en
Feedback
የጽርሐ ጽዮን ሐዋርያት ጎላ ቅዱስ ሚካኤል የፍኖተ ብርሃን ሰ/ት/ቤት (Official Channel)

የጽርሐ ጽዮን ሐዋርያት ጎላ ቅዱስ ሚካኤል የፍኖተ ብርሃን ሰ/ት/ቤት (Official Channel)

Open in Telegram

ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው።

Show more
2 761
Subscribers
+324 hours
+87 days
+4830 days
Posts Archive
የ2017 ዓ.ም የከተራ በዓል በሰላም ተከብሮ ዋለ ታቦታቱም ከመንበረ ክብራቸው ተነስተው ወደ ባህረ ጥምቀቱ ማደሪያ ደርሰዋል።

ታቦተ ሕጉ ከመንበሩ ጥር 10፦ 7:00  ስለሚወጣ 6:00 ሰዓት ተገኙ። ጥር 11፦ 4:00  ስለሚወጣ 3:00 ሰዓት ተገኙ። ጥር 12፦ 4:00 ስለሚወጣ 3:00 ሰዓት ተገኙ።

በዓለ ከተራ ከተራ ምንድን ነው? ከተራ 'ከበበ' ካለው የግእዝ ግሥ የወጣ ነው፡፡ ፍችው ውኃ መከተር፣ መገደብ ማለት ነው፡፡ በጥምቀት ዋዜማ ታቦተ ሕጉ ከቤተ መቅደስ ወጥቶ ውኃ ባለበት አካባቢ ስለሚያድር የየአጥቢያው ሕዝብ እየተሰበሰቡ በወንዝ ዳር ወይም በምንጭ አካባቢ ድንኳን ይተከላሉ፡፡ ድንኳንም ከሌለ ዳስ ሲጥሉ ይውላሉ፡፡ የምንጮች ውኃ እንዲጠራቀም ይከተራሉ (ይገድባሉ) ጉድጓድ እየተቆፈረ ውኃው እንዳይሄድ በመገደብ ለመጠመቂያ (ለጥር 11) ዝግጁ የሚያደርጉበት ዕለት ነው፡፡ በተጨማሪ  በአቅራቢያ የሚገኙት ቤተክርስቲያናት ተሰብስበው ከዚሁ ከተቆፈረው ገንዳ ወይም ከተገደበው ጅረት  አጠገብ ባለው ዳስ ወይም ድንኳን ታቦቶቻቸውን ያሳድራሉ ሊቃውንቱም በዚያው እግዚአብሔርን በማህሌት ሲያመሰግኑ ያድራሉ። በበዓለ ጥምቀት የታቦታቱ ወደ ወንዝ መውረድ መድኃኔ ዓለም ክርስቶስ በእደ ዮሐንስ ለመጠመቅ ከገሊላ ወደ ዮርዳኖስ የመሄዱ ምሳሌ ነው፡፡ ታቦቱ የጌታችን፣ ምሳሌ ሲሆኑ ካህናቱ የመጥምቁ ዮሐንስ ምሳሌ ናቸው፡፡ መዘምራኑና ሕዝቡ ደግሞ ዮሐንስ ያጠመቃቸው ሕዝቦች ምሳሌዎች ናቸው፡፡ መልካም የከተራ በዓል ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው። https://t.me/finotebirhan12 የዩቲዩብ ቻናላችን https://youtube.com/@finotebirhan12 የፌስቡክ ገጻችን https://www.facebook.com/Fbirhan?mibextid=2JQ9oc የቲክቶክ አካውንታችን https://www.tiktok.com/@finotebirhan?_t=8i8eHwFI3Es&_r=1 የዌብሳይት ገጻችን https://finotebirhan.com

