en
Feedback
📚منهج السلف طريقنا الى الله 📚

📚منهج السلف طريقنا الى الله 📚

Open in Telegram

↘️በዚህ ቻናል የሚተላለፉት ↘️በሱና ኡስታዞች የተቀሩ ደርሶች ↘️የሱና ኡስታዞች ሙሀደራዎች ↘️በመቀጠል አስተማሪ ፁሁፎች ➴➴➴➴➴➴➴➴➴➴➴➴ https://t.me/htt_asselfya

Show more
3 819
Subscribers
-524 hours
+1617 days
+15530 days
Posts Archive
ወስን ~ በጫትና በመጠጥ ሱስ ቤትህን እያፈረስክ፣ ልጆችህን እየበተንክ፣ የራስህንም ሆነ የቤተሰብህን ጥሪት እያወደምክ ያለኸው ወገኔ ሆይ! አይበቃም ወይ? እስከ መቼ ቁልቁል እያምዘገዘገህ ባለ ደባል ሱስ ተሸንፈህ ትኖራለህ? ሰው እንዴት የሰው እጅ ጠባቂ ሆኖ ይቅማል? ሰው እንዴት ይህንን የአህያ ሽንት የመሰለ እር.ኩስ መጠጥ ይጠጣል? ሰው እንዴት በገዛ ፈቃዱ ቀጥ ብሎ ወጥቶ እየተንገዳገደ ይመለሳል? ግዴለህም አላህን ፍራ! ለጤናህ አስብ። ለቤተሰብህ አስብ። ለትዳርህ አስብ። ለልጆችህ አስብ። በየሰው ቤት እየተንከራተቱ ገንዘብ ለሚልኩልህ አስብ። ስንት መከራ፣ ስንት ፈተና፣ በረሃ፣ እሳት፣ የሰው ፊት፣ ... አይተው፣ አሳር በልተው የሚልኩትን ገንዘብ ለማይረባ ቅጠል ስታውለው አያሳዝኑህም? ከምንም በላይ ደግሞ ለኣኺራህ አስብ። ወላሂ ከቆረጥክ ማቆም ይቻላል። ብቻ አንተ ወስን። ከዚያም ሰበብ አድርስ። ከልብ ካለቀሱ እምባ አይገድም። Ibnu Munewor = * የቴሌግራም ቻናል https://t.me/IbnuMunewor * የዋትሳፕ ቻናል፦ https://whatsapp.com/channel/0029VaA3X1e5kg7BlsJboa2M * ፌስቡክ https://www.facebook.com/Ibnu.Munewor?mibextid=ZbWKwL

