📚منهج السلف طريقنا الى الله 📚
Open in Telegram
↘️በዚህ ቻናል የሚተላለፉት ↘️በሱና ኡስታዞች የተቀሩ ደርሶች ↘️የሱና ኡስታዞች ሙሀደራዎች ↘️በመቀጠል አስተማሪ ፁሁፎች ➴➴➴➴➴➴➴➴➴➴➴➴ https://t.me/htt_asselfya
Show more3 819
Subscribers
-524 hours
+1617 days
+15530 days
Posts Archive
Repost from Ibnu Munewor (ኢብኑ ሙነወር)
የኮርስ እና የሙሐደራ ፕሮግራም በጂንካ ጃሚዑ-ሰላም መስጂድ‼️
👉ነገ ቅዳሜ ጥር 18, 2016 E.C እና እሁድ ጥር 19, 2016 E.C 🪐በጂንካ ከተማ 🕌ጃሚዑ-ሰላም መስጂድ 🏝 የኮርስና የሙሐደራ ፕሮግራም ተዘጋጅቷል።
🎤የኮርስ ፕሮግራሙ በሁለት ወንድሞች የሚቀርብ ሲሆን፤ ዝርዝሩም እንደሚከተለው ይሆናል።
1) 📖መንዘመቱ አቢ ኢስሃቅ ኢልቢሪ እና ላሚያ
🎤በወንድም አብዱረዛቅ ባጂ
قصيدة أبي إسحاق الألبيري(التائية) و لامية شيخ الإسلام ابن تيمية
الأخ عبد الرزاق الباجي الشافعي
2) 📖ቀዋዒዱል አርበዓህ:
🎤በኡስታዝ አብዱናሲር መኑር አልጃቢሪ
القواعد الأربع
الأستاذ عبد الناصر منور
3) ልዩ ልዩ መሐደራዎች
🎤 በወንድም ኸድር ነጅሙ
አድራሻ:ጂንካ ከተማ ጃሚዑ-ሰላም መስጂድ::
Repost from Ibnu Munewor (ኢብኑ ሙነወር)
‘ሸይኽ ኢብኑ ባዝና አልባኒይ ይጋሩታል ወይስ ይቃረኑታል?’ ስለተባለው ጉዳዩ እኔ የሸይኽ ረቢዕን ኪታቦች በብዛት አላነበብኩም። ይሄ አንድ ነገር ነው። እንደገና ሌላው ነገር እንዳልነው የሱና ሰዎች ከፊሉ ከፊሉን በጭፍን አይከተሉም። እሱን ቢሀይሱና ከልክ እንደወጣ ቢያዩ ኖሮ የሚለውን ለማረም ፅሁፎችን ባወጡ ነበር። የሚለውን ለመመለስ ኪታቦችን ባዘጋጁ ነበር። ምንም ይሁን ምን ሁላችንም እናገኛለን፣ እንስታለን። እንዘነጋለን፣ እናውቃለን። ወላሁል ሙስተዓን።”
ምንጭ፦ https://www.muqbel.net/fatwa.php?fatwa_id=4330
=
* የቴሌግራም ቻናል
https://t.me/IbnuMunewor
* የዋትሳፕ ቻናል፦
https://whatsapp.com/channel/0029VaA3X1e5kg7BlsJboa2M
* ፌስቡክ
https://www.facebook.com/Ibnu.Munewor?mibextid=ZbWKwL
Repost from Ibnu Munewor (ኢብኑ ሙነወር)
"መድኸሊዮች አይደለንም፣ ግን መድኸሊዮች ነን"
~
በኢማሙ ሻፊዒይ ላይ ድንበር የሚያልፍ ሻፊዒይ አትሁን፣ በአልባኒይ፣ በኢብኑ ባዝ ላይ ድንበር አትለፍ ስትል ኮሽታ አያሰማም። በረቢዕ ላይ ድንበር አትለፍ ስትል ግን "ሸይኽ ረቢዕን ሰደብክ" ብሎ አገር ምድሩን ያቃጥላል። ይሄው ነው በቃ የማሰብ አቅማችሁ? ረድ ማለት እናንተ ዘንድ የሰውን ንግግር እያጣመሙ በመተርጎም መጮህ ነው? እናንተ አስተማሪዎቻቸው የሆኑ ሰዎች ምንኛ ያሳዝናሉ?!
