en
Feedback
SPORT 52

SPORT 52

Open in Telegram

SPORT INFORMATION CHANNEL

Show more
871
Subscribers
+124 hours
-87 days
-1630 days

Data loading in progress...

Tags Cloud
No data
Any problems? Please refresh the page or contact our support manager.
Incoming and Outgoing Mentions
---
---
---
---
---
---
Attracting Subscribers
December '24
December '24
+8
in 0 channels
November '24
+6
in 0 channels
Get PRO
October '24
+15
in 0 channels
Get PRO
September '24
+12
in 0 channels
Get PRO
August '24
+68
in 0 channels
Get PRO
July '24
+9
in 0 channels
Get PRO
June '24
+8
in 0 channels
Get PRO
May '24
+9
in 0 channels
Get PRO
April '24
+20
in 0 channels
Get PRO
March '24
+17
in 0 channels
Get PRO
February '24
+25
in 0 channels
Get PRO
January '24
+15
in 0 channels
Get PRO
December '23
+20
in 0 channels
Get PRO
November '23
+28
in 0 channels
Get PRO
October '23
+9
in 0 channels
Get PRO
September '23
+6
in 0 channels
Get PRO
August '23
+20
in 0 channels
Get PRO
July '23
+18
in 0 channels
Get PRO
June '23
+24
in 0 channels
Get PRO
May '23
+11
in 0 channels
Get PRO
April '23
+3
in 0 channels
Get PRO
March '23
+18
in 0 channels
Get PRO
February '23
+7
in 0 channels
Get PRO
January '23
+25
in 0 channels
Get PRO
December '22
+65
in 0 channels
Get PRO
November '22
+95
in 0 channels
Get PRO
October '22
+37
in 0 channels
Get PRO
September '22
+23
in 0 channels
Get PRO
August '22
+941
in 0 channels
Date
Subscriber Growth
Mentions
Channels
21 December0
20 December+2
19 December0
18 December0
17 December0
16 December0
15 December0
14 December0
13 December0
12 December+1
11 December+3
10 December0
09 December0
08 December0
07 December0
06 December0
05 December0
04 December+1
03 December0
02 December0
01 December+1
Channel Posts
ማድሪድ በባርሴሎና ባይሸነፍ ጥሩ ነበር..... ባለፈው እንዳልኳችሁ የማድሪድ መሸነፍ ለሊቨርፑል ፣ ለሲቲ፣ ላባየር ሙኒክና ለአርሰናል ጥሩ አይደለም ብዬ ነበር። #ይኸው ተጀመረ ሪያል ማድሪድ ትሬንት
ማድሪድ በባርሴሎና ባይሸነፍ ጥሩ ነበር..... ባለፈው እንዳልኳችሁ የማድሪድ መሸነፍ ለሊቨርፑል ፣ ለሲቲ፣ ላባየር ሙኒክና ለአርሰናል ጥሩ አይደለም ብዬ ነበር። #ይኸው ተጀመረ ሪያል ማድሪድ ትሬንት አሌክሳንድርን ለማነጋገር ቀጠሮ ሊይዙ መሆኑ ተሰምቷል። ተጨዋቾች በሊቨርፑል የሚያቆየውን ኮንትራት ለማራዘም ፍቃደኛ አይደለም። #ከዚያም ሩድሪ... ማድሪድ ቹማኒን በመጪው የዝውውር መስኮት ለመሸጥ ዝግጁ መሆናቸውን አሳውቀዋል። ይህ ደግሞ ለሲቲ መልካም ዜና አይደለም። ምክንያቱም በጥር የዝውውር መስኮት ባይሆን እንኳን ክረምት ላይ ሩድሪ ወደ ማድሪድ ማቅናቱ የግድ ይሆናል። #ከዚያ ደግሞ..... አልፎንሶ ዴቪስ.....እያለ ሳሊባ ጋር ይደርሳል። ከዚያ ጦሱ ለሌሎችም ይደርሳል።

2
https://youtu.be/eHmpbSYniG0?si=meUEZdO9G5l9k_Ft
385
3
ሰበር ኤሪክ ቴን ሃግ ተባረሩ.. Van Nistelrooy to become Man Utd's interim boss
ሰበር ኤሪክ ቴን ሃግ ተባረሩ.. Van Nistelrooy to become Man Utd's interim boss
393
4
የማድሪድ የትላንት ምሽት ሽንፈት ለአርሰናል፣ ለሊቨርፑል፣ ለባየር ሙኒክና ለማንችስተር ሲቲ መጥፎ ነው። ምክንያቱም #ዊሊያም ሳሊባ #ትሬንት አሌክሳንደር #አልፎንሶ ዳቪስ እና #ሮድሪን መሄዳቸው ነው
የማድሪድ የትላንት ምሽት ሽንፈት ለአርሰናል፣ ለሊቨርፑል፣ ለባየር ሙኒክና ለማንችስተር ሲቲ መጥፎ ነው። ምክንያቱም #ዊሊያም ሳሊባ #ትሬንት አሌክሳንደር #አልፎንሶ ዳቪስ እና #ሮድሪን መሄዳቸው ነው...
