en
Feedback
📚منهج السلف طريقنا الى الله 📚

📚منهج السلف طريقنا الى الله 📚

Open in Telegram

↘️በዚህ ቻናል የሚተላለፉት ↘️በሱና ኡስታዞች የተቀሩ ደርሶች ↘️የሱና ኡስታዞች ሙሀደራዎች ↘️በመቀጠል አስተማሪ ፁሁፎች ➴➴➴➴➴➴➴➴➴➴➴➴ https://t.me/htt_asselfya

Show more
3 819
Subscribers
-524 hours
+1617 days
+15530 days
Posts Archive
Repost from SadatTefsir
ከዚህ በፊት ከሳውዲ ሱና ቴሌቭዥን ላይ ያወረድኩትን የነብዩ (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) ሀዲስ የድምፅ ፋይል ቃል በቃል የተተረጎመ 150 ሐዲስ በአላህ ፍቃድ የሚከተለው ነው።

Repost from Fuad Mohammed
العصبية القبلية Gosummaafii sabummaa https://t.me/fuadorodurus

""ሙሓደራ ክፍል 190 "" አዲስ ሙሓደራ ክፍል 02 ረድ በ ወሰን ተላላፊዎች ላይ የ ሚዳሰሱ ነጥቦች ለ አብነት 👇 ““የ አቡዘር (አቡ ጦልሓ) ስህተቶች እና ግጭጭቶች…““ 🎤 በ ኡስታዝ ኸድር አሕመድ አል ከሚሴ (አቡ ሐቲም) https://t.me/UstazKedirAhmed

ጥንቃቄ ~ አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ እና ብዙ ወጣት ሴቶች በሚዝናኑባቸው ቦታዎች ትላልቅ ከተማዎች ላይ GHB የሚባል ኬሚካል ተበራክቷል። "ጋባዦች" አንድ መጠጥ ውስጥ የGHB ጠብታ ሲጨምሩበት ተጠቂዎች (አብዛኛውን ጊዜ ሴቶች) በጥቂት ደቂቃዎች ውስጥ ያሉበት፣ አብረዋቸው የነበሩበትን እና የተወሰዱበትን ቦታ አያስታውሱም። ገንዘብ ተከፍሏቸው የደነዘዙ ሴቶችን ለማስደፈር የሚያቀርቡ ውጣት ወንዶችም ሴቶችም ይሄንን እየሰሩ የሚኖሩ ብዙዎች ናቸው። በተለይ "የቤት ልጅ" አይነት የሚባሉ (ተማሪዎች) እና ሌሎች ወጣት ሴቶች የዚህ ወንጀል ተጠቂ እየሆኑ ነው። GHB ከሰውነታቸው ወጥቶ ሲነቁ በማይታወቅ ቦታ ብዙ ጉዳት ደርሶባቸው ራሳቸውን ያገኛሉ። ምን እንደተፈጠረ አያውቁም። GHB የሰው ሕይወት ሊያጠፋ ይችላል። በከተሞች መዝናናት እና መገባበዝ ደግሞ የተለመደ ስለሆነ ጥንቃቄ ማድረግ ያስፈልጋል። እንዲህ አይነት ወንጀሎች በቅርብ ጊዜ ወደ ኢትዮጵያ የመጡት ውጪ ከኖሩ ኢትዮጵያውያን ነው። ኮፒ "ሼር" ቢደረግ ለወገን ይጠቅማል። = የቴሌግራም ቻናል፡- https://t.me/IbnuMunewor

ኢብኑ ዑሠይሚን - ረሒመሁላህ - እንዲህ ይላሉ:- "ሚስትህ ጥፋት ብትፈፅምብህ የዛሬውን ጥፋት ብቻ አትመልከት። ወደኋላም ተመልከት። ወደፊትም ተመልከት። ከዚያም በፍትህ ፍረድ።" [ሸርሑ ሪያዲ ሷሊሒን፡ 2/73] ሚስትም የባሏን ጥፋት እንዲሁ ትመልከት። = የቴሌግራም ቻናል፡- https://t.me/IbnuMunewor

