en
Feedback
📚منهج السلف طريقنا الى الله 📚

📚منهج السلف طريقنا الى الله 📚

Open in Telegram

↘️በዚህ ቻናል የሚተላለፉት ↘️በሱና ኡስታዞች የተቀሩ ደርሶች ↘️የሱና ኡስታዞች ሙሀደራዎች ↘️በመቀጠል አስተማሪ ፁሁፎች ➴➴➴➴➴➴➴➴➴➴➴➴ https://t.me/htt_asselfya

Show more
3 819
Subscribers
-524 hours
+1617 days
+15530 days
Posts Archive
አብሺር! ~ አንድ አዕራቢይ ነብዩ ﷺ ዘንድ መጣና أَلَا تُنْجِزُ لِي مَا وَعَدْتَنِي؟ "የገባህልኝ ቃል አትፈፅምልኝም?" አላቸው። " أَبْشِرْ" "አብሺር!" አሉት። [አልቡኻሪይ፡ 4328] [ሙስሊም፡ 2497] Ibnu Munewor = የቴሌግራም ቻናል፡- https://t.me/IbnuMunewor

ደርስ ~ * ሪያዱ ሷሊሒን * ክፍል:- 1️⃣3️⃣2️⃣ * የኪታቡን ሶፍት ኮፒ (በ pdf ) በዚህ ሊንክ ማግኘት ትችላላችሁ https://t.me/IbnuMunewor/3505 * የለቱ ደርስ መነሻ ገፅ 364፣ باب الدعاء للميت بعد دفنه * የሚሰጥበት ቦታ፦ አሸዋ ሜዳ፣ መስጂደል ዋሊደይን * የሚሰጥበት ጊዜ:- ረቡዕ፣ ሐሙስ እና ጁሙዐ = የቴሌግራም ቻናል፡- https://t.me/IbnuMunewor

"ከከፈ'ሩ ክፍርር ነው!" ~ "ከሰለሙ ስልምልም ነው። ከከፈ'ሩ ክፍርር ነው!" ይሄ ንግግር በአንድ ታላቅ የሃገራችን ሸይኽ ስም ሶሻል ሚዲያ ላይ ተደጋግሞ ይታያል። የመጀመሪያው ክፍል "ወደ ኢስላም ጥቅልል ብላችሁ ግቡ" ከሚለው ቁርኣናዊ መልእክት ጋር ይሄዳል። ሁለተኛዋ ግን ካጠፋህ አይቀር ይለይልህ ይዘት ነው ያላት። "ትሰልም ከሆነ በሚገባ ስለም። ካለሆነ ግን በግልፅ ጠቅልለህ ውጣ" አይነት ጥሪ ከባድ ነው። እንደዋዛ ባንጠቀመው መልካም ነው። Ibnu Munewor = * የቴሌግራም ቻናል https://t.me/IbnuMunewor

ከደቂቃዎች በኋላ የሪያዱ ሷሊሒን ደርስ ይኖራል ኢንሻአላህ።

ከሟች ይልቅ ለገዳይ ያደላ ህግ ~ እርጅና የደቆሳቸው ወላጅ እናቱን የገደለውም፣ የገዛ ልጆቹን ገድሎ ለጅብ የሰጠውም፣ ሚስቱን እጅ እግሯን ጠፍሮ ቤንዚን አርከፍክፎ ያቃጠለውም፣ ከደፈረ በኋላ ገድሎ
ከሟች ይልቅ ለገዳይ ያደላ ህግ ~ እርጅና የደቆሳቸው ወላጅ እናቱን የገደለውም፣ የገዛ ልጆቹን ገድሎ ለጅብ የሰጠውም፣ ሚስቱን እጅ እግሯን ጠፍሮ ቤንዚን አርከፍክፎ ያቃጠለውም፣ ከደፈረ በኋላ ገድሎ የጣለውም፣ ጨቅላ ህፃናት ላይ ቢላዋ ያሳረፈውም፣ አንድ ነፍስ ያጠፋውም፣ አስር ሃያ ሰው የገደለውም፣ ... 18 ዓመት፣ 20 ዓመት፣ ወዘተ ነው የሚፈረድበት። በዚህ በከበደ ኑሮ ከቻለ ዘርፎ ሊበላ፣ ካልሆነ ታስሮ ሊቀለብ ነፍሰ በላው ሁሉ ዘና ብሎ የመኖር እድል ተሰጥቶታል። ህሊና የሌለው፣ እምነትና ሞራል የማይገታው ወንጀለኛ ሁሉ ያሻውን ቢያደርግ የከፋ የሚጠብቀው ነገር የለም። 18 አመት ቢፈረድበት በአመክሮ በ 12 ዓመት ሊወጣ ይችላል። እድሜ ልክ የተፈረደበት በ 20 ዓመቱ ይወጣል። ያውም ይሄ "በምህረት" ካልተፈታ ነው። እንጂ አራት፣ አምስት ዓመት ታስሮ የሚወጣው ቀላል አይደለም። ይሄ በጣም የሚያቅለሸልሽ ህግ ነው። ህጉ አራሚ፣ አስተማሪ ባለመሆኑ የተነሳ በየጊዜው የምንሰማቸው ሰቅጣጭ ወንጀሎች በአይነትም፣ በብዛትም ጨምረዋል። ህጉ ያስቀመጠው ቅጣት ፈፅሞ ፍትሃዊም፣ ተመጣጣኝም፣ የሟች ቤተሰብን እንባ የሚያብስም፣ መሰል ወንጀልን የሚገታም አይደለም። ያሳዝናል! ይሄው ወላጅ እናቱን የገደለው 10 አመት ነው የተፈረደበት። ከዚህ ውስጥ በአመክሮ ከ3 አመት በላይ ይነሳለታል። 7 አመት ሳይሞላው ይወጣል። ምናልባት እዚያው ሆኖ መቀለብን ካልፈለገ። Ibnu Munewor = * የቴሌግራም ቻናል https://t.me/IbnuMunewor * የዋትሳፕ ቻናል፦ https://whatsapp.com/channel/0029VaA3X1e5kg7BlsJboa2M * ፌስቡክ https://www.facebook.com/Ibnu.Munewor?mibextid=ZbWKwL