ድንበር ማለፍኮ ይሄው ነው። እንጂማ ድንበር አላፊዎችኮ "ልክ ነው እኛ ድንበር እናልፍለን" ብለው አያውቁምኮ። ብቻ ቢኮሰኩሳችሁም ዋጡት። በሸይኽ ረቢዕ ላይ ድንበር የሚያልፉ ሰዎች በተጨባጭ አሉ። ለዚህም እናንተ ተግባራዊ ማሳያ ናችሁ። ደግሞም "ረቢዕን መልእክተኛ አደረጉትን?" ያልኩት እኔ ሳልሆን ሸይኽ ዐብዱልዐዚዝ አራጂሒይ ናቸው። ብልግናችሁ ለከት አጥቷልና ዝመቱባቸው። ሸይኽ አዝሀር ሲነይቆራም "የሸይኽ ረቢዕ ንግግር ወሕይ ነው ወይ?" ብለዋል። በቀጣይ ዑለማኦች ለሸይኽ ረቢዕ የሰጡትን አድናቆት መዘርዘር ላይ ትጠመዱ ይሆናል። አንድ ትልቅ ዶሴ ብታቀርቡም እውነታው አይቀየርም። በማንም ላይ ድንበር ማለፍ ባጢል ነው። "የጀርሕና ተዕዲል ሰንደቅን ተሸካሚው ረቢዕ ነው" የሚለው የሸይኽ አልባኒይ ንግግርም "ሸይኽ ረቢዕ የተናገረውን ሁሉ ውሰዱ" ማለት አይደለም። በዚህ መልኩ የሚረዱት ማሰቢያቸው የተደፈኑ በቀቀኖች ናቸው። ይሄኮ አይን ያወጣ ድንበር ማለፍ ነው። በፈውዛን ላይ ድንበር ማለፍ አይገባም ሲባል ምንም አይሉም። እንዲያውም በትልልቅ የሰለፍ አኢማዎች ላይ ድንበር ማለፍ አይገባም ሲባልም ምንም አይሉም። በረቢዕ ላይ ድንበር ማለፍ አይገባም ሲባል ግን ይጮሃሉ። አይ ድንበር ማለፍ በረቢዕ ላይ ሲሆን ይፈቀዳልi "ረቢዕን በጭፍን የምትከተል መድኸሊይ አትሁን" ስትባል ከጮህክ መድኸሊይነትህን እያረጋገጥክ ነው ያለኸው።
ለማንኛውም ኢብኑ ተይሚያ ረሒመሁላህ እንዲህ ይላሉ፦
وكلام يحيى بن معين والبخاري ومسلم وأبي حاتم وأبي زرعة والنسائي وأبي أحمد بن عدي و الدارقطني وأمثالهم في الرجال وصحيح الحديث وضعيفه هو مثل كلام مالك والثوري والأوزاعي والشافعي وأمثالهم في الأحكام ومعرفة الحلال من الحرام
"የሕያ ብኒ መዒን፣ ቡኻሪይ፣ ሙስሊም፣ አቢ ሓቲም፣ አቢ ዙር0፣ ነሳኢይ፣ አቢ አሕመድ ብኒ ዐዲይ፣ ዳረቁጥኒይ እና መሰሎቻቸው በዘገባ ሰዎች ላይ እና በሶሒሕና ዶዒፍ ሐዲሥ ብይን ላይ የሚናገሩት ንግግር ልክ ማሊክ፣ ሠውሪይ፣ አውዛዒይ፣ ሻፊዒይና መሰሎቻቸው በፊቅህ ህግጋትና የሐላልና ሐራም እውቀት ላይ እንደሚናገሩት ንግግር ነው።" [ረድ ዐለል በክሪይ፡ 1/72]
ስለዚህ! ልክ በፊቅህ ርእስ ላይ የአንድን ኢማም ንግግር በጭፍን መውሰድ እንደማይገባው በሐዲሥ ብይን ላይ፣ በአስተላላፊዎች ትችትና ሙገሳ ላይ የአንድን ኢማም ንግግር በደፈናው መውሰድም ግዴታ አይሆንም። ይህንን ያልኩት እኔ አይደለሁም። ይልቁንም ሸይኹል ኢስላም ኢብኑ ተይሚያ ናቸው ረሒመሁላህ። ይሄ ቋሚ መርህ ከሺ ዘመናት በኋላ ሸይኽ ረቢዕ ላይ ሲደርስ አይቀየርም። አሁንም ኢብኑ ተይሚያ እንዲህ ይላሉ፦
لا يجوز لأحد أن يجعل الأصل في الدين لشخص إلا لرسول الله ﷺ ولا لقول، إلا لكتاب الله عز وجل ومن نَصَّب شخصاً كائناً من كان فوالى وعادى على موافقته في القول والفعل، فهو (من الذين فرقوا دينهم وكانوا شيعاً)
"በዲን ጉዳይ ላይ መሰረትን ለግለሰብ ሊያደርግ ለአንድም ሰው አይፈቀድም፤ ለአላህ መልእክተኛ ﷺ ቢሆን እንጂ። ለየትኛውም ንግግርም እንዲሁ፤ ለአላህ - ዐዘ ወጀል - መፅሐፍ ቢሆን እንጂ። አንድን ሰው መድቦ - ያ ሰው ማንም ይሁን ማን - በንግግርም ይሁን በተግባር እሱን በመግጠም ላይ ወዳጅነትና ጠላትነት የሚመሰረት አካል እሱ 'ከነዚያ ሃይማኖታቸውን በመለያየት ጭፍራዎች ከሆኑት ነው።' " [አልመጅሙዕ፡ 20/8]
በመጨረሻም ፅሑፌን በሸይኽ ሙቅቢል ረሒመሁላህ ንግግር እዘጋለሁ። እንዲህ የሚል ጥያቄ ቀርቦላቸው ነበር፦
“በሂስና ሙገሳ (ጀርሕ ወተዕዲል) ዘርፍ ላይ በሸይኽ ረቢዕ የሂስ ፅሁፎች ላይ እንዲሁም በሚጓዙበት መንገድ ላይ ይስማማሉ ወይስ ይቃረናሉ? ሸይኽ ኢብኑ ባዝ፣ ኢብኑ ዑሠይሚንና አልባኒይ እንደሚጋሯቸውስ ያውቃሉን?”