359
5
የክለቦች ክፍያ አስተዳደር ስርዓት መመሪያን ባለመተግበር በአራት ክለቦች ላይ የቅጣት ውሳኔ ተላለፈ። በክለቦች የክፍያ ስርዓት አስተዳደር መመሪያ መሰረት ክለቦች የየወሩን ጥቅል የደመወዝ ሪፖርት ወር
የክለቦች ክፍያ አስተዳደር ስርዓት መመሪያን ባለመተግበር በአራት ክለቦች ላይ የቅጣት ውሳኔ ተላለፈ። በክለቦች የክፍያ ስርዓት አስተዳደር መመሪያ መሰረት ክለቦች የየወሩን ጥቅል የደመወዝ ሪፖርት ወር በገባ እስከ 10 ቀን ማሳወቅ እንዳለባቸው ተጠቅሷል። መመሪያው ከሚያዘው ውጪ የፕሪሚየር ሊጉ አራት ክለቦች ሪፖርት ማድረግ ከነበረባቸው ከ12 እስከ 27 ቀናት በላይ በመቆየት ሪፖርት አድርገዋል። የፋይናንስ አሰራር ተቆጣጣሪ ኮሚቴ በክለቦች የክፍያ ስርዓት አስተዳደር መመሪያ ቁጥር 01/2016 አንቀፅ 9 መሰረት በአራት ክለቦች ላይ የቅጣት ውሳኔዎችን አስተላልፏል። በዚህ መሰረትም ሀዋሳ ከተማ ሪፖርት ማድረግ ከነበረበት ከ12 ቀናት በላይ በመዘግየቱ ብር 70,000(ሰባ ሺህ ብር)፣ አዳማ ከተማ ሪፖርት ማድረግ ከነበረበት ከ23 ቀናት በላይ በመዘግየቱ ብር 180,000(አንድ መቶ ሰማኒያ ሺህ ብር)፣ አርባምንጭ ከተማ ሪፖርት ማድረግ ከነበረበት ከ24 ቀናት በላይ በመዘግየቱ ብር 190,000(አንድ መቶ ዘጠና ሺህ ብር)... እንዲሁም ወልዋሎ አዲግራት ዩኒቨርሲቲ ሪፖርት ማድረግ ከነበረበት ከ27 ቀናት በላይ በመዘግየቱ ብር 220,000(ሁለት መቶ ሃያ ሺህ ብር) ተቀጥተዋል። ከዚህ በተጨማሪም የፋይናስን አሰራር ተቆጣጣሪ ኮሚቴው ‘ዝውውራቸው አጠራጣሪ ነው’ ባላቸው 25 ተጫዋቾች እና ክለቦቹ ላይ ተጨማሪ ምርመራ እያደረገ ሲሆን በማስረጃ የሚደረጉ ጥቆማዎችን በተዘጋጁ ኢሜል(kifyatikoma@gmail.com) እና ስልክ ቁጥር(0952111144) እየተቀበለ ይገኛል።
280
6
ያልተጠበቀ ግን አስገራሚ የመቀሌ70 እንደርታ ጉዞ........ #ግብ የሚያገኝበትን መንገድ ማስተካከል ቀጣዩ ስራ ሊሆን ይገባል.... አጀማመሩ ፍፁም አስፈርቶኝ የነበረው መቀሌ 70 እንደርታ ከባድ ይሆኑበታል ከተባሉት የፕራሚየር ሊግ ጨዋታዎች ነጥብ ማግኘቱን ቀጥሎበታል። በመጀመሪያው ጨዋታ አንድ ተጨዋቾች በቀይ ካርድ ከወጣበት ከሃድያ ሆሳና ጋር ባደረገው ጨዋታ 1ለዐ የተሸነበት መንገድ ቡድኑ ቀጣይ አምስት ከባድ ጨዋታዎችን እንዴት ሊወጣው ይችላል የሚል ጥያቄ አንስቼ ነበር። ሆኖም ግን አሰልጣኝ ዳንኤል ፀሃዬ በሊጉ በያዝነው የውድድር ዓመት ለተጋጣሚ ፈታኝ ይሆናሉ ከተባሉት..... #ከመቻል #ከቅዱስ ጊዮርጊስ #ከፋሲል ከነማና ከ #ከድሬደዋ ከነማ ስምንት ነጥብ ወስዷል። ይህ ደግሞ በደረጃ ሰንጠረዡ ሁለተኛ ሆኖ እንዲቀመጥ አድርጎታል። በእኔ ከመጀመሪያ ሳምንት ጨዋታ ምልከታ በኋላ ቡድኑ ቅርፅ ለመያዝ ቢያንስ የ10 ጨዋታ ግዜ ይወስድበታል የሚል እምነት ቢኖረኝም መቀሌ በፍጥነት ጉድለቱን አስተካክሎ ለተጋጣሚ ቡድን በቀላሉ እጅ የማይሰጥ መሆኑን እያሳየ ነው። ከሃድያ ሆሳዕና ጨዋታ በኋላ ቀጣይ አምስቱ መርሃ ግብሮች እንደሚከብዱት ከእኔ አልፎ በሌሎች የተነገረለት አሰልጣኝ ዳንኤል ፀሃዬ ከአራቱ ጠንካራ ከተባሉት ቡድኖች ስምንት ነጥብ ሰብስቦ በቀጣይ ከኢትዮጵያ ቡና ጋር የሚያደርገውን ጨዋታ እየጠበቀ ይገኛል። በዚህ ቡድን ለውጥ ውስጥ አሰልጣኙ እና ተጨዋቾቹ ያበረከቱት አስተዋፅኦ ከፍተኛ መሆኑን እንዳለ ሆኖ የያሬድ ብርሃኑ ምርጥ ብቃት ላይ መገኘት ለቡድኑ የእስከ አሁኑ ውጤታማነት ከፍተኛ ድርሻ ይወስዳል። ያሬድ ብርሃኑ ዛሬ ያስቆጠራቸውን ሁለት ግቦች ጨምሮ በሊጉ አምስት ግቦችን በማስቆጠር የከፍተኛ ግብ አግቢነቱን መምራት ጀምሯል። ይህ ማለት ቡድኑ በአምስት ጨዋታዎች ካስቆጠራቸው ስድስት ግቦች አምስቱን ያስቆጠረው ያለፈውን የውድድር ዓመት በኢትዮ ኤሌክትሪክ ያሳለፈው ያሬድ ብሄርሃኑ ነው። ያሬድ በዚህ ብቃት ላይ ሆኖ ለቡድኑ አምስት ግቦችን በማስቆጠር ትልቅ ስራ እየሰራ ቢሆንም 83% የሚሆኑት ግቦች ከያሬድ ብቻ መገኘታቸው አሰልጣኙ አንድ ትልቅ የቤት ስራ እንደሚጠበቅባቸው የሚጠቁም ነገር አለው። እሱም የግብ አማራጩ ያሬድ ብቻ በመሆኑ ሌሎች የግብ ምንጮችን መጠቀም የሚችልበትን ስልት strategy መንደፍ ነው። በተረፈ ግን መቀሌ 70 እንደርታ ካሰብኩት ፈጥኖ የተለወጠ ቡድን መሆኑን ማመን አሰፈላጊ አግኝቼዋለሁ። ያ ማለት ግን ሁሉን ያሟላ ነው ማለት እንዳልሆነ ሊታወቅልኝ ይገባል። አሁን ላይ ያየነውን ለውጥ መቀበል ግን እንዳለብኝ ይሰማኛል።
296
7
No text...
233
8
ደቡብ ሱዳን ከእኛ የምትሻለበት አንድ ነገር....... በቻን የማጣሪያ ውድድር ኢትዮጵያ በስተሰሜን ከምታዋስነን ከኤርትራ ጋር እንድትጫወት ድልድል መውጣቱ ይታወሳል። ከድልድሉ በኋላ ሁለቱ ሃገራት የ
ደቡብ ሱዳን ከእኛ የምትሻለበት አንድ ነገር....... በቻን የማጣሪያ ውድድር ኢትዮጵያ በስተሰሜን ከምታዋስነን ከኤርትራ ጋር እንድትጫወት ድልድል መውጣቱ ይታወሳል። ከድልድሉ በኋላ ሁለቱ ሃገራት የካፍን መስፈርት ያሟሉ ስታድየም የሌላቸው መሆኑን ተከትሎ የት ይጫወታሉ የሚለው ጉዳይ ሲያነጋግር ቆይቶ በመጨረሻም ሁለቱ ሃገራት የደርሶ መልሱ ጨዋታ በደቡብ ሱዳን ዋና ከተማ ጁባ ከተማ እንዲከናወን መርጠዋል። ደቡብ ሱዳን ከዋናዋ ሱዳን ነፃነቷን ያገኘችው እ.ኤ.አ በ2011 ዓ.ም ሲሆን ሉዐላዊ ሃገር መሆኗ በተባበሩት መንግስታት ድርጅት እውቅና በማግኘቷ እ.ኤ.አ በ2012 ዓ.ም ደግሞ የአፍሪካ እግር ኳስ ኮንፌዴሬሽን እና ፊፋ በአባልነት መዝግቧታል። ደቡብ ሱዳን ይህን ነፃነት ለማግኘት በሚሊየን የሚቆጠሩ ዜጎቿን በሞት በስደት መስዋእት አድርጋ የተለያዩ አለም አቀፍ እና አህጉር አቀፍ ተቋማት አባል ብትሆንም ዜጎቿ በፖሊቲካ እና በኢኮኖሚ ችግር አበሳ ማየታቸውን አላቆመም። ያም ሆኖ ግን ከኢትዮጵያ እና ከኤርትራ የተሻለችበት ነገር እንዳላት ለማየት በቅተናል። ይህም የአፍሪካ እግር ኳስ ኮንፌዴሬሽን የሚያዘጋጃቸውን ውድድሮች ማከናወን የሚያስችል ደረጃውን የጠበቀ ስታዲየም ያላት መሆኑ ነው። ኢትዮጵያ ግን በስታድየም ጉዳይ ሌሎቹን ሃገራት እንተውና ከደቡብ ሱዳን ያነሰች በመሆኗ ብሄራዊ ቡድኗ የስደት መወዳደሩን የሚቀጥል ይሆናል።
