኔን ወግ ማዕረግ የኔን ስኬት ተንሰፍስፎ ለሚጠብቅ አባት እንዴት አድርጌ ተስፋ ልቁረጥ? እንዴት የወረደ ቦታ ተገኝቸ ክብሩን በኔ በልጁ ምክኒያት ላጉድፍ? እንዴት ራሴን ላጥፋ ?,,,,  በረሃብ አንጀቱ እየታጠፈ እኔ ልጁ እንድጠግብለት ለሚኳትን አባት  አስክሬኔን አላስታቅፈውም ብየ ቀኔ እስከሚመጣ ድረስ አንገቴን ደፍቸ ከሰው ተነጥየ ብቻዬን አለሁ ።>> << ሰብሊዬ ምን አይነት ጥንካሬ ነው ያለሽ ? >> << ይሄ'ኮ የኔ ብቻ ታሪክ አይደለም የአብዛኛው ሴቶች ታሪክ ነው ። ደሞ ምርጥ አድማጭ እንደሆንክ ነግሬካለሁ ?>> << ሰብልዬ እያንዳንዱ ቃላቶችሽን በፍቅር ነው ምሰማቸው ምንም እኮ ነው ማትሰለቺ ! ሰብልዋ ። " ልሳምሽ ? >> << Of course >> <<  እምምምምምጷ >>             ✍ Henok

ችላ የምትለው ስህተትህ እንዳልታሰበበት ፅንስ ነው ድንገት አድጎ ያስደተግጠሃል!

ተፈፀመ! መድፈኞቹ የእንግሊዝ ንጉስ ሆኑ! የ22 ዓመታት ረጅም የናፍቆት ጉዞ፣ የእልህ አስጨራሽ ትግል እና የመስዋዕትነት ውጤት! አርሰናል በመጨረሻም የ2025/2026 የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ አሸና
ተፈፀመ! መድፈኞቹ የእንግሊዝ ንጉስ ሆኑ! የ22 ዓመታት ረጅም የናፍቆት ጉዞ፣ የእልህ አስጨራሽ ትግል እና የመስዋዕትነት ውጤት! አርሰናል በመጨረሻም የ2025/2026 የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ አሸናፊ በመሆን የክብር ዋንጫውን በኩራት ተረክቧል! ይህ ስኬት ለሁላችንም ትልቅ ትምህርት ነው፦ የፈለገውን ያህል ጊዜ ብትወድቅ፣ የፈለገውን ያህል ጊዜ ነገሮች ባይሳኩ... በራስህ ማመንህን ካላቆምክ እና በትጋት መስራትህን ከቀጠልክ፣ የድል ቀንህ መምጣቱ አይቀሬ ነው!

በድሮ ጊዜ ንጉሳዊያን ሲደብራቸው እና ህዝቡ ኣእምሮው እንዲዝናና አንድ ጭዋታ ያዘጋጁ ነበረ ። ያንን ጨዋታ ለመጫወት ከጎረቤት - ሩቅ ሃገር ያሉ ሰውነታቸው ፈርጠም ያሉት ተፋላሚዎች ተሰብስበው ይመጣሉ ። ያንን ፍልሚያ ካሸነፉ እስር ወርቅ ወይም የንጉሱን ቤተ መቅደስ የውስጥ አስተዳደርነት ማዕረግ ይሰጣል ። እናም ይህንን ድል ለመቀዳጀት የፍልሚያ ሜዳ ውስጥ መግባት ያስፈልጋል ። ድልን ፣ ስኬትን ለመቀዳጀት መወዳደር ፣ መፋለም ያስፈልጋል ። የድሮውን ስርዓት እንተወውና የአሁኑን ፍልሚያ እንመልከት ... ወጣት ሆይ :- የዚህን ዓለም የህይወት ዉጣውረድ ለማሸነፍ ከፈለክ ራስህን ከሌሎች ጋር ማወዳደሩን ትተህ አንተነትን ተቀበልና ወደ ፍልሚያው ሜዳ የሚያስፈልግህን ቁሳቁስ ይዘህ ግባ ።በዚህ ፍልሚያ ውስጥ መውደቅ አለ ፣ መጠማት አለ ፣ መራብ አለ ፣ መቁሰል አለ፣ መድማት አለ ፣ ግን አንተ የአሁኑን ህመም በቆራጥነትና በእችላለሁ መንፈስ አጥፍተህ ከፊትለፊትህ ያለውን ድል ለመቀዳጀት ተዋጋ ። ዙርያህ ላይ ያሉትን ስኬታማ ሰዎችን አትመልከት <<እንደነሱ ለምን አልሆንኩም >> ብለህ ራስህን አትውቀስ አሁንም አረፈደም ... ተነስ ! ለፍልሚያህ የሚያስፈልጉ ነገሮችን ይዘህ ወደ ሜዳው ግባ ደግሞም አንድ ነገር አስታውስ ድልን የሚቀዳጅ ያጨበጨበ ሳይሆን የተፋለመና የሞከረ ነው ።            ✍ Henok