የሸይኽ ሙቅቢል መልስ ይሄውና :-
أهل السنة منبعهم واحدٌ - الذي يشربون منه -؛ وهو: كتاب الله وسنة رسوله ﷺ؛ فعقيدتهم واحدة، واتجاههم واحد في جميع البلاد الإسلامية.
نحن متفقون على جرح أصحاب البدع والحزبيين، متفقون على هذا، بقي في أناس هم عند شخص من المجروحين، وعند آخر ليسوا من المجروحين، هذا حدث على عهد السلف؛ فرُبّ راوٍ يقول فيه أحمد بن حنبل: ثقة، و يقول فيه يحيى بن معين: كذاب، أو العكس، وهكذا البخاري وأبو زُرعة وأبو حاتم.
والمهم: لا يقلّد بعضهم بعضاً؛ فإذا اختلفنا في توثيق شخص وتجريحه: فليس معنى هذا أننا مختلفون في العقيدة! وليس معنى هذا أننا مختلفون في الاتجاه.
وأما هل الشيخ ابن باز والشيخ الألباني يوافقونه أم يخالفونه؟ فالمسألة أنني أنا ما قرأت كثيراً من كتب الشيخ ربيع، هذا أمر، أمر آخرأيضاً كما قلنا: إن أهل السنة لا يقلِّد بعضهم بعضا، ولو انتقدوا عليه ورأوه خرج عن الصواب لأخرجوا المنشورات في رد ما يقول، وأخرجوا الكتب في دفع ما يقول. وعلى كُلٍّ: كلنا نصيب ونخطئ، ونجهل ونعلم. والله المستعان.
“የሱና ሰዎች የሚቀዱበት ምንጫቸው አንድ ነው። እሱም የአላህ ኪታብና የመልእክተኛው ﷺ ሱና ነው። በሁሉም ኢስላማዊ ሃገራት ዐቂዳቸውም አንድ፣ መንገዳቸውም አንድ ነው። አዎ እኛ የቢድዐ ሰዎችንና ቡድንተኞችን በመሀየስ ላይ እንስማማለን። በዚህ ላይ እንስማማለን። የሚቀረው፡ አንዱ ዘንድ የተተቹ ሌላኛው ዘንድ ግን ያልተተቹ የሆኑ ሰዎች ጉዳይ ነው። ይሄ በሰለፎችም ዘመን ተከስቷል። ምናልባትም አንዱን ዘጋቢ አሕመድ ኢብኑ ሐንበል ‘ታማኝ ነው’ ብሎት የሕያ ኢብኑ መዒን ግን ‘ውሸታም ነው’ ያለው ወይም በተቃራኒው የሆነ ስንት ዘጋቢ ያጋጥማል። ቡኻሪ፣ አቡ ዙርዐና አቡ ሓቲም ዘንድም ተመሳሳይ ነገር ያጋጥማል።
ቁም ነገሩ ከፊላቸው ከፊሉን በጭፍን አይከተሉም። በአንድ ሰው ታማኝነት ወይም ብልሹነት ላይ ብንለያይ ይሄ ማለት ዐቂዳ ላይ ተለያይተናል ማለት አይደለም። በአካሄድ ላይ ተለያይተናል ማለት አይደለም።
Repost from Ibnu Munewor (ኢብኑ ሙነወር)
መድኸሊይ እንዳትሆን!
~
ሸይኽ ረቢዕ አልመድኸሊይ እንደማንኛውም ዓሊም ናቸው። ይሄ ደረጃቸውን ዝቅ ማድረግ አይደለም። ከሳቸው የሚበልጡ ታላላቅ ዑለማኦችን በጭፍን መከተል አይፈቀድም ስንል ደረጃቸውን ዝቅ ማድረግ እንደማይሆነው ማለት ነው። ረቢዕ ልክ እንደሌሎቹ ዓሊሞች በየትኛውም ርእስ ላይ ቢሆን ፍፁም አይደሉም። በትንሽ በትልቁ በሸይኽ ረቢዕ ንግግር የሚያስፈራራ ቢኖር ራሱን ነው የሚሸውደው። ሱናን እከተላለሁ የሚል አካል በየትኛውም ዓሊም ላይ ያለው ምልከታ ለከት ሊኖረው ይገባል። አንድን ዓሊም መለኪያም፣ መስፈሪያም፣ መቁረጫም ማድረግ አይገባም። ሸይኽ ዐብዱልዐዚዝ አራጂሒይ - ሐፊዞሁላህ - የሌሎች ዓሊሞችን ንግግር ገሸሽ በማድረግ የሸይኽ ረቢዕን ንግግር በተለዬ የሚይዙ ስለሆኑ ሰዎች ሲጠየቁ እንዲህ ነበር ያሉት፦
يعني جعلوه رسولا، جعلوا ربيع رسولا، جعلوه رسولا، وهذا باطل، هذا باطل، ربيع ... يخطيء و يصيب و لا هو المييزان، الميزان: كلام الله و كلام الرسول، فمن قال: الميزان ربيع، هذا باطل.
