📚منهج السلف طريقنا الى الله 📚
Open in Telegram
↘️በዚህ ቻናል የሚተላለፉት ↘️በሱና ኡስታዞች የተቀሩ ደርሶች ↘️የሱና ኡስታዞች ሙሀደራዎች ↘️በመቀጠል አስተማሪ ፁሁፎች ➴➴➴➴➴➴➴➴➴➴➴➴ https://t.me/htt_asselfya
Show more3 819
Subscribers
-524 hours
+1617 days
+15530 days
Posts Archive
ሙሓደራ ክፍል 189
አዲስ ሙሓደራ ክፍል 01
ረድ በ ወሰን ተላላፊዎች ላይ
የ ሚዳሰሱ ነጥቦች ለ አብነት 👇
““የ አብዱል ሀሚድ አልለተሚይ እና ሁሰይን ሙሀመድ ስህተቶች እና ግጭጭቶች…““
🎤 በ ኡስታዝ ኸድር አሕመድ አል ከሚሴ (አቡ ሐቲም)
https://t.me/UstazKedirAhmed
ደርስ
~
* ሪያዱ ሷሊሒን
* ክፍል:- 1️⃣4️⃣3️⃣
* የኪታቡን ሶፍት ኮፒ (በ pdf ) በዚህ ሊንክ ማግኘት ትችላላችሁ
https://t.me/IbnuMunewor/3505
* የለቱ ደርስ መነሻ ገፅ 421፣ ሐዲሥ ቁ. 1158
* የሚሰጥበት ቦታ፦ አሸዋ ሜዳ፣ መስጂደል ዋሊደይን
* የሚሰጥበት ጊዜ:- ሐሙስ እና ጁሙዐ
=
የቴሌግራም ቻናል፡-
https://t.me/IbnuMunewor
Repost from Ibnu Munewor (ኢብኑ ሙነወር)
የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳይ ትግራይ ላይ ያደረጉት መልካም ስራ ይበል የሚያሰኝ ነው። ከ67 ሚሊዮን ብር በላይ ግምት ያለው ድጋፍ አደረጉ። አላህ ጀዛቸውን ይክፈላቸው።
=
የቴሌግራም ቻናል
https://t.me/IbnuMunewor
Repost from Ibnu Munewor (ኢብኑ ሙነወር)
አስቸኳይ
~
በሰሜን ወሎ ዳውንት ወረዳ የወረዳው አመራሮች በአካባቢው ሙስሊሞች የውስጥ ጉዳይ ጣልቃ በመግባት ህገ ወጥ ለሆኑ ክፍሎች በመወገናቸው የተነሳ በሙስሊሞች መካከል ደም ሊያፋስሱ ጉዳዩ ጫፍ ደርሷል። የሚመለከታችሁ ክፍሎች ባስቸኳይ እልባት ስጡ። ከቦታው የደረሰኝ መረጃ ነው።
ሼር አድርጉ ባረከላሁ ፊኩም።
=
የቴሌግራም ቻናል
https://t.me/IbnuMunewor
Repost from Ibnu Munewor (ኢብኑ ሙነወር)
ሸይኹል ኢስላም ኢብኑ ተይሚያ ረሒመሁላህ እንዲህ ይላሉ:-
من أحبَّ أن يلحق بدرجة الأبرار ، فلينو في كل يوم نفع الخلق فيما يسر الله من مصالحهم على يديه.
"የደጋጎች ደረጃ ላይ መድረስ የሚወድ በያንዳንዷ ቀን አላህ በሱ ሰበብ ባገራለት መጠን ፍጡራንን ለመጥቀም ያስብ።" [አልኢማኑል አውሰጥ: 1/609]
=
የቴሌግራም ቻናል
https://t.me/IbnuMunewor
ፍትሃዊ እንሁን ….
ጀርሕ እና ተዕዲል …..