ሞትሞትለት ነገር ምትቦትበት አይሁን! እንደውም ለርሱ ላለመሞት መኖር ይገባሃል።

... ፉክክር ውድድር በነውር በክፋት ብቻ ላለመሆን ብቻ ላለመቅረት    ለመቆየት ሲባል ያልሆኑትን መምሰል እስቲ ምን ያደርጋል?   ታብዮ እንደቀረ እንደደነደነ ኣልኖርም እንዳለ እንደተቃረነ ያ ግትር ልባችን   እንደሸሸ እግዜርን   እንደፈራ ሞትን    ሲሸሽ ሲከተለው    እስትንፋስ እያለው   ሊኖር ያልደፈረው ከወዲና ወዲያ እንዲ ሚላተመው    ለሌላኮ ኣደለም   ለመመሳሰል ነው፥ ለመሰንበት ለመቆየት..   ኗሪውን ቆሞ ለማየት   ለማስቆጠር  ሌላ እለት ቀን ይደራርባል ግን መች ይኖረዋል   እንዲሁ እንዳማጠ ለከንቱ እንደለፋ   ላይደርስ እንደሮጠ ኣንድ ቀን... ኣንድ ቀን... ኣንድ ቀን...እንዳለ         እየወላወለ   ዘመኑን ጨረሰ ኣይ የሰው ልጅ ህይወት ለመሆን ኣደለም፡መስሎ ለመታየት በግራና በቀኝ  እንደተጎተተ መኖርን ሳይኖረው እንደሞተ ሞተ፥ ....meron

ካልገራህ አንተነትህን ራስህን ማሳመር ስህተትህን ያበዛዋል።

ትቀርያለሽ_ብየ... [በእውቀቱ ስዩም] ግድየለሽምና ፥ ከልብ ላፈቀረሽ ሶስቴ ተቀጣጥረን፥ አራት ጊዜ ቀረሽ። ዛሬም እንደ ወትሮው፥ ትቀርያለሽ ብየ እድል የላከውን፥ እጣ የሚመስል፤ እጦት ተቀብየ፥ አበባ ሳልቀጥፍ አልጋ ሳላነጥፍ ሙታንታየን ሳልጥፍ በትራስጌየ ላይ ፎቶሽን ሳለጥፍ፥ ትቀርያለሽ ብየ፥ በመስታውቴ ፊት ከልብ አስቀይሜ አንድ እፍኝ ነጭ ሽንኩርት እንደ ተልባ ቅሜ አየሩን መርዤ፥ ህዋሴን አክሜ፤ ትቀርያለሽ ብየ፥ ጥፍሬን ሳልከረክም በመቀስ ሳልንደው፥ የጉያየን ሸክም ትቀርያለሽ ብየ ጀንበርን ቀድሜ፤ ቤቴ ተከትቼ ግቤን ያለ ረዳት፥ በጊዜ መትቼ የከሸፈ ትውልድ አንሶላ ላይ ትቼ ልተኛ ስዘጋጅ፥ እፎይ ብየ አርፌ ከወደ በራፌ “ውዴ! ደርሻለሁ፥ የሚል ድምጽሽ መጣ” ከመግባትሽ በፊት፥ እኔ በየት ልውጣ?

ተስፋ ላለመቁረጥ ትልቁ ምክንያት የፈጠረህ አካል እና የተፈጠርክለት ትርጉም ሲሆን ፥
ከዚህ በመቀጠል ዋናው ነገር ግን አንተ የዓለማችን ምርጡ እና ድንቅ ሰው ስለሆንክ አለም አንዳች ጎኗን (ድክመቷን) እንድታሳርፍላት አብዝታ ትፈልግሀለች። ታዲያ እንዲህ በጉጉት የሚጠበቅ ሰው ከሆንክ ለየትኛውም ችግር ይህን ጉጉት እንዲያመክነው አትፍቀድ። ቢያረፍድም መድረስ ይቻላል .. ነገር ግን በጣም አስገራሚው እና ይህን እንድናምን የሚረዳን እውነታ ምንድነው ?? ውድቀትህ ሊያሸማቅቅህ አይገባም። ምክንያቱም አለም ትፈልግሀለች እንጂ አታውቅህም ፣ ስለዚህ ብትወድቅም ቀይ ካርድ ሰጥታ ከጨዋታ አታስወጣህም፡ አታቅህማ... የት ታቅሀለች🤷።
 ግን ትፈልግሀለች ... መልካም ምሽት ።

