📚منهج السلف طريقنا الى الله 📚
Open in Telegram
↘️በዚህ ቻናል የሚተላለፉት ↘️በሱና ኡስታዞች የተቀሩ ደርሶች ↘️የሱና ኡስታዞች ሙሀደራዎች ↘️በመቀጠል አስተማሪ ፁሁፎች ➴➴➴➴➴➴➴➴➴➴➴➴ https://t.me/htt_asselfya
Show more3 819
Subscribers
-524 hours
+1617 days
+15530 days
Posts Archive
ደርስ
~
* መንሀጁ ሳሊኪን
* ክፍል:- 1️⃣8️⃣
* የደርሹ መነሻ፦ أوقات النهي
* የሚሰጥበት ቦታ፦ የሺ ደበሌ ከፍ ብሎ ሑዘይፋህ መስጂድ
* የሚሰጥበት ጊዜ፦ ዘወትር እሁድ ረፋድ ላይ
=
የቴሌግራም ቻናል፡-
https://t.me/IbnuMunewor
Repost from በሸይኽ ሙሐመድ ዘይን ተቀርተው ያለቁ ደርሶች
✅ አዲስ የተጠናቀቀ ደርስ
📚 የኪታቡ ስም :-
አልዑቡዲያህ / العبودية
✍ የኪታቡ አዘጋጅ :-
شيخ الإسلام ابن تيمية -رحمه الله-
ሸይኹል ኢስላም ኢብኑ ተይሚያህ -ረሒመሁሏህ-
🎙 በሸይኽ ሙሐመድ ዘይን ኣደም -ሐፊዘሁሏህ-
🎶 ከክፍል/01 እስከ ክፍል/37
ሊንኩን በመጫን ሙሉውን ደርስ ማግኘት ይችላሉ👇👇👇
https://t.me/SheikhMuhammedZain/2127
ደርስ
~
* ሪያዱ ሷሊሒን
* ክፍል:- 1️⃣4️⃣2️⃣
* የኪታቡን ሶፍት ኮፒ (በ pdf ) በዚህ ሊንክ ማግኘት ትችላላችሁ
https://t.me/IbnuMunewor/3505
* የለቱ ደርስ መነሻ ገፅ 417፣ باب تجويز صلاة الضحى من ارتفاع الشمس
* የሚሰጥበት ቦታ፦ አሸዋ ሜዳ፣ መስጂደል ዋሊደይን
* የሚሰጥበት ጊዜ:- ሐሙስ እና ጁሙዐ
=
የቴሌግራም ቻናል፡-
https://t.me/IbnuMunewor
Repost from Ibnu Munewor (ኢብኑ ሙነወር)
"ሒጃባችሁን ካላወለቃችሁ ፈተና ላይ አትቀመጡም!" - ዶክተር ዘላለም
በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የሰብዓዊ መብት ትምህርት መምህር ነው :: በዛሬው እለት 2ኛ አመት ተማሪዎችን final exam ይፈትን ዘንድ በገባበት ሒጃቢስቶችን ወይ ሂጃባችሁን አውልቁ ወይ ደግሞ ክላሱን ለቃችሁ ውጡ በማለት በእብሪት ተናግሯል :: የአንዲት እህትንም ሒጃብ ለማውለቅ ሙከራ አድርጓል :: ልትወጣ ስትል ተመለሺ ብሎ ተመልሳ ብትፈተንም እሷ ላይና ሌሎች ሒጃቢስቶች ላይ በሙሉ ፈርሟል ::
ድፍረት ነው ! ጋጠ ወጥነት ነው ! ሙስሊም ጠልነት ነው ! ጉዳዩን ጀመዓው ይዞ እስከ ጥግ ድረስ ይሄዳል :: መድረስ እስካለብን እንደርሳለን :: ሁላችሁም በንቃት ተከታተሉ ::
በሒጃባችን ላይ የሚሰነዘርን ምንም ነገር አንታገስም ! በየክላሳችሁ በሀይማኖታችን ላይ የሚቀረሹ መምህራን ካሉ በአላህ ይሁንባችሁ አትታገሷቸው :: በሚገባቸው ቋንቋ አናግሯቸው ::
ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ተማሪዎች
Repost from Ibnu Munewor (ኢብኑ ሙነወር)
የሚጮሁትን የማይኖሩ ጉዶች!