ቀ.ውሱ ወሊይ አሕመደል በደዊይ ~ በሙስሊሙ ዓለም ስማቸው ከገነኑ የሱፊያ ወልዮች ውስጥ አንዱ አሕመደል በደዊይ ነው። በደዊይ በያመቱ በሚሊዮን የሚቆጠር ህዝብ ቀብሩን ይጎበኛል። ያገራችን ሱፍዮች:- "አሕመደል በደው ጠላታችንን ገደል ሰደደው!" እያሉ የሚመፃደቁበት ታላቅ ወሊያቸው ነው። ምን አይነት ሰው ነበር? ብዙ ፀሐፊዎች ቀ.ውስ እንደነበር ሲገልፁ ሌሎች ደግሞ እብ.ድ እብ.ድ የሚጫወት የበኑ ዑበይድ ሺዐዎች ሰላይ ነበር ይላሉ። የዐብዱሶመድ ዘይኑዲን አልአሕመዲይን ምስክርነት ላስቀምጥ። እንዲህ ይላል ስለ በደዊይ፦ وأقام على سطح الدار لا يفارقه ليلًا ولا نهارًا، وإذا عرض له الحال يصيح صياحًا متصلًا، وتزيَّى أحمد البدوي بزي المجاذيب، وظل ضاربًا اللثامين على وجهه، وكان إذا لبس ثوبًا أو عمامة لا يخلعها لغسل حتى تذوب، فيبدلونها بغيرها "በቤቱ ጣራ ላይ ኑሮውን አደረገ። ሌትም ቀንም ከሱ አይለይም። ሓሉ ሲነሳበት ረጅም ጩኸት ይጮሃል። አሕመደል በደዊይ የወፈ -ፌዎችን ገፅታ የተላበሰ ነበር። ፊቱ ላይ መከናነቢያ እንዳደረገ ነበር የሚቆየው። ቀሚስ ወይም ጥምጣም ሲለብስ ላዩ ላይ (ቆሻሻው) እስከሚቀልጥ ድረስ አያወልቀውም ነበር። ከዚያ ሰዎች በሌላ የሚቀይሩለት።" [አሰዪዱል በደዊይ ዲራሳህ ነቕዲያህ፡ 15] ሲዩጢይ (911 ሂ.) እና አልሙናዊይም (1031 ሂ.) ቀደም ብለው ይህንን እውነታ ገልፀውታል። [ሑስኑል ሙሓዶራ፣ ሲዩጢይ፡ 1/522] [አልከዋኪቡ ዱሪያህ፣ መናዊይ፡ 2/388] ታዋቂው የታሪክ ፀሐፊ አልመቅሪዚይ (845 ሂ.) ደግሞ በአንድ ወቅት ጁሙዐ ቀን ኹጥባ ተጠናቆ ሶላት ሊሰገድ ኢቃማ ከተደረገ በኋላ አሕመደል በደዊይ ተነስቶ ህዝብ እያየው ሃፍረተ ገላውን ገልጦ ልብሱ ላይ፣ የመስጂዱ ምንጣፍ ላይ ሽንቱን እንደሸና ፅፈዋል። ሶላት የለ፣ ምን የለ። [ዱረሩል ዑቁድ፡ 3/77] በ"ዳኢረቱል መዓሪፊል ኢስላሚያህ" ላይ ደግሞ እንዲህ የሚል እናገኛለን፦ وكان يمكث طوال نهاره وليله قائمًا شاخصًا ببصره إلى السماء، وقد انقلب سواد عينيه بحمرة تتوقد كالجمر، وكان يمكث الأربعين يومًا وأكثر لا يأكل ولا يشرب ولا ينام "ቀንና ሌቱን ሙሉ አይኑን ወደ ሰማይ ገልብጦ ነበር የሚቆየው። የአይኑ ጥቁሩ ክፍል እንደ ፍም የሚንቀለቀል ቀይ ሆኖ ተቀይሮ ነበር። አርባ ቀን ሳይበላ፣ ሳይጠጣ፣ ሳይተኛ ይቆያል።" [ቅፅ 2፣ ገፅ፡ 476] በደዊይ ብዙ ወዳጆቹ እንደሚሉት የአእምሮ ህመምተኛ ከሆነ ወሊይ ሳይሆን "መርፉዐል ቀለም" ነው። ነብያችን ﷺ "ቀለም ተነስቶላቸዋል" ማለትም ተጠያቂዎች አይደሉም ካሏቸው ውስጥ አንዱ ያበ'ደ ሰው ነውና። ሰውየው አንዳንዶች እንደሚሉት ለበኑ ዑበይድ የሚሰልል ሺ0 ከነበረ አላህ የስራውን ይስጠው። ብቻ ሱፍዮች ድንበር የሚያልፉበት ይሄ ሰው ሻል ቢል ሶላት የማይሰግድ፣ መስጂድ ውስጥ የሚሸና እብ.ድ ነው። በሱፍያው ዓለም ብዙ ቀውስ ወሊዮች ስላሉ ይሄ ብዙም የሚገርም አይደለም። ማሳሰቢያ፦ ምንጭ ጠቅሼ ነው የፃፍኩት። * ምስሉ በግብፅ ጠንጣ ከተማ ውስጥ የሚገኝ በአመት ሁለት ጊዜ ከሁለት ሚሊዮን በላይ ህዝብ የሚሰባሰብበት ዶሪሕ (ቀብር) ነው። ( Ibnu Munewor ፣ ረጀብ 06/1445 (ጥር 08/ 2016)) = * የቴሌግራም ቻናል https://t.me/IbnuMunewor * የዋትሳፕ ቻናል፦ https://whatsapp.com/channel/0029VaA3X1e5kg7BlsJboa2M * ፌስቡክ https://www.facebook.com/Ibnu.Munewor?mibextid=ZbWKwL

