የጽርሐ ጽዮን ሐዋርያት ጎላ ቅዱስ ሚካኤል የፍኖተ ብርሃን ሰ/ት/ቤት (Official Channel)
Open in Telegram
ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው።
Show more2 756
Subscribers
+124 hours
+17 days
+4230 days
Posts Archive
የተንገላታችበትን እዩና በቃ በሉ፤ሁሉን የሚያግባባ ነገር ፈልጉና ችግሮችን በሰላማዊ ውይይት ፍቱ፤ በዚህ አማራጭ እናት ሀገር እፎይታ እንድታገኝ ኣድርጉ፤ ይህንም ለውድ እናት የሚደረግ ካሣ አድርጋችሁ ውሰዱት፤ የቤተ ክርስቲያናችን ወቅታዊ መልእክትና ጥሪም ይህ ነው፤
በመጨረሻም የቤተ ክርስቲያናችን መንፈሳዊ፣ ማኅበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊና አስተዳደራዊ አፈጻጸማችን በመገምገም ለቀጣዩ ጊዜ የስራ አቅጣጫን የሚያስቀምጠው የርክበ ካህናቱ የቅዱስ ሲኖዶስ ቀኖናዊ ጉባኤ በዛሬው ዕለት የተጀመረ መሆኑን ለኦርቶዶክሳውያን ሕዝበ ክርስቲያን እናበስራለን።
እግዚአብሔር የተባረከና የተቀደሰ ጉባኤ ያድርግልን!
እግዚአብሔር ኢትዮጵያንና ሕዝቦችዋን ይባርክ!
ወስብሐት ለእግዚአብሔር አሜን!
አባ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት፣
ግንቦት ፮ ቀን ፳፻፲፯ ዓ.ም
አዲስ አበባ ኢትዮጵያ
ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው።
https://t.me/finotebirhan12
የዩቲዩብ ቻናላችን
https://youtube.com/@finotebirhan12
የፌስቡክ ገጻችን https://www.facebook.com/Fbirhan?mibextid=2JQ9oc
የቲክቶክ አካውንታችን https://www.tiktok.com/@finotebirhan?_t=8i8eHwFI3Es&_r=1
የዌብሳይት ገጻችን
https://finotebirhan.com
የግንቦት 2017 ዓ.ም ርክበ ካህናት ቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ መጀመርን አስመልክቶ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት ያስተላለፉት የጉባኤው መክፈቻ መልእክት እንደሚከተለው ቀርቧል።
በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!
ብፁዕ አቡነ አብርሃም የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ጽ/ቤት ዋና ስራ አስኪያጅ፣ የባሕር ዳርና የሰሜን ጎጃም አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ፣ ብፁዕ አቡነ ሄኖክ
የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ፤
ብፁዓን ኣበው ሊቃነ ጳጳሳት የቅዱስ ሲኖዶስ አባላት!!
እንደዚሁም በዚህ ቀኖናዊና ዓመታዊ የርክበ ካህናት የቅዱስ ሲኖዶስ ምልአተ ጉባኤ ላይ የተገኛችሁ በሙሉ፤ ጸጋንና ሐዋርያነትን ያጐናጸፈን ጌታችን አምላካችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ቅድስት ትንሣኤውን በሰላም አክብረን ይህንን ዓመታዊውን የቅዱስ ሲኖዶስ ጉባኤ ለማካሄድ ስለ ሰበሰበን ክብርና ምስጋና ለእርሱ ይሁን፤ የጉባኤው አባላት የሆናችሁ ብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳትም እንኳን ለርክበ ካህናት ጉባኤ አደረሳችሁ! እንኳንም በሰላም መጣችሁ!
“ረከብነ ጸጋ ወተሰየምነ ሓዋርያተ ከመ ናስምዖሙ ለአሕዛብ ወይእመኑ በስሙ፡- ከእምነት የሚነሣ መታዘዝ እንዲገኝ ጸጋንና ሐዋርያነትን ተቀበልን” (ሮሜ.፩÷፭)፤
ይህ ሐዋርያዊ አስተምህሮ የኛን ተልዕኮና ተልዕኮው ያስፈለገበትን ምክንያት አጉልቶ ያሳያል፤ የተቀበልነው ስጦታም ምን ያህል ታላቅ እንደ ሆነ ምንባቡ ያስረዳል፤ ሐዋርያው በዚህ መልእክት የቅዱስ ወንጌል ኣስተምህሮ ዋና ግብ ከእምነት የሚነሣ መታዘዝ እንዲገኝ ማድረግ ነው በማለት ያስተምረናል፤ እውነት ነው ድሮውኑም ቢሆን ለእግዚአብሔር መታዘዝ አቅቶን ነው የወደቅነው፤ ዛሬም የምንነሣው ከእምነት የተነሣ መታዘዝን ገንዘብ ስናደርግ ነው፤ ከሁሉ በፊት እምነት ይቀድማል፤ ከሱ በኋላ ደግሞ ለእምነቱ በሙሉ ልብ መታዘዝ ይከተላል፤ ይህ ሲሆን መዳንና ትንሣኤ ይገኛል፤ ዓለም በእግዚአብሔር እየተደረገለት ያለ ጥሪ ይኸው የመታዘዝ ጥሪ ነው፤
ይህንን መለኮታዊ ጥሪ ለዓለም የማድረስ ኃላፊነትም ለኛ ለቅዱስ ሲኖዶስ አባላት የተሰጠ እንደሆነ ሐዋርያው አስገንዝቦአል፤ ኃላፊነቱ ሲሰጠን ከነመሳርያው ነው፤ እሱም ጸጋና ሐዋርያነት ነው፤ እኛም እሱን ተቀብለናል፤ እንግዲያውስ የተቀበልነውን ጸጋና ሐዋርያነት በዓለም ውስጥ ላለው ሕዝበ እግዚአብሔር አገልግሎት ማዋል ከኛ ይጠበቃል፡፡
ብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት የቅዱስ ሲኖዶስ አባላት!!
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ በአሁኑ ጊዜ የሌለበት ክፍለ ዓለም የለም፤ ምክንያቱም የዚህ ሲኖዶስ ወኪሎች ሊቃነ ጳጳሳት በአፍሪካ፣ በአውሮፓ፣ በሰሜን አሜሪካ፣ በላቲን አሜሪካ፣ በካናዳና በመካከለኛው ምሥራቅ፣ በእስያና በአውስትራሊያ ወዘተ የሚገኙ ሕዝበ እግዚአብሔር ምእመናንን በማገልገል ላይ ይገኛሉና ነው፤ ይህ ዕድል የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ መለኮታዊ ተልኮውን በአጽናፈ ዓለም ሁሉ ለማድረስ ምቹ መደላድል ፈጥሮለታል፡፡ከዚህም በመነሣት በየክፍለ ዓለሙ የሚገኙ የቤተ ክርስቲያናችን ሊቃነ ጳጳሳት ከትውልደ ኢትዮጵያውያን ባሻገር የየአካባቢውን ሕዝብ በማስተማርና በማቀፍ የተጣለባችሁን ሐዋርያዊ ተልእኮ በትጋትና በንቃት መወጣት ይኖርባችኋል፡፡
በማዕከል ሆኖ እየመራ የሚገኝ ቅዱስ ሲኖዶስም ለዚህ ተልእኮ ምቹ መደላድል የመፍጠር ኃላፊነቱን በአግባቡ መወጣት ይገባዋል፡፡ በተለይም ትምህርተ ሃይማኖትንና ቀኖና ቤተ ክርስቲያንን የተማሩና በጥልቀት የተገነዘቡ፣ ብስለትም ያላቸው፤ እንዲሁም በቋንቋና በሥነ ልቦና ዕውቀት የላቀ ሀብተ ጸጋ ያላቸውን በሐዋርያነት እያሠለጠነ በአጽናፈ ዓለም ሁሉ ሊያሰማራ ይገባል፡፡
ብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት የቅዱስ ሲኖዶስ አባላት!
በብሂለ አበው (ፀሐይ ለመስኮቷ ሳታበራ…) እንደሚባለው ለሌላው በብቃት መድረስ እንችል ዘንድ እኛ የቅዱስ ሲኖዶስ አባላት የሲኖዶሱ መንበር በሚገኝባት ምድረ ኢትዮጵያ ከመቸውም የተሻለ ስራ በመስራት ለእግዚአብሔር መታዘዝ ሕዝቡንም ማገልገል ይገባናል፤ ሁላችንም እንደ ምንገነዘበው በሲኖዶሳችን ያልታቀፉ ብዙ ወገኖች በሀገር ውስጥ አሉን፤ እነዚህ ወገኖች አንዳንዶቹ በተለያየ ምክንያት ከኛ የወጡ ናቸው፡፡ ይሁን እንጂ የሄዱት ወደ ቤታቸው እንዲመለሱ፣ ሌሎችም ወደ መንጋው እንዲቀላቀሉ በርትቶ መስራት የዚህ ጉባኤ ተቀዳሚ ተልእኮ ነው፤ ምክንያቱም ጸጋንና ሐዋርያነትን የተቀበልንበት ዋናው ምክንያት ይህንን ለማድረግ ነውና፡፡ ከዚህ አኳያ የቤተ ክርስቲያናችን ተደራሽነት በሳሳበት ኣካባቢ ሁሉ የተለየ ትኵረት ሰጥተን መስራትና ተጨባጭ ለውጥ ማምጣት ይኖርብናል፤
ብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት የቅዱስ ሲኖዶስ አባላት!
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ውሉደ ክህነትና ምእመናን የሆን ሁላችን፣ ከሁሉ በፊት ያለንን አቅምና ብቃት በአግባቡ መገንዘብ ይኖርብናል፤ ለእግዚአብሔር ክብርና ምስጋና ይሁንና ለፈጣሪው በቈራጥነት የሚታዘዝ ምእመን፣ ወጣት፣ ካህን አለን፤ ይህ ትልቅ ጸጋ ነው፤ ይህንን ጸጋ እግዚአብሔር፡ ለእግዚአብሔር መንግሥት በሚመች ሁናቴ ዝቅ ብሎ ማገልገል የክብር ክብር ነው፡፡ በመሆኑም ይህንን የእግዚአብሔር ሕዝብ በሓቅ፣ በቅንነት፣ በትጋትና በታማኝነት ቆመን ካገለገልነውና አባትነታችንንና መሪነታችንን በመልካም አሰራር በትክክል በኅሊናው እንዲቀረጽ ካደረግን፣ ይህ ኃይል ከጐናችን እንደማይለይ እርግጠኞች መሆን እንችላለን፤ ይህንን ካሳካን ለኛ የተሰጠ ኃይልና ብቃት በየትም አይገኝም፡፡
በዚህም በዚያም ሃይማኖቱ የሚጠይቀውን ስብእና እና ቁመና ይዘን ከተገኘን፣ ሕዝበ ክርስቲያኑ ያለውን ብቻ ሳይሆን ሕይወቱን ሳይቀር ለመስጠት ወደ ኋላ የማይል የእግዚአብሔር ሕዝብ አለን፤ ስለዚህ ይህንን ማሳካት እንችል ዘንድ ከእምነት የሚነሣ መታዘዝ እንድናስገኝ የተቀበልነውን ጸጋና ሐዋርያነት በክብር እንያዝ፤
ብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት የቅዱስ ሲኖዶስ ኣባላት!!