ክፍል - 4
~
ያያያዝኩት የባህሩ ተካ ንግግር ነው። የውሸት እርከኑን በዚህ መጠን ከፍ አድርጎታል። ውሸቱን ሲለማመደው ጊዜ "አንባቢ ይታዘበኛል" የሚለውንም ትቶታል። እንዲያው አንድ ሰው መስሎት ተሳስቶ ቢናገር ይሁን። ይሄ ሐያእ የቀለለው ፍጡር ግን በምን መልኩ ሰው ላይ እንደሚዋሽ ተመልከቱ። ሳዳት ነው ወደነዚህ አካላት የሚጣራው? በሐዲሥ እንደመጣው ከሙናፊቅ ምልክቶች ውስጥ ሁለቱ ሲያወሩ መዋሸት እና በሙግት ላይ አመፀኝነት ወይም ገልብጦ መወንጀል ነው። በነዚህ አጥፊዎች ላይ ረድ መስጠት ነው ወደነሱ መጣራት ተብሎ የሚገለፀው? ጥላቻ አናቱ ላይ ወጥቶ በትክክል ማየት እንዳይችል ጋርዶታል። በረድ ስም እየዋሸ መለጠፍ ጣፋጭ ምግብ ሆኖለታል። እጅ እጅ የሚል ፅሁፉን ውሸት ጣል ሲያደርግበት ውበትና ጥንካሬ የሚጨምር ይመስለው እንደሁ አላውቅም። "የሰካራም ግጥም ሁሌ ቅዳ ቅዳ" እንዲሉ ወጥሮ የውሸት አውቶማቲክ መተኮሱን ተያይዞታል። ረድ ማለት የጠሉት ሰው ላይ የፈለጉትን መለጠፍ ሆኗል ባህሩ ዘንድ። ሰው እንዴት በዚህ ደረጃ ውሸትን ስራዬ ብሎ አጥብቆ ይይዛል? ነብዩ ﷺ እንዲህ ብለዋል፦
وإِيَّاكُمْ والْكَذِبَ، فَإِنَّ الْكَذِبَ يَهْدِي إِلَى الْفُجُورِ، وإِنَّ الْفُجُورَ يَهْدِي إِلَى النَّارِ، ومَا يَزَالُ الرَّجُلُ يَكْذِبُ ويَتَحَرَّى الْكَذِبَ حَتَّى يُكْتَبَ عِنْدَ اللَّهِ كَذَّابًا
“አደራ ውሸትን ተጠንቀቁ! ውሸት ወደ ጥመት ይመራል፤ ጥመት ደግሞ ወደ እሳት ይመራል፡፡ አንድ ሰው ሲዋሽና ውሸትም ላይ ሲያተኩር አላህ ዘንድ ውሸታም ተብሎ ይመዘገባል።” [ቡኻሪይ እና ሙስሊም]
ሳዳትን በማጠልሸት ላይ እንቅልፍ ከምታጡ ራሳችሁን ከዚህ የውሸት ሱስ አውጡ። ሳዳት እናንተን ከነ ንዝንዛችሁ እርግፍ አድርጎ ትቶ አነሰም በዛም የራሱ ስራ ላይ ነው ያለው። ደግሞም በተለይ ተራውን ህዝብ በማንቃት ላይ ባለው አስተዋፅኦ አንዳችሁ እንኳ የሚስተካከል ቀርቶ የሚቀርብ ነገር የላችሁም። የራሳችሁን ድርሻ ባግባቡ እንደመወጣት ሰዎች የሱን ትምህርት እንዳይከታተሉ ጥላሸት መቀባትን ጂሃድ አድርጋችሁታል። ይሄ ነው የናንተ ስኬት።
ባህሩ ተካ እንደምታዩት ወንድማችን ሳዳትን ወደ "ቲክ – ቶክ መንደር ወርዶ ወጣቱን ወደ ዮኒ ማኛና ኢክራም አውቶሞቲቭ" ይጣራል እያለ ነው።
* ሳዳት ከአጥፊዎች ነው ያስጠነቀቀው። ባህሩ ደግሞ አጥፊዎቹን ጥሎ ሳዳትን መዝለፍ ላይ ነው የተጠመደው። ከአጥፊዎች ማስጠንቀቅ ወደነሱ መጣራት ከሆነ እንዳበደ ውሻ ሁሉን የምትናከሱት እናንተ አጥፊዎች ወደምትሏቸው እየተጣራችሁ ኖሯል ለካ? መቼም በራሳችሁ ጩኸት ስለደነቆራችሁ ሂሳባችሁ ምን እንደሚሰጥ አይገባችሁም።
* ምናልባት አጥፊዎቹን ፊት ለፊት ተገኝቶ መምከሩን ከሆነ ወደነሱ መጣራት የምትለው ይሄ ምን ያህል በልብህ ያረገዝከው ጥላቻ ነገሮችን የመረዳት አቅምህንም እንዳሽመደመደው ነው የሚያሳየው። እንዲያው አቀራረቡ ላይ ሂስ አለኝ ብትል እንኳ እንዳንተ አይነቱ በቆሻሻ የብሄር ካባ ተጀቡኖ የጉራጌ ካፊ'ሮች ጋር አንድነት ስለማድረግ የሚሰብክ ሰው ሂስ የመሰንዘሩን ድፍረት እንዴት ነው የሚያገኘው? የጥላቻ ብቅል ይህን ያክል ያሰክራል ለካ! የሚገርመው በዚህ መልኩ አይኑን በጨው አጥቦ እየዋሸ "ውሸታም" ተባልኩ ብሎ ሲብሰው ማየት ነው። የእውነት ህሊና ካለህ ከመባልህ ይልቅ መሆንህ ባስጨነቀህ ነበር። ያለበለዚያ ነገሮችን እየገለበጥክ ማየትህን ትቀጥላለህ። ጠቢቡ ኢብኑል ቀዪም ረሒመሁላህ ምን እንደሚሉ ተመልከት:-
إياك وَالْكذب فَإِنَّهُ يفْسد عَلَيْك تصور المعلومات على مَا هِيَ عَلَيْهِ وَيفْسد عَلَيْك تصورها وَتَعْلِيمهَا للنَّاس فَإِن الْكَاذِب يصور الْمَعْدُوم مَوْجُودا وَالْمَوْجُود مَعْدُوما وَالْحق بَاطِلا وَالْبَاطِل حَقًا وَالْخَيْر شرا وَالشَّر خيرا فَيفْسد عَلَيْهِ تصَوره وَعلمه عُقُوبَة لَهُ.