ከረጀብ ወር ጋር የሚያያዙ ደካማ ሐዲሦች ~ ከረጀብ ጋር ብዙ መሰረተ ቢስ ቅጥፈቶችና ደካማ ሐዲሦች አሉ። ለምሳሌ ያክል፦ [1ኛ]፡- رجب شهر الله وشعبان شهري ورمضان شهر أمتي “ረጀብ የአላህ ወር ነው። ሸዕባን የኔ ወር ነው። ረመዷን ደግሞ የህዝቦቼ ወር ነው።” አልባኒይ ደካማ እንደሆነ ገልፀዋል። [አዶዒፋህ፡ 4400] [2ኛ]፡- ረጀብ ሲገባ እንዲህ ይሉ ነበር፡- اللهم بارك لنا في رجب وشعبان، وبلغنا رمضان “አላህ ሆይ! ረጀብንና ሸዕባንን ባርክልን። ረመዷንም አድርሰን።” ነወዊይ በ“አዝካር”፣ ዘሀቢይ በ“ሚዛን”፣ ኢብኑ ሐጀር በ"ተብዪኑል ዐጀብ" ደካማ እንደሆነ ብይን የሰጡ ሲሆን አልባኒይም “ደካማ ነው” ብለዋል። [ዶዒፉል ጃሚዕ፡ 4395] [3ኛ]፡- فضل شهر رجب على الشهور كفضل القرآن على سائر الكلام “የረጀብ ወር በሌሎች ወራት ላይ ያለው ብልጫ ቁርኣን በሌሎች ንግግሮች ላይ እንዳለው ብልጫ ነው።” ኢብኑ ሐጀር፣ ሙላ ዐሊይ አልቃሪ፣ አልዐጅሉኒይ፣ አልገዚይ እና አዘርቃኒይ “መሰረተ ቢስ ቅጥፈት ነው" (መውዱዕ) ብለዋል። [4ኛ]፡- خمس ليال لا ترد فيهن الدعوة أول ليلة من رجب، وليلة النصف من شعبان، وليلة الجمعة، وليلة الفطر، وليلة النحر “አምስት ሌሊቶች በነሱ ውስጥ የተደረገ ዱዓእ አይመለስም። የመጀመሪያው የረጀብ ሌሊት፣ የሸዕባን አጋማሽ ሌሊት፣ የጁሙዐ ሌሊት፣ የዒደል ፊጥር ሌሊት እና የዒደል አድሓ ሌሊት ናቸው።” አልባኒይ “መሰረተ ቢስ” ብለውታል። [አዶዒፋህ፡ 1452] [ዶዒፉል ጃሚዕ፡ 2852] [5ኛ]፡- رجب شهر عظيم يضاعف الله فيه الحسنات، فمن صام يوما من رجب، فكأنما صام سنة، ومن صام منه سبعة أيام، غلقت عنه سبعة أبواب جهنم، ومن صام منه ثمانية أيام، فتحت له ثمانية أبواب الجنة، ومن صام منه عشرة أيام، لم يسأل الله شيئا إلا أعطاه إياه، … “ረጀብ አላህ መልካም ምንዳዎችን የሚያነባብርበት ታላቅ ወር ነው። ከረጀብ አንድ ወር የፆመ ሰው አመት እንደፆመ ነው። ከሱ ሰባት ቀናትን የፆመ ሰባቱ የጀሀነም በሮች ይዘጉለታል። ከሱ ስምንት ቀናትን የፆመ ስምንቱ የጀነት በሮች ይከፈቱለታል። ከሱ አስር ቀናትን የፆመ አላህን የሆነ ነገር አይጠይቅም፣ እሱኑ የሰጠው ቢሆን እንጂ፣ …” አልባኒይ “መሰረተ ቢስ” ብለውታል። [አዶዒፋህ፡ 5413] [6ኛ]፡- إن في الجنة نهرا يقال له رجب ماؤه أشد بياضا من اللبن وأحلى من العسل من صام يوما من رجب سقاه الله من ذلك النهر “በጀነት ውስጥ ረጀብ የሚባል ወንዝ አለ። ውሃው ከወተት የነጣ፣ ከማር የጣፈጠ ነው። ከረጀብ አንድ ቀን የፆመ ሰው አላህ ከዚያ ወንዝ ያጠጣዋል።” አልባኒይ “መሰረተ ቢስ” ብለውታል። [ዶዒፉል ጃሚዕ፡ 1902] [7ኛ]፡- صوم أول يوم من رجب كفارة ثلاث سنين، والثاني كفارة سنتين، والثالث كفارة سنة، ثم كل يوم شهرا “የረጀብን የመጀመሪያ ቀን መፆም የሶስት አመት ወንጀል ያብሳል። ሁለተኛው የሁለት አመት ያብሳል። ሶስተኛው ደግሞ የአመት ያብሳል። ከዚያም እያንዳንዱ ቀን የወር ነው።” አልባኒይ ደካማ ብለውታል። [ዶዒፉል ጃሚዕ፡ 3500፣ 5649] [8ኛ]፡- لا تغفلوا عن أول جمعة من رجب فإنها ليلة تسميها الملائكة الرغائب “ከረጀብ የመጀመሪያ ጁሙዐ አትዘናጉ። እርሷ መላእክት ‘አረጋኢብ’ ብለው የሚጠሯት ሌሊት ነች።” ‘ሶላተ ረጋኢብን’ በተመለከተ ነወዊይ እንዲህ ብለዋል፡- “እርሷን የፈጠረን ሰው አላህ ይርገመው! እርሷ አስቀያሚ ቢድዐ ነች!” [ሸርሑ ሙስሊም] በተጨማሪም እሷንና የሸዕባን አጋማሽ ሌሊት ሶላትን አስመልክተው “… ቢድዐና አስቀያሚ ፈጠራዎች ናቸው። በ‘ቁቱል ቁሉብ’፣ ‘ኢሕያእ ዑለሚዲን’ ኪታብ ውስጥ ስለተጠቀሱ ማንም እንዳይሸወድ። እነሱን በሚጠቁመው ሐዲሥም እንዲሁ (እንዳይሸወድ)። ምክንያቱም ሁሉም ውድቅ ነውና” ብለዋል። [አልመጅሙዕ፡ 3/548] [9ኛ]፡- أن رسول الله -ﷺ- لم يصم بعد رمضان إلا رجبًا وشعبان “የአላህ መልእክተኛ ከረመዷን በኋላ ረጀብንና ሸዕባንን እንጂ አልፆሙም።” ኢብኑ ሐጀር በጣም ደካማ ነው ብለውታል። [ተብዪኑል ዐጀብ፡ 12] [10ኛ]፡- من صلى المغرب في أول ليلة من رجب ثم صلى بعدها عشرين ركعة يقرأ في كل ركعة بفاتحة الكتاب، وقل هو الله أحد مرة، ويسلم فيهن عشر تسليمات، أتدرون ما ثوابه؟ قال: حفظه الله في نفسه وأهله وماله وولده، وأجير من عذاب القبر، وجاز الصراط كالبرق بغير حساب ولا عذاب “በረጀብ የመጀመሪያ ሌሊት መግሪብን ሰግዶ ከዚያም በእያዳንዷ ረከዐ ፋቲሐንና ቁል ሁላሁ አሐድን አንድ ጊዜ እየቀራ፣ በአስር ተስሊማት እያሰላመተ ሃያ ረከዐ የሰገደ ሰው ምንዳው ምን እንደሆነ ታውቃላችሁ? አላህ በነፍሱም፣ በቤተሰቡም፣ በገንዘቡም፣ በልጁም ይጠብቀዋል። ከቀብር ቅጣትም ይጠበቃል። ሲራጥንም ያለ ሂሳብና ያለ ቅጣት እንደ ብልጭታ ያቋርጧል።” ኢብኑል ጀውዚና ኢብኑ ሐጀር መሰረተ ቢስ ቅጥፈት እንደሆነ ገልፀዋል። [አልመውዱዓት፡ 2/123] [ተብዪኑል ዐጀብ፡ 20] [11ኛ]፡- من صام من رجب وصلى فيه أربع ركعات ... لم يمت حتى يرى مقعده من الجنة أو يُرى له “ከረጀብ ፁሞ፣ በሱ ውስጥ አራት ረከዓዎችን የሰገደ ሰው … በጀነት ውስጥ መቀመጫውን ሳያይ ወይም ሳይታይለት አይሞትም።” ኢብኑል ጀውዚና ኢብኑ ሐጀር መሰረተ ቢስ ቅጥፈት እንደሆነ ገልፀዋል። [አልመውዱዓት፡ 2/124] [ተብዪኑል ዐጀብ፡ 21] [12ኛ]፡- إن شهر رجب شهر عظيم، من صام منه يومًا كتب الله له صوم ألف سنة ... “የረጀብ ወር ታላቅ ወር ነው። ከሱ አንድ ቀን የፆመ ሰው አላህ አንድ ሺ አመት ፆም ይመዘግብለታል።” ኢብኑል ጀውዚና ኢብኑ ሐጀር መሰረተ ቢስ ቅጥፈት እንደሆነ ገልፀዋል። [አልመውዱዓት፡ 2/206-207] [ተብዪኑል ዐጀብ፡ 26] ከረጀብ ጋር የሚያያዙት ዘገባዎች እነዚህ ብቻ አይደሉም። እነዚህን ለምሳሌ ያክል ይዘን ሌሎቹንም ጭምር በሚመዝን የዓሊሞች ንግግር ልቋጭ:— 1/ አልሓፊዝ ኢብኑ ሐጀር - ረሒመሁላህ - “የረጀብን ወር ልዩ ብልጫም፣ መፆሙን ወይም ከፊሉን በተለየ እንዲፆም፣ ወይም ከሱ ውስጥ የተገደበን ሌሊት በሶላት ማሳለፍን፣… የሚጠቁም ለማስረጃነት የሚበጅ ትክክለኛ ሐዲሥ አልተላለፈም" ብለዋል። [ተብዪኑል ዐጀብ፡ 6 እና 8] 2/ አልሓፊዝ አቡ ዐብዲላህ ሙሐመድ ኢብኑ አቢ በክር አዲመሽቂይ (691 ሂ.) ደግሞ “እያንዳንዱ የረጀብን ፆም እና ከፊል ሌሊቶቹን መስገድን የሚጠቁም ሐዲሥ ውሸት፣ ቅጥፈት ነው” ብለዋል። [አልመናሩል ሙኒፍ፡ 1/96] ልብ በሉ! በዚህ ወር ውስጥ ፆምና ሶላት አይኑር ለማለት አይደለም። ወሩን ከሌሎቹ ወራት በተለየ መልኩ መያዝ አይገባም ነው አጠቃላይ ጭብጡ። Ibnu Munewor = * የቴሌግራም ቻናል https://t.me/IbnuMunewor

