en
Feedback
📚منهج السلف طريقنا الى الله 📚

📚منهج السلف طريقنا الى الله 📚

Open in Telegram

↘️በዚህ ቻናል የሚተላለፉት ↘️በሱና ኡስታዞች የተቀሩ ደርሶች ↘️የሱና ኡስታዞች ሙሀደራዎች ↘️በመቀጠል አስተማሪ ፁሁፎች ➴➴➴➴➴➴➴➴➴➴➴➴ https://t.me/htt_asselfya

Show more
3 819
Subscribers
-524 hours
+1617 days
+15530 days
Posts Archive
ደርስ ~ * منهج السالكين * ክፍል:- 1️⃣5️⃣ * የደርሹ መነሻ፦ باب سجود السهو * የሚሰጥበት ቦታ፦ የሺ ደበሌ ከፍ ብሎ ሑዘይፋህ መስጂድ * የሚሰጥበት ጊዜ፦ ዘወትር እሁድ ረፋድ ላይ = የቴሌግራም ቻናል፡- https://t.me/IbnuMunewor

የሸይኽ ዐብዱ ያሲን - ረሒመሁላህ - ቀብር ላይ የገረመኝ ነገር እጅግ በርካታ ሰው በቪዲዮ ቀረፃ የተጠመደ መሆኑ ነው። ኧረ አላህን እየፈራን ጎበዝ! ምናለ ለአንዳንድ ተግባሮቻችን ቢያንስ ቦታ ብንመርጥላቸው? ሱብሓነላህ! Ibnu Munewor = * የቴሌግራም ቻናል https://t.me/IbnuMunewor