"ውሸትን ተጠንቀቅ። እሱ መረጃዎችን ባሉበት ሁኔታ (በትክክለኛ ቅርፃቸው) የመረዳት አቅምህን ይበክልብሃል። በተጨባጭ መሳልና ማሳወቅንም እንዲሁ ያበላሽብሃል። ውሸታም የሌለውን እንዳለ፣ ያለውን እንደሌለ፣ እውነቱን ሃሰት፣ ሃሰቱን እውነት፣ ኸይሩን ሸር፣ ሸሩን ደግሞ ኸይር አድርጎ ገልብጦ ያቀርባል። በውሸቱ ይቅቀጣ ዘንድ የመረዳት አቅሙም እውቀቱም ይበላሽበታል።" [አልፈዋኢድ፡ 135]
ውሸትን እንደ ፅድቅ ማየት የሚመጣው በዚህ ምክንያት ነው። "የማይበስል ጭንቅላት መብሰሉ ላይቀር የሰው ማገዶ ያስጨርሳል።"
=
የቴሌግራም ቻናል
https://t.me/IbnuMunewor
ደርስ
~
* ሪያዱ ሷሊሒን
* ክፍል:- 1️⃣4️⃣1️⃣
* የኪታቡን ሶፍት ኮፒ (በ pdf ) በዚህ ሊንክ ማግኘት ትችላላችሁ
https://t.me/IbnuMunewor/3505
* የለቱ ደርስ መነሻ ገፅ 410፣ باب استحباب الاضطجاع بعد ركعتي الفجر
* የሚሰጥበት ቦታ፦ አሸዋ ሜዳ፣ መስጂደል ዋሊደይን
* የሚሰጥበት ጊዜ:- ረቡዕ፣ ሐሙስ እና ጁሙዐ
=
የቴሌግራም ቻናል፡-
https://t.me/IbnuMunewor
ደርስ
~
* ሪያዱ ሷሊሒን
* ክፍል:- 1️⃣4️⃣0️⃣
* የኪታቡን ሶፍት ኮፒ (በ pdf ) በዚህ ሊንክ ማግኘት ትችላላችሁ
https://t.me/IbnuMunewor/3505
* የለቱ ደርስ መነሻ ገፅ 405፣ ሐዲሥ ቁ.1085
* የሚሰጥበት ቦታ፦ አሸዋ ሜዳ፣ መስጂደል ዋሊደይን
* የሚሰጥበት ጊዜ:- ረቡዕ፣ ሐሙስ እና ጁሙዐ
=
የቴሌግራም ቻናል፡-
https://t.me/IbnuMunewor
Repost from Ibnu Munewor (ኢብኑ ሙነወር)
የሚጮሁትን የማይኖሩ ጉዶች!
ክፍል - 3
~
ከሶስት አመት በፊት ኮምቦልቻ ላይ በተካሄደ ደውራ ላይ ከወንድሞች ጋር ተካፍዬ ነበር። በጊዜው አንድ ሸይኽ ከሳዑዲ በስልክ እንዲያስተምር ይደረጋል። በእለቱ እኔ የተሰጠኝን ላስተምር የተገኘሁ ተጋባዥ እንግዳ እንጂ የፕሮግራም አስተባባሪ አልነበርኩም። የሰውየውን ትምህርትም አልተከታተልኩም። እነዚህ ውሸት የቀለላቸው ፍጡሮች ግን ልክ ሰውየውን እኔ እንደጋበዝኩ አድረገው ደጋግመው መክሰሳቸውን ቀጥለዋል። እኔ ስለ ሰውየው አላውቅም ብልም እምቢ ብለው እየተቀባበሉት ነው። "ሞኝ እምቢ ብሎ ይረታል" ይባላል። አይናቸውን በጨው አጥበው ቀጥለዋል። የዚህ ቅጥፈት መነሻ የሆነው ፀሐፊ ያኔውኑ መጥቶ አናግሮኝ ስለ ሸይኹ የማውቀው ነገር እንደሌለ፣ እንዲቀርብ ያደረግሁትም እኔ እንዳልሆንሁ ተናግሬ ነበር። ይህንን ከማውራታችን ጋር ነው እንግዲህ እኔ እንደጋበዝኩ አድርጎ የፃፈው። የዚህን ቀጣፊ ወሬ ነው እነ በህሩ ተካ የሚቀባበሉት።
ሰውየው ማነው? ማንስ ጋበዘው?