ለሕዝበ እግዚአብሔር የምናበረክተው አገልግሎት በመንፈሳዊ ብቻ ሳይሆን በኢኮኖሚውና በማኅበራዊው አገልግሎትም ጭምር ነው፤ ከዚህ አንጻር ሕዝባችን የተሻለ ማኅበራዊ አገልግሎት እንዲያገኝ፣ በኢኮኖሚውም ከድህነት የተላቀቀ እንዲሆን፤ እንደዚሁም ሰላሙና አንድነቱ የተጠበቀ እንዲሆን፣ በማስተማርም በተግባር በመሳተፍም የሕዝቡ መሪዎችና አርኣያ ሆነን መስራት ይገባናል፤በተለይም ከሰላም እጦት የተነሣ በእጅጉ እየተጎዳ ያለውን ሕዝባችን ሰላምና ፍትሕ እንዲያገኝ በጸሎትም በትምህርትም፣ በምክርም ተግተን መስራት አለብን፤
እንዳጋጣሚ ሆኖ የኢትዮጵያ ሕዝብ ከእንግልት የተላቀቀበት ጊዜ ብዙ እንዳልሆነ ይታወቃል፤ ለእንግልት እየተዳረገ ያለውም የሌሎች እጅ ባይለየውም በዋናነት በገዛ ልጆቹ ነው፤ እናት በገዛ ልጆቿ ስትንገላታ ማየት እጅግ አሳዛኝ ነገር ነው፤ እንደዚህ ያለው ነገር በደንብ ያልታሰበበት አካሄድ በብስለትና በንስሓ ማስተካከል አሸናፊነትን እንጂ ተሸናፊነትን አያሳይምና እንዲታሰብበት እንመክራለን፤ ከዚህ አንጻር ኢትዮጵያን ወደ ተሻለ ልማትና ዕድገት እናሻግራለን ብላችሁ እየደከማችሁ ያላችሁ ወገኖቻችን እባካችሁ መለስ ብላችሁ እናታችሁ
ግንቦት 05 ቀን 2017 ዓ.ም. የቅዱስ ሲኖዶስ ርክበ ካህናት ጉባኤ መክፈቻ ጸሎት ተካኼደ።
+++++++++
በመንበረ ፓትርያርክ ቅድስተ ቅዱሳን ማርያም ገዳም በተከፈተው የቅድመ ጉባኤ ጸሎት መርሐ ግብር የዳዊት መዝሙር፣ ውዳሴ ማርያም፣ መልክአ ማርያምና መልክአ ኢየሱስ የተጸለየ ሲኾን በተጨማሪም አድኅነነ ሕዝበከ የሚለው የምህላ ጸሎት፣ የሠርክ መስተብቁዕ፣ በዜማ ስብሐተ እግዚአብሔር ቀርቧል፤ ጸሎተ ወንጌልና መጽሐፈ ኪዳን ተደርሷል፤ የዳዊት መዝሙር ልብሰ ተክህኖ በለበሱ ዲያቆናት ተዚሟል። በማቴዎስ ወንጌል (ማቴ18÷18) ላይ የተጻፈው ቃለ ወንጌል ተነቧል።
በቅዱስነታቸው መልካም ፈቃድ ብፁዕ አቡነ ኤልያስ የኖርዲክ ሀገራት ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ መርሐ ግብሩን አስመልክተው ትምህርተ ወንጌል ሰጥተዋል።
በመጨረሻም በብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርኩ ጸሎትና ቡራኬ የጉባኤ መክፈቻ መርሐ ግብሩ ተጠናቋል።
+++++++
ምንጭ፡- የኢ/ ኦ/ተ/ቤ መገናኛ ብዙኀን አገልግሎት ሥርጭት ገጽ
ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው።
https://t.me/finotebirhan12
የዩቲዩብ ቻናላችን
https://youtube.com/@finotebirhan12
የፌስቡክ ገጻችን https://www.facebook.com/Fbirhan?mibextid=2JQ9oc
የቲክቶክ አካውንታችን https://www.tiktok.com/@finotebirhan?_t=8i8eHwFI3Es&_r=1
የዌብሳይት ገጻችን
https://finotebirhan.com
"ስለዚህ አንድ ሥጋ ናቸው እንጂ ወደ ፊት ሁለት አይደሉም። እግዚአብሔር ያጣመረውን እንግዲህ ሰው አይለየው።" ማቴ 19 ÷6
ሚያዝያ26 /2017 ዓ.ም ጋብቻችሁን በቅድስት ቤተክርስቲያን ሥርዓት የፈጸማችሁት የሰንበት ትምህርት ቤታችን የፍኖተ ብርሃን አገልጋይ ወንድማችን ያሬድ ጥላሁን እና እህታችን ምሕረት የአብርሃምን እና የሳራን ጋብቻ የባረከ አምላክ ጋብቻችሁን ይባርክላችሁ።
ሊቀ መላእክት ቅዱስ ሚካኤል በክንፉ ከልሎ በፍቅርና በጤና ይጠብቃችሁ ዘንድ መልካም ምኞታችን ነው!
