en
Feedback
Endod + እንዶድ +

Endod + እንዶድ +

Open in Telegram

www.endod.net በአስተውሎት ንጽህና፣ በአብሮነት መድህን፣ ከተፈጥሮ በተቀዳ ጽናት ኃላፊነት የሚሰማው ሰው ሆኖ መገኘት መቻል እና ሌሎችን ማስቻልን መነሻው አድርጎ ወደ ወድ አድማጮቹ በFM Addis 97.1 የሚደርስ የራድዮ መሰናዶ ነው።

Show more
1 226
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days
Posts Archive
እንዶዳውያን -፪ : አንዳች ረብ ያለው ነገር እንደማታጡብን በማመን አብራችሁን ስለመዝለቃችኹ የተሰናዳ ሁለተኛ መሰናዶ! ለወትሮ በእልፍኝ አስከልካይ ጥንቅራችን እንስማው የነበረውን ሀሳባችሁን ከእናን
እንዶዳውያን -፪ :  አንዳች ረብ ያለው ነገር እንደማታጡብን በማመን አብራችሁን ስለመዝለቃችኹ የተሰናዳ ሁለተኛ መሰናዶ! ለወትሮ በእልፍኝ አስከልካይ ጥንቅራችን እንስማው የነበረውን ሀሳባችሁን ከእናንተው አንደበት በቀጥታ የምናደምጥበት ልዩ ምሽት! ዛሬ ሐምሌ 05 2015 ዓ.ም ምሽት በFM Addis 97.1 እንዲሁም አስተያየት መስጫው ላይ በተቀመጠው ማስፈንጠርያ በመላው ዓለም ወደ እናንተ ይደርሳል! በ0931717191 አሊያም ከ linktr.ee/shegafuture በመረጡት ሀሳብዎን ያጋሩን!

ውድ የአገር ልጆች... አንዳች ወጥኖ፣ ውጥንን በዝርዝር ነድፎ፣ ልብ በሻተው መልኩ፣ ቀድመው በልቦና፣ ከዚያም በወረቀት የነደፉትን ልቅም አድርጎ ማጠናቀቅ በቃላት የማይገለጥ ልዩ ስሜት ይፈጥራል፤ አብዝቶ ለተሻለ አበርክቶም ያነቃል፣ ያበረታል፣ ያጸናልም! መጋቢት 16 2015 ዓ.ም “‹ቃል እና ምግባር› ስንል በሰየምነው የእንዶድ ምዕራፍ ፪ ፣ ካብዕ (ሁለተኛ) ተከታታይ መሰናዶ በቀጣዮቹ 20 ክፍሎች እንዲህ አብረን እንድንቆይ አቅደናል!” ካልናችሁ ኋላ፣ 28 ክፍሎችን (20 ተከታታይ ክፍሎች፣ 4 የማጠቃለያ መሰናዶዎች፣ 4 ጊዜውን ለመዋጀት የተሰነጉ ጥንቅሮች) አብረናችሁ ቆይተን፣ ትናንት ሐምሌ 1 2015 ዓ.ም የማሳረጊያውን ክፍል አስደምጠናችኹ ስናጠናቅቅም እንዲህ ነው የተሰማን! ይህ ልዩ ስሜት እንዲያድርብን ምክንያቶቹ እናንተ ናችሁና ውድ እንዶዳውያን፣ 'ኑልን' ስንላችኹ 'ቅሌን፣ ጨርቄን' ሳትሉ በዚህም ይሁን በቀደመው ምዕራፍ እንግዶቻችን ለመሆን ለወደዳችኹ ሁሉ አብዝተን እናመሰግናለን፤ በጉልድፍ ቃላቶች ምስጋናችንን እንዳናኮስሰውም "ልብ ይመርቅ" ብቻ ልንላችኹ ወደናል! "እንዶዳውያን ፪"፣ " ማለፊያ" (ባለ ፬ ክፍሎች ምጥን ተከታታይ መሰናዶ) እና "...ሒዱ መጣን!"( ባለ 30 ክፍሎች ተከታታይ መሰናዶ) ቀጣዮቹ የእንዶድ ቤት ያፈራቸው እና ከገበታው ለመዋል ተራቸውን የሚጠብቁ ጥንቅሮች ናቸው! አብረን እንዝለቅ!!! አዎን! ለተሻለ ነገ እናዋጣለን