ስሙ ዓዲል ብኑ ሙሐመድ አሱበይዒይ ይባላል። ይህንን ሸይኽ የጋበዘው ደግሞ ጠሀ ኸዲር ነው። ጠሀ ማለት የዚህ ሰካራም አንጃ አካል እንደሆነ ያዙ። ስለዚህ የጠሀ ቻናል ላይ ፍንጭ እንደማገኝ በማሰብ ገባሁ። ግምቴ ልክ ነበር።
1ኛ፦ ሸይኹን የጋበዝነው እኛ ከሆንን ከባድ ወንጀል ነው አይደል? እናንተስ ከሆናችሁ? ይሄው ሸይኹን የጋበዘው ጠሀ ኸዲር ነው። ራሱ በጊዜው የፃፈውን አያይዤላችኋለሁ። አሁንስ ክሱን ወደሱ ታዞራላችሁ?
2ኛ፦ ሸይኽየው እናንተ ዘንድ የጋበዘው ሳይቀር የሚወነጀልበት ከባድ የመንሀጅ ችግር ያለበት ነው ኣ? ይሄው ጠሀ ኸዲር ዘንድ ደግሞ ሰውየው ሌላ ነው። "ፈዲለቱ ሸይኽ"፣ "ሸይኻችን"፣ "አልሙጃሂድ"፣ "አልሙረቢ"፣ "አልዋሊድ"፣ "ፈዲለቱ ሸይኽ አልኡስታዝ አልሙሐዲሥ"፣ "ሸይኹነል ከሪም" እያለ በመግለፅ ደጋግሞ ያሰራጭለታል።
በነገራችን ላይ ስለ ሸይኹ ዛሬም ድረስ ክፉም ደግም አላውቅም። እንደሚሉት ችግር ያለበት ከሆነ ግን እነ ጠሀ ስንት ፊት እንዳላቸው ተመልከቱ። ሳዑዲ ሌላ፣ ኢትዮጵያ ሌላ። ሌላው ቀርቶ ሳዑዲ ኤምባሲ ወይም የሳዑዲ የባህል ማዕከል ዘንድ ራሱ ሌላ ፊት ነው ያላቸው። እዚያ የሚያልሙት መስለሐ ስላለ የሚቀርቡበት ሌላ ጭምብል አላቸው። ከኢኽዋን ቁንጮዎች ጋር አግድም ተሰልፎ ፎቶ መነሳትም ችግር የለውም። በፊጥራ ጥሪ ላይ ድንገተኛ መገጣጠም ብቻ እንደተከሰተ አድርጎ ባህሩ ተካ ፅፎ አይቻለሁ። ከዚያ እንዳይወጡ በጥበቃ ተከልከለው ነው ኣ? ከዚያም አፈሙዝ ደቅነው አንድ ላይ ተሰልፈው ፎቶ እንዲነሱ አደረጓቸው አይደል? የፊጥራውን እንለፈው። በቅርቡ የተካሄደው ኮንፈረንስ ፊጥራ አልነበረም። የዚህ ቡድን አባል የሆነው ኡስታዝ (ነዚፍ) ራሱ ድግሱ ላይ ፕሮግራም አቅራቢ ነበር። በህሩ እንደለመደው ነው እየዋሸ ያለው። እኔ እነዚህን ነጥቦች የማነሳው ለተብዲዕ አይደለም። ጩኸታቸውና ግብራቸው የማይገናኝ እንደሆነ ለመጠቆም ያህል ብቻ ነው።
ወደ ተነሳሁበት ስመለስ ሰዎቹ ራሳቸው ባቀረቡት ሰው ሰበብ ዞረው የሚናደፉ እባቦች ናቸው። ከላይ የተጠቀሰው ሸይኽ እንደሚሉት ችግር ያለበት ከሆነ ተጠያቂው ጦሀ ኸዲር ነበር። ሰውየው ችግር ያለበት ከመሆኑ ጋር "ሸይኻችን" እያለ የሚገልፀው፣ የቴሌግራም ቻናሉን የሚያስተዋውቅለት እሱ እንጂ እኛ አይደለንም። ከሰውየው ላይ ቁጭ ብሎ የሚማረው ራሱ ነው። ቢሆንም ቡድናዊ ያለመከሰስ መብት ስላለው አይነኩትም። ይባስ ብለው በሱ "ችግር" የሚከሰሰው ሌላ ነው።
አንዱ ይህንን ቅጥፈት እያሰራጨ ያለው በህሩ ተካ ነው። በህሩ ሲበዛ ውሸት የቀለለው ፍጡር ነው። እነዚህ ሰዎች ላይ እንዳጠቃላይ የማየው ችግር ስለ 'ረድ' ያላቸው ግንዛቤ በጣም የተንሻፈፈ መሆኑ ነው። የሚናገሩበትን ሰው ያጠልሽላቸው እንጂ እውነት ይናገሩ ውሸት አያስጨንቃቸውም። ችግራቸው በሚጠሉት አካል ላይ ሆነ ብለው የሚያሳድሩት ክፉ ቀስዳቸው ብቻ አይደለም። ንግግሮችን የሚረዱበት አቅምም ሲበዛ የወረደ ነው። ክፉ እሳቤ እና እጅግ የወረደ የመረዳት አቅም ከቅጥፈት ጋር ሲጣመር ውጤቱ አሁን እነሱ የሚያሳይቱን ይሰጣል።
=
የቴሌግራም ቻናል
https://t.me/IbnuMunewor
Repost from WKU Muslim student ጀምዓ(አስ ሰለፊይ)
ውድ ወደ ወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ አዲስ ለተመደባችሁ የሬሚዲያል ሙስሊም ተማሪዎች በሙሉ!!