311
9
የሶስትዮሽ ስህተት...... #አሰልጣኙ በመጨረሻም ለቀዋል....... ከጊኒ ጨዋታ በኋላ በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ ከአምስት ቀን በኋላ ብሄራዊ ቡድኑን እለቃለሁ ያሉት አሰልጣኝ ገብረመድህን መልቀቃቸው ይፋ ሆኗል። በምትካቸው ረዳታቸው ሆኖ ሲያገለግል የነበረው አሰልጠኝ መሳይ ተፈሪ ቡድኑን በግዚያዊነት እንዲያሰለጥን ሃላፊነት ተሰጥቶታል። አሰልጣኝ ገብረመድህን ከቡድኑ ጋር በነበራቸው የአስራ ሁለት ወራት ቆይታ በአለም ዋንጫና በአፍሪካ ዋንጫ ማጣሪያ ስምንት ጨዋታዎችን አድርገው አራት ነጥብ ብቻ ከማግኘታቸውና ሁለት ግቦችን ከማስቆጠራቸው ባለፈ አንድም ጨዋታ አላሸነፉም። 13 ግቦችም ተቆጥረውበታል። ይህ ቁጥራዊ መረጃ ቡድናችን በሜዳ ውስጥ በሁሉም ነገር መበለጡን ከማሳየቱ በተጨማሪ አሰልጣኝ ገብረመድህን ከቡድኑ ጋር ጥሩ ግዜ አለማሳለፋቸውን ይነግረናል። ይህ ሊሆን የቻለበት ብዙ ምክንያቶች ቢኖሩትም አንደኛው ምክንያት ግን ሁለት ቡድን ለማሰልጠን በወሰዱት ከባድ ሃላፊነት ሳቢያ የተፈጠረ ነው። ምክንያቱም በተረጋጋ ሁኔታ ቡድኑን ማሰልጠን እንዳይችሉ አድርጓቸዋልና.... ለመሆኑ በአሰልጣኝ ገብረመድህን ቅጥር ውስጥ ስህተት የሰራው ማነው....? የተጎዳውስ ማነው...? የሚለውን በጥልቀት አዳስሰዋለሁ። #የገብረመድህን ስህተት..... አሰልጣኝ ገብረመድህን ሃይሌ በኢትዮጵያ እግር ኳስ ረጅም አመት በማሰልጠንና ዋንጫዎችን በማንሳት ከፍተኛ ልምድ ያካበቱ እንዲሁም ኢትዮጵያ መድህን ወደ ፕሪሚየር ሊጉ ባደገበት አመት ጠንካራ ተፎካካሪ ማድረግ የቻለ አሰልጣኝ ናቸው። ከዚህ አንፃር የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን እሳቸውን መቅጠሩ እሳቸውም ጥያቄውን መቀበላቸው ምንም ስህትት የለውም። ነገር ግን ስህተቱ ፌዴሬሽኑ ድርብ ሃላፊነት መስጠቱ እና እሳቸውም መቀበላቸው ነው። ከላይ እንደጠቀስኩት አሰልጣኙ ከፍተኛ ልምድ ያካበቱ ናቸው። ይህ ልምዳቸው ለሞያው ስኬታማነት ከፍተኛ እገዛ ከማድረጉ ባሻገር የተሳሳቱ ውሳኔዎችን እንዳይወስኑ ያግዛቸዋል። ያም ሆኖ ግን አሰልጣኙ በዚህ ሞያ ውስጥ ሳሉ ትልቁን ስህተት ሰርተው በመጨረሻም ከብሄራዊ ቡድኑ ጋር መለያየታቸው የግድ ሆኗል። ይህን ልል የቻልኩበት ዋነኛ ምክንያት አሰልጣኙ ውጤት በማጣታቸው ሳይሆን ብሄራዊ ቡድንኑና ኢትዮጵያ መድህንን በአንድነት ለማሰለጠን መድፈራቸው ነው። አሰልጣኝ ገብረመድህን ለረጅም አመታት በአሰልጣኝነት የሰሩ ከመሆኑ አንፃር ስራው ምን ያህል ከባድና አስጨናቂ እንደሆነ ከእሳቸው እና ከመሰሎቻቸው በላይ የሚረዳ ሰው ያለ አይመስለኝም። ይህንንም ብዙ አሰልጣኞች ሲናገሩ ከመስማቴ በተጨማሪ በዚህ ጉዳይ ሃሳባቸውን የሰጡኝ አንድ አሰልጣኝ "ሞያችን አስጨናቂና የዛፍ ላይ እንቅልፍ" ነው ሲሉ መናገራቸው አንዱ ማሳያ ነው። ይህንን እኔም የምጋራው ሆኖ ይህን ላልኩበት ደግሞ አንድ ቀላል ምሳሌ ልጥቀስ.... አንድ አሰልጣኝ አንድ ጨዋታ ካሸነፈ ከጥቂት ሰአታት በኋላ በቂ የአዕምሮና አካለዊ እረፍት ሳያገኝ ቀጣዩን ጨዋታ እንዴት ማሸነፍ እንዳለበትና ምን አይነት የልምምድ እቅድ ማዘጋጀት እንዳለበት በመቀመር አዕምሮውን ይበልጥ መስጨነቁን ይቀጥላል። ይህ አይነቱ ጭንቀት የእግር ኳስ የውድድር ዓመቱ እስኪጠናቀቅ ድረስ ከአሰልጣኞች የማይለይ የእለት ተዕለት ጉዳይ በመሆኑ እረፍት የለሽ አመት ያሳልፋሉ። በዚህ ላይ አንድ አሰልጣኝ ሁለት ቡድን ሲያሰለጥን ደግሞ ጫናው ምን ያህል ከባድ እንደሆነ መገመት አያስቸግርም። ይህንን ደግሞ አሰልጣኙ ከፍተኛ ጫና ውስጥ መሆናቸውን በመናገር ድርብ የአሰልጣኝነት ስራ አስጨናቂ መሆኑን መስክረዋል። ይህ ንግግራቸው ደግሞ ሁለት ቡድን ለማሰልጠን የወሰዱት ሃላፊነት ስህተት እንደነበር ያስገነዝበናል። #የፌዴሬሽኑ ስህተት....? የቅጥር ሂደቱ ምንም ይሁን ምን የመጨረሻው ውሳኔ የስራ አስፈፃሚ ኮሚቴው ነው። ይህ ኮሜቴ የኢትዮጵያን እግር ኳስ በተመለከተ ከፍተኛ ሃላፊነት ያለበት ከመሆኑ አንፃር እግር ኳሱን የማይጎዳ ውሳኔ መወሰን ይጠበቅበታል። ምንም እንኳን አመራሮቹ ባለሞያ professionals ባይሆኑም በአመንክዮ አንድ አሰልጣኝ ሁለት ቡድን ቢያሰለጥን ምን አሉታዊ ችግር ሊከሰት ይችላል የሚለውን በመገመት እንዲህ አይነት ውሳኔዎች ከመወሰን መቆጠብ መቻል ግን ከባድ አልነበረም። ግን አልሆነም ሃገርን ዋጋ ያስከፈለ ሊደገም የማይገባው ቅጥር ተፈፅሟል። ውሳኔያቸውም ለፀፀት ሳይዳርጋቸው እንደማይቀር ይታመናል። #ወጥ የሆነ አሰራር ቢኖር...... የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን አሰልጣኞችን ሲቀጥር አሰልጣኞች ክለባቸውን የመልቀቅ ግዴታ እንዳለባቸው በመግለፅ ሲቀጥር እንደነበር ይታወሳል። ይህ ከወንዶች ብሄራዊ ቡድን ቅጥር ባለፈ በሴቶች ብሄራዊ ቡድን ቅጥር ላይ ተፈፃሚ ሲሆን ቆይቷል። ይህ አይነቱ አሰራር ወጥ ሆኖ ቢሆን ኖሮ የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽንን ለምን ብሎ ለመጠየቅ የሚቻልበት ሁኔታ ላይኖር ይችል ነበር። ይሁን እንጂ የአሰልጣኝ ገብረመድህን ቅጥር ከቀድሞው አሰራር የተፈፀመ መሆኑ ከግምት ሲገባ ፌዴረሽኑ ከቅጥር ጋር በተያያዘ ወጥ የሆነ መመሪያ የለውም እንዴ የሚል ጥያቄ ያስነሳል። ከሌለው ግን የብሄራዊ ቡድን አሰልጣኞችን በተመለከተ መመሪያ ማዘጋጀት አስፈላጊ መሆኑ ምንም ጥርጥር የሌለው ስለሆነ ነገ ዛሬ ሳይባል መፍትሄ ሊሰጠው ይገባል። በተረፈ ግን ከዚህኛው የተሳሳተ ቅጥር አሰልጣኝ ገብረመድህን ሃይሌ፣ የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽንና ኢትዮጵያ መድህን ትልቅ ትምህርት ያገኙበት አጋጣሚ ይሆናል። #የኢትዮጵያ መድህ ስህተት... ሌላው በዚህ ጉዳይ ተወቃሽ የሚሆነው ኢትዮጵያ መድህን ስፖርት ክለብ ነው። ክለቡ በሚሳተፍበት ውድድር ውጤታማ ለመሆን በየዓመቱ ከፍተኛ በጀት መመደቡ ይታወቃል። ይህ ሲሆን ታዲያ አሰልጣኞቹና ተጨዋቾቹ ሃሳባቸውን ሰብስበው ሙሉ ትኩረታቸውን ቡድናቸው ላይ ማድረግ ይኖርባቸዋል። ይህ ማለት ሃሳብን ለሁለት በሚከፍል ጉዳይ ላይ መሳተፍ (ከአቅም በላይ የሆነ ችግር ካልገጠመ በቀር) አይኖርባቸውም ማለት ነው። ያም ሆኖ ግን ኢትዮጵያ መድህን አሰልጣኙ ሁለት ቦታ እንዲያሰለጥኑ የፈቀደ ሲሆን ይህም የማታ ማታ ክለቡ ዋጋ እንዲከፍል ምክንያት ሆኗል። ስለሆነም ለተፈጠረው ስህተት ሃላፊነቱን መውሰድ ከሚገባቸው አካላት መካከል አንዱ ክለቡ ራሱ መሆኑ የግድ ይሆናል። እንዴት ከተባለ ኢትዮጵያ መድህን ቡድኑ ውጤታማ እንዲሆን ከፍተኛ ወጪ ከማድረጉ ባሻገር ለአሰልጣኙም ከፍተኛ ወርሃዊ ክፍያ ይፈፅማል። ሆኖም ግን ቡድኑ ባለፈው አመት ላለመውረድ ከመጫወቱ በተጨማሪ ዘንድሮ ደግሞ ከሶስት የፕሪማየር ሊግ ጨዋታ ሁለት ነጥብ ብቻ የማግኘታቸው ሚስጥር ከዚሁ ከተሳሳተ ውሳኔ ጋር ሊያያዝ እንደሚችል ምንም ጥርጥር የለውም። በዚህ ውሳኔ ምክንያት አሰልጣኙም ተጨንቀዋል ቆይተዋል...ብሄራዊ ቡድኑም ሆነ ኢትዮጵያ መድህን ውጤት ተቃሮ ላይ ተቀምጠዋል። እናም ቅጥሩ የጎዳው ሶስቱንም እንደሆነ ሊሰመርበት ይገባል።
274
10
No text...
261
11
ከ53 ዓመት በኋላ..... # ዝግጅቱ ብዙ ቅድመ ሁኔታዎችን ይፈልጋል..... ኢትዮጵያ የአፍሪካ ዋንጫን የማዘጋጀት አቅም እንዳላት የቀደሞ ታላላቅ የአፍሪካ እግር ኳስ ተጨዋቾች ከተለያዩ የሃገራችን ሚዲያዎች ጋር በነበራቸው ቆይታ ሲናገሩ ሰምተናል። ተጨዋቾቹ ኢትዮጵያ የአፍሪካ ዋንጫን የማዘጋጀት አቅም አላት ሲሉ ከምን ተነስተው እንደሆነ ግልፅ ባይሆንም ሃገራችን ውድድሩን እንድታዘጋጅ ቅስቀሳ ማድረጋቸው ግን በመልካም ጎኑ ሊወሰድ ይችላል። እርግጥ ነው ኢትዮጵያ የአፍሪካ ዋንጫን የማዘጋጀት አቅም አላት። ግን እንዴት.....? ውድድሩን ለማዘጋጀት የሚያስችለውን መስፈርት ማሟላት ሲቻል ብቻ...... ይህ ዜና ከተሰማ በኋላ ሃገራችን እነዚህን ቅድመ ሁኔታዎችን አሟልታ አዘጋጅተንም ቢሆን ብሄራዊ ቡድናችን በአፍሪካ ዋንጫ ይሳተፍ ከሚል ስሜት ነገሩን በተስፋ መጠበቅ የጀመሩ ብዙዎች ናቸው። ከምንም በላይ ደግሞ የኮንፌዴሬሽኑ ፕሬዚዳንት ዶክተር ፓትሪስ ሙሳፔ ከጠቅላይ ሚኒስተር ደ/ር አብይ አህመድ ጋር በመሆን በግንባታ ላይ የሚገኘውን የአደይ አበባ ስታድየም (ግንባታው እንደቆመ ነው) ያለበትን ቁመና መጎብኘታቸው ደግሞ ተስፋውን አግዝፎታል። እንደውም ከስታድየሙ ጉብኝት በኋላ ፕሬዝዳንቱ የሰጡትን አስተያየት መነሻ በማድረግ እንዳንዶች የኮንፌዴሬሽኑ ፕሬዚዳንት ባዩት ነገር ደስተኛ በመሆናቸው ኢትዮጵያ የ2029 ኙን የአፍሪካ ዋንጫ እንድታዘጋጅ እድሉን ሊሰጡ ይችላሉ ብለዋል። ኢትዮጵያ የአፍሪካ ዋንጫን ለማዘጋጀት በጠቅላይ ሚኒስተር ዶ/ር አብይ አህመድ በኩል ይፋዊ ጥያቄ ማድረጓን የገለፁት ዶ/ር ሙሳፔ ግን በካፍ መመዘኛ መሰረት የኢትዮጵያ ጥያቄ ተገምግሞ ምላሽ እንደሚሰጠው ጠቁመዋል። ይህ አስተያየታቸው ዶክተር ፓትሪስ ሙሳፔ ምንም እንኳን የተቋሙ አውራ ቢሆኑም በራሳቸው መወሰን የማይችሉ መሆኑን የሚጠቁም