“አሁንም ቀድሞ በነበረበት ነው።” ~ የአላህን ከዐርሹ በላይ መሆን የሚያስተባብሉ ሰዎች ከሚያጣቅሷቸው “መረጃዎቻቸው” ውስጥ አንዱ እንዲህ የሚል ነው፦ كَانَ اللَّهُ وَلَا شَيْءَ مَعَهُ ‌وَهُوَ ‌الْآنَ ‌عَلَى ‌مَا ‌عَلَيْهِ ‌كَانَ “አላህ ነበር። ከሱ ጋር ምንም አልነበረም። እርሱ አሁንም ቀድሞ በነበረበት ነው።” የመጨረሻውን ክፍል አሽዐሪዮች በሰፊው ያራግቡታል። እነሱ ዘንድ ሙስሊም ከዘገቡት ሐዲሡል ጃሪያ በላይ ዋጋ አለው። እንዲያውም አንዳንዶቹ ቡኻሪ ውስጥ ከሚገኝ ሐዲሥ ላይ በማያያዝ ሶሒሕ ቡኻሪ ውስጥ የሚገኝ አስመስለው ሲያወሩት ያጋጥማል። ይሄ የለየለት ማጭበርበር ነው። ቡኻሪ ውስጥ ቀርቶ የትኛውም የሐዲሥ ድርሳን ውስጥ አይገኝም። በሶሒሕ ይቅርና በደካማ ሰነድም አይታወቅም። ኢብኑ ሐጀር አልዐስቀላኒይ - ረሒመሁላህ እንዲህ ይላሉ፦ وَقَعَ فِي بَعْضِ الْكُتُبِ فِي هَذَا الْحَدِيثِ كَانَ اللَّهُ وَلَا شَيْءَ مَعَهُ وَهُوَ الْآنَ عَلَى مَا عَلَيْهِ كَانَ وَهِيَ زِيَادَةٌ لَيْسَتْ فِي شَيْءٍ مِنْ كُتُبِ الْحَدِيثِ نَبَّهَ عَلَى ذَلِكَ الْعَلَّامَةُ تَقِيُّ الدِّينِ بْنُ تَيْمِيَةَ وَهُوَ مُسَلَّمٌ فِي قَوْلِهِ وَهُوَ الْآنَ إِلَى آخِرِهِ “በአንዳንድ ኪታቦች ውስጥ በዚህ 'አላህ ነበር። ከሱ ጋር ምንም አልነበረም' በሚለው ሐዲሥ ላይ 'እርሱ አሁንም ቀድሞ በነበረበት ነው' የሚል ገብቷል። ይቺ ግን በየትኛውም የሐዲሥ ኪታቦች ውስጥ የማትገኝ ጭማሬ ናት። ይህንንም ታላቁ ሊቅ ተቂዩዲን ኢብኑ ተይሚያ ጠቁመውታል። 'እርሱ አሁንም ቀድሞ በነበረበት ነው፤ ...' በሚለው ላይ የሳቸው ንግግር እጅ የሚሰጥለት (ተቀባይነት ያለው) ነው።” [ፈትሑል ባሪ፡ 6/289] “ታዲያ በሐዲሥ ድርሳናት ውስጥ ከሌለ ከየት አመጡት?” ከተባለ ሌላ አንድ ጥቅሳቸውን ልጨምርና አብሬ እመልሳለሁ። እርሱም እንዲህ የሚል ነው፦ إن الله تعالى خلق العرش إظهارًا لقدرته لا مكانا لذاته “የላቀው አላህ ዐርሹን የፈጠረው ችሎታውን ለማሳየት እንጂ ለዛቱ ቦታ እንዲሆን አይደለም።” እነዚህን ሁለት ጥቅሶች ዐሊይ ብኑ አቢ ጧሊብ የተናገሯቸው ናቸው በማለት ያወራው ዐብዱል ቃሂር አቡ መንሱር አልበግዳዲ ነው። [አልፈርቅ በይነል ፊረቅ፡ 321] ሰነድ አለው ወይ? በጭራሽ! በ429 ሂ. በሞተው አቡ መንሱርና በ40 ሂ. በሞቱት ዐሊይ መካከል የ 389 አመት ርቀት አለ። ቅብብሎሹን የሚያሳይ ሰነድ ከሌለ በየት አቆራርጦ ነው ከዐሊይ የሚሰማው? ይህንን “ዶዒፍ” እንኳን መባል የሚበዛበት ውዳቂ ወሬ ነው ለዐቂዳቸው ማስረጃ የሚያደርጉት። እንግዲህ ተመልከቱ! የቁርኣንና ሐዲሥ ጉልህ መልእክት በአላህ ሲፋት ላይ ማስረጃ አይሆኑም የሚሉ ጉዶች፣ ለሶሒሕ ቡኻሪና ሶሒሕ ሙስሊም እጅ የማይሰጡ ፍጡሮች ናቸው እንዲህ አይነቱን ወፍ ዘራሽ ወሬ ለዐቂዳቸው እማኝ አድርገው የሚያቀርቡት! ደግሞኮ አቡ መንሱር የሐዲሥ ሊቅ አይደለም። ይልቁንም ከሐዲሥ ይልቅ ዐቅሉን የሚያስቀድም የዒልመል ከላም ፍልስፍና አራማጅ ነው። ምን እንደሚል አይታችሁ ፍረዱ፦ “አንድ ዘጋቢ አእምሮ የማይቀበለው ነገር ከዘገበ እና ትክክለኛ በሆነ መልኩ ተእዊል ለማድረግ (ለመቆልመም) ካልተመቸ ዘገባው ውድቅ ይሆናል። … ታማኝ የሆነው ዘጋቢ የዘገበው ሐዲሥ ጉልህ መልእክቱ አእምሮን የሚያስደነግጥ ከሆነና ነገር ግን ከአእምሯዊ ጉዳዮች ጋር በሚስማማ መልኩ ማዞር (መቆልመም) የሚቻል ከሆነ ዘገባውን ተቀብለን ከአእምሮ ጋር እንዲስማማ አድርገን መልእክቱን እናዞረዋለን (እንቆለምመዋለን)።” [ኡሱሉዲን፡ 23] ሐዲሥ ላይ ብይን ለመስጠት ያስቀመጠውን መስፈርት ተመልከቱ። የሐዲሥ ጥናት ሳይሆን የነሱን በፍልስፍና የተበከለ አእምሮ። ከቻሉ መረጃዎቹን እየቆለመሙ ሌላ ትርጉም መስጠት። ይህንን ነው ተእዊል የሚሉት። ለቁልመማ ፈፅሞ የማይመቹ ከሆኑ እንዲሁ “ዶዒፍ ናቸው” ብሎ መጣል! በቃ! በዚህ መልኩ ሶሒሕ ሐዲሥ ላይ የሚፈርድ ሰው ብልሹ እምነቱን ለማፅናት ግን ሰነድ አልባ ወሬ በዐሊይ ስም ያወራል። ከዚያ እንዲህ አይነቱን ከንቱ ወሬ በማስቀደም የቁርኣንና የሐዲሥ ማስረጃዎችን ይጥላሉ። ይሄ የጤና ነው? Ibnu Munewor = * የቴሌግራም ቻናል https://t.me/IbnuMunewor * የዋትሳፕ ቻናል፦ https://whatsapp.com/channel/0029VaA3X1e5kg7BlsJboa2M * ፌስቡክ https://www.facebook.com/Ibnu.Munewor?mibextid=ZbWKwL