አሰላሙ አለይኩም ወራህመቱሏሂ ወበረካትሁ
ወደ ወልቅጤ ዩኒቨርሲቲ በአቅም ማሻሻያ (remedial) ፕሮግራም አዲስ የተመደባችሁ ሙስሊም ተማሪዎች በሙሉ እንደሚታወቀው በ2016 ዓ.ም ወደ ወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ የተመደቡ የሬሚዲያል ተማሪዎች የመግቢያ ቀን ጥር 27 እና 28 2016 ዓ.ም እንደሆነ ይታወቃል።
ስለሆነም ይህን በማስመልከት የወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ተማሪዎች ጀመዓ እናንተን ሙስሊም ወንድምና እህቶቹን ተቀብሎ ማንኛውንም ዲናዊም ሆነ አካዳሚክ መረጃዎችን ለመስጠት እንዲሁም ስለሌሎች ሊያጋጥሟችሁ የሚችሉ አዲስ ነገሮች በሙሉ የሚያስፈልጓችሁን ድጋፍና ትብብር ለማድረግ ሙሉ ዝግጅታቸውን አድርገው የናንተን መምጣት ብቻ በጉጉት እየጠበቁ ይገኛሉ።
ስለዚህ ስለሚያስፈልጋችሁ ማንኛውም አይነት ጥያቄም ይሁን ትብብር ከዚህ በታች በተዘረዘሩት ስልኮች ደውላችሁ ሙሉ መረጃ ማግኘትና እና ያለምንም እንግድነት ስሜት ውድ ጀመዐችንን መቀላቀል ትችላላችሁ ስንል ትብብራችንን እንገልጻለን።
አላህ እኛንም እናንተንም ሰላም አድርጎ በሰላም እንዲያቀላቅለን እንጠይቀዋለን!!
1)ወንድም Yusuf A.
ስ.ቁ 09 67 62 30 89
2)ወንድም AWOL A
ስ.ቁ 09 60 37 36 34
3)ወንድም Abdulmejid M.
09 14 61 01 62
NB: እህቶች ከላይ ባሉት ስልኮች በመደወል የእህቶችን ስልክ ማግኘት ትችላላቹ!!!
Kabajamtoota barattoota muslimaa sirreeffamaa haaraa Yuunivarsiitii Wolqiteetti ramadamtan hundaa!!
Assalamu Alaikum Warahmatullahi Wobarekathu
Barattoota muslimaa sagantaa sirreeffamaatiin Yuunivarsiitii Wolqiteetti haaraa ramadamtan hundaaf, barattoonni sirreeffamaa Wolqiteetti ramadaman ta'uu beekuu barbaanna University in the year 2016 will enter on January 27 and 28, 2016. A.D. jedhamuun beekama
Kanaaf kana yaada keessa galchuun barattoonni muslimaa Yuunivarsiitii Wolqite isin obboleeyyan isaanii muslimaa ta'an isin simachuuf qophii guutuu ta'aniiru isin odeeffannoo amantaa ykn barnootaa kamiinuu yoo qabaattan, akkasumas deeggarsa fi tumsa isin barbaachisu hunda isiniif kennuuf, akkasumas dhufaatii keessan hawwii guddaan eeggachaa jirtu.
Kanaaf gaaffii ykn tumsa gosa kamiyyuu yoo barbaaddan bilbiloota armaan gaditti tarreeffaman bilbilaa, odeeffannoo guutuu argadhaatii miira keessummeessituu tokko malee Jama'aa keenya jaallatamotti makamaa
Obboleessa REMEDAN S.
Lakk 09 16 45 35 31
በጉራጊኛ ቋንቋ
የሙሽሪኮች ሙግት የውመል ቂያማህ።
___
🎤አቡ ሙሀመድ አብዱልናስር መኑር አል ጃቢሪይ
https://t.me/twhidsunabegegnea
ደርስ
~
* መንሀጁ ሳሊኪን
* ክፍል:- 1️⃣7️⃣
* የደርሹ መነሻ፦ باب صلاة التطوع
* የሚሰጥበት ቦታ፦ የሺ ደበሌ ከፍ ብሎ ሑዘይፋህ መስጂድ
* የሚሰጥበት ጊዜ፦ ዘወትር እሁድ ረፋድ ላይ
=
የቴሌግራም ቻናል፡-
https://t.me/IbnuMunewor
ደርስ
~
* ሪያዱ ሷሊሒን
* ክፍል:- 1️⃣3️⃣9️⃣
* የኪታቡን ሶፍት ኮፒ (በ pdf ) በዚህ ሊንክ ማግኘት ትችላላችሁ
https://t.me/IbnuMunewor/3505
* የለቱ ደርስ መነሻ ገፅ 400፣ ሐዲሥ ቁ.1068
* የሚሰጥበት ቦታ፦ አሸዋ ሜዳ፣ መስጂደል ዋሊደይን
* የሚሰጥበት ጊዜ:- ረቡዕ፣ ሐሙስ እና ጁሙዐ
=
የቴሌግራም ቻናል፡-
https://t.me/IbnuMunewor
Repost from Muhammed Sultan (أبو عائشة) Channel
ነገ በአላህ ፈቃድ የከሽፍ አሽሹቡሃት ደርስ ይጀመራል በአካል መገኘት በሚፈልግ አዲስ አበባ ቀራኒዮ ሁዘይፋ መስጅድ
https://t.me/ibnusultan38
Repost from Ibnu Munewor (ኢብኑ ሙነወር)
የሚጮሁትን የማይኖሩ ጉዶች!