መልካም ቢድዐ ሌላ! መልካም ሱና ሌላ! ~ ቢድዐን ለሁለት የሚከፍሉ ሰዎች ከሚመረኮዙባቸው ሐዲሦች አንዱ ይሄ ሐዲሥ ነው፡- “በኢስላም ውስጥ መልካም የሆነችን ሱና የጀመረና ከሱም በኋላ ከተሰራባት የሰራባት ሰው አምሳያ ምንዳ (ለጀማሪው) ይፃፍለታል። ከምንዳዎቻቸው ምንም አይቀንስባቸውም። በኢስላም ውስጥ መጥፎ የሆነን ሱና የጀመረና ከሱም በኋላ ከተሰራባት በሱ (በጀማሪው) ላይ የሚሰራባት ሰው አምሳያ ወንጀል አለበት። ከወንጀሎቻቸው ምንም አይቀንስላቸውም።” [ሙስሊም] በተለያዩ ዘርፎች ቢድዐ ላይ የወደቁ አካላት ዘወትር ይህንን ሐዲሥ ሲያስተጋቡ ይሰማሉ። ከፊሎቹ እያወቁ ከፊሎቹ ደግሞ በሚገባ ባለማገናዘብ ሐዲሡን ከትክክለኛ መልእክቱ ሲያስወጡት ማየት የተለመደ ነው። በርግጥ አንዳቸው “ጥሩ” የሚሉትን ሌሎቹ እንደመጥፎ ስለሚቆጥሩት ከአካባቢያዊ ልማድና ውርርስ ባለፈ የሚያግባባቸው የጋራ ቋንቋ የለም። ወደ ሐዲሡ ስንመለስ መልእክቱን በሚገባ ለመረዳት ያግዘን ዘንድ የተነገረበትን ክስተትና የሐዲሡን አገባብ ማስተዋሉ የሚበጅ ነው። ሶሐባው ጀሪር ብኑ ዐብዲላህ ረዲየላሁ ዐንሁ እንዲህ ይላሉ፡- “በአንድ ረፋድ ላይ ከአላህ መልእክተኛ ﷺ ዘንድ ነበርን። ባዶ እግራቸውን የሆኑ፣ የታረዙ ሰዎች ዝንጉርጉር ለምድ (ቆዳ) ለብሰው፣ ሰይፎቻቸውን አንግተው መጡ። አብዛኞቹ ከሙዶር ጎሳ ናቸው። ኧረ ሁሉም ከሙዶር ናቸው። ያሉበትን ችግር ሲመለከቱ ጊዜ የአላህ መልእክተኛ ﷺ ፊታቸው ተቀያየረ። ወደቤት ገቡ። ከዚያም ወጡና ቢላልን አዘው አዛንና ኢቃማ አደረገ። ከዚያም ኹጥባ አደረጉ። … አንዱ ከዲናሩ፣ ሌላው ከዲርሃሙ፣ ከልብሱ፣ ከቁና ስንዴ ሰደቃሰጡ። ‘በተምር ክፋይም ብትሆን (ሰድቁ)’ አሉ። ሰዎች ችላ ሲሉ ጊዜ ነብዩ ﷺ ቅሬታቸው ፊታቸው ላይ ታየ። ከዚያ ግን ከአንሷር የሆነ ሰው እጁ ሊያቅተው የቀረበ ብር የያዘ ከረጢት ይዞ መጣ። ኧረ እንዲያውም አቅቶታል! ከዚያም ሰዎች (በሶደቃው) ተከታተሉ። ሁለት የምግብና የልብስ ክምሮችን እስከምመለከት ድረስ። የነብዩን ﷺ ፊት (ከመደሰታቸው የተነሳ) ወርቅ እስከሚመስል ድረስ ሲያንፀባርቅ ተመለከትኩኝ። በዚህን ጊዜ እንዲህ አሉ፦ مَنْ سَنَّ فِي الْإِسْلَامِ سُنَّةً حَسَنَةً، فَلَهُ أَجْرُهَا، وَأَجْرُ مَنْ عَمِلَ بِهَا بَعْدَهُ مِنْ غَيْرِ أَنْ يَنْقُصَ مِنْ أُجُورِهِمْ شَيْءٌ، وَمَنْ سَنَّ فِي الْإِسْلَامِ سُنَّةً سَيِّئَةً، كَانَ عَلَيْهِ وِزْرُهَا، وَوِزْرُ مَنْ عَمِلَ بِهَا مِنْ بَعْدِهِ مِنْ غَيْرِ أَنْ يَنْقُصَ مِنْ أَوْزَارِهِمْ شَيْءٌ .» ‘በኢስላም ውስጥ መልካም የሆነን ሱና የጀመረና ከሱም በኋላ ከተሰራባት የሰራባት ሰው አምሳያ ምንዳ (ለጀማሪው) ይፃፍለታል። ከምንዳዎቻቸው ምንም አይቀንስባቸውም። በኢስላም ውስጥ መጥፎ የሆነን ሱና የጀመረና ከሱም በኋላ ከተሰራባት በሱ (በጀማሪው) ላይ የሚሰራባት ሰው አምሳያ ወንጀል አለበት። ከወንጀሎቻቸው ምንም አይቀንስላቸውም።’” [ሙስሊም፡ 1017] ሐዲሡን ኢማም ሙስሊም ናቸው የዘገቡት። ጥንካሬው አስተማማኝ ነው። መልእክቱን በተመለከተ ለማንም በግልፅ እንደሚታየው ይሄ ሐዲሥ አዲስ ዒባዳ እየደነገጉ፣ ቢድዐ እየፈጠሩ ለሚሟገቱ ሰዎች ምርኩዝ መሆን አይችልም። ምክንያቱም ሐዲሡ የሚያወራው ስለሱና እንጂ ስለቢድዐ አይደለምና። የሐዲሡ አገባብ የሚያሳየው ለሌሎች በኸይር ስራ ላይ ምሳሌ ስለሚሆን ሰው እንጂ አዲስ ቢድዐ ስለሚፈጥር አይደለም። በሐዲሡ ውስጥ የተጠቀሰው ዒባዳ ሶደቃ ነው። ሶደቃ (ምፅዋት መስጠት) በብዙ መረጃዎች የፀና ዒባዳ እንጂ አዲስ የመጣ ቢድዐ አይደለም። ነብዩ ﷺ “በኢስላም ውስጥ መልካም የሆነን ሱና የጀመረ” ያሉት በየትኛው ቅፅበት ላይ እንደሆነ ከሐዲሡ እናስተውል። ሌሎችን ያነሳሳ ሶደቃ በተሰደቀ ጊዜ ነው። ይህም ጥሩ ሱና ማለት ጥሩ ቢድዐ ማለት እንዳልሆነ ፍንትው ያደርግልናል። የዚህ ሐዲሥ መልእክት በሌላ ሐዲሥ በአጭሩ ተገልጿል። እንዲህ በሚል፦ “በመልካም ነገር ላይ ያመላከተ ለሱ የፈፃሚው አምሳያ ምንዳ አለው።” [ሙስሊም፡ 1893] ኢማም ሙስሊም ሁለቱን ሐዲሦች በአንድ ርእስ ስር መዘገባቸው የመልእክታቸውን ተመሳሳይነት ይጠቁመናል። ስለዚህ በቁርኣንና በሐዲሥ መሰረት ያለው ዒባዳ ላይ ሰዎች ሲዘናጉ በዚያ ምሳሌ ሆኖ ያነሳሳቸው ሰው ራሱ በፈፀመውም፣ እሱን አይተው በተነሳሱትም አጅር ይኖረዋል። የሐዲሡ መልእክት ይሄ ነው። እንጂ በቁርኣንና በሐዲሥ ውስጥ የማይገኝ አዳዲስ ቢድዐ መደንገኝ የሚያበረታታ አይደለም የሐዲሡ መልእክት። ይሄ ቢሆንማ ሁሉም የራሱን ቢድዐ እየፈጠረ መቋጫ የሌለው ትርምስ ነበር የሚከተለው። Ibnu Munewor = * የቴሌግራም ቻናል https://t.me/IbnuMunewor * የዋትሳፕ ቻናል፦ https://whatsapp.com/channel/0029VaA3X1e5kg7BlsJboa2M * ፌስቡክ https://www.facebook.com/Ibnu.Munewor?mibextid=ZbWKwL