ከደርስ የተቆረጠ አጭር ምክር
https://t.me/Muhammedsirage
Repost from Ibnu Munewor (ኢብኑ ሙነወር)
ከየትኛውም አካል፣ በየትኛውም መልኩ የሚቀርብን እርምት በጥሩ ኒያ ባይሆን እንኳ ለኔ እስከጠቀመኝ ድረስ - ከምስጋና ጋር - ለመቀበል ዝግጁ ነኝ ኢንሻአላህ። የአቋም ስህተት ከሆነ እማርበታለሁ ፣ አቋሜንም አስተካክላለሁ። በቅጡ ያልታሰበበት የቃላት ስህተት ከሆነም አስፈላጊ በምለው መጠን አስተካክለሁ፣ ወይም አስወግደዋለሁ።
በዚህም መሰረት ጠቅላዩ የመጣ ሰሞን ስለሱ ያኔ በደጋፊም በነቃፊም በኩል ሲራገብ በነበረው ጉዳይ ላይ በልክ እንድንሆን የፃፍኩት ፅሁፍ ፋይዳ-ቢስ እና አላስፈላጊ ቃል የያዘ በመሆኑ አስወግጀዋለሁ።
رحم الله امرأ أهدى إلي عيوبي
=
የቴሌግራም ቻናል
https://t.me/IbnuMunewor
የሚጮሁትን የማይኖሩ ጉዶች!
ክፍል - 6
{ረይስና ሱለይማን አሩሐይሊ ከመንሀጅ ውጭ ናቸው!}
~
ረይስን "እሱን ተወው" ፤ "ሙአኸዛ አለበት"፣ "የሱ ኢጅቲሃድ ነው ማለት፣ የሱለይማን አሩሐይሊ ኢጅቲሃድ ነው ማለት፣ .. ውድቅ ነው፣ ኤክስ ነው። ሙዕተበር የሆኑ ዓሊሞችን አምጣ። ... የነዚህ የነዚህን ተዋቸው። ከመንሀጅ ውጭ ናቸው።" ረይስ "ሚስኪን ነው።"
ከዚህም በተጨማሪ ከውስጣቸው ረይስን በኢርጃእ የሚከሱት እንዳሉ በተጨባጭ አውቃለሁ።
"የቢድዐ ሰዎች ምልክት የሱና ሰዎችን መንካት ነው" የሚለውን በመያዝ ሌሎች ላይ በተብዲዕ የሚዘምቱ ሰዎች ራሳቸው እንዳሻቸው ከመናገር አይመለሱም።
ያያያዝኩት ድምፅ የለተሞ ድምፅ ነው። ያለቦታው ሰቃቅለው የጀርሕና ተዕዲል ዓሊም አድርገውት በዚህ መልኩ በድፍረት ይፈርዳል። ነጥቤ ረይስና ሱለይማን አሩሐይሊን አለመቀበሉ አይደለም። ረይስም፣ ሩሐይሊም፣ ረቢዕም፣ ፈውዛንም፣ ... ከነዚህ የበለጠም፣ ያነሰም ቢሆነ በጭፍን አንቀበልም። ታዲያ ርእስ እየመረጡ ሳይሆን አንድ ዓሊም ሌላውን ስላጎደፈ ራሱ በጭፍን ልንወስድ አይገባም። ማንም ቢሆን ያ ዓሊም። ረቢዕ ጋር ሲሆን የሚቀየር ነገር የለም። ረይስ ወይም ሌላ ሰው አንድ ዓሊም ላይ ያላግባብ ቢናገሩ እንደማንቀበለው ረቢዕ ወይም ሙሐመድ ብኑ ሃዲ አንድ ሰው ላይ ስለተናገሩም በጭፍን አንወስድም። የትኛውንም በሰለፊያ ካባ ተጠቅልሎ የሚቀርብ ቡድንተኝነት አሽቀንጥሮ መጣል ይገባል።
የነዚህ ሰዎች ሁኔታ የሚገርመው ግን መንሀጁ ችግር አለበት ከሚሉት ረይስ ጋር እነ ጠሀ ኸዲር ጥብቅ ትስስር ያላቸው መሆኑ ነው። ቻናሉም ላይ ደጋግሞ ያሰራጭለታል። የመንሀጅ ችግር ካለበት ለምንድነው ከሱ ጋር የምትተባበሩት? ለናንተ ሲሆን ከሰለፊያ መንሀጅ ውጭ ካለ አካል ጋር መተባበር ይቻላል ማለት ነው?