photo content

የእንዶድ ምዕራፍ ፪ ሁለተኛ ተከታታይ መሰናዶ "ቃል እና ምግባር" አራተኛ የማጠቃለያ መሰናዶ እና የተከታታይ መሰናዶው የማሳረጊያ ክፍል ከምሽቱ 2:00 ጀምሮ በFM Addis 97.1 በቀጥታ ይተላለፋል፤ ታዳምጡት ዘንድ ጋበዝናችሁ! ባልደረቦቻችን ጠርሲዳ ከበደ፣ ያልፋል አሻግር እና ሜሪ መኮንን አብረዋችሁ ያመሻሉ። እነሆ 4ተኛው የማጠቃለያ እና የማሳረጊያ መሰናዷችን! በይዘቱም በቃል እና ምግባር ተከታታይ መሰናዶ በክፍል 14 ከ አፋን ኦሮሞ በተዋስነው "ዱቢን አቡልቱ!" (እስኪ ይደር) ፣ በክፍል 15 ወደ ትግራይ ተጉዘን በመዘዝነው ብሂል " ፀርፊ ተፃራፊኡ ይመስል!"( "ስድብ ተሳዳቢውን ይመስላል!") ፤ በክፍል 16 የሀዲይሳን (የሀዲያ ማህበረሰብ ቋንቋ) ስነቃላዊ ሐብቶች ስናገላብጥ ባገኘነው "እያከኣ ገሜአኮኦክ፣ ድላ ገሜኦኮ!" (“አዝለውት ሲሰርቁ ያየ፣ ወርዶ ይሰርቃል!”) ፤ በክፍል 17 በጋምቤላ ክልል ከሚነገሩ ቋንቋዎች አንዱ በሆነው ቱክ-ኙዌር በሚነገረው "ቢመር፡በፈታሪ፡እዉ፡መርሞ፡እንደን፡ጓደ!" ("የሚረባኝን በባትሪ እፈልጋለሁ!") በክፍል 18 "Honde verkies eintlik nie bene om vleis te eet nie; Dis net dat niemand hulle ooit vleis gee nie."(“ውሾች ከስጋው አብልጠው አጥንቱን ስለምን ወደዱ? ስጋ የሚሰጣችው ስላጡ!”) በደቡብ አፍሪካ አገልግሎት ላይ ከሚውሉ የስራ ቋንቋዎች አንዱ በሆነው 'አፍሪካንስ' ቋንቋ የሚነገር ብሂል መነሻ በማድረግ ፤ በክፍል 19 "ለዓይን የከበደው ... በልጥ ሲታሰር " በሚል ርዕስ የሰርከስ ዝሆንን መነሻ በማድረግ የታሰርንባቸውን 'ልጦች ' እየቃኘን እንዲሁም በክፍል 20 “ሜዳ ጠፋ ብሎ ተራራ መናድ” (ከእያዩ ፈንገስ ቴዓትር የማጀቢያ ሙዚቃ በተዋስነው ስንኝ) አብረናችሁ ያደረግናቸውን ሸጋ ቆይታዎች አብረን እንከልሳለን። አብራችሁን አምሹ!በቀጥታ ልታደምጡን ካሻችሁ አስተያየት ማስቀመጫው ላይ በተቀመጠው ማስፈንጠሪያ ታገኙላችሁ ! በ 0931 71 71 91 ፃፉልን!