ደርስ ~ * መንሀጁ ሳሊኪን * ክፍል:- 1️⃣6️⃣ * የደርሹ መነሻ፦ ويسن سجود التلاوة * የሚሰጥበት ቦታ፦ የሺ ደበሌ ከፍ ብሎ ሑዘይፋህ መስጂድ * የሚሰጥበት ጊዜ፦ ዘወትር እሁድ ረፋድ ላይ = የቴሌግራም ቻናል፡- https://t.me/IbnuMunewor

ምስልን ለእርዳታ ስራ መጠቀም ~ የምስል ቀረፃን በተመለከተ በዑለማኦች የተለያዩ ሃሳቦች እንደተሰነዘሩ ይታወቃል። ሸይኽ ኢብኑ ዑሠይሚን ጉዳዩ የኢጅቲሃድ ርእስ ሆኖ ሳለ በዚህ ጉዳይ ተጠምደው በሚበጠብጡ ሰዎች እንደሚደነቁ ገልፀዋል። ንግግራቸውን በዚህ ሊንክ ማግኘት ይቻላል፦ https://youtu.be/8YY84nvhTtM?si=MFIpTMghTEYZ_e3F ሸይኽ ሙሐመድ ባዝሙልም በተመሳሳይ የሸይኽ ኢብኑ ዑሠይሚንን ንግግር አያይዘው ጉዳዩ የኢጅቲሃድ ርእስ እንደሆነ ይገልፃሉ። https://fb.watch/pAsU7is-K1/?mibextid=Nif5oz ይህንን የማያይዘው በዚህ ርእስ የተነሳ የመሻይኾችን፣ ዱዓቶችን ስም የሚያጎድፉ ቂላ -ቂሎች ስለበዙ ነው። ሚዛን የሚደፋውን ከመውሰድ ባሻገር በመሰል ጉዳዮች ሰዎችን እየመዘኑ "እከሌ አቋሙ ወረደ" የሚሉ በሱና ስም የሚጮሁ ሞኞ -ችን ማየት ያሳቅቃል። ይህንን እንደ መግቢያ ካልኩ ከዚህ በፊት ቀረፃን ለደዕዋ ስራ ስለመጠቀም የዑለማኦችን ንግግር በማያያዝ ፅፌ ነበር። ዛሬ ደግሞ በተራድኦ ስራ ላይ ስላለ ቀረፃ አነሳለሁ። በእርዳታ ስራ ላይ የቪዲዮም ሆነ የፎቶግራፍ ምስሎችን መጠቀም የተለመደ ነው። በጦርነት የተፈናቀሉ፣ በጎርፍ የተጠቁ፣ በተለያዩ ሰበቦች ችግር ላይ የወደቁ ወገኖች ያሉበትን ሁኔታ በማየት ሰዎች/ ድርጅቶች እንዲረዷቸው ለማድረግ ምስላቸውን መውሰድና ማሰራጨት የተለመደ ነው። ልክ እንዲሁ ለመሰል አካላት እርዳታ ካደረሱ በኋላ መረጃውን ለረጂዎቹ በምስል ማቅረብም በግለስቦችም፣ በእርዳታ ድርጅቶችም ይፈፀማል። እነዚህ አሰራሮች ለተጎጂዎቹ እርዳታ ለማፈላለግ፣ ለረጂዎቹ ደግሞ መረጃ ለማቅረብ ያግዛሉ። ለመሰል ችግርም ቢሆን ምስል መጠቀምን የሚከለክሉ አሉ። ለምሳሌ ሸይኽ ፈውዛን። በመሰል ሁኔታ ላይ የሚፈቅዱም አሉ። ለምሳሌ ሸይኽ ሱለይማን አሩሐይሊይ። በርግጥ ለምስኪኖች በሚሰጥ እርዳታ ላይ ቀረፃን ማራቅ ነው የሚሻለው። ሸይኽ አልኸሥላን የበጎ አድራጎት ተግባራትን በምስል መቅረፅን በተመለከተ የተለያዩ ነገሮች ይጋረጡበታል ይላሉ። አንደኛ ነገር፦ ኢኽላስን ሊጎዳ ይችላል። { إِن تُبۡدُوا۟ ٱلصَّدَقَـٰتِ فَنِعِمَّا هِیَۖ وَإِن تُخۡفُوهَا وَتُؤۡتُوهَا ٱلۡفُقَرَاۤءَ فَهُوَ خَیۡرࣱ لَّكُمۡۚ } "ምጽዋቶችን ብትገልጹ እርሷ ምንኛ መልካም ናት። ብትደብቋትና ለድሆች ብትሰጧትም እርሱ ለናንተ በላጭ ነው።" [አልበቀረህ፡ 271] ሁለተኛ ነገር ድሃውን የሚፈትን ሊሆን ይችላል። ድሃው መቀረፁን ላይወድ ይችላል። ይሄ ደግሞ ከአጉል መመፃደቅና ማስቸገር ውስጥ እንዳይገባ ያሰጋል። አላህ እንዲህ ይላል፦ { یَـٰۤأَیُّهَا ٱلَّذِینَ ءَامَنُوا۟ لَا تُبۡطِلُوا۟ صَدَقَـٰتِكُم بِٱلۡمَنِّ وَٱلۡأَذَىٰ كَٱلَّذِی یُنفِقُ مَالَهُۥ رِئَاۤءَ ٱلنَّاسِ وَلَا یُؤۡمِنُ بِٱللَّهِ وَٱلۡیَوۡمِ ٱلۡـَٔاخِرِۖ } "እናንተ ያመናችሁ ሆይ! እንደዚያ ገንዘቡን ለሰዎች ማሳየት ሲል እንደሚሰጠውና በአላህና በመጨረሻውም ቀን እንደማያምነው ሰው ምጽዋቶቻችሁን በመመጻደቅና በማስከፋት አታበላሹ።" [አልበቀረህ፡ 264] ከዚህ አንፃር ባይቀረፁ የተሻለ ነው። እርዳታው ለሚገባው አካል እንደ ደረሰ መረጃ ማቅረብ የሚሻ አካል ቢሆን እንጂ። በዚህን ጊዜ ቀረፃው ለመረጃነት እንደተፈለገ በመንገር ችግረኛውን ማስፈቀድ ጥሩ ነው። ምንም ሐጃ በሌለበት መቅረፅ ግን ምናልባት አጅርን እንዳያጠፋ ያሰጋል። [በቪዲዮ ከቀረበ ፈትዋ ተነካክቶ የተወሰደ።] በመጨረሻም ባያያዝኩት ቪዲዮ ውስጥ የሚሰማው ድምፅ የወንድማችን ሑሰይን ሙሐመድ አሲልጢ ድምፅ ነው። ለጥቂት የበግ እርዳታ ማስረጃ ይሆን ዘንድ የቪዲዮ ቀረፃ እያቀረበ ነው። ራሱ ለጥፎት ነው ያገኘሁት። የማቀርበው ለትችት አይደለም። እዚያ አካባቢ በቡድን የታጠሩ፣ የዑለማእ ንግግር ቢቀርብም ደንታ የማይሰጣቸው አካላት ስለበዙ ቢያንስ "የኛ" በሚሉት አካል ጉዳዩ ሲፈፀም ሲያዩ ሰከን ቢሉ ብዬ ነው። ወንድም ጠሀ ኸዲር እንኳ የፌስቡክ አካውንቱ በርካታ ምስሎች አሉበት። ሴትና ወንድ የተቀላቀሉበት ቪዲዮ ጭምር ያሉበት የፋና ዘገባ ሊንክ ሲያይዝ ነበር። እና ከስር የምትጮሁ አካላት ለሌላ ሳይሆን እንዲያው ለራሳችሁ ብታዝኑ መልካም ነው ለማለት አካባቢ ነው። ልመለስ እችላለሁ። Ibnu Munewor = * የቴሌግራም ቻናል https://t.me/IbnuMunewor * የዋትሳፕ ቻናል፦ https://whatsapp.com/channel/0029VaA3X1e5kg7BlsJboa2M * ፌስቡክ https://www.facebook.com/Ibnu.Munewor?mibextid=ZbWKwL