እንኳን ደስ አላችሁ ፍኖተ ብርሃን ሰ/ት/ቤት
ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው።
https://t.me/finotebirhan12
የዩቲዩብ ቻናላችን https://youtube.com/@finotebirhan12
የቲክቶክ አካውንታችን https://www.tiktok.com/@finotebirhan?_t=8i8eHwFI3Es&_r=1
የፌስቡክ ገጻችን
https://www.facebook.com/Fbirhan?mibextid=2JQ9oc
የዌብሳይት ገጻችን https://finotebirhan.com
''ዕቅበተ እምነት''
ክፍል አንድ
በመ/ር ዲ/ን ዳንኤል ታደለ
የቅዳሜ የትምህርት መርሐግብር
የፊታችን ቅዳሜ ግንቦት 02/2017 ዓ.ም ከምሽቱ 11:45 ሰዓት ላይ ቀጠሮዎትን በጎላ ቅዱስ ሚካኤል ቤ/ክ ያድርጉ ይምጡ ይማሩ በብዙ ያተርፋሉ እንዳይቀሩ።
የቴሌግራም ቻናላችን
https://t.me/finotebirhan12
የዩቲዩብ ቻናላችን
https://youtube.com/@finotebirhan12
የቲክቶክ አካውንታችን https://www.tiktok.com/@finotebirhan?_t=8i8eHwFI3Es&_r=1
የፌስቡክ ገጻችን https://www.facebook.com/Fbirhan?mibextid=2JQ9oc
የዌብሳይት ገጻችን
https://finotebirhan.com
ለገዳማዊያን አበምኔቶች እና እመምኔቶች
ሲሰጥ የቆየው የስልጠና ተጠናቀቀ።
በመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት በገዳማት አስተዳደር መምሪያ አዘጋጅነት ለሁለት ቀናት ለገዳማዊያን አበምኔቶችና እመምኔቶች ሀገር አቀፍ የገዳማት ወቅታዊ ሁኔታ፣ የገዳማውያን ሕይወት እና አገልግሎትን የሚዳስሰው የሥልጠናና የምክክር መርሐ ግብር ዛሬ ቅዱስ ፓትርያርኩ በተገኙበት ባለ 12 ነጥብ መግለጫ በማውጣት ተጠናቀቀ።
በመርሐ ግብሩ ላይ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት የተገኙ ሲሆን ቃለ ምዕዳን ቡራኬና ትምህርተ ወንጌል ሰጥተዋል።
የገዳማት አስተዳደር መምሪያ ለገዳማውያን አበምኔቶች እና እመምኔቶች ሲሰጥ በሰነበተው የስልጠና መርሐ ግብር በበርካታ ሊቃውንት ሰፊ ጥናታዊ እና ትምህርታዊ ጽሑፎችን አቅርበው ውይይቶች ተደርጎባቸዋል። በመጨረሻም የአቋም መግለጫ በማውጣት መርሐ ግብሩ ተጠናቋል።
የአቋም መግለጫው ሙሉ ቃል እንደሚከተለው ይነበባል።
የአቋም መግለጫ
1. ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት በመጀመሪያው የገዳማት ጉባኤ ላይ የሰጡትን አባታዊ መመሪያና በየጊዜው በተለያዩ መድረኮች ገዳማትን በተመለከተ የሰጡትን እና የሚሰጡትን አባታዊ መመሪያ ለመተግበር ቃል እንገባለን፡፡