=
https://t.me/IbnuMunewor
Repost from Ibnu Munewor (ኢብኑ ሙነወር)
“ህመምተኞቻችሁን በሶደቃ አክሙ።”
~
አቡበክር አልኹባዚይ እንዲህ ይላሉ፦
"የሆነ ጊዜ አደገኛ ህመም ታመምኩኝ። አንድ ደግ ጎረቤቴ አየኝና ' 'ህመምተኞቻችሁን በሶደቃ አክሙ' የሚለውን የአላህ መልእክተኛን ﷺ ንግግር ተጠቀም' አለኝ።
ወቅቱ በጋ ነበር። ብዙ ሃብሃብ ገዛሁ። በርካታ ድሃዎችና ህፃናት ተሰብስበው በሉ። ከዚያም እጆቻቸውን ወደ አላህ አንስተው እንዲያድነኝ ዱዓእ አደረጉልኝ። ከዚያ ወላሂ! ከአላህ - ተባረከ ወተዓላ - ጥሩ ጤና ያገኘሁ ሆኜ እንጂ አላነጋሁም።"
📖 [ሲየሩ አዕላሚ ኑበላእ፡ 18/44]
=
* የቴሌግራም ቻናል
https://t.me/IbnuMunewor
* የዋትሳፕ ቻናል፦
https://whatsapp.com/channel/0029VaA3X1e5kg7BlsJboa2M
* ፌስቡክ
https://www.facebook.com/Ibnu.Munewor?mibextid=ZbWKwL
Repost from Ibnu Munewor (ኢብኑ ሙነወር)
የለተሞ መንጋ
~
እኛ በሸይኽ ረቢዕ ላይ ድንበር ማለፍ አይገባም እንላለን፣ ለካስ ሰዎቹ ሌላ ዓለም ነው ያሉት። ጭራሽ በሑሴን ሙሐመድ ላይ ድንበር እያለፉ ኖሯል። "የሐበሻው ኢብኑ ባዝ" ተብሏል ለካ! ምናልባትም እንዲህ ዓይነቱ ቡድንተኝነት የወለደው ከንቱ ሙገሳ ይሆናል ልባቸውን አሳብጦ ገደል እየከተታቸው ያለው። አንደኛውንም "ሸይኹል ኢስላም" እያሉት እንደሆነ ሰምቼ ነበር። እውነት ይሆን?
ከቅጥፈቱ በላይ የገረመኝ ጠሀ ኸዲር ይህንን አሳፋሪ ወሬ ቁም ነገር አድርጎ መለጠፉ ነው። ሰዎቹ ግን እኛ ከምንገምታቸውም በጣም የራቁ ናቸው።
=
* የቴሌግራም ቻናል
https://t.me/IbnuMunewor
Repost from Ibnu Munewor (ኢብኑ ሙነወር)
ሲጋራ
~
ሲጋራ ጎጂ የሆነ ሱስ ነው። ጎጂ ነገር በኢስላም ሐራም ነው። ስለሆነም ጎጂ ነገርን መጠቀምም በጎጂ ነገር መነገድም ሐራም ነው። ሸይኽ ኢብኑል ዑሠይሚን - ረሒመሁላህ - እንዲህ ይላሉ፦
"ለማንም ሰው ሲጋራ ሊሸጥ አይፈቀድለትም። ምክንያቱም ሲጋራ የተከለከለ ነውና። አላህ አንድን ነገር ከከለከለ የሽያጭ ዋጋውንም ነው የሚከለክለው። እንዲሁም ሲጋራን መሸጥ በወንጀልና ወሰን በመተላለፍ ላይ መተባበር ነው።" [አሊቃኡ ሸህሪይ፡ 22/57]
ኢብኑ ባዝ - ረሒመሁላህ - እንዲህ ብለዋል፦
"ሲጋራ ማጨሱም፣ መሸጡም፣ በሱ መነገዱም አይፈቀድም። በዚህ ላይ ከባድ ጉዳትና መጥፎ ፍፃሜ አለበትና።" [አልፈታዋ፡ 6/456]
=
* የቴሌግራም ቻናል
https://t.me/IbnuMunewor
* የዋትሳፕ ቻናል፦
https://whatsapp.com/channel/0029VaA3X1e5kg7BlsJboa2M
* ፌስቡክ
https://www.facebook.com/Ibnu.Munewor?mibextid=ZbWKwL
Repost from Ibnu Munewor (ኢብኑ ሙነወር)
የሚጮሁትን የማይኖሩ ጉዶች!