እነሆ የእንዶድ ምዕራፍ ፪ ሁለተኛ ተከታታይ መሰናዶ "ቃል እና ምግባር" የማጠቃለያ ዝግጅት- ሶስተኛ ክፍል! የግል ባህሪያችንን (Character , መገለጣችንን፟) በኪነ ሕንጻ ታሪክ ውስጥ ትልቅ ቦ
እነሆ የእንዶድ ምዕራፍ ፪ ሁለተኛ ተከታታይ መሰናዶ "ቃል እና ምግባር" የማጠቃለያ ዝግጅት- ሶስተኛ ክፍል! የግል ባህሪያችንን (Character , መገለጣችንን፟)  በኪነ ሕንጻ ታሪክ ውስጥ ትልቅ ቦታ ያለውን ቪትሪቪየስን (ከክርስቶስ ልደት በፊት የነበረ አርክቴክት እና የጦር መሀንዲስ) ሶስቱን “የጥሩ ኪነ-ሕንጻ መርሆች” በማንጸሪያነት በመጠቀም “እኔ” የምንለውን ማንነታችንን ንድፍ ቆም ብለን እናይበት ዘንድ በተሰናዳው "ንድፈ-ሰብዕና-፩" ፤  የዘመናዊ ኪነ-ሕንፃ ሰባት መርሆችን በማንጸርያነት በመጠቀም የሰደርናቸውን  "ንድፈ-ሰብዕና-፪ እና ፫" ፤ እንዲሁም በሰብዓዊ ምህንድስና ቃኝተን ያስደመጥናችሁን  "ንድፈ-ሰብዕና-፬"  (በኪነ-ሕንጻ ማንጸርያነት የተሰናዱ የተከታታይ መሰናዶው ንዑስ ክፍሎች “ቃል እና ምግባር- ንድፈ ሰብዕና” - ከክፍል 10- 14) ዛሬ አብረን እንከልሳለን! ከምሽቱ 2:00 ጀምሮ በFM Addis 97.1 በቀጥታ ይተላለፋል፤  ታዳምጡት ዘንድ ጋበዝናችሁ! ባልደረቦቻችን ጠርሲዳ ከበደ፣ ያልፋል አሻግር፣ ሜሪ መኮንን እና ጸጋ ካህሳይ ይህን ሸጋ መሰናዶ አዘጋጅተውላችኋል። አብራችሁን አምሹ! በቀጥታ ልታደምጡን ካሻችሁ አስተያየት ማስቀመጫው ላይ በተቀመጠው ማስፈንጠሪያ ታገኙላችሁ ! በ 0931 71 71 91 ፃፉልን!

ዒድ ሙባረክ! እንዶድ በመላው ዓለም ለሚገኙ የእስልምና ዕምነት ተከታዮች በሙሉ እንኳን ለ1444ኛው የኢድ አል አድሃ (አረፋ) በዓል በሰላም አደረሳችሁ ይላል። በዓሉ የሰላም፣ የመተሳሰብ እና የፍቅር
ዒድ ሙባረክ! እንዶድ በመላው ዓለም ለሚገኙ የእስልምና ዕምነት ተከታዮች በሙሉ እንኳን ለ1444ኛው የኢድ አል አድሃ (አረፋ) በዓል በሰላም አደረሳችሁ ይላል። በዓሉ የሰላም፣ የመተሳሰብ እና የፍቅር ይሆንላችሁ ዘንድ መልካም ምኞቱን ይገልጻል።

በባልደረቦቻችን ያልፋል አሻግር፤ ጠርሲዳ ከበደ፣ ሜሪ መኮንን እና ጸጋ ካሕሳይ ተዘጋጅተው የቀረቡትን የ"ቃል እና ምግባር" ተከታታይ መሰናዶ የማጠቃለያ ዝግጅቶች እንዴት አገኛችኋቸው? ቀጣዮቹን ሁለት
በባልደረቦቻችን ያልፋል አሻግር፤ ጠርሲዳ ከበደ፣ ሜሪ መኮንን እና ጸጋ ካሕሳይ ተዘጋጅተው የቀረቡትን  የ"ቃል እና ምግባር"  ተከታታይ መሰናዶ የማጠቃለያ ዝግጅቶች እንዴት አገኛችኋቸው? ቀጣዮቹን ሁለት ክፍሎች ለማዳመጥስ ዝግጁ ናችሁ?

የእንዶድ ምዕራፍ ፪ ሁለተኛ ተከታታይ መሰናዶ "ቃል እና ምግባር" ሁለተኛ የማጠቃለያ ክፍል ከምሽቱ 2:00 ጀምሮ በFM Addis 97.1 በቀጥታ ይተላለፋል፤ ታዳምጡት ዘንድ ጋበዝናችሁ! በዛሬው መሰ
የእንዶድ ምዕራፍ ፪ ሁለተኛ ተከታታይ መሰናዶ "ቃል እና ምግባር" ሁለተኛ የማጠቃለያ ክፍል ከምሽቱ 2:00 ጀምሮ በFM Addis 97.1 በቀጥታ ይተላለፋል፤ ታዳምጡት ዘንድ ጋበዝናችሁ! በዛሬው መሰናዶ ባልደረቦቻችን ጠርሲዳ ከበደ፣ ያልፋል አሻግር፣ ሜሪ መኮንን እና ጸጋ ካህሳይ "ቃል እና ምግባር"- ፮ : "የአንደበት መዓዛ እና ቃና..." "ቃል እና ምግባር"- ፮ : "የቃል እና ምግባር ፍጹም ቅጣት ምት ፩- እግር ኳስ..." "ቃል እና ምግባር"- ፮ : "የቃል እና ምግባር ፍጹም ቅጣት ምት ፪ - ቀብዶቻችን " እንዲሁም በልዩ መሰናዶነት በሙንሺድ ሙዓዝ ሐቢብ እንግድነት ያስደመጥናችሁን "አንደበት በኢስላም" የምንከልስበት ሸጋ መሰናዶ አዘጋጅተውላችኋል። አብራችሁን አምሹ! በቀጥታ ልታደምጡን ካሻችሁ አስተያየት ማስቀመጫው ላይ በተቀመጠው ማስፈንጠሪያ ታገኙላችሁ ! በ 0931 71 71 91 ፃፉልን!

የእንዶድ ምዕራፍ 2 ሁለተኛ ተከታታይ መሰናዶ "ቃል እና ምግባር" ቀዳሚ የማጠቃለያ ክፍል አየር ላይ ነው፤ ታዳምጡት ዘንድ ጋበዝናችሁ!
የእንዶድ ምዕራፍ 2 ሁለተኛ ተከታታይ መሰናዶ "ቃል እና ምግባር" ቀዳሚ የማጠቃለያ ክፍል አየር ላይ ነው፤ ታዳምጡት ዘንድ ጋበዝናችሁ!

photo content

ውድ እንዶድውያን፣ ቃል እና ምግባር 20+1 : "የመጨረሻው ፌርማታ" ቃል እና ምግባር የእንዶድ ምዕራፍ ፪: ካብዕ ተከታታይ መሰናዶ ሆኖ ሲሰደር የታቀደለት የ40 ሰዓታት ቆይታ ነበር፤ በመሃል ጊዜውን ለመዋጀት ስንል ከሰነግናቸው ልዮ መሰናዶዎች ("አንደበት በኢስላም" ፣ "ቅርሚያ" እና "እንዶዳውያን-፩") ጋር ለ45 ሰዓታት ከአየር ቢውልም ከማጠቃለያ ክፍሎቹ በፊት አንድ ተጨማሪ ክፍል አስፈልጎናል፤ "ቃል እና ምግባር 20+1 - የመጨረሻው ፌርማታ" በሚል ርዕስ አሰናድተነዋል፤ በታዳሚ ማዕረግ ያላችሁ እንዶዳውያን ወደ እንዶድ ድግስ ስትመጡ ሸክፋችሁ የመጣችኋቸው ጥያቄዎች ናቸው ይህን መሰናዶ የወለዱት! ታዲያ ይህን ልብ በሉልን፡ የሸከፍነው ምላሾች አይደለም፤ ይልቁንም እንደጥጥ ያሉ (አንድም የነጡ፣ አንድም የበዙ) ጥያቄዎቻችሁን እናባዝትበት ዘንድ ወደ ስነ-ግጥም ዞር ብለናል! ከፌርማታው አረፍ ብለው ሊያወጓችሁ ባልደረቦቻችን መኮንን ሞገሴ እና ጸጋ ካህሳይ ይጠብቋችኋል፤ ከ"ዘቢቱ እልፊቱ" የግጥም መድብል በምንዋሳቸው ስንኞቹ ውክልና ጋዜጠኛው፣ ገጣሚው እና ፈላስፋው ሰለሞን ደሬሳ፤ እንዲሁም ከ"ክብ ልፋት" የግጥም መድብሉ ላይ በምናነሳቸው ግጥሞቹ እንደራሴነት ወጣቱ ገጣሚ መስፍን ወልደትንሳይም በፌርማታችን ይታደማሉ! ኑ ስለ ረጅሙ መንገዳችን ከፌርማታው አረፍ ብለን እናውጋ! ዛሬ ቅዳሜ ሰኔ 10 2015 ዓ.ም ከምሽቱ 2:00 ጀምሮ በFM Addis 97.1 በመላው ኢትዮጵያ እንዲሁም በአስተያያት መስጫው ላይ በተቀመጠው ማስፈንጠሪያ በመላው ዓለም መደመጥ ይጀምራል። እልፍኝ አስከልካያችኹ ያልፋል አሻግርም በ0931717191 የሰደዳችሁልንን የቸር ልቦቻችሁ ረጢብ ስንቆች መልሰው ወደ እናንተ የሚደርሱበት ጥንቅሩን አሰናድቷል። ሸጋ ሸጋ ጥያቄዎች የተሰደሩበት መሰናዶ ነውና ያድምጡ፣ ይሳተፉ፣ ሸጋ ጥያቄዎች ይሸምቱ ስንል ጋበዝንዎ! ለተሻለ ነገ እናዋጣለን! Linktr.ee/shegafuture