ክፍል - 2
~
ሰለፎች ሙብተዲዕ ጋር አብሮ ከመቀማመጥ የከለከሉባቸው መረጃዎች በተጨባጭ አሉ። በርግጥ ከሰለፎች ከዚህ የተለየ ይዘት ያላቸው መረጃዎችም በተጨባጭ አሉ። ይህም ጉዳዩ 2 ሲደመር 2 ይሆናል አራት አይነት በጥሬው የሚያዝ እንዳልሆነ ይጠቁማል። (ራሱን ችሎ እመለስበታለሁ ኢንሻአላህ። እስከዚያ እንደለመዱት ይጩሁ።)
ለጊዜው ግን አንድ ነገር ላቅርብ። ያያዝኳቸውን ምስሎች ተመልከቱ። የመጀመሪያው ምስል ላይ በሰማያዊ የተጠቆመው፣ 2ኛው ላይ ደግሞ በቀይ የተጠቆመው የነሱ ሰዎች ናቸው።
ሙብተዲዕ ጋር ስለ መቀማመጥ ሰርክ የሚጮሁ ሰዎች የራሳቸው መስለሐ ያለበት ቦታ ግን እንዲህ ይጣዳሉ። የመጀመሪያው የባለፈው ረመዷን ሲሆን ሁለተኛው ደግሞ በቅርቡ የተደገመ ነው። ምስሉ ሲሰራጭ ጊዜ "ሸይኽ ፉላን ሰርግ ላይ መገኘት ይቻላል ብለዋል" የሚል ማመሀኛ አምጥተዋል።
1ኛ ነገር ይሄ ሰርግ አይደለም አታምታቱ።
2ኛ ነገር ሰርግስ ቢሆን ሴቶች ጋር ተቀላቅሎ መቀመጥ ይቻላል? (በቀይ የሸፈንኩት ሴቶች ናቸው። ቪዲየዎቹ ላይ ደግሞ በሰፊው ማየት ይቻላል።) ደግሞ አያፍሩም ይህንን ዘገባ ግድግዳቸው ላይ ይለጥፋሉ።
በተጨማሪም ዩሱፍ አሕመድም (ባህር ዳር) ከሸይኽ ሙሐመድ ዘይን ዘህረዲን ጋር ተቃቅፎ ሞቅ አድርጎ ሰላምታ ሲለዋወጥ ነበር። ቀደም ብሎም ከላይ ከሚታዩት ጋር ባንድ ላይ ፎቶ ተነስቷል።
በነገራችን ላይ ክፍለ ሃገር ላይ የመጅሊስ መዋቅር ውስጥ የገቡ አሉ። እሱን የምመጣበት ጊዜ አለኝ ፣ ኢንሻአላህ።
እና ቀመራችሁ እንዴት ነው? መለኪያችሁ ስሜት ብቻ ነው። የሰለፎች ንግግሮች የሚጠቀሱት እንዲሁ ለሽፋን ያህል ነው።
=
የቴሌግራም ቻናል
https://t.me/IbnuMunewor
የሚጮሁትን የማይኖሩ ጉዶች!
ክፍል - 1
~
ወንድማችን ሳዳት ከማል የነዚህን ከራሳቸው ጋር እንኳ የማይግባቡ ጉዶች የተሳከረ አካሄድ ሲነቅፍ ጊዜ "በጀርሕ እና ተዕዲል ዒልም ላይ ተሳለቀ" ብለው ላንቃቸው እስኪበጠስ ሲጮሁ ነበር። የተቸው የነሱን ቅጣንባሩ የጠፋው አካሄድ እንደሆነ ጠፍቷቸው አይደለም። ሆነ ብለው ጩኸታቸው እንዲደምቅላቸው እና ቂላቂሎችን ለመጥለፍ አላማ ነው በዚያ መልኩ ያቀረቡት። ይሄው የራሳቸው ሰው በነብዩ ﷺ ሐዲሥ ላይ ሲሳለቅ ስሙት። (ሂሳቡ የራሳችሁ ነው።)
ደግሞ አያፍሩም ይስቁለታል!