ክፍል - 5
~
ያያያዝኩት የባህሩ ተካ ፅሁፍ ነው። እንደምታዩት ከካ'ፊሮች ጋር አንድነት ወደ መፍጠር እየተጣራ ነው። ይሄ የወላእና በራእን ዐቂዳ የሚፃረር ብልሹ ስብከት ነው። ከስላሴ አማኞች ጋር ምን አይነት አንድነት ለመመስረት እንደሚጣራ አላህ ይወቅ። ሠላሠቱል ኡሱል የቀራ ህፃን እንኳ ከሺርክ እና ከሙሽሪኮች መጥራት እንዳለበት ያውቃል። እዚህ የምናየው ግን ሌላ ነው። በዚህ የግንዛቤ መጠን የሆነ ነው እንግዲህ ሰርክ ስለ ተምይዕ የሚያወራው። ምናልባት ተምይዑ ከነሷራ ጋር ሲሆን ሌላ ሑክም ይኖረው ይሆን? ነው ወይስ ተምይዑ የናንተ ሲሆን ቅዱስ ነው? ይሄ ከነሷሪዎች ጋር አንድነት ወደ መፍጠር የተጣራው ከነሱ የተለየ ሰው ቢሆን ብላችሁ አስቡ። ባህሩም፣ ያ ከባባድ ውንጀላዎችን ለመለጠፍ ለአፍታ ቆም ብሎ ማሰብ የማይሻው ጭፍራም ጩኸቱ ከባድ ነበር። ችግሩ "የኛ" የሚሉት ላይ ሲሆን ግን "ከአገልግሎት መስጫ ክልል ውጭ" ይሆናሉ። ከዚህ በፊት ከውስጣቸው ከዚህ ባነሰ ጉዳይ እንኳ በ "ወሕደተል አድያን" ስብከት የሚከሱ ገጥመውኛል።
በነገራችን ላይ ይሄ ስብከት ኢኽዋኒዮች የሚታወቁበት ስብከት ነው። የሚያልሙትን መስለሐ ያስገኝልናል ብለው እስካሰቡ ድረስ የወላእና በራእ ዐቂዳ ጉዳይ አያስጨንቃቸውም፡፡ በሕሩም ተመሳሳይ ጥፋት ነው የፈፀመው። እንደሚታወቀው ነብያችን ﷺ በዘር፣ በጎሳ፣ በሃገር ከሚጋሯቸው የመካ አጋሪዎች ጋር አንድነት ወደ መመስረት አልተጣሩም።
ከኢስላማዊ ግንዛቤ የራቀ ፖለቲከኛ ቢያደርገው ቃላቱን በሸሪዐ የመመዘን ትኩረቱ አናሳ ነውና ብዙም አይደንቅም። በዚያ ላይ ሃይማኖትን መሰረት አድርጎ የሚያስተዳድረውን ህዝብ ይለያያል እንዳይባል 'ሙጃመላ' ያደርጋል። በሕሩ ተካስ ምንድነው የሚያልምበት? ከነሷራ ጋር አንድነት ወደ መፍጠር የሚሰብክ ሰው ነው እንግዲህ ሲለው የሰው ንግግር እየቆለመመ፣ ሲያሰኘው ደግሞ ከመሬት አንስቶ በሃሰት እየከሰሰ ሙስሊሞችን የሚያጠለሸው። የውጭ አልጋ፣ የቤት ቀጋ ማለት እንዲህ ነው።
=
የቴሌግራም ቻናል
https://t.me/IbnuMunewor
Repost from Ibnu Munewor (ኢብኑ ሙነወር)
"አምላካችሁም እግዚአብሔር #ከእናንተ_ጋር_የተማማለውን_ቃል_ኪዳን #እንዳትረሱ፥ አምላክህም እግዚአብሔር የከለከለውን በማናቸውም ቅርጽ የተቀረጸውን ምስል እንዳታደርጉ ተጠንቀቁ።" (ኦሪት ዘዳግም 4:23)
"በላይ በሰማይ ካለው፥ በታችም በምድር ካለው፥ ከምድርም በታች በውኃ ካለው ነገር #የማናቸውንም_ምሳሌ #የተቀረጸውንም_ምስል ለአንተ አታድርግ፤" (ኦሪት ዘዳግም 5:8)