እነሆ የእንዶድ ምዕራፍ ፪ ሁለተኛ ተከታታይ መሰናዶ የመጨረሻ ክፍል! ቃል እና ምግባር 20: "ሜዳ ጠፋ ብሎ ተራራ መናድ" በነጠላም ይሁን በወል ሕይወታችን እንደ 'ሜዳው' ላሉ ጉዳዮች ስንል የገረስ
እነሆ የእንዶድ ምዕራፍ ፪ ሁለተኛ ተከታታይ መሰናዶ የመጨረሻ ክፍል! ቃል እና ምግባር 20: "ሜዳ ጠፋ ብሎ ተራራ መናድ" በነጠላም ይሁን በወል ሕይወታችን እንደ 'ሜዳው' ላሉ ጉዳዮች ስንል የገረስስናቸውን የስነ ምግባር የአቋም ደንቦች እናነሳበት ዘንድ ወደን በረከት በላይነህ ለ"እያዩ ፈንገስ፡ ፌስታሌን" ቴዓትር ማጀቢያ ሙዚቃ ከጻፈው ግጥም የተዋስነውን ስንኝ ገዢ ሀሳባችን አድርገነዋል። በቃል እና ምግባር ዓውድ የሳትንባቸውን ጉዳዮች እናነጽርበታን፤ ወዲህም "የነጠላ ሕይወቴ መልከዓ ምድር እንዴት ያለ ነው?" ብለን እንጠይቃለን! አንጋፋው ጋዜጠኛ እና ደራሲ ዮናስ አብርሃም አብሮን ያመሻል፤ ከባልደረቦቻችን መኮንን ሞገሴ እና ፀጋ ካህሳይ ጋር ሸጋ ጊዜ እንመኝላችኋለን። ዛሬ ረቡዕ ሰኔ 07 2015 ዓ.ም ከምሽቱ 2:00 ጀምሮ በFM Addis 97.1 በመላው ኢትዮጵያ እንዲሁም በአስተያያት መስጫው ላይ በተቀመጠው ማስፈንጠሪያ በመላው ዓለም መደመጥ ይጀምራል። እልፍኝ አስከልካያችኹ ያልፋል አሻግርም በ0931717191 የሰደዳችሁልንን የቸር ልቦቻችሁ ረጢብ ስንቆች መልሰው ወደ እናንተ የሚደርሱበት ጥንቅሩን አሰናድቷል። ሸጋ ሸጋ ጥያቄዎች የተሰደሩበት መሰናዶ ነውና ያድምጡ፣ ይሳተፉ፣ ሸጋ ጥያቄዎች ይሸምቱ ስንል ጋበዝንዎ! ለተሻለ ነገ እናዋጣለን! Linktr.ee/shegafuture