ወስን ~ በጫትና በመጠጥ ሱስ ቤትህን እያፈረስክ፣ ልጆችህን እየበተንክ፣ የራስህንም ሆነ የቤተሰብህን ጥሪት እያወደምክ ያለኸው ወገኔ ሆይ! አይበቃም ወይ? እስከ መቼ ቁልቁል እያምዘገዘገህ ባለ ደባል ሱስ ተሸንፈህ ትኖራለህ? ሰው እንዴት የሰው እጅ ጠባቂ ሆኖ ይቅማል? ሰው እንዴት ይህንን የአህያ ሽንት የመሰለ እር.ኩስ መጠጥ ይጠጣል? ሰው እንዴት በገዛ ፈቃዱ ቀጥ ብሎ ወጥቶ እየተንገዳገደ ይመለሳል? ግዴለህም አላህን ፍራ! ለጤናህ አስብ። ለቤተሰብህ አስብ። ለትዳርህ አስብ። ለልጆችህ አስብ። በየሰው ቤት እየተንከራተቱ ገንዘብ ለሚልኩልህ አስብ። ስንት መከራ፣ ስንት ፈተና፣ በረሃ፣ እሳት፣ የሰው ፊት፣ ... አይተው፣ አሳር በልተው የሚልኩትን ገንዘብ ለማይረባ ቅጠል ስታውለው አያሳዝኑህም? ከምንም በላይ ደግሞ ለኣኺራህ አስብ። ወላሂ ከቆረጥክ ማቆም ይቻላል። ብቻ አንተ ወስን። ከዚያም ሰበብ አድርስ። ከልብ ካለቀሱ እምባ አይገድም። Ibnu Munewor = * የቴሌግራም ቻናል https://t.me/IbnuMunewor * የዋትሳፕ ቻናል፦ https://whatsapp.com/channel/0029VaA3X1e5kg7BlsJboa2M * ፌስቡክ https://www.facebook.com/Ibnu.Munewor?mibextid=ZbWKwL