" #ለተቀረጸ_ምስል የሚሰግዱ #ሁሉ፥ በጣዖቶቻቸውም የሚመኩ ይፈሩ፤ መላእክቱ ሁሉ፥ ስገዱለት።" (መዝሙረ ዳዊት 97:7)
(ኢብኑ ሙነወር፣ ጥር 28/2011)
=
* የቴሌግራም ቻናል
https://t.me/IbnuMunewor
* የዋትሳፕ ቻናል፦
https://whatsapp.com/channel/0029VaA3X1e5kg7BlsJboa2M
* ፌስቡክ
https://www.facebook.com/Ibnu.Munewor?mibextid=ZbWKwL
Repost from Ibnu Munewor (ኢብኑ ሙነወር)
የማርያም ወዳጅ እንጂ ጠላት አይደለንም!
~
ሰሞኑን #እስቴ ላይ መስጂዶች የተቃጠሉት በአንድ የሙስሊም ሰርግ ቤት ለዲኮርነት በተበተነ ወረቀት ላይ "የማርያም ምስል" መገኘቱ ነው። በርግጥ ወረቀቱ ባህርዳር ከተማ ውስጥ ከሚገኝ ማተሚያ ቤት የተገዛ ሲሆን በተበተነው ወረቀት ውስጥ የተገኘው ዘግይቶ ከሰአት በኋላ ነው። ሆን ተብሎ አልተፈፀም ማለት ነው።
·
በርግጠኝነት ይሄ ወረቀት የተገኘው ከአንድ ክርስቲያን ሰርግ ላይ ቢሆን የአራት የአምስት ሰዎች አጀንዳ እንኳን መሆን አይችልም ነበር። ስለዚህ ጉዳዩ ያ ሁሉ ጥፋት የተከተለው አጀንዳ የሆነው ከሙስሊም ቤት መገኘቱ ነው። ወይ ሙስሊሞች ሆነ ብለው ለትንኮሳ አድርገውታል ብሎ ከማሰብ ወይም ለማርያም ክብር የላቸውም ከሚል እሳቤ የመነጨ ነው።
በርግጥ እኛ እንደ ሙስሊም የማንም ምስል ቢሆን ለስእል ክብር የለንም። የእየሱስም ተባለ የሙሐመድ፣ የማርያምም ተባለ የዓኢሻ ለኛ ልዩነት የለውም። ነገር ግን ይህንን አቋማችንን ለትንኮሳና ለብጥብጥ አናውለውም።
·
ስለ ማርያም ያለን እምነት ግን በአክብሮት የተሞላ ነው። አክብሮታችንም ከቁርኣንና ከነብያችን (የአላህ ሶላትና ሰላም በሳቸው ላይ ይስፈንና) አስተምህሮት የተቀዳ ነው። ለምሳሌ ያክል ጥቂት ብናይ:–
① ማርያም በአምላካዊ እንክብካቤ ስር በሥርዓት ተኮትኩታ ያደገች እንደሆነች ቁርኣን ይመሰክራል
(وَأَنْبَتَهَا نَبَاتًا حَسَنًا)
"(ጌታዋም) በመልካም አስተዳደግ አሳደጋት፡፡" [ኣሉ ዒምራን: 37]
② ማርያም ጌታዋን ፈሪ፣ ህጉን አክባሪ፣ የተሟላ ስብእና ባለቤት ነች ይላል የፈጠራት ጌታ
(وَإِذْ قَالَتِ الْمَلَائِكَةُ يَا مَرْيَمُ إِنَّ اللَّهَ اصْطَفَاكِ وَطَهَّرَكِ وَاصْطَفَاكِ عَلَى نِسَاءِ الْعَالَمِينَ * يَا مَرْيَمُ اقْنُتِي لِرَبِّكِ وَاسْجُدِي وَارْكَعِي مَعَ الرَّاكِعِينَ )