photo content

"ቅርሚያ!" ከሣቴ ብርሃን ተሰማ በ1951 በታተመው የዐማርኛ መዝገበ ቃላታቸው "ቅርሚያ"ን ፡.... የመኸር እህልን መቃረም ... ከወደቀበት እያነሡ ማስቀመጥ። " ሲሉ ይፈቱታል። እኛም ያለ ወትሮ ለ 1 ሰዓት ብቻ የሚደርሰውን የ እንዶድ መሰናዶ በቀደሙት የቃል እና ምግባር ተከታታይ ክፍሎች ወደ እናንተ ልናደርሳቸው ሽተን ሸክፈን ስቱድዮ ከደረስን ኋላ  በጊዜ እጥረት አሊያም በእኛ በአዘጋጆቹ መዘናጋት የተንጠባጠቡ ሃሳቦችን አብረን እንቀርምበት ዘንድ ወደድን! በቃል እና ምግባር ተከታታይ መሰናዶ ክፍል 14 ከ አፋን ኦሮሞ በተዋስነው "ዱቢን አቡልቱ!" (እስኪ ይደር) ፣ በክፍል 15 ወደ ትግራይ ተጉዘን በመዘዝነው ብሂል " ፀርፊ ተፃራፊኡ ይመስል!"( "ስድብ ተሳዳቢውን ይመስላል!")  በክፍል 16 የሀዲይሳን (የሀዲያ ማህበረሰብ ቋንቋ) ስነቃላዊ ሐብቶች ስናገላብጥ ባገኘነው "እያከኣ ገሜአኮኦክ፣ ድላ ገሜኦኮ!" (“አዝለውት ሲሰርቁ ያየ፣ ወርዶ ይሰርቃል!”)  ፤ በክፍል 17 በጋምቤላ ክልል ከሚነገሩ ቋንቋዎች አንዱ በሆነው ቱክ-ኙዌር በሚነገረው "ቢመር፡በፈታሪ፡እዉ፡መርሞ፡እንደን፡ጓደ!" ("የሚረባኝን በባትሪ እፈልጋለሁ!") እንዲሁም በክፍል 18 "Honde verkies eintlik nie bene om vleis te eet nie; Dis net dat niemand hulle ooit vleis gee nie."(“ውሾች ከስጋው አብልጠው አጥንቱን ስለምን ወደዱ? ስጋ የሚሰጣችው ስላጡ!”) በደቡብ አፍሪካ አገልግሎት ላይ ከሚውሉ የስራ ቋንቋዎች አንዱ በሆነው 'አፍሪካንስ' ቋንቋ የሚነገር ብሂል መነሻ አድርገን  ሸጋ ቆይታ ማድረጋችን ይታወሳል፤  ባሳለፍነው ግንቦት 30 2015 ዓ.ም ደግሞ በክፍል 19  "ለዓይን የከበደው ... በልጥ ሲታሰር " በሚል ርዕስ የሰርከስ ዝሆንን መነሻ በማድረግ የታሰርንባቸውን 'ልጦች ' እየቃኘን አብረናችሁ አምሽተናል። ዛሬ ቅዳሜ ሰኔ 03 2015 ዓ.ም ከምሽቱ 2:00 ጀምሮ በFM Addis 97.1 በመላው ኢትዮጵያ እንዲሁም በአስተያያት መስጫው ላይ በተቀመጠው ማስፈንጠሪያ በመላው ዓለም መደመጥ ይጀምራል።  ከባልደረቦቻችን መኮንን ሞገሴ እና ፀጋ ካህሳይ ጋር ሸጋ ጊዜ እንመኝላችኋለን። እልፍኝ አስከልካያችኹ ያልፋል አሻግርም በ0931717191 የሰደዳችሁልንን የቸር ልቦቻችሁ ረጢብ ስንቆች መልሰው ወደ እናንተ የሚደርሱበት ጥንቅሩን አሰናድቷል። ሸጋ ሸጋ ጥያቄዎች የተሰደሩበት መሰናዶ ነውና ያድምጡ፣ ይሳተፉ፣ ሸጋ ጥያቄዎች ይሸምቱ ስንል ጋበዝንዎ! ለተሻለ ነገ እናዋጣለን! Linktr.ee/shegafuture

photo content

"ለዓይን የከበደው ... በልጥ ሲታሰር!" በቃል እና ምግባር ተከታታይ መሰናዶ ክፍል 14 ከ አፋን ኦሮሞ በተዋስነው "ዱቢን አቡልቱ!" (እስኪ ይደር) ፣ በክፍል 15 ወደ ትግራይ ተጉዘን በመዘዝነው ብሂል " ፀርፊ ተፃራፊኡ ይመስል!"( "ስድብ ተሳዳቢውን ይመስላል!")  በክፍል 16 የሀዲይሳን (የሀዲያ ማህበረሰብ ቋንቋ) ስነቃላዊ ሐብቶች ስናገላብጥ ባገኘነው "እያከኣ ገሜአኮኦክ፣ ድላ ገሜኦኮ!" (“አዝለውት ሲሰርቁ ያየ፣ ወርዶ ይሰርቃል!”)  ፤ በክፍል 17 በጋምቤላ ክልል ከሚነገሩ ቋንቋዎች አንዱ በሆነው ቱክ-ኙዌር በሚነገረው "ቢመር፡በፈታሪ፡እዉ፡መርሞ፡እንደን፡ጓደ!" ("የሚረባኝን በባትሪ እፈልጋለሁ!") እንዲሁም በክፍል 18 "Honde verkies eintlik nie bene om vleis te eet nie; Dis net dat niemand hulle ooit vleis gee nie."(“ውሾች ከስጋው አብልጠው አጥንቱን ስለምን ወደዱ? ስጋ የሚሰጣችው ስላጡ!”) በደቡብ አፍሪካ አገልግሎት ላይ ከሚውሉ የስራ ቋንቋዎች አንዱ በሆነው 'አፍሪካንስ' ቋንቋ የሚነገር ብሂል መነሻ አድርገን  ሸጋ ቆይታ ማድረጋችን ይታወሳል፤ ዛሬ ደግሞ ከባልደረቦቻችን  ሳሙኤል ተ/የሱስ፣ መኮንን ሞገሴ እና ፀጋ ካህሳይ ጋር የሰርከስ ዝሆንን መነሻ በማድረግ የታሰርንባቸውን 'ልጦች ' እየቃኘን አብረናችሁ ልናመሸ ወደናል። ዛሬ ረቡዕ ግንቦት 30 2015 ዓ.ም ከምሽቱ 2:00 ጀምሮ በFM Addis 97.1 በመላው ኢትዮጵያ እንዲሁም በቀጣዩ ማስፈንጠሪያ በመላው ዓለም መደመጥ ይጀምራል።  በ0931717191 የሰደዳችሁልንን የቸር ልቦቻችሁ ረጢብ ስንቆች መልሰው ወደ እናንተ የሚደርሱበት የእልፍኝ አስከልካይ ጥንቅርም ተሰናድቷል። ሸጋ ሸጋ ጥያቄዎች የተሰደሩበት መሰናዶ ነውና ያድምጡ፣ ይሳተፉ፣ ሸጋ ጥያቄዎች ይሸምቱ ስንል ጋበዝንዎ! ለተሻለ ነገ እናዋጣለን! Linktr.ee/shegafuture