ከረጀብ ወር ጋር የሚያያዙ ደካማ ሐዲሦች ~ ከረጀብ ጋር ብዙ መሰረተ ቢስ ቅጥፈቶችና ደካማ ሐዲሦች አሉ። ለምሳሌ ያክል፦ [1ኛ]፡- رجب شهر الله وشعبان شهري ورمضان شهر أمتي “ረጀብ የአላህ ወር ነው። ሸዕባን የኔ ወር ነው። ረመዷን ደግሞ የህዝቦቼ ወር ነው።” አልባኒይ ደካማ እንደሆነ ገልፀዋል። [አዶዒፋህ፡ 4400] [2ኛ]፡- ረጀብ ሲገባ እንዲህ ይሉ ነበር፡- اللهم بارك لنا في رجب وشعبان، وبلغنا رمضان “አላህ ሆይ! ረጀብንና ሸዕባንን ባርክልን። ረመዷንም አድርሰን።” ነወዊይ በ“አዝካር”፣ ዘሀቢይ በ“ሚዛን”፣ ኢብኑ ሐጀር በ"ተብዪኑል ዐጀብ" ደካማ እንደሆነ ብይን የሰጡ ሲሆን አልባኒይም “ደካማ ነው” ብለዋል። [ዶዒፉል ጃሚዕ፡ 4395] [3ኛ]፡- فضل شهر رجب على الشهور كفضل القرآن على سائر الكلام “የረጀብ ወር በሌሎች ወራት ላይ ያለው ብልጫ ቁርኣን በሌሎች ንግግሮች ላይ እንዳለው ብልጫ ነው።” ኢብኑ ሐጀር፣ ሙላ ዐሊይ አልቃሪ፣ አልዐጅሉኒይ፣ አልገዚይ እና አዘርቃኒይ “መሰረተ ቢስ ቅጥፈት ነው" (መውዱዕ) ብለዋል። [4ኛ]፡- خمس ليال لا ترد فيهن الدعوة أول ليلة من رجب، وليلة النصف من شعبان، وليلة الجمعة، وليلة الفطر، وليلة النحر “አምስት ሌሊቶች በነሱ ውስጥ የተደረገ ዱዓእ አይመለስም። የመጀመሪያው የረጀብ ሌሊት፣ የሸዕባን አጋማሽ ሌሊት፣ የጁሙዐ ሌሊት፣ የዒደል ፊጥር ሌሊት እና የዒደል አድሓ ሌሊት ናቸው።” አልባኒይ “መሰረተ ቢስ” ብለውታል። [አዶዒፋህ፡ 1452] [ዶዒፉል ጃሚዕ፡ 2852] [5ኛ]፡- رجب شهر عظيم يضاعف الله فيه الحسنات، فمن صام يوما من رجب، فكأنما صام سنة، ومن صام منه سبعة أيام، غلقت عنه سبعة أبواب جهنم، ومن صام منه ثمانية أيام، فتحت له ثمانية أبواب الجنة، ومن صام منه عشرة أيام، لم يسأل الله شيئا إلا أعطاه إياه، … “ረጀብ አላህ መልካም ምንዳዎችን የሚያነባብርበት ታላቅ ወር ነው። ከረጀብ አንድ ወር የፆመ ሰው አመት እንደፆመ ነው። ከሱ ሰባት ቀናትን የፆመ ሰባቱ የጀሀነም በሮች ይዘጉለታል። ከሱ ስምንት ቀናትን የፆመ ስምንቱ የጀነት በሮች ይከፈቱለታል። ከሱ አስር ቀናትን የፆመ አላህን የሆነ ነገር አይጠይቅም፣ እሱኑ የሰጠው ቢሆን እንጂ፣ …” አልባኒይ “መሰረተ ቢስ” ብለውታል። [አዶዒፋህ፡ 5413] [6ኛ]፡- إن في الجنة نهرا يقال له رجب ماؤه أشد بياضا من اللبن وأحلى من العسل من صام يوما من رجب سقاه الله من ذلك النهر “በጀነት ውስጥ ረጀብ የሚባል ወንዝ አለ። ውሃው ከወተት የነጣ፣ ከማር የጣፈጠ ነው። ከረጀብ አንድ ቀን የፆመ ሰው አላህ ከዚያ ወንዝ ያጠጣዋል።” አልባኒይ “መሰረተ ቢስ” ብለውታል። [ዶዒፉል ጃሚዕ፡ 1902] [7ኛ]፡- صوم أول يوم من رجب كفارة ثلاث سنين، والثاني كفارة سنتين، والثالث كفارة سنة، ثم كل يوم شهرا “የረጀብን የመጀመሪያ ቀን መፆም የሶስት አመት ወንጀል ያብሳል። ሁለተኛው የሁለት አመት ያብሳል። ሶስተኛው ደግሞ የአመት ያብሳል። ከዚያም እያንዳንዱ ቀን የወር ነው።” አልባኒይ ደካማ ብለውታል። [ዶዒፉል ጃሚዕ፡ 3500፣ 5649] [8ኛ]፡- لا تغفلوا عن أول جمعة من رجب فإنها ليلة تسميها الملائكة الرغائب “ከረጀብ የመጀመሪያ ጁሙዐ አትዘናጉ። እርሷ መላእክት ‘አረጋኢብ’ ብለው የሚጠሯት ሌሊት ነች።” ‘ሶላተ ረጋኢብን’ በተመለከተ ነወዊይ እንዲህ ብለዋል፡- “እርሷን የፈጠረን ሰው አላህ ይርገመው! እርሷ አስቀያሚ ቢድዐ ነች!” [ሸርሑ ሙስሊም] በተጨማሪም እሷንና የሸዕባን አጋማሽ ሌሊት ሶላትን አስመልክተው “… ቢድዐና አስቀያሚ ፈጠራዎች ናቸው። በ‘ቁቱል ቁሉብ’፣ ‘ኢሕያእ ዑለሚዲን’ ኪታብ ውስጥ ስለተጠቀሱ ማንም እንዳይሸወድ። እነሱን በሚጠቁመው ሐዲሥም እንዲሁ (እንዳይሸወድ)። ምክንያቱም ሁሉም ውድቅ ነውና” ብለዋል። [አልመጅሙዕ፡ 3/548] [9ኛ]፡- أن رسول الله -ﷺ- لم يصم بعد رمضان إلا رجبًا وشعبان “የአላህ መልእክተኛ ከረመዷን በኋላ ረጀብንና ሸዕባንን እንጂ አልፆሙም።” ኢብኑ ሐጀር በጣም ደካማ ነው ብለውታል። [ተብዪኑል ዐጀብ፡ 12] [10ኛ]፡- من صلى المغرب في أول ليلة من رجب ثم صلى بعدها عشرين ركعة يقرأ في كل ركعة بفاتحة الكتاب، وقل هو الله أحد مرة، ويسلم فيهن عشر تسليمات، أتدرون ما ثوابه؟ قال: حفظه الله في نفسه وأهله وماله وولده، وأجير من عذاب القبر، وجاز الصراط كالبرق بغير حساب ولا عذاب “በረጀብ የመጀመሪያ ሌሊት መግሪብን ሰግዶ ከዚያም በእያዳንዷ ረከዐ ፋቲሐንና ቁል ሁላሁ አሐድን አንድ ጊዜ እየቀራ፣ በአስር ተስሊማት እያሰላመተ ሃያ ረከዐ የሰገደ ሰው ምንዳው ምን እንደሆነ ታውቃላችሁ? አላህ በነፍሱም፣ በቤተሰቡም፣ በገንዘቡም፣ በልጁም ይጠብቀዋል። ከቀብር ቅጣትም ይጠበቃል። ሲራጥንም ያለ ሂሳብና ያለ ቅጣት እንደ ብልጭታ ያቋርጧል።” ኢብኑል ጀውዚና ኢብኑ ሐጀር መሰረተ ቢስ ቅጥፈት እንደሆነ ገልፀዋል። [አልመውዱዓት፡ 2/123] [ተብዪኑል ዐጀብ፡ 20] [11ኛ]፡- من صام من رجب وصلى فيه أربع ركعات ... لم يمت حتى يرى مقعده من الجنة أو يُرى له “ከረጀብ ፁሞ፣ በሱ ውስጥ አራት ረከዓዎችን የሰገደ ሰው … በጀነት ውስጥ መቀመጫውን ሳያይ ወይም ሳይታይለት አይሞትም።” ኢብኑል ጀውዚና ኢብኑ ሐጀር መሰረተ ቢስ ቅጥፈት እንደሆነ ገልፀዋል። [አልመውዱዓት፡ 2/124] [ተብዪኑል ዐጀብ፡ 21] [12ኛ]፡- إن شهر رجب شهر عظيم، من صام منه يومًا كتب الله له صوم ألف سنة ... “የረጀብ ወር ታላቅ ወር ነው። ከሱ አንድ ቀን የፆመ ሰው አላህ አንድ ሺ አመት ፆም ይመዘግብለታል።” ኢብኑል ጀውዚና ኢብኑ ሐጀር መሰረተ ቢስ ቅጥፈት እንደሆነ ገልፀዋል። [አልመውዱዓት፡ 2/206-207] [ተብዪኑል ዐጀብ፡ 26] ከረጀብ ጋር የሚያያዙት ዘገባዎች እነዚህ ብቻ አይደሉም። እነዚህን ለምሳሌ ያክል ይዘን ሌሎቹንም ጭምር በሚመዝን የዓሊሞች ንግግር ልቋጭ:— 1/ አልሓፊዝ ኢብኑ ሐጀር - ረሒመሁላህ - “የረጀብን ወር ልዩ ብልጫም፣ መፆሙን ወይም ከፊሉን በተለየ እንዲፆም፣ ወይም ከሱ ውስጥ የተገደበን ሌሊት በሶላት ማሳለፍን፣… የሚጠቁም ለማስረጃነት የሚበጅ ትክክለኛ ሐዲሥ አልተላለፈም" ብለዋል። [ተብዪኑል ዐጀብ፡ 6 እና 8] 2/ አልሓፊዝ አቡ ዐብዲላህ ሙሐመድ ኢብኑ አቢ በክር አዲመሽቂይ (691 ሂ.) ደግሞ “እያንዳንዱ የረጀብን ፆም እና ከፊል ሌሊቶቹን መስገድን የሚጠቁም ሐዲሥ ውሸት፣ ቅጥፈት ነው” ብለዋል። [አልመናሩል ሙኒፍ፡ 1/96] ልብ በሉ! በዚህ ወር ውስጥ ፆምና ሶላት አይኑር ለማለት አይደለም። ወሩን ከሌሎቹ ወራት በተለየ መልኩ መያዝ አይገባም ነው አጠቃላይ ጭብጡ። Ibnu Munewor = * የቴሌግራም ቻናል https://t.me/IbnuMunewor