"መልእክተኛ አደረጉት ማለት ነው?! ረቢዕን መልእክተኛ አደረጉት?! ይሄ ውድቅ ነው። ይሄ ውድቅ ነው። ረቢዕ ... ይስታል፣ ያገኛል። ሚዛን አይደለም። ሚዛኑ የአላህ ንግግር እና የመልእክተኛው ንግግር ነው። ሚዛኑ ረቢዕ ነው የሚል ይሄ ውድቅ ንግግር ነው።" [ከድምፅ ቅጅ የተወሰደ ነው።]
ስለዚህ የአልባኒይ፣ የኢብኑ ባዝ፣ የኢብኑ ዑሠይሚን፣ ወዘተ ንግግር በጭፍን እንደማይወሰደው የረቢዕ ንግግርም በጭፍን አይወሰድም። ረቢዕ በሌሎች መሻይኾች ላይ የሚናገሩትም በማስረጃ የተደገፈ ሲሆን ይወሰዳል፣ ካልሆነ ይጣላል። እንጂ ተናጋሪው ረቢዕ በመሆናቸው ብቻ ይወሰዳል ማለት አይደለም። አልባኒያ፣ ባዚያ፣ ዑሠይሚኒያ፣ ፈውዛኒያ፣ ... የሚባል መዝሀብ እንደሌለው መድኸሊያ የሚባል መዝሀብም የለም። ስለዚህ አኢማዎችን በጭፍን የሚከተል ሐነፊይ፣ ማሊኪይ፣ ሻፊዒይ፣ ሐንበሊይ፣ ... መሆን እንደሌለብህ ሁሉ ረቢዕን በጭፍን የሚከተል መድኸሊይ ልትሆንም አይገባም። እዚህ ላይ በቃል ደረጃ ችግር የለም። በተግባር ግን በተለያዩ መሻይኾች ላይ ድንበር ማለፍ ስላለ ጥንቃቄ እንዲኖረን ማስታወስ ነው የፈለግኩት። (ለጥጠው ሌላ ትርጉም ከሰጡ በኋላ በራሳቸው ምናብ ላይ ነብር ሆነው ለረድ የሚነሱ እንደሚኖሩ እጠብቃለሁ።)
በተረፈ የኢኽዋን ጀሌዎች እዚህ እንዳትመጡ። የዚህ ፅሑፍ ጭብጥ በቅርብም በሩቅም ከናንተ ጋር የሚገናኝ አይደለም። የኢኽዋን ቡድን ዘንድ የአንጃቸውን ጥመት ከተናገርክ፣ የነ ሐሰን አልበና፣ ሰይድ ቁጥብ፣ ቀርዷዊይ፣ ... ጥፉ አካሄዶች ካስጠነቀቅክ፣ ... በኢኽዋን ቫይረስ በተጠቁ አካላት ዘንድ አንተ መድኸሊይ ወይም ጃሚይ ነህ። ልክ የሙታን አምልኮን፣ በአላህ ሲፋት ላይ ማራቆትን ስታወግዝ "ወሃቢይ" እንደምትባለው ማለት ነው። ለነዚህ ሸይኽ ዒምራን ዐሊይ ሪድዋን አልፋሪሲይ - ረሒመሁላህ - እንዳሉት እንላለን፦
قُـلْ لِلَّذِي اتَّـخَـذَ الـتَّـجَـهُّـمَ مَـرْكَـبًـا
وَ رَآهُ دِيـنًـا و ارْتَــضَـاهُ مَـذْهَــــبًـا
وَ لِـمَـذهَبِ الأَبـــرَارِ صَارَ مُـكَـذِّبـًـا
إنْ كَانَ تَـابِـعُ أَحـمَــــدٍ مُـتَـوَهِّــبًـا *** فَـأَنـا الـمُــــقِـرُّ بِـأَ نَّـنِـي وَهَّـــابِي
Ibnu Munewor
=
* የቴሌግራም ቻናል
https://t.me/IbnuMunewor
* የዋትሳፕ ቻናል፦
https://whatsapp.com/channel/0029VaA3X1e5kg7BlsJboa2M
* ፌስቡክ
https://www.facebook.com/Ibnu.Munewor?mibextid=ZbWKwL
ደርስ
~
* ሪያዱ ሷሊሒን
* ክፍል:- 1️⃣3️⃣8️⃣
* የኪታቡን ሶፍት ኮፒ (በ pdf ) በዚህ ሊንክ ማግኘት ትችላላችሁ
https://t.me/IbnuMunewor/3505
* የለቱ ደርስ መነሻ ገፅ 396፣ باب فضل صلاة الصبح والعصر