2. ብፁዕ አቡነ አብርሃም የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ፤ የባሕርዳርና የሰሜን ጎጃም አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ በጉባኤው መክፈቻ ያስተላለፉትን አባታዊ መመሪያ በየመጣንበት ገዳማት ለመተግበር ቃል እንገባለን፡፡
3. በሦስቱም የቤተ ክርስቲያን ሊቃውንት በቀረቡት ጥናታዊ ጽሑፎች በጥናታዊ ጽሑፍ የቀረቡት ገዳውያኑን የሚመለከቱትን መልእክቶች ለመፈጸም ቃል እንገባለን፡፡
4. ገዳማት የትምህርት የሥርዓት ምንጭ በመሆን ቀደምት አባቶቻችን ገዳማቱን በማጠናከር ለሀገር ግንባታና ለቤተ ክርስቲያን አንድነት ያበረከቱት ተጋድሎ ታሪክ የሚዘክረው ነው፡፡ በመሆኑም እኛም ከየገዳማቱ የመጣን መነኮሳትና መነኮሳይያት የአባቶቻችንን ፈለግ በመከተል ገዳማቱ ለሀገርና ለቤተ ክርስቲያን አንድነት መወጣት ያለባቸውን ተግባር በተሰጠን ኃላፊነት በትጋት ለመሥራት ቃል እንገባለን።
5. አዳዲስ ገዳማት ሲገደሙ በሀገረ ስብከቱ ሊቀ ጳጳስ ጥብቅ ክትትል ተደርጎ በገዳሙ ለሚቀመጡ አበው መተዳደሪያቸው ጭምር ታስቦበት እንዲገደም እንጠይቃለን፤
6. ሁለተኛ መነኮሳትና መነኮሳይያት ለተልእኮ ወደ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ሲመጡ ማረፊያ እንዲዘጋጅላቸው በተደጋጋሚ ተጠይቆ መልስ አልተሰጠውም ትልቁ ቤታችን የመጨረሻ ራስ ቤተ ክርስቲያን የሆነው መንበረ ፓትርያርክ ነው ፡፡ ስለሆነም ለተልዕኮ ገዳም የሚመጡ አባቶችና እናቶች ማረፊያ አጥተው በየከተማው ዘመድና ማረፊያ ፍለጋ መንከራተታቸው ከምናኔ ሕይወታቸው ጋር የማይሄድ መሆኑን ታሳቢ በማድረግ ቅዱስ ሲኖዶስ ማረፊያ እንዲያመቻችልን ዝቅ ብለን እንጠይቃለን፣
7. ምንኩስና የሚሰጥበት ቦታና ሰጪው አካል ተለይቶ ታውቆ የማያዳግም ውሳኔ እንዲሰጥበት በአጽንዎ እንጠይቃለን፣
8.ሁሉም ገዳማት ታይተው ችግራቸው ተለይቶ የጎደላቸው ተሟልቶ እንዲጠናከሩ እንጠይቃለን፡፡
9. የመነኮሳትን ፍልሰት ለማቆም አድራሻ የሌለው መነኩሴ አድራሻ የሌለውን ቄስ አድራሻ የሌለውን ዲያቆን በጥብቅ ቁጥጥር ተለይቶ ለመነኮሳቱም ለቀሳውስቱም ራሱን የቻለ የጠቅላይ ቤተ ክህነት አርማ ያለውና ለቁጥጥር አመቺ የሆነ መለያ ቁጥር ያለው ዲጂታል መታወቂያ ተዘጋጅቶ በሥራ ላይ እንዲውል እንጠይቃለን፡፡
10. በየገዳማቱ አብነት ት/ቤቶች ተከፍተው መነኮሳቱና የአካባቢውን ልጆች በተገባ መንገድ የማብቃት ሥራ እንዲሠራ እንጠይቃለን፡፡
11. በየገዳማቱ ማሠልጠኛ ኑሮ ከማሠልጠኛው በቅተው የሚወጡ መነኮሳት ብቻ የሚማሩበትና የመነኮሳት ኮሌጅ እንዲከፈትልን እንጠይቃለን፡፡