“አሁንም ቀድሞ በነበረበት ነው።” ~ የአላህን ከዐርሹ በላይ መሆን የሚያስተባብሉ ሰዎች ከሚያጣቅሷቸው “መረጃዎቻቸው” ውስጥ አንዱ እንዲህ የሚል ነው፦ كَانَ اللَّهُ وَلَا شَيْءَ مَعَهُ ‌وَهُوَ ‌الْآنَ ‌عَلَى ‌مَا ‌عَلَيْهِ ‌كَانَ “አላህ ነበር። ከሱ ጋር ምንም አልነበረም። እርሱ አሁንም ቀድሞ በነበረበት ነው።” የመጨረሻውን ክፍል አሽዐሪዮች በሰፊው ያራግቡታል። እነሱ ዘንድ ሙስሊም ከዘገቡት ሐዲሡል ጃሪያ በላይ ዋጋ አለው። እንዲያውም አንዳንዶቹ ቡኻሪ ውስጥ ከሚገኝ ሐዲሥ ላይ በማያያዝ ሶሒሕ ቡኻሪ ውስጥ የሚገኝ አስመስለው ሲያወሩት ያጋጥማል። ይሄ የለየለት ማጭበርበር ነው። ቡኻሪ ውስጥ ቀርቶ የትኛውም የሐዲሥ ድርሳን ውስጥ አይገኝም። በሶሒሕ ይቅርና በደካማ ሰነድም አይታወቅም። ኢብኑ ሐጀር አልዐስቀላኒይ - ረሒመሁላህ እንዲህ ይላሉ፦ وَقَعَ فِي بَعْضِ الْكُتُبِ فِي هَذَا الْحَدِيثِ كَانَ اللَّهُ وَلَا شَيْءَ مَعَهُ وَهُوَ الْآنَ عَلَى مَا عَلَيْهِ كَانَ وَهِيَ زِيَادَةٌ لَيْسَتْ فِي شَيْءٍ مِنْ كُتُبِ الْحَدِيثِ نَبَّهَ عَلَى ذَلِكَ الْعَلَّامَةُ تَقِيُّ الدِّينِ بْنُ تَيْمِيَةَ وَهُوَ مُسَلَّمٌ فِي قَوْلِهِ وَهُوَ الْآنَ إِلَى آخِرِهِ “በአንዳንድ ኪታቦች ውስጥ በዚህ 'አላህ ነበር። ከሱ ጋር ምንም አልነበረም' በሚለው ሐዲሥ ላይ 'እርሱ አሁንም ቀድሞ በነበረበት ነው' የሚል ገብቷል። ይቺ ግን በየትኛውም የሐዲሥ ኪታቦች ውስጥ የማትገኝ ጭማሬ ናት። ይህንንም ታላቁ ሊቅ ተቂዩዲን ኢብኑ ተይሚያ ጠቁመውታል። 'እርሱ አሁንም ቀድሞ በነበረበት ነው፤ ...' በሚለው ላይ የሳቸው ንግግር እጅ የሚሰጥለት (ተቀባይነት ያለው) ነው።” [ፈትሑል ባሪ፡ 6/289] “ታዲያ በሐዲሥ ድርሳናት ውስጥ ከሌለ ከየት አመጡት?” ከተባለ ሌላ አንድ ጥቅሳቸውን ልጨምርና አብሬ እመልሳለሁ። እርሱም እንዲህ የሚል ነው፦ إن الله تعالى خلق العرش إظهارًا لقدرته لا مكانا لذاته “የላቀው አላህ ዐርሹን የፈጠረው ችሎታውን ለማሳየት እንጂ ለዛቱ ቦታ እንዲሆን አይደለም።” እነዚህን ሁለት ጥቅሶች ዐሊይ ብኑ አቢ ጧሊብ የተናገሯቸው ናቸው በማለት ያወራው ዐብዱል ቃሂር አቡ መንሱር አልበግዳዲ ነው። [አልፈርቅ በይነል ፊረቅ፡ 321] ሰነድ አለው ወይ? በጭራሽ! በ429 ሂ. በሞተው አቡ መንሱርና በ40 ሂ. በሞቱት ዐሊይ መካከል የ 389 አመት ርቀት አለ። ቅብብሎሹን የሚያሳይ ሰነድ ከሌለ በየት አቆራርጦ ነው ከዐሊይ የሚሰማው? ይህንን “ዶዒፍ” እንኳን መባል የሚበዛበት ውዳቂ ወሬ ነው ለዐቂዳቸው ማስረጃ የሚያደርጉት። እንግዲህ ተመልከቱ! የቁርኣንና ሐዲሥ ጉልህ መልእክት በአላህ ሲፋት ላይ ማስረጃ አይሆኑም የሚሉ ጉዶች፣ ለሶሒሕ ቡኻሪና ሶሒሕ ሙስሊም እጅ የማይሰጡ ፍጡሮች ናቸው እንዲህ አይነቱን ወፍ ዘራሽ ወሬ ለዐቂዳቸው እማኝ አድርገው የሚያቀርቡት! ደግሞኮ አቡ መንሱር የሐዲሥ ሊቅ አይደለም። ይልቁንም ከሐዲሥ ይልቅ ዐቅሉን የሚያስቀድም የዒልመል ከላም ፍልስፍና አራማጅ ነው። ምን እንደሚል አይታችሁ ፍረዱ፦ “አንድ ዘጋቢ አእምሮ የማይቀበለው ነገር ከዘገበ እና ትክክለኛ በሆነ መልኩ ተእዊል ለማድረግ (ለመቆልመም) ካልተመቸ ዘገባው ውድቅ ይሆናል። … ታማኝ የሆነው ዘጋቢ የዘገበው ሐዲሥ ጉልህ መልእክቱ አእምሮን የሚያስደነግጥ ከሆነና ነገር ግን ከአእምሯዊ ጉዳዮች ጋር በሚስማማ መልኩ ማዞር (መቆልመም) የሚቻል ከሆነ ዘገባውን ተቀብለን ከአእምሮ ጋር እንዲስማማ አድርገን መልእክቱን እናዞረዋለን (እንቆለምመዋለን)።” [ኡሱሉዲን፡ 23] ሐዲሥ ላይ ብይን ለመስጠት ያስቀመጠውን መስፈርት ተመልከቱ። የሐዲሥ ጥናት ሳይሆን የነሱን በፍልስፍና የተበከለ አእምሮ። ከቻሉ መረጃዎቹን እየቆለመሙ ሌላ ትርጉም መስጠት። ይህንን ነው ተእዊል የሚሉት። ለቁልመማ ፈፅሞ የማይመቹ ከሆኑ እንዲሁ “ዶዒፍ ናቸው” ብሎ መጣል! በቃ! በዚህ መልኩ ሶሒሕ ሐዲሥ ላይ የሚፈርድ ሰው ብልሹ እምነቱን ለማፅናት ግን ሰነድ አልባ ወሬ በዐሊይ ስም ያወራል። ከዚያ እንዲህ አይነቱን ከንቱ ወሬ በማስቀደም የቁርኣንና የሐዲሥ ማስረጃዎችን ይጥላሉ። ይሄ የጤና ነው? Ibnu Munewor = * የቴሌግራም ቻናል https://t.me/IbnuMunewor * የዋትሳፕ ቻናል፦ https://whatsapp.com/channel/0029VaA3X1e5kg7BlsJboa2M * ፌስቡክ https://www.facebook.com/Ibnu.Munewor?mibextid=ZbWKwL