አንድ ነጥብ ~ የትግራይ ህዝብ በጦርነቱ ከፍተኛ ጉዳት እንደደረሰበት የሚታወቅ ነው። ሰሞኑን የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳይ ሰዎች ከ67 ሚሊዮን ብር በላይ ግምት ያለው እርዳታ ማድረጋቸው ጥሩ የድጋፍ ስራ መሆኑን አውስቼ "አላህ ጀዛቸውን ይክፈላቸው" ብል ይሄ ስሜት ያሰከረው መንጋ ሲንጫጫ ነበር። ከዚህ በፊት የመስጂድ ቦታ ለሰጡን አካላት ምስጋና ስገልፅ ምንም ያላሉት እነዚያ ሙስሊሞች ስላልሆኑ ነው። አንዳንድ ሰዎች ዘንድ "እናመሰግናለን፣ አላህ ይስጥልን" ማለት ለሙስሊሞች ሲሆን የቢድዐን አካል ማወደስ፣ የመንሀጅ መንሸራተት ሲሆን ለካፊሮች ሲሆን ግን ችግር የለውም። እንዲያውም እንደ ንቃት ነው የሚቆጠረው። ነገሮች እንዴት እየተያዙ እንደሆነ ቆም ብለን እናስተውል። በተረፈ የመጅሊስ ሰዎች አካሄድ እንከን የለሽ ነው የሚል አቋም የለኝም። ባደባባይ ከሚታዩ ችግሮቻቸው ውስጥ በአንድ ሁለቱ ላይ ከዚህ ቀደም በግልፅ ፅፌያለሁ። ለማንኛውም አንድ አካል ችግር ቢኖርበት እንኳ በመልካም ስራው ላይ "ጀዛሁላሁ ኸይራ" ማለት አቧራ የሚያስነሳ አይደለም። 1- ኢብኑ ባዝ - ረሒመሁላህ - ከሙሐመድ አልገዛሊ "መዐ'ላህ" ኪታብ በረጅሙ ከወሰዱ በኋላ መጨረሻ ላይ "ጀዛሁላሁ ኸይራ" ይላሉ። [ነቅዱል ቀውሚየቲል ዐረቢያ] [መጅሙዑ ፈታዋ፡1/317] 2- ሸይኹል አልባኒይም - ረሒመሁላህ - አሕመድ ዲዳትን ትልቅ ጂሃድ ላይ እንዳሉ በመግለፅ "ጀዛሁላሁ ኸይራ" ይላሉ። [ሲልሲለቱል ሁዳ ወኑር] 3- ሸይኽ ሙሐመድ ዐሊ ኣደምም እንዲሁ ከዩሱፍ አልቀርዳዊ "ፊቅሁ ዘካ" ኪታቡ ረዘም ያለ ክፍል ከወሰዱ በኋላ "ጀዛሁላሁ ኸይራ" ይላሉ። [ዘኺራ፡ 22/168] አለፍ ብለውም እንዲህ ሲሉ ስራውን ከማድነቅ ጋር ዱዓእ ያደርጋሉ:- انتهى ما كتبه الدكتور القرضاويّ شكر اللَّه سعيه، وهو بحثٌ نفيسٌ جدًا. የቀርዷዊ ማንነት የሚታወቅ ነው። አሁንም ሸይኹል አልባኒይ ለሙሐመድ አልገዛሊይ እና ዩሱፍ አልቀርዷዊይ አድናቆታቸውን ከገለፁ በኋላ ለቀርዷዊ "አላህ ይጠብቀው። ሙስሊሞችንም ይጥቀምበት" ብለዋል። [ጋየቱል መራም፡ 7] አልባኒይ የነዚህን አካላት ብልሹ አካሄድ በመተቸት የታወቁ ናቸው። ከመሆኑም ጋር "በመልካም ስራቸው" ላይ አላህ እንዲመነዳቸው ዱዓእ ሲያደርጉ እናያለን። መሰል አካሄድ ብንፈልግ ሌሎችም ጋር እናገኛለን። "ሙብተዲዕን ማድነቅ ይቻላል" እያልኩ አይደለም። ይልቁንም ነገሮችን መለየትና በልክ መያዝ እንልመድ እያልኩ ነው። ያያያዝኩት በሕሩ ተካ በጉራጌ ዞን ጉንችሬ ላይ የነበረን ሁከት ተከትሎ የነበረውን ሂደት አስመልክቶ ርስቱ ይርዳውን፣ የፍትህ ሚኒስቴርን፣ አስተዋይና ሚዛናዊ ብሎ የገለፃቸውን ክርስቲያኖችን፣ የጉንችሬና የእነሞር አመራሮችን ያደነቀበትና ያመሰገነበት ነው። ለሽፋን ከሚቀርቡ ሰሞንኛ ግርግር ውጭ እነዚህ የተጠቀሱት አካላት ለአካባቢው ችግር ወይ ጠንሳሽ ናቸው። ወይ አፍራሽ ሚና የነበራቸው ናቸው። ወይ ደግሞ ኃላፊነታቸውን ባለመወጣት ችግሩ እንዲቀጥል ያደረጉ ናቸው። (የተነሳውን ነጥብ ጥለው በማስቀየስ ላይ እንደሚጠመዱ እጠብቃለሁ።) = የቴሌግራም ቻናል፡- https://t.me/IbnuMunewor