ነገሮች "በዝግታ"ና በመዋከብ ሲፈጸሙ  ትልቅ ልዩነት እንዳላቸው ለመረዳት ከፈለክ! አንድን ሙዚቃ በተለያየ የድምጽ መጠን አዳምጠው።

ምክንያቱ እንጂ ሞቱ አንድ ነው ስለዛ ለምክንያቱ መሞት በተዘዋዋሪው ለሞቱ ትሞታለህ።

አንድ ሰው "ፈጣሪ ለምን ለጸሎቴን ወዲያው አይመልስም?" ብሎ አምላኩን ይወቅስ ነበር። .... አንድ ቀን በባህር ላይ ሲጓዝ መርከባቸው ተሰበረችና ብቻውን በአንድ ደሴት ላይ ቀረ። ለብዙ ቀናት "ጌታ ሆይ አድነኝ!" እያለ ጸለየ። ... ቀረብ ወዳለው ደሴት ተጠግቶ  መጠለያ እንዲሆነውም ከደረቁ ቅጠሎችና ቅርንጫፎች ትንሽ ጎጆ ቀለሰ። አንድ ቀን ግን ምግብ ፍለጋ ሄዶ ሲመለስ ጎጆው በእሳት ተያይዞ አመድ ሆኖ አገኘው። ... ሰውየው በጣም አለቀሰ፤ "ጌታ ሆይ! መጠለያዬንም አቃጠልከው? ለምን እንዲህ ታደርግብኛለህ?" ብሎ አማረረ። ከሰዓታት በኋላ ግን አንድ ትልቅ መርከብ እሱን ለመርዳት መጣች። "እዚህ መሆኔን እንዴት አወቃችሁ?" ሲላቸው፣ "ከደሴቱ የሚወጣውን ጭስ አይተን ነው!" አሉት።  ያ ያማረረው እሳት ለመዳኑ ምክንያት ሆነ። ... ፈጣሪ የሚመልስልን እኛ በምንፈልገው መንገድ ሳይሆን እኛን በሚጠቅመን መንገድ ነው። በሕይወታችን ውስጥ "ጥፋት" የመሰሉን ነገሮች ትልቅ በረከት ይዘው ሊመጡ ይችላሉ። ማን ያውቃል?? የእግዜር ጊዜ ገና ቢሆንስ??

🚨Breaking News የፕሪምየር ሊግ አሸናፊነት ሜዳሊያ ባሁኑ እሁድ ለአርሰናል ተጫዋቾች ተላልፎ አይሰጥም። ምክንያቱ ደግሞ ተጫዋቾቹ ፋይዳ መታወቂያ አላያያዙም😂

ተገቢ የህዝብ ጥያቄ ነው።

ይድረስ ለ Ethio telecom "Unlimited Data" ገዝተን ኢንተርኔት በነፃነት የመጠቀም መብታችን በምን ህግ ነው የሚታገደው? ብዙዎቻችን ተመሳሳይ ችግር እየገጠመን ነው። Unlimited ጥቅል (Package) ገዝተን ለጥቂት ደቂቃዎች ብቻ ከሰራ በኋላ ጨርሶ አይሰራም። የሚገርመው ነገር፣ ጥቅሉ እያለ አልሰራም ስላለኝ ብቻ ሌላ ተጨማሪ ጥቅል ለመግዛት ተገድጄ በሌላኛው ጥቅል ግን በሰላም እጠቀማለሁ። ይህ ማለት ችግሩ ከኔ ስልክ ሳይሆን ሆን ተብሎ Unlimited ጥቅሉ ላይ የሚደረግ ማገጃ (Restriction) እንዳለ በግልጽ ያሳያል። የበለጠ የሚያናድደው ደግሞ ወደ ደንበኞች አገልግሎት ማዕከል (994) ደውለን ስንጠይቅ የሚሰጠን ምላሽ ነው። እንደ ጀማሪ ኢንተርኔት ተጠቃሚ "ስልክህን አጥፍተህ አብራ"፣ "ይሄን አስተካክል" እያሉ ከጉዳዩ ጋር የማይገናኝ እና አቅጣጫ የሚያስለውጥ መልስ ይሰጡናል። ይህ አሰራር ፍፁም ትክክል አይደለም! ከተጠቃሚው ህዝብ ላይ ያለ አግባብ ገንዘብ መውሰድ ካልተባለ ምን ሊባል ይችላል? ኢትዮ ቴሌኮም ለከፈልንበት አገልግሎት ተገቢውን ምላሽና ጥራት ሊሰጠን ይገባል! እዚ Post ስር የተሰጡትን አስተያየቶች ተመልክታችሁ ምላሽ ብትሰጡን #EthioTelecom #Ethiopia #ConsumerRights #InternetQuality ግንቦት 12 2018 - እሮብ