ደርስ ~ * መንሀጁ ሳሊኪን * ክፍል:- 1️⃣6️⃣ * የደርሹ መነሻ፦ ويسن سجود التلاوة * የሚሰጥበት ቦታ፦ የሺ ደበሌ ከፍ ብሎ ሑዘይፋህ መስጂድ * የሚሰጥበት ጊዜ፦ ዘወትር እሁድ ረፋድ ላይ = የቴሌግራም ቻናል፡- https://t.me/IbnuMunewor

ምስልን ለእርዳታ ስራ መጠቀም ~ የምስል ቀረፃን በተመለከተ በዑለማኦች የተለያዩ ሃሳቦች እንደተሰነዘሩ ይታወቃል። ሸይኽ ኢብኑ ዑሠይሚን ጉዳዩ የኢጅቲሃድ ርእስ ሆኖ ሳለ በዚህ ጉዳይ ተጠምደው በሚበጠብጡ ሰዎች እንደሚደነቁ ገልፀዋል። ንግግራቸውን በዚህ ሊንክ ማግኘት ይቻላል፦ https://youtu.be/8YY84nvhTtM?si=MFIpTMghTEYZ_e3F ሸይኽ ሙሐመድ ባዝሙልም በተመሳሳይ የሸይኽ ኢብኑ ዑሠይሚንን ንግግር አያይዘው ጉዳዩ የኢጅቲሃድ ርእስ እንደሆነ ይገልፃሉ። https://fb.watch/pAsU7is-K1/?mibextid=Nif5oz ይህንን የማያይዘው በዚህ ርእስ የተነሳ የመሻይኾችን፣ ዱዓቶችን ስም የሚያጎድፉ ቂላ -ቂሎች ስለበዙ ነው። ሚዛን የሚደፋውን ከመውሰድ ባሻገር በመሰል ጉዳዮች ሰዎችን እየመዘኑ "እከሌ አቋሙ ወረደ" የሚሉ በሱና ስም የሚጮሁ ሞኞ -ችን ማየት ያሳቅቃል። ይህንን እንደ መግቢያ ካልኩ ከዚህ በፊት ቀረፃን ለደዕዋ ስራ ስለመጠቀም የዑለማኦችን ንግግር በማያያዝ ፅፌ ነበር። ዛሬ ደግሞ በተራድኦ ስራ ላይ ስላለ ቀረፃ አነሳለሁ። በእርዳታ ስራ ላይ የቪዲዮም ሆነ የፎቶግራፍ ምስሎችን መጠቀም የተለመደ ነው። በጦርነት የተፈናቀሉ፣ በጎርፍ የተጠቁ፣ በተለያዩ ሰበቦች ችግር ላይ የወደቁ ወገኖች ያሉበትን ሁኔታ በማየት ሰዎች/ ድርጅቶች እንዲረዷቸው ለማድረግ ምስላቸውን መውሰድና ማሰራጨት የተለመደ ነው። ልክ እንዲሁ ለመሰል አካላት እርዳታ ካደረሱ በኋላ መረጃውን ለረጂዎቹ በምስል ማቅረብም በግለስቦችም፣ በእርዳታ ድርጅቶችም ይፈፀማል። እነዚህ አሰራሮች ለተጎጂዎቹ እርዳታ ለማፈላለግ፣ ለረጂዎቹ ደግሞ መረጃ ለማቅረብ ያግዛሉ። ለመሰል ችግርም ቢሆን ምስል መጠቀምን የሚከለክሉ አሉ። ለምሳሌ ሸይኽ ፈውዛን። በመሰል ሁኔታ ላይ የሚፈቅዱም አሉ። ለምሳሌ ሸይኽ ሱለይማን አሩሐይሊይ። በርግጥ ለምስኪኖች በሚሰጥ እርዳታ ላይ ቀረፃን ማራቅ ነው የሚሻለው። ሸይኽ አልኸሥላን የበጎ አድራጎት ተግባራትን በምስል መቅረፅን በተመለከተ የተለያዩ ነገሮች ይጋረጡበታል ይላሉ። አንደኛ ነገር፦ ኢኽላስን ሊጎዳ ይችላል። { إِن تُبۡدُوا۟ ٱلصَّدَقَـٰتِ فَنِعِمَّا هِیَۖ وَإِن تُخۡفُوهَا وَتُؤۡتُوهَا ٱلۡفُقَرَاۤءَ فَهُوَ خَیۡرࣱ لَّكُمۡۚ } "ምጽዋቶችን ብትገልጹ እርሷ ምንኛ መልካም ናት። ብትደብቋትና ለድሆች ብትሰጧትም እርሱ ለናንተ በላጭ ነው።" [አልበቀረህ፡ 271] ሁለተኛ ነገር ድሃውን የሚፈትን ሊሆን ይችላል። ድሃው መቀረፁን ላይወድ ይችላል። ይሄ ደግሞ ከአጉል መመፃደቅና ማስቸገር ውስጥ እንዳይገባ ያሰጋል። አላህ እንዲህ ይላል፦ { یَـٰۤأَیُّهَا ٱلَّذِینَ ءَامَنُوا۟ لَا تُبۡطِلُوا۟ صَدَقَـٰتِكُم بِٱلۡمَنِّ وَٱلۡأَذَىٰ كَٱلَّذِی یُنفِقُ مَالَهُۥ رِئَاۤءَ ٱلنَّاسِ وَلَا یُؤۡمِنُ بِٱللَّهِ وَٱلۡیَوۡمِ ٱلۡـَٔاخِرِۖ } "እናንተ ያመናችሁ ሆይ! እንደዚያ ገንዘቡን ለሰዎች ማሳየት ሲል እንደሚሰጠውና በአላህና በመጨረሻውም ቀን እንደማያምነው ሰው ምጽዋቶቻችሁን በመመጻደቅና በማስከፋት አታበላሹ።" [አልበቀረህ፡ 264] ከዚህ አንፃር ባይቀረፁ የተሻለ ነው። እርዳታው ለሚገባው አካል እንደ ደረሰ መረጃ ማቅረብ የሚሻ አካል ቢሆን እንጂ። በዚህን ጊዜ ቀረፃው ለመረጃነት እንደተፈለገ በመንገር ችግረኛውን ማስፈቀድ ጥሩ ነው። ምንም ሐጃ በሌለበት መቅረፅ ግን ምናልባት አጅርን እንዳያጠፋ ያሰጋል። [በቪዲዮ ከቀረበ ፈትዋ ተነካክቶ የተወሰደ።] በመጨረሻም ባያያዝኩት ቪዲዮ ውስጥ የሚሰማው ድምፅ የወንድማችን ሑሰይን ሙሐመድ አሲልጢ ድምፅ ነው። ለጥቂት የበግ እርዳታ ማስረጃ ይሆን ዘንድ የቪዲዮ ቀረፃ እያቀረበ ነው። ራሱ ለጥፎት ነው ያገኘሁት። የማቀርበው ለትችት አይደለም። እዚያ አካባቢ በቡድን የታጠሩ፣ የዑለማእ ንግግር ቢቀርብም ደንታ የማይሰጣቸው አካላት ስለበዙ ቢያንስ "የኛ" በሚሉት አካል ጉዳዩ ሲፈፀም ሲያዩ ሰከን ቢሉ ብዬ ነው። ወንድም ጠሀ ኸዲር እንኳ የፌስቡክ አካውንቱ በርካታ ምስሎች አሉበት። ሴትና ወንድ የተቀላቀሉበት ቪዲዮ ጭምር ያሉበት የፋና ዘገባ ሊንክ ሲያይዝ ነበር። እና ከስር የምትጮሁ አካላት ለሌላ ሳይሆን እንዲያው ለራሳችሁ ብታዝኑ መልካም ነው ለማለት አካባቢ ነው። ልመለስ እችላለሁ። Ibnu Munewor = * የቴሌግራም ቻናል https://t.me/IbnuMunewor * የዋትሳፕ ቻናል፦ https://whatsapp.com/channel/0029VaA3X1e5kg7BlsJboa2M * ፌስቡክ https://www.facebook.com/Ibnu.Munewor?mibextid=ZbWKwL