ደርስ ~ * ሪያዱ ሷሊሒን * ክፍል:- 1️⃣4️⃣4️⃣ * የኪታቡን ሶፍት ኮፒ (በ pdf ) በዚህ ሊንክ ማግኘት ትችላላችሁ https://t.me/IbnuMunewor/3505 * የለቱ ደርስ መነሻ ገፅ 426፣ باب استحباب قيام رمضان * የሚሰጥበት ቦታ፦ አሸዋ ሜዳ፣ መስጂደል ዋሊደይን * የሚሰጥበት ጊዜ:- ሐሙስ እና ጁሙዐ = የቴሌግራም ቻናል፡- https://t.me/IbnuMunewor

ኢስራእ እና ሚዕራጅ መቼ ተካሄደ? ~ ብዙ ሰዎች በተለይም ሱፍዮች አካባቢ ኢስራእ እና ሚዕራጅ ረጀብ 27 እንደተካሄደ ያምናሉ። ግና ይህን የሚያስረዳ ሶሒሕ ማስረጃ ማቅረብ አይችሉም ። ክስተቱ በምን ቀን፣ በምን ወር፣ በየትኛው አመት እንደተፈፀመ በውል አይታወቅም። በዚህም ሳቢያ የዑለማዎች ሐሳብ ተለያይቷል። ጊዜውን የሚጠቁም አንድም ሶሒሕ ማስረጃ በሌለበት ረጀብን እየጠበቁ የሚያከብሩ ሰዎች የሚገርሙ ናቸው። ረጀብ ነው የሚለውን "ግልፅ የሆነ ውሸት ነው" ብለው የገለፁት አሉ። አመቱን በተመለከተ ① ከሂጅራ በፊት ስድስት ወር ቀደም ብሎ፣ ② ከሂጅራ አንድ አመት በፊት ③ ከሂጅራ ከ 3 አመት በፊት፣ ④ ከሂጅራ ከ5 አመት በፊት፣ ⑤ ከመላካቸው በፊት፣ ወዘተ የሚሉ አሉ። ከሂጅራ ከ8 ወር በፊት፣ ከሂጅራ ከ11 ወር በፊት፣ ከሂጅራ ከ15 ወር በፊት፣ ከሂጅራ ከ17 ወር በፊት፣ ከሂጅራ ከ18 ወር በፊት፣ ከሂጅራ ከ20 ወር በፊት እና ሌሎችም። ወሩን በተመለከተነው ① ረቢዑል አወል ወር ነው የሚል ዘገባ አለ። [ጦበቃት ኢብኒ ሰዕድ: 1/213–214] ② ዙል ቂዕዳ ወር ያሉ አሉ። [አልቢዳያ ወኒሃያህ: 3/109] ③ ረጀብ ወር ነው ያሉ አሉ። ④ ረመዳን ነው ያሉም አሉ። ⑤ ረቢዑል ኣኺር ያሉም አሉ። ⑥ ሸዋል ወር ያሉም አሉ። ከነዚህ ውስጥ አመቱንም ወሩንም የሚጠቁም አንድም ሶሒሕ ማስረጃ የለም። ያሉት ማስረጃዎች በሙሉ ደካማ ናቸው። ስለዚህ ኢስራእና ሚዕራጅ አላህ ለነብዩ ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም የዋለው ትልቅ ተአምር ቢሆንም ጊዜው በትክክል አይታወቅም። ይህም በሱፍዮች እንደሚደረገው አመት እየጠበቁ ክስተቱን ማክበር ቀደምቶች ዘንድ እንዳልነበር በቂ ማስረጃ ነው። ሰለፎች ዘንድ ቢከበር ኖሮ ጊዜው በውል ይታወቅ ነበርና። (ኢብኑ ሙነወር፣ ሚያዚያ 16/2009) = የቴሌግራም ቻናል፡- https://t.me/IbnuMunewor