* የሚሰጥበት ቦታ፦ አሸዋ ሜዳ፣ መስጂደል ዋሊደይን
* የሚሰጥበት ጊዜ:- ረቡዕ፣ ሐሙስ እና ጁሙዐ
=
የቴሌግራም ቻናል፡-
https://t.me/IbnuMunewor
Repost from Ibnu Munewor (ኢብኑ ሙነወር)
ራሱን ባጠፋ ሰው ላይ መስገድ
~
በኢስላም ራስን ማጥፋት ትልቅ ወንጀል ነው። ሆነ ብሎ ራሱን ያጠፋ ሰው ከባድ ወንጀል ነው የፈፀመው። ይሄ ማለት ግን አላህ እንዲምረው ዱዓእ ማድረግ፣ በሱ ላይ ሶላተል ጀናዛ መስገድ አይቻልም ማለት አይደለም። እንዲያውም ይበልጥ ዱዓእ ያስፈልገዋል። ራስን ማጥፋት ከኢስላም አያስወጣም። ሙስሊምነቱ ከታወቀ ደግሞ በሱ ላይ ሶላተል ጀናዛ መስገድ አይከለከልም። ነብያችን ﷺ ራሱን ባጠፋ ሰው ላይ ያልሰገዱት ከዚህ ጥፋት ሰዎችን ለማስጠንቀቅ ነው። እንጂ ሌሎች እንዳይሰግዱበት አልከለከሉም። በተመሳሳይ ሁኔታ ሶላተል ጀናዛ አለመስገዱ ሌሎችን የሚያስደነግጥ የሆነ ሰው ባይሰግድ ተመራጭ ይሆናል። ሌሎች ሰዎች ግን ለሟች እንደ ማንኛውም ሙስሊም ዱዓእ ሊያደርጉለት፣ ሶላተል ጀናዛ ሊሰግዱበት ይወደዳል።
Ibnu Munewor
=
* የቴሌግራም ቻናል
https://t.me/IbnuMunewor
* የዋትሳፕ ቻናል፦
https://whatsapp.com/channel/0029VaA3X1e5kg7BlsJboa2M
* ፌስቡክ
https://www.facebook.com/Ibnu.Munewor?mibextid=ZbWKwL
Repost from Ibnu Munewor (ኢብኑ ሙነወር)
"የአህዛብ ጣኦታት የሰው እጅ ስራ ናቸው።"
~
"ሁሉን መርምሩ፥መልካሙን ያዙ።" [ወደ ተሰሎንቄ ሰዎች፡ 5፥ 21]
=
የቴሌግራም ቻናል፡-
https://t.me/IbnuMunewor
ደርስ
~
* ሪያዱ ሷሊሒን
* ክፍል:- 1️⃣3️⃣7️⃣
* የኪታቡን ሶፍት ኮፒ (በ pdf ) በዚህ ሊንክ ማግኘት ትችላላችሁ
https://t.me/IbnuMunewor/3505
* የለቱ ደርስ መነሻ ገፅ 389፣ باب فضل الوضوء
* የሚሰጥበት ቦታ፦ አሸዋ ሜዳ፣ መስጂደል ዋሊደይን
* የሚሰጥበት ጊዜ:- ረቡዕ፣ ሐሙስ እና ጁሙዐ
=
የቴሌግራም ቻናል፡-
https://t.me/IbnuMunewor
Repost from Ibnu Munewor (ኢብኑ ሙነወር)
ፖሊስ ማለት ከህገ ወጦች የህዝብን ደህንነት የሚጠብቅ፣ ወንጀልን የሚከላከል፣ ወንጀለኛን ለህግ የሚያቀርብ፣ ሰላማዊ ድባብ እንዲኖር የሚተጋ ነበር። ወይም መሰለኝ። ፖሊሶች ሆይ! ለምን ግን በአቅራቢያችን ስትኖሩ ይበልጥ ስጋት እንዲሰማን ታደርጉናላችሁ? ለምንድነው ግን እጅ ከፍንጅ ከተያዙ ወንጀለኞች በላይ አቅመ ደካሞች ላይ ጉልበታችሁ የሚበረታው? እናንተ ከህዝብ አይደለም የወጣችሁት? እናት አባት የላችሁም ወይ? "አይበጅም!" አታውቁም ወይ? ነውር የሚባል እንዳለ አልሰማችሁም ወይ? አዛውንት ወላጃችሁ ላይ ይሄ ሲፈፀም ብታዩ ምን ይሰማችኋል? እንደ ህግ አስፈፃሚ የበለጠ ኃላፊነት ሊሰማችሁ ይገባ ነበር። እሺ እሱ ይቅር፣ ቢያንስ እንደማንኛውም ሰው ሰብአዊነት ቢኖራችሁ ምናለ?