"አስቸኳይ መልዕክት ! ~~~~~~~~~~~~~ አሠላሙ ዓለይኩም ወረህመቱላሂ ወበረካቱ ውድ የተከበራችሁ ወንድም እና እህቶቼ ከታች በምስሉ ላይ የምትመለከቷት ልጅ ዘህራ ጣሃ እባላለው አለች።ከወራቤ ፈ
"አስቸኳይ መልዕክት ! ~~~~~~~~~~~~~ አሠላሙ ዓለይኩም ወረህመቱላሂ ወበረካቱ ውድ የተከበራችሁ ወንድም እና እህቶቼ ከታች በምስሉ ላይ የምትመለከቷት ልጅ ዘህራ ጣሃ እባላለው አለች።ከወራቤ ፈይነት ሩቃ ቤት ነው ጠፍቼ የወጣሁት አለች ። የምታውቋት በዚህ ስልክ ቁጥር በመደወል ማግኘት ትችላለችሁ ። 0930887835 ወይም 0949283077

ደርስ ~ * ሪያዱ ሷሊሒን * ክፍል:- 1️⃣3️⃣5️⃣ * የኪታቡን ሶፍት ኮፒ (በ pdf ) በዚህ ሊንክ ማግኘት ትችላላችሁ https://t.me/IbnuMunewor/3505 * የለቱ ደርስ መነሻ ገፅ 381፣ كتاب الفضائل * የሚሰጥበት ቦታ፦ አሸዋ ሜዳ፣ መስጂደል ዋሊደይን * የሚሰጥበት ጊዜ:- ረቡዕ፣ ሐሙስ እና ጁሙዐ = የቴሌግራም ቻናል፡- https://t.me/IbnuMunewor