=
የቴሌግራም ቻናል
https://t.me/IbnuMunewor
Repost from Ibnu Munewor (ኢብኑ ሙነወር)
ኢኽ^ዋንን በጨረፍታ፣ በዑለማዎች እይታ
~
ልብ በሉ! የማቀርበው የዑለማኦችን ንግግር እንጂ የራሴን አይደለም። ይህንን የማሳስበው ኢኽዋን ሲነካ ደርሰው አራስ ነብር ለሚሆኑ አካላት ለአፍታ ቆም ብለው ጉዳዩን እንዲያጤኑት ለማስታወስ ነው። አብዛኞቹ ኢኽዋን ሲነካ የሚንጨረጨሩ ወገኖቻችን በተሳሳተ ስብከት ስለተሞሉ እንጂ ለሐቅ ጥላቻ ኖሯቸው አይደለም። ስለዚህ ጉዳዩን ከተለያዩ አቅጣጫዎች እንዲመለከቱ በማገዝ ከሰመመናቸው እንዲነቁ መስራት ያስፈልጋል። ከነዚህ መንገዶች ውስጥ አንዱ ደግሞ የዑለማእ ንግግሮችን ማሳየት ነው። በኢኽዋን ክፉ ስብከት ተበክለው ዑለማኦችን እስከመወንጀል የደረሱ ቢኖሩም ዛሬም ድረስ ለታላላቅ የሱና ዑለማኦች ክብር ያላቸው ወገኖቻችን ቀላል አይደሉም። ወደ ዑለማኦቹ ንግግር አልፋለሁ።
1. አሕመድ ሻኪር (ግብፃዊ)፡-
“የሸይኽ ሐሰን አልበና እና የሙስሊም ወንድማማቾቹ ንቅናቄ የኢስላማዊ ደዕዋን ወደ አፍራሽ የጥፋት ደዕዋ የገለበጡ ናቸው። ኮሙኒስቶች እና አይሁዳውያን እንደሚረዱት በተጨባጭ እናውቃለን።” [ሹኡኑ ተዕሊም ወልቀዷእ፡ 48]
2. ኢብኑ ባዝ፡-
“አላህ መልካም ይዋልልዎትና ህዝቦቼ ወደ 73 ቡድኖች ይከፋፈላሉ። አንዷ ስትቀር ሁሉም የእሳት ነው የሚለውን የነብዩ ﷺ ሐዲሥ መሰረት በማድረግ ሺርካ ሺርክና ቢድዐዎች ያለባቸው የተብሊግ ቡድን እና ቡድንተኝነትና በመሪዎች ላይ በማመፅ ሰሚና ታዛዥ ባለመሆን ልዩነት የሚፈጥሩት ኢኽዋነል ሙስሊሚን እነዚህ ሁለት አንጃዎች ከጠፊዎቹ አንጃዎች ውስጥ ይካተታሉን?”
መልስ፡- ከ72ቱ ውስጥ ይገባሉ። የአህሉ ሱናን ዐቂዳ የጣሰ ከ72ቱ ውስጥ ይገባል። “ህዝቦቼ” ሲሉ የተፈለገው ለጥሪያቸው አዎንታዊ መልስ የሰጡትና እሳቸውን መከተልን ያንጸባረቁትን ነው። እነዚህም 73 ናቸው። የምትድነዋ ያቺ የተከተለቻቸውና በዲናቸውም ላይ የፀናችው ናት። በ72ቱ ውስጥ ግን ከ ሃ ዲም ይኖራል፤ ወንጀለኛ ይኖራል። ሙብተዲዕም ይኖራል። ብዙ ክፍል ነው።
ጠያቂ፡- ስለዚህ እነዚህ ሁለት አንጃዎች ከ72ቱ (ጠፊ አንጃዎች) ውስጥ ይገባሉ ማለተ ነው?”
ኢብኑ ባዝ፡- አዎ! ከ72ቱ ውስጥ ናቸው።” [ሸርሑል ሙንተቃ የካሴት ቅጂ]
ይሄ ፈትዋ ከመሞታቸው ሁለት አመት ወይም ከዚያ ባነሰ ጊዜ ጧኢፍ ውስጥ የተናገሩት ነው።
3. ሸይኽ ሙቅቢል አልዋዲዒይ (የመናዊ)፡-
ጥያቄ፡- በዘመናችን የሚገኙት የሱሩሪያና የኢኽ^ዋን ቡድኖች ከሱና ከሚወጡ ቡድኖች ውስጥ ናቸውን?”
መልስ፡- ከአህሉ ሱና አይቆጠሩም። ክብረ ቢስ ናቸው። የሚቀረው በተናጠል አባላቶቻቸው ላይ ብይን መስጠት ነው። አባሎቻቸው ላይ በተናጠል ብይን መስጠት አንችልም። ምክንያቱም አላዋቂ መሀይም ሊሆን ይችላልና። የኢኽ^ዋንና የሱሩሪያን ሰበካ የሚያውቅ ወደዚያ የሚጣራና ለነሱ በጭፍን የሚሞግት የሆነው ቁንጮ ግን እሱ ከምትድነዋ አንጃ ውስጥ አይደለም ልንል ይቻለናል።” [ቱሕፈቱል ሙጂብ፡ 10]
ጥያቄ፡- ከኢኽ^ዋን አልሙስሊሚን አንፃር የአህሉ ሱና ወልጀማዐ አቋም ምን ሊሆን ይገባል?”