Addis Ababa Police እባካችሁ! መሰል ጥፋቶች በጣም በዝተዋል። ፖሊሶችን ስነ ምግባር ማስተማር ላይ በደንብ ስሩ። በፖሊስ አባላት ጥፋቶች ሲፈፀሙም አስተማሪ እርምጃ ውሰዱ። የእርምት እርምጃዎችን ለህዝብ ብታሳውቁ ደግሞ ጥቅሙ ለሁሉም ነው። ብዙ ሰው ዛሬ ከዘራፊዎች በላይ ፖሊስን እየፈራ ነውና መተማመን እንዲኖር በቂ ስራ ስሩ።
Ibnu Munewor
=
* የቴሌግራም ቻናል
https://t.me/IbnuMunewor
* የዋትሳፕ ቻናል፦
https://whatsapp.com/channel/0029VaA3X1e5kg7BlsJboa2M
* ፌስቡክ
https://www.facebook.com/Ibnu.Munewor?mibextid=ZbWKwL
Repost from Ibnu Munewor (ኢብኑ ሙነወር)
ፋጢማ ቢንቱ ዐብዲልመሊክ - ረሒመሀላህ - የኸሊፋው ዑመር ብኑ ዐብዲልመሊክ - ረሒመሁላህ - ሚስት ነች። ስለ ዑመር ዒባዳህ ስትጠየቅ እንዲህ ብላ መለሰች:-
"والله ما كان بأكثر الناس صلاةً، ولا أكثرهم صياماً، ولكن والله ما رأيت أحداً أخوَف لله من عمر!، لقد كان يذكر الله في فراشه، فينتفض انتفاض العصفور من شدّة الخوف حتى نقول: "ليُصبحنّ الناس، ولا خليفة لهم!!".
"በአላህ ይሁንብኝ! ከሰዎች የበዛ ሶላት ያለው አልነበረም። ፆሙም እንዲሁ ከሰዎች የበዛ አልነበረም። ነገር ግን ወላሂ! ከዑመር በላይ አላህን የሚፈራ አላየሁም። መኝታው ላይ ሆኖ አላህን ሲያወሳ ከፍራቻው ብርታት የተነሳ ልክ ወፍ እንደሚርገፈገፈው ይርገፈገፍ ነበር። 'ሰዎች ኸሊፋ ሳይኖራቸው ሊያነጉ ነው' (ሊሞት ነው) እስከምንል ድረስ።"
ረዲየላሁ ዐንሁ ወአርዷሁ።
📖 [ሲረቱ ዑመር ብኒ ዐብዲልዐዚዝ፣ ኢብኑ ዐብዲልሐከም]
Ibnu Munewor
=
* የቴሌግራም ቻናል
https://t.me/IbnuMunewor
* የዋትሳፕ ቻናል፦
https://whatsapp.com/channel/0029VaA3X1e5kg7BlsJboa2M
* ፌስቡክ
https://www.facebook.com/Ibnu.Munewor?mibextid=ZbWKwL
Repost from Ibnu Munewor (ኢብኑ ሙነወር)
ወሳኝ የጥቢ፞ ህግጋት
~
በሃገራችን ወላጆች ልጆቻቸውን ጎረቤት ወይም ጓደኛ ዘንድ ጥለው ሲሄዱ የተተወባት እናት ልጁን ማጥባት የተለመደ ነው። ነገር ግን የሚከተለው ሸሪዐዊ ህግጋት እንዳለ ስለማያውቁ ለጉዳዩ ተገቢውን ትኩረት አይሰጡትም። ይሄ ትልቅ ርእስ ስለሆነ እናቶች ተገቢውን ጥንቃቄና ክትትል ሊያደርጉ ይገባል።
በኢስላም ጥቢ፞ ከተራና አላፊ እለታዊ ክስተት ያለፈ ትርጉም አለው፡፡ ማለትም አጥቢና ጠቢን ያማከሉ ሰፋ ያሉ ሸሪዐዊ ህጎች ስላሉ ሙስሊሞች ተያያዥ ብይኖችን ማወቅ ይጠበቅባቸዋል፡፡ ይህንን ከሚያረጋግጡ ማስረጃዎች ውስጥ አንዱ እናታችን ዓኢሻ ረዲየላሁ ዐንሃ ያስተላለፈችው ሐዲሥ ነው፡፡ በዚህ ሐዲሥ ነብዩ ﷺ እንዲህ ብለዋል፡-
"الرَّضَاعَةُ تُحَرِّمُ مَا تُحَرِّمُ الْوِلَادَةُ".