የሱፊያ "ወሃ.ቢዮች!" ~ “አላህ ከዐርሹ በላይ ነው” የሚለው እምነት በቁርኣንና በሐዲሥ የፀና የሰለፎች እምነት ነው። አንዳንዶች ግን አይናቸውን በጨው አጥበው “የወሃብዮች እምነት ነው” ይላሉ። ይሄ እምነት ሌላው ቀርቶ የጥንት ሱፊዮችም እምነት ነው። እንደለመዱት “ወሃቢዮች” ብለው ከኢስላም ያስወጧቸው ከሆነ እናያለን። ጥቂቶቹን ልጥቀስ፦ 1. አልወዚር ዐሊይ ብኑ ዒሳ (334 ሂ.) ረሒመሁላህ እንዲህ ብለዋል፦ الربُّ عزَّ وجلّ فِي السَّمَاءِ يَقْضِي ويُمْضِي “ጌታ - ዐዘ ወጀል - በሰማይ ነው! ይፈርዳል፣ ይፈፅማል።” [አልሒልያህ፡ 13/367] 2. መዕመር ብኑ ዚያድ አልአስበሃኒይ (418 ሂ.) የጥንት ሱፊዮችን ጨምሮ የዑለማኦችን ኢጅማእ ሲያወሱ እንዲህ ብለዋል፡- وَأَن اللَّه عَزَّ وَجَلَّ اسْتَوَى عَلَى عَرْشه بِلَا كَيفَ وَلَا تَشْبِيه وَلَا تَأْوِيل، فالاستواء مَعْقُول، والكيف فِيهِ مَجْهُول، والإِيمان بِهِ وَاجِب، والإِنكار لَهُ كفر، وَأَنه جلّ جَلَاله مستو عَلَى عَرْشه بِلَا كَيفَ، وَأَنه جلّ جَلَاله بَائِن من خلقه والخلق بائنون مِنْهُ “አላህ - ዐዘ ወጀል - ያለ እንዴት ማለት፣ ያለ ማመሳሰል፣ ያለ ቁልመማ ከዐርሹ በላይ ከፍ ብሏል። ከፍ ማለቱ የታወቀ ነው። አኳኋኑ አይታወቅም። በዚህ ማመን ግዴታ ነው። ይህን ማስተባበል ክህደት ነው። እርሱ - ጀለ ጀላሉሁ - ያለ አኳኋን በዐርሹ ላይ ከፍ ብሏል። እርሱ - ጀለ ጀላሉሁ - ከፍጡሩ ተለይቶ፣ ፍጡሮቹም ከሱ ተለይተው ነው ያሉት።” [አልሑጃህ፣ ተይሚ፡ 1/248] 3. የሕያ ብኑ ዐማር (422 ሂ.) እንዲህ ብለዋል፡- نقُول: هُوَ بِذَاتِهِ عَلَى الْعَرْش، وَعلمه مُحِيط بِكُل شَيْء “እርሱ በዛቱ በዐርሹ ላይ ነው እንላለን። እውቀቱ ግን ሁሉንም ነገር ያካበበ ነው።” [አልሑጃ፣ ተይሚ፡ 2/109] 4. አቡ ኑዐይም አልአስፈሃኒይ (430 ሂ.) እንዲህ ብለዋል፡- وأجمعوا أنَّ اللهَ فَوْقَ سماواتِهِ، عالٍ عَلَى عرشِهِ، مُسْتَوٍ عليهِ، لاَ مُسْتَولٍ عَلَيهِ كَمَا تقولُ الجهميَّةُ “(የሱና ሰዎች) ‘አላህ ከሰማያቱ በላይ፣ በዐርሹ ላይ እንደሆነና በሱ ላይ ከፍ ብሎ እንጂ ጀህሚያዎች እንደሚሉት እሱን መቆጣጠር አይደለም’ ብለው ተስማምተዋል።” [መሐጀቱል ዋሢቂን፡ አቡ ኑዐይም] [መጅሙዑል ፈታዋ፡ 5/60] 5. አቡ ኢስማዒል አልሀረዊይ (481 ሂ.)፡- “አልአርበዑን ፊ ደላኢሊ ተውሒድ” በተሰኘው ኪታባቸው ውስጥ “አላህ በሰማይ ለመሆኑ ማስረጃ” የሚልና “አላህ በዐርሹ ላይ ለመሆኑ ማስረጃ” የሚሉ ሁለት ርእሶችን ሰጥተው ዘርዝረዋል። [ገፅ፡ 53-55] የአላህን ከዐርሹ በላይ መሆን በማያምኑ ላይ የተሰላ ሰይፍ ነበሩ። በዚህ የተነሳ አሽዐሪዮች ሊያጠፏቸው ብዙ ዶልተውባቸዋል። አንዱን ልጥቀስ። ንጉስ አልብ አርሰላን ወደ ሄራት ሲገባ የሃገሬው መሻይኽና መኳንንት ተሰብስበው አልሀረዊይ ዘንድ በመግባት ሰላምታ አቅርበው፡ “ንጉሱ እየመጣ ስለሆነ ወጥተን ልንቀበለው ወስነናል። አንተን በመጎብኘት ልንጀምር ወደድን” አሏቸው። የመጡት ግን ለእኩይ አላማ ነበር። ቀስ ብለው በሀረዊይ መስጂድ ሚሕራብ ውስጥ ከመስገጃቸው ስር ከነሐስ የተሰራ ጣኦት አስቀምጠው ወጡ። ሀረዊይ አላስተዋሉም። ንጉሱ ዘንድ ሲደርሱ ሀረዊይ እንዳስቸገሯቸው፣ አላህን በፍጡር የሚያመሳስሉ ሙጀሲም እንደሆኑ እና ከሚሕራቡ ውስጥ የአላህ ምስል ነው በማለት ያስቀመጡት ጣኦት እንዳለ አቀነባብረው ከሰሷቸው። ንጉሱ ነገሩ ሰቀጠጠው። ሰው ቢልክ እንደሚያገኘው ሲነግሩት ላከ። መልእክተኛው ጣኦቱን አምጥቶ ከንጉሱ ፊት ጣለው። ንጉሱ ሀረዊይ እንዲቀርቡለት አዘዘ። ሲደርሱ ጣኦቱንም ዑለማዎቹንም ተመለከቱ። ንጉሱ ቁጣው ገንፍሏል። “ምንድን ነው ይሄ?” አላቸው። “አሻንጉሊት የመሰለ ከመዳብ የተሰራ ጣኦት” አሉት። “ስለሱ አልጠየቅኩህም” አላቸው። “እናስ ንጉሱ ስለምን ኖሯል የሚጠይቀኝ?” አሉ። “የምታመልከው ይህንን እንደሆነና አላህ በዚህ አምሳል ነው ብለህ እንደምትሞግት እነዚህ እየሞገቱ ነው” አለ። ድምፃቸውን ከፍ በማድረግ {ጥራት ይገባህ! ይሄ ትልቅ ቅጥፈት ነው!} የሚለውን የቁርኣን አንቀፅ ቀሩ። ነገሩ ሴራ እንደሆነ ሲረዳ በክብር ወደ ቤታቸው ሸኛቸው። ከዚያ “እውነቱን ንገሩኝ!” በማለት እነዚያን ሴረኞች ሲያፋጥጣቸው፡ “እኛ ይሄ ሰውየ ህዝቡን ስለያዘው ፈተና ላይ ነን። እና ተንኮሉን ልንገላገል ነበር ይህን ያደረግነው” አሉ። ንጉሱ አዋርዶ አባረራቸው። [አሲየር፡ 18/512] ቢሳካላቸው የሚሆነውን አስቡት። ከዚያም በአህሉል ሐዲሥ ላይ ምን አይነት ታሪክ እንደሚፅፉ ሳሉት። አዑዙ ቢላህ! 6. ዐብዱል ቃዲር አልጀይላኒይ (561 ሂ.)፡- የአላህን ከዐርሹ በላይ መሆንም ደጋግመው አስረግጠዋል። ለምሳሌ ያክል ጥቂት ንግግሮቻቸውን ላጣቅስ፡- وعرش الرحمن فوق الماء، والله تعالى على العرش “የአረሕማን ዐርሽ ከውሃው በላይ ነው። ከፍ ያለው አላህ ከዐርሹ በላይ ነው።” [አልጉንያ፡ 1/123] وَهُوَ بِجِهَةِ العُلُوِّ، مُسْتَو عَلَى العَرْشِ “እርሱ በላይ አቅጣጫ ከዐርሹ በላይ ከፍ ብሎ ነው።” [አልጉንያ፡ 1/121] የአላህን ከዐርሹ በላይ መሆን ያስተባበላችሁ ሱፊዮች ሆይ! ይሄው ከኢጅማዕ ብቻ ሳይሆን ከቀደምት ሱፍዮች መስመርም አፈንግጣችኋልና እባካችሁን ተመለሱ! Ibnu Munewor = * የቴሌግራም ቻናል https://t.me/IbnuMunewor * የዋትሳፕ ቻናል፦ https://whatsapp.com/channel/0029VaA3X1e5kg7BlsJboa2M * ፌስቡክ https://www.facebook.com/Ibnu.Munewor?mibextid=ZbWKwL

ከደቂቃዎች በኋላ የሪያዱ ሷሊሒን ደርስ ይኖራል ኢንሻአላህ።