መልስ፡- ከኢኽ^ዋን አልሙስሊሚን አንፃር የአህሉ ሱና ወልጀማዓ አቋም መንገዳቸው የፈጠራ መንገድ እንደሆነ ይፈርዳሉ። በተናጠል አባላቱ ዘንድ ስንመጣ መንገዱን ካወቀ በኋላ የሚፀናበትም እንዲሁ ሙብተዲዕ ነው። መንገዱን ሳያውቅ እንዲሁ ኢስላምንና ሙስሊሞችን እረዳለሁ ብሎ የሚያስብ ግን እንደ ስህተተኛ ይቆጠራል።” [ቱሕፈቱል ሙጂብ፡ 10]
ሐሰን አልበና እና ሰይድ ቁጥብ ወደ አላህ በሚደረገው ጥሪ ላይ ኢማሞች (መሪዎች) ናቸው የሚል አለ” ተብለው ሲጠየቁ “አዎ ኢማሞች ናቸው። ነገር ግን ኢማምነታቸው ለቢድዐ ባለቤቶች ነው…” ብለው ነው የመለሱት።
4. ሸይኽ ፈውዛን
ጥያቄ፡- እነዚህ አንጃዎች ከ72ቱ ጠፊ አንጃዎች ውስጥ ይገባሉን?
መልስ፡- አዎ። ወደ ኢስላም ራሱን ከሚያስጠጋ ውስጥ በደዕዋ ወይም በዐቂዳ ወይም በሆነ የኢማን መሰረቶች ውስጥ የአህሉ ሱና ወልጀማዐን ዐቂዳ የሚጣረስ ሁሉ ከ72ቱ አንጃዎች ውስጥ ይገባል። ዛቻውም ይመለከተዋል። በተቃርኖው ልክ ውግዘትና ዛቻም ይኖረዋል።” [አልአጅዊባ]
5. ሸይኽ ዐብዱል ሙሕሲን አልዐባድ
ስለተብሊግና ኢኽ^ዋን ቡድኖች ሲጠየቁ እንዲህ ብለው መልሰዋል፡-
እነዚህ የተለያዩ አዳዲስ ቡድኖች መጤዎች ናቸው። በ14ኛው ክ/ዘመን ነው የተወለዱት። … ለምሳሌ የኢኽዋን ቡድን ከነሱ ዘንድ የገባ ወዳጃቸው ነው። ይወዳጁታል። ከነሱ ያልሆነን ከሱ ተቃራኒ ይሆናሉ። ከነሱ ጋር ከሆነ ግን ቆሻሻ ከሆኑ የአላህ ፍጡሮች ቢሆንም፣ ራ*ፊ*ዳ (ሺዐ) ቢሆንም ወንድማቸው ወዳጃቸው ነው። ለዚህም ነው አካሄዳቸው ያለፈ ያገደመን የሚሰበስበው። ሶሐባን የሚጠላ ራ*ፊ*ዲ ለምን አይሆንም?!...” [ፈታወል ዑለማእ ፊልጀማዓት ወአሠሪሃ ፊ ቢላዲል ሐረመይን]
6. ሷሊሕ ኣሊ ሸይኽ
የኢኽ^ዋን አልሙስሊሚን ቡድንን በተመለከተ ጎላ ካሉ መታወቂያዎቻቸው ውስጥ አንዱ ትክክለኛ ማንነታቸውን መደበቅ፣ መለዋወጥ፣ ይጠቅመናል ብለው የሚያስቡት ዘንድ መቀራረብ፣ ትክክለኛ ገፅታቸውን ግልፅ አለማውጣት ነው። ማለትም በሆነ በኩል ሲታይ ባ*ጢ*ኒ*ያ ናቸው።…
ሌላኛው ኢኽዋኖችን ከሌሎች የሚለያቸው እነሱ ሱናን አያከብሩም። የሱና ሰዎችንም አይወዱም። ምንም እንኳን ይህንን አደባባይ ባያወጡትም። ግና በተጨባጭ ሱናን አይወዱም። ወደሱና ሰዎችም አይጣሩም። ..” [ፈታወል ዑለማእ ፊልጀማዓት ወአሠሪሃ ፊ ቢላዲል ሐረመይን] የቻለ ሙሉውን ይስማ።
ይህንን እንደ ሰደድ እሳት የተሰራጨ ብልሹ አስተሳሰብ የዑለማዎችን ፈትዋዎች በማጣቀስ፣ የኢኽ^ዋኖች ከባባድ የዐቂዳ ጥፋቶችን ሚዛናዊ የሆነና ለዐቂዳው ዋጋ የሚሰጥ ሰው አይቶ እንዲፈርድ በማቅረብ ማጋለጥ ያስፈልጋል። አቡበክር ብኑ ዐያሽ ረሒመሁላህ “ሱኒይ ማነው?” ተብለው ሲጠየቁ ሱኒይ ማለት “ስሜቶች (ቢድዐዎች) ሲወሱ (ሲጋለጡ) ለየትኛዋም ወግኖ የማይቆጣ ነው” ይላሉ። [አሸሪዐህ፡ ቁ.፡ 2112]
=
(ኢብኑ ሙነወር፣ የካቲት 02/2009)
* የቴሌግራም ቻናል
https://t.me/IbnuMunewor
* የዋትሳፕ ቻናል፦
https://whatsapp.com/channel/0029VaA3X1e5kg7BlsJboa2M
* ፌስቡክ
https://www.facebook.com/Ibnu.Munewor?mibextid=ZbWKwL