"Honde verkies eintlik nie bene om vleis te eet nie; Dis net dat niemand hulle ooit vleis gee nie." “ውሾች ከስጋው አብልጠው አጥንቱን ስለምን ወደዱ? ስጋ የሚሰጣችው ስላጡ!” በደቡብ አፍሪካ አገልግሎት ላይ ከሚውሉ የስራ ቋንቋዎች አንዱ በሆነው እና ደቡብ አፍሪካን ጨምሮ በናሚብያ፣ በቦትስዋና፣ ፣ በዛምቢያ እና በዚምቡዋቤ ከ20 ሚሊየን በላይ ሰዎች በሚናገሩት 'አፍሪካንስ' የተሰኘ ቋንቋ የሚነገር ብሂል ነው፣   ዛሬም ወደ ውስይችን እንዲገቡ የምንፈቅዳቸውን ሀሳቦች እናነጥርበት ዘንድ የእንዶድ ሁለተኛ ምዕራፍ ፣ ሁለተኛ ተከታታይ መሰናዶ 18ኛ ክፍል ገዢ ሀሳብ እንዲሆን መርጠነዋል። በቃል እና ምግባር ተከታታይ መሰናዶ ክፍል 14 ከ አፋን ኦሮሞ በተዋስነው "ዱቢን አቡልቱ!" (እስኪ ይደር) ፣ በክፍል 15 ወደ ትግራይ ተጉዘን በመዘዝነው ብሂል " ፀርፊ ተፃራፊኡ ይመስል!"( "ስድብ ተሳዳቢውን ይመስላል!")  በክፍል 16 የሀዲይሳን (የሀዲያ ማህበረሰብ ቋንቋ) ስነቃላዊ ሐብቶች ስናገላብጥ ባገኘነው "እያከኣ ገሜአኮኦክ፣ ድላ ገሜኦኮ!" (“አዝለውት ሲሰርቁ ያየ፣ ወርዶ ይሰርቃል!”)  እንዲሁም በክፍል 17 በጋምቤላ ክልል ከሚነገሩ ቋንቋዎች አንዱ በሆነው ቱክ-ኙዌር በሚነገረው "ቢመር፡በፈታሪ፡እዉ፡መርሞ፡እንደን፡ጓደ!" ("የሚረባኝን በባትሪ እፈልጋለሁ!") ሸጋ ቆይታ ማድረጋችን ይታወሳል፤ ዛሬ ደግሞ ከባልደረቦቻችን መኮንን ሞገሴ፣ ጠርሲዳ ከበደ፣ እና ሜሪ መኮንን ጋር ወደ ደቡብ አፍሪካ አቅንተን በቀጠናው ከሚነገሩት ቋንቋዎች አንዱ በሆነው አፍሪካንስ (የኙዌር ማሕበረሰብ ቋንቋ) ከሚነገሩ ስነ-ቃሎች በአንዱ አብረናችሁ ወደናል። ዛሬ ረቡዕ ግንቦት 26 2015 ዓ.ም ከምሽቱ 2:00 ጀምሮ በFM Addis 97.1 በመላው ኢትዮጵያ እንዲሁም በቀጣዩ ማስፈንጠሪያ በመላው ዓለም መደመጥ ይጀምራል።  https://zeno.fm/radio/ebc-fm-addis-97-1/ እልፍኝ አስከልካያችኹ ያልፋል አሻግርም በ0931717191 የሰደዳችሁልንን የቸር ልቦቻችሁ ረጢብ ስንቆች መልሰው ወደ እናንተ የሚደርሱበት ጥንቅሩን አሰናድቷል። ሸጋ ሸጋ ጥያቄዎች የተሰደሩበት መሰናዶ ነውና ያድምጡ፣ ይሳተፉ፣ ሸጋ ጥያቄዎች ይሸምቱ ስንል ጋበዝንዎ! ለተሻለ ነገ እናዋጣለን! Linktr.ee/shegafuture