ነው። ከዚህ በተጨማሪም በአንድ ዘመናዊ ስታድየም ብቻ የአፍሪካ ዋንጫን ማስተናገድ ስለማይቻል ኢትዮጵያ ውድድሩን እንድታዘጋጅ ይፈቀድላታል ብሎ ዛሬ ላይ ጮቤ መርገጥ ተገቢ አይደለም። ይህን የምልበት ዋነኛ ምክንያት ኢትዮጵያ የአህጉሪቱን ትልቅ የእግር ኳስ ውድድር ለማስተናገድ ደረጃ A የሆኑ ውድድሮችን ማከናወን የሚችሉ ደረጃቸውን የተጠበቁ ስታድየሞች ሊኖሯት ስለሚገባ ነው። #መስፈርቱ..... ኢትዮጵያ የአፍሪካን ዋንጫ ለመጨረሻ ግዜ ያስተናገደችው እ.ኤ.አ በ1976 ዓ.ም ነው። የ2029ኙን የማስተናገድ እድል ካገኘች ደግሞ ከ53 ዓመት ወዲህ ለመጀመሪያ ግዜ ይሆናል ማለት ነው። ይህን እድል ለማግኘት ደግሞ የአፍሪካ እግር ኳስ ኮንፌዴሬሽን ያስቀመጣቸውን መስፈርቶች ማማሟላት የሚገባ ሲሆን ከእነዚህ መካከል አንዱ ደረጃቸውን የጠበቁ ስታድየሞችን ማዘጋጀት ነው። ይሁን እንጂ አሁን ባለው ተጨባጭ ሁኔታ ይህን አህጉር አቀፍ የእግር ኳስ ውድድር ማስተናገድ የሚችሉ ጥራት ያላቸው ሜዳዎች የሉንም። ግን ደግሞ ውድድሩን ከ 53 አመታት በኋላ ወደ ሃገራችን ለማምጣት አምስት አመት የዝግጅት ግዜ አለን። ይህ ደግሞ ግንባታቸው ተጀምሮ ያልጠናቀቁትን ለማጠናቀቅ እንዲሁም አዳዲስ ስታድየሞችን መገንባት ካለብን ለመገንባት በቂ ግዜ በመሆኑ አጋጣሚ ጥሩ ሊሆን ይችላል። ይህም ቢሆን ግን ውድድሩን ለማዘጋጀት ብቁ ያደርገናል ማለት እንዳልሆነ ሊሰመርበት ይገባል። ምክንያቱም ውድድሩ በሚካሄድባቸው ከተሞች ከስታድየሞች ባሻገር ቢያንስ ቢያንስ ተወዳዳሪ ቡድኖች ልምምድ የሚሰሩባቸው ምናልባት በአንድ ውድድር በሚካሄድበት ከተማ አራት ሊሆን ይችላል ጥራት ያላቸውን የልምምድ ሜዳዎችን ማዘጋጀትና የአየር ማሪፊያን እንዲሁም ባለ ኮከብ ሆቴሎች የመሳሰሉ መሰረተ ልማቶችን ማሟላት ይገባል። እነዚህ ነገሮች መሰረታዊ ከመሆናቸው አንፃር ባልተሟሉበት ሁኔታ የአፍሪካ ዋንጫን የማዘጋጀት እድል እናገኛለን ብሎ ማሰብ ዘበት ነው። ይህ እንዳለ ሆኖ ሌላው ከግምት ሊገባ የሚገባው ነገር ቢኖር የፀጥታ ጉዳይ ነው። የአፍሪካ እግር ኳስ ኮንፌዴሬሽን ውድድሩ ለማዘጋጀት ጥያቄ ለሚያቀርቡ ሃገራት እንደ መመዘኛ አድርጎ የሚወስደው አንዱ መመዘኛ የፀጥታ ሁኔታ ነው። ኮንፌዴሬሽኑ የፀጥታ ችግር ላለባቸው ሃገራት በተለይ ከ2010 የአፍሪካ ዋንጫ የካቢንዳ ጥቃት በኋላ እንዲህ አይነት ውድድሮችን አሳልፎ የፀጥታ ችግር ባለባቸው ሃገራት ውድድሮችን ደፍሮ የመስጠት ዝንባሌ አይታይበትም። በሃገራችን አንዳንድ ክፍሎች አሁንም ቢሆን ያልተፈቱ የፀጥታ ችግሮች ያሉ ሲሆን እነዚህ ችግሮች በቀጣይ አምስት አመታት የማይፈቱ ከሆነ ውድድሩን ማዘጋጀት አስቸጋሪ ያደርገዋል። ስለሆነም ከላይ በጠቀስኳቸው ምክንያቶች ውድድሩን የማዘጋጀት ትልማችን እንከን እንዳይገጥመው ይህንን ከወዲሁ ማሰብ ያስፈልጋል። ያም ሆኖ ግን በጠቅላይ ሚኒስትሩ በኩል ይህ ጥያቄ ሲቀርብ የኢትዮጵያ መንግስት የአፍሪካ እግር ኳስ ኮንፌዴሬሽን የሚያስቀምጣቸውን መመዘኛዎች ለማሟላት ዝግጁ ነው ማለት ነው።
338
12
No text...