"አስቸኳይ መልዕክት ! ~~~~~~~~~~~~~ አሠላሙ ዓለይኩም ወረህመቱላሂ ወበረካቱ ውድ የተከበራችሁ ወንድም እና እህቶቼ ከታች በምስሉ ላይ የምትመለከቷት ልጅ ዘህራ ጣሃ እባላለው አለች።ከወራቤ ፈ
"አስቸኳይ መልዕክት ! ~~~~~~~~~~~~~ አሠላሙ ዓለይኩም ወረህመቱላሂ ወበረካቱ ውድ የተከበራችሁ ወንድም እና እህቶቼ ከታች በምስሉ ላይ የምትመለከቷት ልጅ ዘህራ ጣሃ እባላለው አለች።ከወራቤ ፈይነት ሩቃ ቤት ነው ጠፍቼ የወጣሁት አለች ። የምታውቋት በዚህ ስልክ ቁጥር በመደወል ማግኘት ትችላለችሁ ። 0930887835 ወይም 0949283077

‏لا تغُرنك منازل الناس في الدُّنيَا؛ فالقيامة ستعيد ترتيب منازلهم..! قال تعالى: {خافضة رافعة}.. - تخفض أقواما إلى أسفل السافلين إلى الجحيم، وإن كانوا في الدنيا أعزاء!.. - وترفع آخرين إلى أعلى العليين، إلى النعيم المقيم، وإن كانوا في الدنيا وضعاء!. منقول

ደርስ ~ * ሪያዱ ሷሊሒን رياض الصالحين * ክፍል:- 1️⃣3️⃣1️⃣ * የኪታቡን ሶፍት ኮፒ (በ pdf ) በዚህ ሊንክ ማግኘት ትችላላችሁ https://t.me/IbnuMunewor/3505 * የለቱ ደርስ መነሻ ገፅ 360፣ باب ما يقرأ في صلاة الجنازة * የሚሰጥበት ቦታ፦ አሸዋ ሜዳ፣ መስጂደል ዋሊደይን * የሚሰጥበት ጊዜ:- ረቡዕ፣ ሐሙስ እና ጁሙዐ = የቴሌግራም ቻናል፡- https://t.me/IbnuMunewor

ደርስ ~ * ሪያዱ ሷሊሒን * ክፍል:- 1️⃣3️⃣0️⃣ * የኪታቡን ሶፍት ኮፒ (በ pdf ) በዚህ ሊንክ ማግኘት ትችላላችሁ https://t.me/IbnuMunewor/3505 * የለቱ ደርስ መነሻ ገፅ 355፣ باب ما يقال عند الميت * የሚሰጥበት ቦታ፦ አሸዋ ሜዳ፣ መስጂደል ዋሊደይን * የሚሰጥበት ጊዜ:- ረቡዕ፣ ሐሙስ እና ጁሙዐ = የቴሌግራም ቻናል፡- https://t.me/IbnuMunewor