photo content

"Bimer befetari inghu mermo enden guade!" "ቢመር፡በፈታሪ፡እዉ፡መርሞ፡እንደን፡ጓደ!" "የሚረባኝን በባትሪ እፈልጋለሁ!" በቱክ-ኙዌር (የኙዌር ማሕበረሰብ ቋንቋ) የሚነገር በቃ
"Bimer befetari inghu mermo enden guade!" "ቢመር፡በፈታሪ፡እዉ፡መርሞ፡እንደን፡ጓደ!" "የሚረባኝን በባትሪ እፈልጋለሁ!" በቱክ-ኙዌር (የኙዌር ማሕበረሰብ ቋንቋ) የሚነገር በቃል እና ምግባር ዓውድ ወደ ሕይወታችን የምናስጠጋቸውን ሀሳቦች፣ ግለሰቦች እና ቡድኖች እናጤንበት ዘንድ የእንዶድ ሁለተኛ ምዕራፍ ፣ ሁለተኛ ተከታታይ መሰናዶ 16ኛ ክፍል ገዢ ሀሳብ እንዲሆን መርጠነዋል። በቃል እና ምግባር ተከታታይ መሰናዶ ክፍል 14 ከ አፋን ኦሮሞ በተዋስነው "ዱቢን አቡልቱ!" (እስኪ ይደር) ፣ በክፍል 15 ወደ ትግራይ ተጉዘን በመዘዝነው ብሂል " ፀርፊ ተፃራፊኡ ይመስል!"( "ስድብ ተሳዳቢውን ይመስላል!")  እና በክፍል 16 የሀዲይሳን (የሀዲያ ማህበረሰብ ቋንቋ) ስነቃላዊ ሐብቶች ስናገላብጥ ባገኘነው "እያከኣ ገሜአኮኦክ፣ ድላ ገሜኦኮ!" (“አዝለውት ሲሰርቁ ያየ፣ ወርዶ ይሰርቃል!”) ሸጋ ቆይታ ማድረጋችን ይታወሳል፤ ዛሬ ደግሞ ከባልደረቦቻችን መኮንን ሞገሴ እና ጸጋ ካህሳይ ጋር ወደ ጋምቤላ አቅንተን በክልሉ ከሚነገሩት ቋንቋዎች አንዱ በሆነው ቱክ-ኙዌር (የኙዌር ማሕበረሰብ ቋንቋ) ከሚነገሩ ስነ-ቃሎች በአንዱ አብረናችሁ ወደናል። ዛሬ ረቡዕ ግንቦት 23 2015 ዓ.ም ከምሽቱ 2:00 ጀምሮ በFM Addis 97.1 በመላው ኢትዮጵያ እንዲሁም በቀጣዩ ማስፈንጠሪያ በመላው ዓለም መደመጥ ይጀምራል።  https://zeno.fm/radio/ebc-fm-addis-97-1/ የእልፍኝ አስከልካይ ጥንቅርም በ0931717191 የሰደዳችሁልንን የቸር ልቦቻችሁ ረጢብ ስንቆች መልሰው ወደ እናንተ ይደርሱበት ዘንድ ተዘጋጅቷል። ሸጋ ሸጋ ጥያቄዎች የተሰደሩበት መሰናዶ ነውና ያድምጡ፣ ይሳተፉ፣ ሸጋ ጥያቄዎች ይሸምቱ ስንል ጋበዝንዎ! ለተሻለ ነገ እናዋጣለን! Linktr.ee/shegafuture