“ጥቢ፞ መዋለድ (ከመጋባት) የሚከለክለውን ይከለክላል፡፡” [ቡኻሪ፡ 2646] [ሙስሊም፡ 1444]
ስለዚህ ጥቢ፞ ከስጋዊ ዝምድና ጋር የሚጋራቸው ነገሮች አሉ ማለት ነው። እነዚህም አራት ናቸው፡-
① ጋብቻ:–
በስጋ እናት ሰበብ ለመጋባት ክልክል የሆነ ሁሉ በተመሳሳይ በጥቢ፞ እናት ሰበብም ክልክል ይሆናል። ዝርዝሩ ወደፊት ይመጣል።
② እይታ (ነዞር):–
በስጋ እናት ሰበብ መመልከት የሚፈቀድ ሁሉ በተመሳሳይ በጥቢ፞ እናት ሰበብም የተፈቀደ ይሆናል። ስለዚህ እናቱን፣ እህቱን፣ አክስቱን፣… ማየት፣ መጨበጥ፣ መሳም እንደሚፈቀደው ሁሉ በጥቢ፞ ሰበብ ተመሳሳይ ብይን የሚይዙንም መመልከት፣ በሰላምታ መጨበጥና መሳም ይፈቀዳል። ስጋት እስከሌለ ድረስ።
③ ተገልሎ መቆየት:–
እንደሚታወቀው ለአንድ ወንድ ከአጅነቢያ ሴት ጋር ከሰው እይታ ተገልሎ መቀመጥ አይፈቀድም። ነገር ግን ከስጋ እናት፣ እህት፣… ጋር ተገልሎ መቀመጥ እንደማይከለከለው ከጥቢ፞ እናት፣ እህት፣ አክስትም፣… ጋርም ተገልሎ መቀመጥ አይከለከልም።
④ የጉዞ ጓደኛ መሆን:–
አንድ ወንድ ለወላጅ እናቱ፣ ለእህቱ፣ ለአክስቱ፣… የጉዞ ጓደኛ እንደሚሆነው ሁሉ ለጥቢ፞ እናቱ፣ እህቱ፣ አክስቱም መሆን ይችላል።
•
መጠነኛ ትንታኔ
~
1. አንድ ሰው ልጅ እያለ አንዲት ወላጅ እናቱ ያልሆነች ሴት ብታጠባው ያቺ አጥቢ እንደ እናቱ ትታሰባለች፡፡ ሴቶች ልጆቿ እንደ እህቶቹ፣ ወላጆቿ እንደ አያቶቹ፣ እህቶቿ እንደ የሹማዎቹ፣ ስታጠባው ጊዜ ያለው ባሏ እንደ አባቱ፣ የባሏ ወላጆች እንደ አያቶቹ፣ የባሏ እህቶች እንደ አክስቶቹ፣ የባሏ ሌሎች ሚስቶች እንደ አባቱ ሚስቶች፣ ባሏ ከሌላ ሚስት የወለዳቸው ልጆች ልክ እንደ እህትና ወንድሞቹ ይቆጠራሉ፡፡
የጠባችው ሴት ከሆነችም ተመሳሳይ ንፅፅር እንሰራለን፡፡ ባጭሩ የአጥቢዋ ወንዶች ልጆች ለጠቢዋ ወንድሞቿ፣ የአጥቢዋ ወንድሞች ለጠቢዋ አጎቶች፣ … ይሆናሉ፡፡ አጅነቢዮች አይሆኑም።
2. ልክ በመዋለድ (በስጋዊ ዝምድና) የተነሳ ለማግባት እንደማትፈቀድ ሴት፣ በጥቢ፞ የሷን ብይን የምትይዝን ሴትም (ለምሳሌ የጥቢ፞ እህት፣ የጥቢ፞ እናት፣ የጥቢ፞ አክስት፣ የጥቢ፞ የሹሜ፣ …) አንድ ወንድ ሊያገባ አይፈቀድለትም፡፡ ጋብቻ ተፈፅሞ ከሆነም መለያየት ግዴታ ነው፡፡
ማሳሰቢያ፡-
~
1. ዋጋ የሚኖረው ጥቢ፞ በሁለት አመት የህፃንነት እድሜ ክልል ውስጥ የተጠባ ጥቢ፞ ከሆነ ነው። [አልበቀራ: 233] ከሁለት አመት እድሜ በላይ እያለ የተፈፀመ ጥቢ፞ ከቁምነገር አይቆጠርም።
2· ጥቢ፞ው አምስት ጊዜና ከዚያ በላይ የጠባ ከሆነ ነው፡፡ [ሙስሊም: 1452]
አንድ ጊዜ ጡቱን ከያዘ በኋላ ለመተንፈስ፣ ውሃ ለመጠጣት፣ ወደሌላኛው ጡት ለመቀየር የሚኖረው ቆይታ ተፅእኖ የለውም። ረጅም ጊዜ ካልኖረ በስተቀር እንደ አንድ ነው የሚቆጠረው። ይሄ አንድ ተብሎ በዚህ መልኩ አምስት ጊዜ ከተጠባ የጥቢ፞ ህግጋት ታሳቢ ይሆናሉ። ከአምስት ጊዜ ያነሰ ጥቢ፞ ከግምት አይገባም፡፡
3. የጥቢ፞ ህግጋት የሚመለከተው የጠባውን አካል ብቻ እንጂ ያልጠቡ የስጋ ወንድሞቹንና እህቶቹን አይደለም፡፡ ማለትም የጠባው አካል ከጠባበት ቤት ቤተሰብ ይሆናል፡፡ እንጂ የሱ የስጋ ቤተሰቦች በሱ መጥባት የተነሳ ለጥቢ፞ እናቱ ቤተሰብ አይሆኑም፡፡