"መላእክትም ያሉትን (አውሳ)፡፡ «መርየም ሆይ! አላህ በእርግጥ መረጠሸ፡፡ አነፃሽም፡፡ በዓለማት ሴቶችም ላይ መረጠሽ፡፡» «መርየም ሆይ! ለጌታሽ ታዘዢ፡፡ ስገጂም፡፡ ከአጎንባሾቹም ጋር አጎንብሺ፡፡» [ኣሉ ዒምራን: 42–43]
ስለዚህ ማርያም የከበረች ሙስሊማ ነች። ሙስሊም ማለት ለፈጣሪ እጅ የሰጠ፣ ለትእዛዙ ያደረ ማለት ነው። ማርያም ደግሞ በሚገባ ለጌታዋ እጅ የሰጠች ነበረች።
③ ማርያም ከተወነጀለችበት የዝሙት ወንጀል ፍፁም የራቀች፣ ይልቁንም በአምላክ ፈቃድ በተአምር ፀንሳ የወለደች ናት። አላህ በቁርአን እንዲህ ይላል:–
(إِذْ قَالَتِ الْمَلَائِكَةُ يَا مَرْيَمُ إِنَّ اللَّهَ يُبَشِّرُكِ بِكَلِمَةٍ مِنْهُ اسْمُهُ الْمَسِيحُ عِيسَى ابْنُ مَرْيَمَ وَجِيهًا فِي الدُّنْيَا وَالْآخِرَةِ وَمِنَ الْمُقَرَّبِينَ )
"መላእክት ያሉትን (አውሳ)፡- ‘መርየም ሆይ! አላህ ከርሱ በሆነው ቃል ስሙ መሲሑ ዒሳ የመርየም ልጅ በዚህ ዓለምና በመጨረሻውም ዓለም የተከበረ ከባለሟሎችም በሆነ (ልጅ) ያበስርሻል፡፡’ " [ኣሉ ዒምራን: 45]
④ ልጇም የዝሙት ልጅ ሳይሆን ከታላላቅ የፈጣሪ መልእክተኞች እንደሆነ በቁርአን ተመስክሯል።
( إِنَّمَا الْمَسِيحُ عِيسَى ابْنُ مَرْيَمَ رَسُولُ اللَّهِ وَكَلِمَتُهُ أَلْقَاهَا إِلَى مَرْيَمَ وَرُوحٌ مِنْهُ )
"መሲሑ የመርየም ልጅ ዒሳ የአላህ መልክተኛ፣ ወደ መርየም የጣላት ‘የሁን’ ቃሉ እና ከእርሱ የሆነ መንፈስም ነው፡፡" [አኒሳእ: 171]
⑤ ማርያም የእውነተኞች ተምሳሌት ናት። ፈጣሪ እንዲህ ይገልፃታል:–
(مَا الْمَسِيحُ ابْنُ مَرْيَمَ إِلَّا رَسُولٌ قَدْ خَلَتْ مِنْ قَبْلِهِ الرُّسُلُ وَأُمُّهُ صِدِّيقَةٌ)
"መሲሑ የመርየም ልጅ ከበፊቱ መልክተኞች በእርግጥ ያለፉ የሆነ መልክተኛ እንጅ ሌላ አይደለም፡፡ እናቱም በጣም እውነተኛ ናት፡፡" [አልማኢዳህ: 75]
⑥ ባጠቃላይ ማርያም የጌታ ተአምር ነች ማለት ይቻላል። በቁርአን እንዲህ ተገልፃለች: –
(وَجَعَلْنَا ابْنَ مَرْيَمَ وَأُمَّهُ آيَةً )
"የመርየምን ልጅ እና እናቱንም ተዓምር አደረግናቸው፡፡" [አልሙእሚኑን: 50]