"እንኳን ለብርሃነ ጥምቀቱ በሰላም አደረሰን፤ አደረሳችሁ።" ለሰንበት ት/ቤታችን የጥምቀት ዘማርያን በሙሉ የጥምቀት በዓል ላይ ከጥምቀት ዘማርያን ምን ይጠበቃል? ቅድመ በዓል 👉ጽ/ቤቱ ባስተላለፈው መሠረት ጸጉር መስተካከል፤ ጥፍር መቆረጥ ፤ የእጅና የጆሮ ጌጥ አለማድረግ፤ የዓይን እና ሌሎች ማስዋቢዎችን አለመጠቀም  የግል ንጽህናን መጠበቅ(ሰውነትን መታጠብ)፤ ከውኃ ውጭ አለመጠጣት! 👉ሥርዓተ ቤተክርስቲያንን የጠበቀ አለባበስ መልበስ 👉ልብሰ ስብሐቱ ካጠረን ከረዘመው ጋር መቀያየር 👉ልብሰ ስብሐቱን ከመልበስ በፊት አቡነ ዘበሰማያት መድገም 👉የእኛን ልብሰ ስብሐት ለሌላ ሰው ሰጥተን ማዘመር አይቻልም። መዘመር ካልቻልን ለሚመለከተው  ክፍል ማሳወቅ እና መመለስ። ጊዜ በዓል 👉በሥርዓት ሆኖ መዘመር 👉ያለ አስተባባሪው ፈቃድ በዝማሬ የጀመሩበትን ቦታ አለመቀየር እና አቋርጦ አለመውጣት ድኅረ በዓል 👉መንገድ ላይ እየተራመዱ ልብሰ ስብሐት ማውለቅ ፈጽሞ የተከለከለ ነው። 👉ጸበል ጸዲቅ ከተዘጋጀበት ቦታ ምግብ ከበላን በኋላ ንግግራችን መጠን አድርገን፣ ያለመንጓተት እና ያለመላፋት በረከታችንን ወደ ቤታችን ይዘን መሄድ 👉ከዝማሬ በኋላ ልብሰ ስብሐት ይዞ መጠጥ መጠጣት፣ መደባደብ፣ ያልተገባ ንግግር መናገር ፈጽሞ የተከለከለ ነው። 👉ስንቀመጥም፣ ስንነሳም፣ ስንሄድም፣ ስናስቀምጥም ልብሰ ስብሐቱን በተቻለን አቅም እናክብረው።             ታቦተ ሕጉ ከመንበሩ ጥር 10፦ 7:00  ስለሚወጣ 6:00 ሰዓት ተገኙ። ጥር 11፦ 4:00  ስለሚወጣ 3:00 ሰዓት ተገኙ። ጥር 12፦ 4:00 ስለሚወጣ 3:00 ሰዓት ተገኙ።   ቅዱስ እግዚአብሔር አገልግሎታችንን ይቀበለልልን። የበረከት በዓል ያድርግልን። ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው። https://t.me/finotebirhan12 የዩቲዩብ ቻናላችን https://youtube.com/@finotebirhan12 የፌስቡክ ገጻችን https://www.facebook.com/Fbirhan?mibextid=2JQ9oc የቲክቶክ አካውንታችን https://www.tiktok.com/@finotebirhan?_t=8i8eHwFI3Es&_r=1 የዌብሳይት ገጻችን https://finotebirhan.com

''የእግዚአብሔር ፍቅር '' የአቡነ ሺኖዳ የአውደ ምሕረት ስብከቶች ስብስብ የሰንበት ት/ት ቤታችን አባል በሆነው ወንድማችን ዮሴፍ አምሐ የተዘጋጀ የትርጉም መጽሐፍ ሲሆን መጽሐፉ በሁለት ክፍሎች የተ
+2
''የእግዚአብሔር ፍቅር '' የአቡነ ሺኖዳ የአውደ ምሕረት ስብከቶች ስብስብ የሰንበት ት/ት ቤታችን አባል በሆነው ወንድማችን ዮሴፍ አምሐ የተዘጋጀ የትርጉም መጽሐፍ ሲሆን መጽሐፉ በሁለት ክፍሎች የተዘጋጀ ስለሆነ እየገዛችሁ በማንበብ ወንድማችንን በማበረታታት የድርሻችንን እንወጣ። ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው። https://t.me/finotebirhan12 የዩቲዩብ ቻናላችን https://youtube.com/@finotebirhan12 የፌስቡክ ገጻችን https://www.facebook.com/Fbirhan?mibextid=2JQ9oc የቲክቶክ አካውንታችን https://www.tiktok.com/@finotebirhan?_t=8i8eHwFI3Es&_r=1 የዌብሳይት ገጻችን https://finotebirhan.com