ከደቂቃዎች በኋላ የሪያዱ ሷሊሒን ደርስ ይኖራል ኢንሻአላህ።

የሸይኽ ሱለይማን አሩሐይሊ የኪታቡ ተውሒድ ሸርሕ = የቴሌግራም ቻናል https://t.me/IbnuMunewor

የቪዲዮ ምስልን ለደዕዋ መጠቀም ~ ምስልን ለአስገዳጅ ጉዳይ መጠቀምን በተመለከት ምስል መጠቀምን የሚከለክሉ ዓሊሞች ጭምር የሚፈቅዱት እንደሆነ የሚታወቅ ነው። በዚህ ላይ የተለየ አቋም መኖሩን አላውቅም። እናም ወንጀለኞችን ለማደን፣ የጠፋን ለማፈላለግ፣ ለመታወቂያ፣ ለመንጃ ፈቃድ፣ ለፓስፖርት፣ ወዘተ ፈቃጁም ከልካዩም ወገን ይፈቅዱታል። ምስልን ለደዕዋ መጠቀምን በተመለከተ ግን ከልካዮቹ ሃሳባቸው ለሁለት ይከፈላል። ከፊሎቹ ለማስተማሪያም ቢሆን ድምፅ በቂ ነው በሚል በወጥነት ይከለክላሉ። ለምሳሌ ሸይኹል አልባኒይን መውሰድ ይቻላል። በሌላ በኩል ለደዕዋ አገልግሎት መጠቀምን የፈቀዱ አሉ። ለምሳሌ ሸይኽ ኢብኑ ባዝን መውሰድ ይቻላል። የሸይኽ ኢብኑ ዑሠይሚንን አቋም ከልካዩም ፈቃጁም ስለሚጓተተው ትቼዋለሁ። እንደ ሸይኽ ፈውዛን ያሉት ደግሞ ክልከላቸው ቢታወቅም በቪዲዮ የተቀዱ ትምህርቶቻቸው ግን በሰፊው ይሰራጫሉ። እስካሁን ያወራሁት ከልካዮቹን በተመለከተ ነው። ምክንያታቸው ቢለያይም በደፈናው የሚፈቅዱም በተጨባጭ እንዳሉ ለማህበራዊ መገናኛዎች ቅርበት ያለው አካል የሚያረጋግጠው ነው። ለደዕዋና መሰል ሐጃዎች ቀርቶ “ከእከሌ ጋር ተገናኘን” እያሉ የሚለጥፉ ብዙ መሻይኾች አሉ። እነዚህን በዑለማኦቹ በኩል የሚታዩትን የተለያዩ ሁኔታዎች ስንመለከት ከታች ያለው ማህበረሰበ እነሱን ተከትሎ በጉዳዩ ላይ እንደሚለያይ የሚጠበቅ ነው። ከፊሉ በወጥነት ይከለክላል። ከፊሉ ለዶሩራ እና ወይም ለሐጃ ይፈቅዳል። ከፊሉ በደፈናው ይፈቅዳል። ከኛ የሚጠበቀው አንደኛ ጉዳዩን ከስሜት ነፃ ሆኖ መመርመርና አቋም መያዝ ነው። ሁለተኛ ጉዳዩን ዑለማኦቹ በያዙት መጠን መያዝ ነው። በዒልም መተራረሙ እንዳለ ሆኖ ፈቃጅ ዑለማኦች ከልካዮቹን በፅንፈኝነት አልፈረጁም። ማሾፍና መሳለቅ ውስጥም አልገቡም። ከልካዮቹም የፈቃጆቹን መንሃጅ ጥያቄ ውስጥ አልከተቱም። ለማጉደፍና የጥላቻ ዘመቻ ለመክፈትም አልተጠቀሙትም። እኛስ ዘንድ ያለው? እኛ ጋር በፈቃጅም ይሁን በከልካይ በኩል የሚታይ ፅንፍ አለ። ፈቃጁ ውስጥ፦ እነ እከሌ ትናንት ይከለክሉ እንዳልነበር ይሄው ዛሬ ራሳቸው በቪዲዮ መቅረብ ያዙ እያለ ለሹፈት ለመሳለቅ የሚያነሳ አለ። በጉዳዩ ላይ ግለሰቦች የአቋም ለውጥ ካሳዩም ምንም ለሹፈት የሚያበቃ ነገር የለም። መስለሐን በማስላት ወይም የፈቃጆቹ ትንታኔ አሳምኗቸው አቋም ቢቀይሩ ይሄ ፈፅሞ የሚያስወግዝ ነገር አይደለም። መረጃ አሳምኗቸው ሳይሆን ስሜታዊነት አሸንፏቸው ከሆነ ሂሳባቸው ከጌታቸው ዘንድ ነው። በሌላ በኩል ደግሞ ከከልካዩ ውስጥ ጉዳዩን ለቡድናዊ ፍረጃ የሚያውል እንዳለ የታወቀ ነው። ይሄ ክፍል ጉዳዩን ለማውገዝ የሚያስጮኸው ሰው እየመረጠ ነው። ከዑለማኦች ውስጥ የሚፈቅዱ እንዳሉ ያውቃል። እነሱ ላይ ትንፍሽ አይልም። ሌላው ቀርቶ እዚያው ከጎኑ የተሰለፉ ምስል የሚጠቀሙ እንዳሉ እያወቀ የውግዘት ዘመቻ ውስጥ አይገባም። ጉዳዩን የሚያነሳው የሆኑ ቂም የተጋባቸውን አካላት ለማጠልሸት በማለም ነው። በሱ ቤት ለዲን፣ ለሱና መታገሉ ነው። የለየለት ቡድንተኝነት እያራመደ ሰዎችን በቡድንተኝነት ይፈርጃል። ወንድሜ! ሰዎችን ብትሸውድ አላህን አትሸውድም። ሃሳቤን በሸይኽ ሱለይማን አሩሐይሊይ ትንታኔ ልዝጋ። ጨመቅ አድርጌ ነው የማቀርበው። ሸይኹ ህይወት ያላቸው ነገሮችን መሳልን ለአራት ይከፍሉታል። 