⑦ መርየም ከታላላቅ የጀነት (ገነት) ሴቶች ውስጥ እንደሆነች ነብያችን መስክረዋል ። [ሙስነድ አሕመድ: 2668]
·
ይሄ እምነታችን ከቁርኣን የወሰድነው፣ ከቀደምቶቻችን የወረስነው ነው። ይሄ ሐቅ ሙስሊሞች በጣም ጥቂትና ደካሞች በነበሩበት የመካ ዘመን ጀምሮ ሃገር እስከመሰረቱበት የመዲና ዘመን ድረስ የፀና ነው። በአንድ ወቅት የቁረይሽ ዐረቦችን ክፋት ሸሽተው ወደ ሐበሻ ተሰደው ይኖሩ የነበሩት ሙስሊሞችን የኢትዮጵያው ንጉስ ስለ ዒሳ ሊጠይቃቸው ፈልጎ ሰው ላከባቸው። ንጉሱ በጊዜው አልሰለመም ነበርና ምን ብለው ሊመልሱለት እንደሚገባ ለመመካከር ተሰባሰቡ። "ስለ ዒሳ ከጠየቃችሁ ምንድነው መልሳችሁ?" ተባባሉ።
"ወላሂ! በዚህ ጉዳይ ላይ የፈለገ አካል ቢመጣ ስለሱ አላህ የተናገረውን ፣ ነብያችን ያደረሱንን ነው የምንናገረው!" ተባባሉ።
ንጉሱ ዘንድ እንደገቡም "የማርያም ልጅ ስለሆነው እየሱስ ምን ትላላችሁ?" የሚል ጥያቄ ቀረበላቸው። እየመራቸው የገባው የነብዩ የአጎት ልጅ የሆነው ጀዕፈር እንዲህ አለ:–
"ስለሱ ነብያችን ያመጣልንን ነው የምንለው። እሱ (ዒሳ) የአላህ ባሪያና መልእክተኛ ነው። እርሱ ከፈጠራቸው ነፍሶች ውስጥና ወደ ድንግሏ መርየም የጣለው የሁን ቃሉም ነው።"
ንጉሱ በዚህን ጊዜ በእጁ መሬቱን መታና እንጨት አንስቶ የመርየም ልጅ ዒሳ ከተናገርከው ይቺን እንጨት የምታክል አላለፈም" አለ። [ሙስነድ አሕመድ: 1742]
·
ይህ ነው ስለ ማርያም ያለን እምነት። ድንበር ማለፍ የሌለበት፣ እሷን ወደ ማምለክና ወደ መማፀን የማይሻገር ፍፁም አክብሮት። ይሄ ስለሷ ብቻ ሳይሆን ስለሌሎችም ፃድቃን ያለን እምነት ነው።
በእርግጥ "የማርያም ምስል" ተብሎ አሁን ክርስቲያኖች ዘንድ የሚገኘውን ስእል በተመለከተ እሷን ለመምሰሉ ማንም ማረጋገጫ ሊያቀርብለት አይችልም። ምክንያቱ ለማንም አይሰወርም።
·
በነገራችን ላይ ስእሎችን ማክበር መጽሐፍ ቅዱሳዊ መሰረት የለውም። ለምሳሌ ያክል ጥቂት ጥቅሶችን እንይ:–
"በላይ በሰማይ ካለው፥ በታችም በምድር ካለው፥ ከምድርም በታች በውኃ ካለው ነገር #የማናቸውንም_ምሳሌ፥ #የተቀረጸውንም_ምስል ለአንተ አታድርግ።" (ኦሪት ዘጸአት 20:4)
" እኔ እግዚአብሔር አምላካችሁ ነኝና ለእናንተ ጣዖት አታድርጉ፥ #የተቀረጸም_ምስል ወይም ሐውልት አታቁሙ፤ ትሰግዱለትም ዘንድ በምድራችሁ ላይ የተቀረጸ ድንጋይ አታኑሩ።"
(ኦሪት ዘሌዋውያን 26:1)
"#እንዳትረክሱ! #የተቀረጸውን ምስል የማናቸውንም ነገር ምሳሌ፥ በወንድ ወይም በሴት መልክ የተሠራውን፥ … ምሳሌ እንዳያደርጉ።" (ኦሪት ዘዳግም 4:16–18)