ከጥፋት የተመለሰ ሰው በቀድሞ ጥፋቱ አይወቀስም ~ አላህን ፈርቶ፣ ኣኺራውን አስቦ ከወንጀል የተመለሰ ሰው በኢስላም ትልቅ ደረጃ ነው ያለው። ነብዩ ﷺ እንዲህ ብለዋል፦ كلُّ بني آدم خَطَّاءٌ، وخيرُ الخَطَّائِينَ التوابون "የአደም ልጅ በሙሉ በጣም አጥፊ ነው። ከአጥፊዎች ሁሉ በላጮቹ ተመላሾቹ ናቸው።" [ቲርሚዚይና ኢብኑ ማጀህ ዘግበውታል።] ተውበት ወንጀልን ይጠርጋል። የአላህን ውዴታ ያስገኛል። በአንድ ሰው ተውበት አላህ እንዴት እንደሚደሰትበት በትክክል ይሄ ነው ብሎ መግለፅ አይቻልም። ይህንን እውነት በሚገባ ማወቅ ብቻ ሳይሆን ትኩረት መስጠትም ያስፈልጋል። ማህበራዊ ሚዲያ ላይ ከሚታዩ ፀያፍ ልማዶች ውስጥ አንዱ አንድ ሰው ከጥፋቱ "ተመልሻለሁ" ሲል የስድብና የውግዘት መዓት ይዞ መረባረብ ነው። ይሄ ሌሎች ሰዎችም እንዳይመለሱ በር መዝጋት ነው። እውነተኛ ተውበት ላደረገ ሰው አላህ የትኛውንም አይነት ወንጀል ይምራል። {قُلۡ یَـٰعِبَادِیَ ٱلَّذِینَ أَسۡرَفُوا۟ عَلَىٰۤ أَنفُسِهِمۡ لَا تَقۡنَطُوا۟ مِن رَّحۡمَةِ ٱللَّهِۚ إِنَّ ٱللَّهَ یَغۡفِرُ ٱلذُّنُوبَ جَمِیعًاۚ إِنَّهُۥ هُوَ ٱلۡغَفُورُ ٱلرَّحِیمُ} "በላቸው 'እናንተ በነፍሶቻችሁ ላይ ድንበር ያለፋችሁ ባሮቼ ሆይ! ከአላህ እዝነት ተስፋ አትቁረጡ፡፡ አላህ ኃጢኣቶችን በመላ ይምራልና፡፡ እነሆ እርሱ መሓሪው አዛኙ ነውና።' " [አዙመር፡ 53] አንድ ሰው ወንጀሉ የፈለገ ቢከፋ፣ የፈለገ ቢደጋገም "ተመልሻለሁ" ሲል ልንደሰት፣ ከጎኑ ልንቆም፣ ልናበረታታ፣ አላህ ፅናትን እንዲያድለው ዱዓእ ልናደርግለት ነው የሚገባን። እንጂ በተመለሰበት ጥፋቱ ሊያሸማቅቁ መሞከር ወላሂ ነውረኝነት ነው። ሰውን በተመለሰበት ጥፋቱ ማነወር ብልግና ነው። "እኔ ግን አልሳሳትም" የሚል ግብዝነት ነው ያለው በውስጡ። ሸይኹል ኢስላም ኢብኑ ተይሚያ ረሒመሁላህ እንዲህ ይላሉ፦ ولا يجوز لوم التائب باتفاق الناس .. وإذا أَظهر التوبة أُظهر له الخير. "በሰዎች ወጥ ስምምነት ከጥፋቱ ተመላሽ የሆነ ሰው (በተመለሰበት ጥፋት) አይወቀስም፡፡ ... መመለሱን ካንፀባረቀ መልካምን ነው ለሱ ልናንፀባርቅ የሚገባው።" [አልኣዳቡ ሸርዒያህ ፡ 1/96] በነብዩ ﷺ ዘመን አንድ ከዝሙት ተውበት ያደረገን ወጣት "ቆሻሻ" ብሎ ለገለፀ ሰው ነብያችን ﷺ እንዲህ ሲሉ ነበር የመለሱት፦ "لَهُوَ أَطْيَبُ عِنْدَ اللَّهِ مِنْ رِيحِ الْمِسْكِ" "በርግጥም እሱ ከአላህ ዘንድ ከሚስክ ሽታ የጣፈጠ ነው።" [አቡ ዳውድ፡ 4435] Ibnu Munewor = * የቴሌግራም ቻናል https://t.me/IbnuMunewor * የዋትሳፕ ቻናል፦ https://whatsapp.com/channel/0029VaA3X1e5kg7BlsJboa2M * ፌስቡክ https://www.facebook.com/Ibnu.Munewor?mibextid=ZbWKwL