1. ቅርፆች:- እንደ ሃውልትና ቅርፃ ቅርፅ ያሉ ጥላ ያላቸው ምስሎችን መሳል በክልክልነቱ ላይ ዑለማኦች ተስማምተዋል። ከትልልቅ ወንጀሎች ውስጥ ነው። 2. የእጅ ስእሎች:- ጥላ የሌለው ወረቀት፣ ጨርቅና መሰል ነገሮች ላይ በእጅ ተነድፎ የሚሳል ምስል አብዛኞቹ ዓሊሞች ከልክለውታል። ከፊል ታቢዒዮችና ጥቂት ዑለማኦች ወደ መፍቀዱ ሄደዋል። ሚዛን የሚደፋው - አዋቂው አላህ ነው - ሐራም ነው የሚለው ነው። (ምክንያታቸውን ቦታው ላይ ዘለግ አድርገው ስላሰፈሩ የፈለገ ይመልከተው።) 3. ፎቶግራፎች፦ እንደ ካሜራና ሞባይል ስልክ ባሉ መሳሪያዎች ተንቀሳቃሽ ያልሆኑ ቋሚ ምስሎችን ማንሳትን በተመለከተ የዘመናችን ዑለማኦች ተለያይተውበታል። * ከፊሎቹ ስእል መሳልን የሚከለክሉ መረጃዎች ጠቅላይ ስለሆኑ እንዲሁም በነዚህ መሳሪያዎች የሚፈፀመውም ሁሉም እንደሚስማሙት ምስል መሳል (ተስዊር) ስለሆነ ሐራም እንደሆነ ገልፀዋል። * ከፊሎቹ ደግሞ የተለያዩ መነሻዎችን በመጥቀስ የተፈቀደ ነው ብለዋል። ሸይኹ መጨረሻ ላይ ይሄኛውም ሐራም እንደሆነ ገልፀዋል። (የሚቀርቡትን ትንታኔዎችና የሸይኹን ምላሾች የፈለገ ከቦታው ይመልከት።) ባይሆን እንደ የህክምና ጉዳይ ላሉ አስገዳጅ ጉዳዮች እና ለበጎ አድራጎት ተግባራት በማስረጃነት የሚውሉ ለአንገብጋቢ ሐጃዎች ይፈቀዳል ብለዋል። 4. ተንቀሳቃሽ ምስሎች:- ይህኛውን ለሁለት ከፍለውታል። * አንደኛው የቀጥታ ስርጭት ሲሆን ይፈቀዳል ይላሉ። ልክ በመስታዎት እያንፀባረቁ የሰዎችን ምስል እንደመመልከት እንደሆነም ይገልፃሉ። * ሁለተኛው ቀጥታ ያልሆነውን (የቪዲዮ) ቅጂ በተመለከተ ከፊል ዓሊሞች ለደዕዋ መጠቀምን ጨምሮ ሐራም ነው ይላሉ። ከፊሎቹ ግን ሐራም እንደሆነ ከመግለፃቸው ጋር ለደዕዋ ማስተላለፊያ መጠቀምን ይፈቅዳሉ። የኢብኑ ባዝ አቋም እዚህ ላይ ነው የረጋው። ቀድመው ይከለክሉ ነበር። ኋላ ግን ለፓስፖርትና ለዶክመንቶች ከመጠቀም ይልቅ ይሄኛው የበለጠ አንገብጋቢ እንደሆነ በማመን በቴሌቪዥን እየቀረቡ ማስተማርን ፈቅደዋል። የራሳቸውም የተወሰኑ ትምህርቶች በቪዲዮ ተቀርፀው ወጥተዋል። * ከፊል ዓሊሞች ደግሞ ይሄ ልክ እንደ መስታዎት ነፀብራቅ እንጂ ከነ ጭራሹ ምስል መሳል አይደለም በማለት ፈቅደውታል። እኔ ዘንድ ግን - “እኔ ዘንድ” ማለት የሚግገባኝ ከሆንኩኝ - ከዑለማኦቹ አቋሞች ውስጥ ሚዛን የሚደፋው - አዋቂው አላህ ነው - በቪዲዮ መቀረፅ ከአሻሚ ጉዳዮች ውስጥ ነው። ግልፅ ከሆነ ሐላልም አይደለም። ግልፅ ከሆነ ሐራምም አይደለም። ወደ ክልከላው የሚጠራ ነገር አለ። እሱም ምስል ነውና። ይህን የሚገፋ ደግሞ አለበት። አማኝ ሊርቀው የተገባ ነው። ለእምነቱም፣ ለክብሩም የተሻለ ነው ይሄ። እንደ ሙሓዶራትና የኪታብ ትምህርቶች ያሉ ፋይዳዎች (መስለሐዎች) ካልታየበት በስተቀር። በመጨረሻም እኔ በታየኝ ድምዳሜ ላይ ልትስማማም፣ ልትቃረንም ትችላለህ ይላሉ። [ሸርሑ ኪታቢ ተውሒድ፡ 1627 - 1635] (ኪታቡ በጣም ምርጥ ሸርሕ ነው። የምትፈልጉ ካላችሁ የpdf ፋይሉን ቴሌግራም ቻናሌ ላይ ላያይዝላችሁ እችላለሁ።) ረጅሙ ፅሑፌ በአንድ አረፍተ ነገር ሲጠቃለል ጉዳዩን ዑለማኦቹ በያዙት መጠን በልኩ እንያዘው የሚል ነው። አደብ የጎደለው ሃሳብ ይሰረዛል። Ibnu Munewor = * የቴሌግራም ቻናል https://t.me/IbnuMunewor * የዋትሳፕ ቻናል፦ https://whatsapp.com/channel/0029VaA3X1e5kg7BlsJboa2M * ፌስቡክ https://www.facebook.com/Ibnu.Munewor?mibextid=ZbWKwL