12. ይህ የገዳማውያን አባቶችና እናቶች የውይይትና የምክክር መርሐ ግብር በየዓመቱ ከርክበ ካህናት በፊት እንዲቀጥል ተደርጎ የገዳማቱ አባቶችና እናቶች የየገዳማቸውን ጠንካራና ደካማ ጎን በሪፖርት ለመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት የገዳማት መምሪያ ተልኮ መመምሪያው መርምሮ በገዳማቱ የአንድነት ጉባኤ ከታየ በኋላ በቅዱስ ሲኖዶስ የርክበ ካህናት ምልዓተ ጉባኤ ግብአት ስለሚሆን በቅዱስ ሲኖዶስ በየዓመቱ የሚደረገውን የገዳማውያን አንድነት ጉባኤ እንዲያጸድቅልን በታላቅ ትህትና እንጠይቃለን፡፡
በመጨረሻ ቅዱስ ሲኖዶስ የሁሉም አባትና እናት እንደመሆኑ እዚህ ያለነው የኢትዮጵያ ገዳማት አባቶችና እናቶች ስንሰባሰብ የቀሩ የታላላቅ ገዳማት አበምኔቶችና እመምኔቶች አሉ ለዚህም ቅዱስ ሲኖዶስ ለቤተ ክርስቲያን አንድነት ቅደሚያ በመስጠት በመካል ያለውን ችግር ከሚመለከታቸው ሁሉ ጋር ተቀራርቦ በመነጋገር ያለውን ልዩነት ፈትቶ አንድነትን እንዲፈጥርልን እኛ ገዳማውያን በመጣንባቸው ቅዱሳንና ጸድቃን ስም ዝቅ ብለን በአጽኖት እንጠይቃለን፡፡
ብፁዕ ወቅዱስ አባታችን በጉባኤያችን ላይ በመገኘት አባታዊ መመሪያና ቡራኬ ስለሰጡን ከልብ በማመስገን ቡራኬዎ አይለየን እንላለን፡፡ ብፁዕ አቡነ አብርሃም የጠቅላይ ቤተ ክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ የባሕርዳርና የሰሜን ጎጃም አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ጉባኤው እንዲዘጋጅ በማድረግና በጉባኤው በመገኘት አባታዊ መመሪያና ቡራኬ ስለሰጡን ከልብ እናመሰግናለን፡፡ገዳማውያኑ በዚህ መልክ ተገናኝተን ስለሁለንተናው የቤተ ክርስቲያናችን ሁኔታና ስለገዳማቶቻችን እንድንወያይ መድረኩን የገዳማት መምሪያ ኃላፊዎችንና ሠራተኞችንና በአጠቃላይ ለመርሐግብሩ መሳካት አስተዋጽኦ ያደረጉትን አካላት እናመሰግናለን።
ወስብሐት ለእግዚኣብሔር፤የቅዱስነትዎ ቡራኬ ይድረሰን!!
ሚያዚያ 29 ቀን 2017 ዓ.ም
አዲስ አበባ ኢትዮጵያ
©ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ
ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው።
https://t.me/finotebirhan12
የዩቲዩብ ቻናላችን
https://youtube.com/@finotebirhan12
የፌስቡክ ገጻችን https://www.facebook.com/Fbirhan?mibextid=2JQ9oc
የቲክቶክ አካውንታችን https://www.tiktok.com/@finotebirhan?_t=8i8eHwFI3Es&_r=1
የዌብሳይት ገጻችን
https://finotebirhan.com
