en
Feedback
Psych Addis - ሳይክ አዲስ

Psych Addis - ሳይክ አዲስ

Open in Telegram

ይህ ገጽ የሥነ-ልቦና ሳይንስን ለሕይወታችን እንዲመች አድርገን እንድንጠቀም የሚያስችል መረጃ የምናገኝበት ነው:: ሰብስክራይብ በማድረግ አባል ይሁኑ!

Show more
4 082
Subscribers
-124 hours
-87 days
-4030 days
Posts Archive
እውነተኛ ፈውስ የሚጀምረው ከውስጥህ ነው! ወላጆችህ ላደረሱብህ የስነ-ልቦና ጉዳትና ጠባሳ የሚጠይቁህ ይቅርታ ብቻውን አያድንህም። ከእነሱ ጋር ያለህን ግንኙነት ለማስተካከል ሊረዳ ይችላል፤ ነገር ግን
እውነተኛ ፈውስ የሚጀምረው ከውስጥህ ነው! ወላጆችህ ላደረሱብህ የስነ-ልቦና ጉዳትና ጠባሳ የሚጠይቁህ ይቅርታ ብቻውን አያድንህም። ከእነሱ ጋር ያለህን ግንኙነት ለማስተካከል ሊረዳ ይችላል፤ ነገር ግን የመተዉ፣ የመገለል፣ የበደል እና የእንክብካቤ ማጣት ቁስሎች በሙሉ በውስጣዊ አዕምሮህ (subconscious) እና በነርቭ ስርዓትህ ውስጥ ቀድመው ስር ሰደዋል። ለደንበኞቼ ሁልጊዜ የምነግራቸው ትልቅ እውነት አለ፦ ወላጆችህ ዛሬ ላይ ተለውጠው የተሻለ ባህሪ ቢያሳዩ እንኳን፣ ያንን ቀድሞ የደረሰ ጉዳት ከእንግዲህ ሊለውጡት አይችሉም። እናም፤ ጉዳቱን ማከም የሚችለው ብቸኛው ሰው አንተው ነህ :- - እነሱ ሊሸከሙት ያልቻሉትን ህመም በድፍረት በመጋፈጥ፣ - እንዲሰማህ ያልተፈቀደልህን ስሜት አውጥተህ እንዲሰማህ በማድረግ፣ - ስታድግ በስሜት እንደተጣለ የተሰማውን ያንን ትንሽ ልጅ እንደ አዲስ በፍቅር በማሳደግ። እውነተኛ ፈውስ የሚመጣው በልጅነትህ አግኝተኸው የማታውቀውን ነገር በመጨረሻ ከሌላ ሰው ለማግኘት በመታገል አይደለም፤ ይልቁንም አግኝተሃቸው የማታውቃቸውን አስፈላጊ ፍላጎቶች በማመን፣ በማዘን እና አሁን ለራስህ መስጠትን በመማር ነው! ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ የትውልድ የሕመም ዑደትን መስበር እና ያልተፈቱ ቁስሎችህን በግንኙነቶችህ ውስጥ ከመድገም መቆጠብ የምትችለው በዚህ መንገድ ብቻ ነው። ይህንን ቪድዮ እዩና ራሳችሁን ገምግሙ 👉https://youtu.be/_jprKPWKcEk

የተጨናነቀው «ቀላል» መንገድ እና የብዙሃኑ ስነልቦና! ቀላል ቢሆን ኖሮ ሁሉም ሰው ያደርገው ነበር። ከባድ በመሆኑ ልትደሰት የሚገባህም በዚሁ ምክንያት ነው። ምክንያቱም «ቀላል» የሚባለው ቦታ በምድር ላይ እጅግ በጣም ህዝብ የበዛበት ስፍራ ነው:: ህልሞች መካከለኛ ሆነው የሚቀሩበት እና ውድድሩ ከባድ የሆነበት ቦታ እሱ ነው:: እውነታው ግን ከባድነቱ እንቅፋት አይደለም። እሱ ማጣሪያው ነው። ቁርጠኝነት የሌላቸውን ሰዎች ከክፍሉ ውጪ ለማስቀረት የተቀየሰ የደህንነት ስርዓት ነው። ወደ ተራራው ጫፍ የሚወስደው መንገድ የተጠረገ አውራ ጎዳና ቢሆን ኖሮ፣ ከጫፉ ላይ የሚታየው እይታ ምንም ዋጋ አይኖረውም ነበር። ይህ አባባል ባዶ የማበረታቻ ቃል አይደለም፤ ከጀርባው ጥልቅ የስነልቦና እውነታዎችን የያዘ ህግ እንጂ፦ 1. የህመም ፍርሃት እና ምቾት፤ በስነልቦና ሳይንስ "Risk Aversion" የምንለው ጽንሰ-ሐሳብ አለ። አብዛኛው ሰው ከውጤቱ ይልቅ ሊያጋጥመው የሚችለውን ውድቀትና ህመም አጉልቶ ስለሚያይ ሁልጊዜ አስተማማኝና «ቀላል» የሚመስለውን መንገድ ይመርጣል። የሰዎች ስብስብ (Mob) ባለበት ቦታ መገኘት የደህንነት ስሜት ስለሚሰጥ ብቻ ሚሊዮኖች መካከለኛነት ውስጥ ተቀርቅረው ይኖራሉ። 2. የጥረቱ ዋጋ መጨመር፤ በሌላ በኩል ደግሞ "Effort Justification" የሚባል ህግ አለ። አንድን ነገር ለማግኘት ጥረት በጨመርን ቁጥር፣ የከፈልንው ዋጋና ያሳለፍነው ፈተና ለውጤቱ የምንሰጠውን ዋጋ እጥፍ ያደርገዋል። በቀላሉ ያገኘኸው ነገር ስሜት የማይሰጥህ፣ ተራራውን በእግርህ ወጥተህ ስትጨርሰው ግን እይታው ልዩ የሚሆንብህ ለዚህ ነው። 3. ፈተናው እንደ ማጣሪያ፤ አሸናፊዎች ችግር ሲገጥማቸው እንደ እንቅፋት ሳይሆን እንደ «ማጣሪያ» ያዩታል። አብዛኛው ሰው እንቅፋት ሲያይ ወደኋላ ይመለሳል፤ አንተ ግን ፈተናውን «ቁርጠኛ ያልሆኑትን ማጥሪያ ደወል» አድርገህ ካሰብከው፣ አዕምሮህ በችግሩ ከመሸበር ይልቅ በደስታ ይመልከተዋል። ዛሬ እየገጠመህ ያለው ፈተና፣ ድካም እና እንቅፋት አንተን ለማስቆም የመጣ አይደለም፤ ቁርጠኝነት የሌላቸውን ሰዎች ከውድድሩ አውጥቶ ላንተ መንገዱን ክፍት ለማድረግ የተዘጋጀ «የደህንነት ስርዓት» እንጂ! ዛሬ ላንተ ያለኝ ጥያቄ ይሄ ነው፤ እያሳደድከው ያለው ህልም የትኛው ነው? ህዝብ የበዛበት «ቀላሉ» መንገድ ወይስ ጥቂቶች ብቻ የሚደፍሩት «ከባዱ» የተራራ ጫፍ?