💐💐 💐ክፍል :①⑨ 💐ሙኽተሶር ኪታቡ ሲያም ሸርሑ ሙምቲዕ💐 💐የሸይኽ ሙሐመድ ሷሊህ አል ዑሰይሚን ረሂመሁሏህ💐 💐ተ  💐   💐 ጀ  💐       💐 ም  💐         💐 ሯ  💐            💐ል  💐 💐የቀጥታ ስርጭት የላይቭ ሊንክ💐⤵️⤵️ https://t.me/tewhidfirst29?livestream=15f75e32fd58b90dce

نسألٌ الله وسلاما

እውነት አእምሮ ካለህ ካላበድክ አላህን ፍራ የአርሹን ጌታ ፍራ የሰማይና የምድሩን ጌታ ፍራ አታጥፋ እጅህን ሰብስብ ከሰማይ በላ እንዳያወርድብህ ፍራ

نسألٌ الله وسلاما

እውነት አእምሮ ካለህ ካላበድክ አላህን ፍራ የአርሹን ጌታ ፍራ የሰማይና የምድሩን ጌታ ፍራ አታጥፋ እጅህን ሰብስብ ከሰማይ በላ እንዳያወርድብህ ፍራ

ቆይ ምንድነው የምፈራው??

እውነት አእምሮ ካለህ ካላበድክ አላህን ፍራ የአርሹን ጌታ ፍራ የሰማይና የምድሩን ጌታ ፍራ አታጥፋ እጅህን ሰብስብ ከሰማይ በላ እንዳያወርድብህ ፍራ

ኢሊያስ ገብተህ ተማር

ቀጥታ ስርጭት የቀልብ መድረቅ 🎙Ustaz ibrahim heyredin 👇👇👇ቀጥታ ስርጭት        ተ             ጀ                    ም                         ሯ                                ል      ሺርርርር እያደርጋችሁ t.me/+kKY_gazIcRoyNWQ0 t.me/+kKY_gazIcRoyNWQ0

እውነት አእምሮ ካለህ ካላበድክ አላህን ፍራ የአርሹን ጌታ ፍራ የሰማይና የምድሩን ጌታ ፍራ አታጥፋ እጅህን ሰብስብ

እውነት አእምሮ ካለህ ካላበድክ አላህን ፍራ የአርሹን ጌታ ፍራ

እውነት አእምሮ ካለህ ካላበድክ አላህን ፍራ

ታላቁን ጌታ ፍራው!!