ምሳሌ፡- ፋጢማ፣ ሙሐመድን ብታጠባ እሷ ለሱ እናቱ ነች፡፡ ልጆቿም እህቶቹና ወንድሞቹ ናቸው፡፡ ሴቶች ልጆቿን እህቶቹ ስለሆኑ ሊያገባ አይፈቀድለትም፡፡ ነገር ግን ህጉ እሱን እንጂ የስጋ ወንድምና እህቶቹን አይመለከትም፡፡ ምክንያቱም የፋጢማ እናትነት ለሱ እንጂ ለነሱ አይደለምና፡፡
4. የጥቢ፞ ህግ እስከ መዋረስ፣ ቀለብ መስፈር፣ ለጋብቻ ሃላፊ (ወሊይ) መሆን አይደርስም፡፡ ማለትም ለምሳሌ በጥቢ፞ የተነሳ እናቱ ወይም አባቱ የሆነ ሰው ስለሞተ ንብረት መውረስ አይችልም፡፡ ለጥቢ፞ እህቱ የጋብቻ ወሊይ መሆን አይችልም። ለወላጅ እናቱ ቀለብ የመስፈር ግዴታ ስላለበት ዘካ መስጠት አይፈቀድለትም፡፡ ለጥቢ፞ እናቱ ግን ቀለብ ግዴታ ስላልሆነበት ዘካ መስጠት ይችላል፡፡
5. ጥቢ፞ ተከስቷል ወይስ አልተከሰተም በሚለው ላይ ጥርጣሬ ካለ መነሻ የሚሆነን ጥቢ፞ውን እንደሌለ መቁጠር ነው፡፡ በጥርጣሬ ላይ ተመርኩዘን የጥቢ፞ን ህግጋት አንተገብርም፡፡
የጥቢ፞ው መጠን ላይ ከተጠራጠርንም እርግጠኛ የሆንበትን ማለትም ዝቅተኛውን እንወስዳለን፡፡ [አልሙግኒ፣ ኢብኑ ቁዳማ: 7/537]
6· በጥቢ፞ ጉዳይ ታማኝ ከሆነች የአንዲት ሴት ምስክርነት ብቻውን በቂ ነው። ለምሳሌ አንዲት ሴት ቀርባ "ሁለቱንም አጥብቻቸዋለሁ" ካለች ምስክርነቷ ተቀባይነት አለው። ተጋብተው ከሆነ ይለያያሉ። [ቡኻሪይ: 2659]
7· የተብራራ ያልሆነ ድፍን ምስክርነት ተቀባይነት የለውም። ስለዚህ የጥቢ፞ውን ዘመንና ቁጥር በተጨባጭ መግለፅ ያስፈልጋል። ይሄ ባልሆነበት የጥቢ፞ን ህግጋት አንተገብርም። [አልሙግኒ፣ ኢብኑ ቁዳማ: 7/537]
አዋቂው አላ፞ህ ነው። እርምት ያለው ሰው ቢያጋራኝ ደስ ይለኛል።
(ኢብኑ ሙነወር፣ ረቢዑል አወል 17/1441)
(ህዳር 04/2012)
=
* የቴሌግራም ቻናል
https://t.me/IbnuMunewor
* የዋትሳፕ ቻናል፦
https://whatsapp.com/channel/0029VaA3X1e5kg7BlsJboa2M
* ፌስቡክ
https://www.facebook.com/Ibnu.Munewor?mibextid=ZbWKwL
Repost from Ibnu Munewor (ኢብኑ ሙነወር)
አስደናቂ ገጠመኝ ከሽይኽ ዐብዱረዛቅ አልበድር
=
የቴሌግራም ቻናል፡-
https://t.me/IbnuMunewor
ደርስ
~
* ሪያዱ ሷሊሒን
* ክፍል:- 1️⃣3️⃣6️⃣
* የኪታቡን ሶፍት ኮፒ (በ pdf ) በዚህ ሊንክ ማግኘት ትችላላችሁ
https://t.me/IbnuMunewor/3505
* የለቱ ደርስ መነሻ ገፅ 385፣ باب في الحث على سور وآيات مخصوصة
* የሚሰጥበት ቦታ፦ አሸዋ ሜዳ፣ መስጂደል ዋሊደይን
* የሚሰጥበት ጊዜ:- ረቡዕ፣ ሐሙስ እና ጁሙዐ
=
የቴሌግራም ቻናል፡-
https://t.me/IbnuMunewor
Repost from Ibnu Munewor (ኢብኑ ሙነወር)
አላህ ይሁነን!
~
አልኢማም አልአውዛዒይ - ረሒመሁላህ - እንዲህ ይላሉ፦
" 'የማያሙ፣ የማይመቀኙ እና የማይጠሉ ሰዎች የሚኖሩበት የሆነን ቤት መጎራበት እፈልጋለሁ' በማለት አንድን ሰው ጠየቅኩት።
ከዚያ ሰውየው ወደ መቃብር ወሰደኝና 'ይሄው እዚህ አሉልህ' አለኝ።"
📖 [ጃሚዑል ዑሉም ወልሒከም፡ 2/182]
Ibnu Munewor
=
* የቴሌግራም ቻናል
https://t.me/IbnuMunewor