ደርስ ~ * ሪያዱ ሷሊሒን * ክፍል:- 1️⃣2️⃣9️⃣ * የኪታቡን ሶፍት ኮፒ (በ pdf ) በዚህ ሊንክ ማግኘት ትችላላችሁ https://t.me/IbnuMunewor/3505 * የለቱ ደርስ መነሻ ገፅ 351፣ ሐዲሥ ቁ. 902 * የሚሰጥበት ቦታ፦ አሸዋ ሜዳ፣ መስጂደል ዋሊደይን * የሚሰጥበት ጊዜ:- ረቡዕ፣ ሐሙስ እና ጁሙዐ = የቴሌግራም ቻናል፡- https://t.me/IbnuMunewor

‏في قوله عز وجل: ﴿ولا أقسم بالنفس اللوامة﴾ قال الحسن البصري رحمه الله: إن المؤمن لا تراه إلا يلوم نفسه؛ يقول: ما أردت بكلمتي؟! يقول: ما أردت بأكلتي؟! فلا تراه إلا يعاتبها، وإن الفاجر يمضي قدما فلا يعاتب نفسه. *الزهد للإمام أحمد رحمه الله

ከደቂቃዎች በኋላ የሪያዱ ሷሊሒን ደርስ ይኖራል ኢንሻአላህ።