295
13
የታክቲክ ሰሌዳ፦ #ከኳስ ውጪ ያለ እንቅስቃሴ በእግር ኳስ ወሳኙ ነገር..... ትላንት አሰልጣኝ ገብረመድህን ሃይሌ ከሰጡት አስተያየት መካከል አንዱ ተጨዋቾቹ ኳስ ሲያገኙ እንጂ ከኳስ ውጭ መጫወት አይችሉም ያሉበት ይገኛል። አሰልጣኙ የሰጡት አስተያየት በኢትዮጵያ እግር ኳስ ውስጥ ለአመታት የቆየ ችግር በመሆኑ ብዙዎቻችንን ሊያስማማን ይችል ይሆናል። ነገር ግን የችግሩ ለረጅም ግዜ መኖርና መፍትሄ አለማግኘት አሰልጣኞችን ተጠያቂ ከማድረግ የሚያድን ሃሳብ መስሎ አልታየኝም። ለምሳሌ ተጨዋቾች ለብሄራዊ ቡድን የሚጠሩት ከክለቦች ሲሆን በየ ክለቡ ውስጥ ያሉ ተጨዋቾችን ከሚያሰለጥኑት አሰልጣኞች መካከል አንዱ አሰልጣኝ ገብረመድህን ሃይሌ ይገኙበታል። ያም ለበርካታ አመታት በማሰልጠንና ሁለት የፕሪሚየር ሊግ ዋንጫን በማግኘት ይታወቃሉ። ስለሆነም የኢትዮጵያ ተጨዋቾች ከኳስ ውጪ ደካማ መሆናቸውን ከተናገሩ ችግሩ ያለው አሰልጣኝ ገብረመድህን ሃይሌ ጋ እና መሰሎቻቸው መሆኑንም ማመን ያስፈልጋል። አይ በዚህ ረገድ እኛ መወቀስ የለብን የሚል አካል ካለ ደግሞ ተጨዋቾችን ለብሄራዊ ቡድን አስመረጥኩ ብሎ የሚፎክር የክለብ አሰልጣኝ ሊኖር አይገባም። #ለመሆኑ ከኳስ ውጪ መጫወት አይቹሉም ማለት ምን ማለት ነው....? በእግር ኳስ ጨዋታ ማጥቃትና መከላከል የጨዋታው ዋናው አካል ሲሆን ኳስ የያዘ ቡድን ያጠቃል ያልያዘው ቡድን ደግሞ በአብዛኛው የመከላከል ስራ ይሰራል። ስለዚህ እንደ የአሰልጣኝ ገብረመድህን ሃይሌ አባባል የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን ተጨዋች ከመከላከል ወደ ማጥቃት የነበራቸው ሽግግር ደካማ መሆኑን የሚያሳይ ሲሆን ይህም ኳስ መቀማት ላይ ችግር ነበረባቸው ማለት ነው። #በጨዋታ ግዜ ከባዱ ነገር ምንድነው...? በእግር ኳስ ለአሰልጣኞችም ሆነ ለተጨዋቾች ከባዱን ስራ ከኳስ ውጪ የሚደረግ እንቅስቃሴ ነው። ይህንን ደግሞ ተጫውተው ያሳለፉ ጠንቅቀው ያውቁታል። ለተጨዋች ኳስ ለመንጠቅ ተጋጣሚውን እንደማሳደድ አስቸጋሪ ስራ የለም። ለዚህም ማሳያ ይሆን ዘንድ የሚከተለውን ማሳያ እንመልከት........ በአንድ ወቅት FIFA football bible ባወጣው አንድ ፅሁፍ ላይ አንድ ተጨዋች በአማካይ በአንድ ጨዋታ ሶስት ደቂቃ ብቻ ኳስ ይነካል ይላል። ይህ አገላለፅ አንድ ተጨዋቾች 87ቱን ደቂቃ ከኳስ ውጪ ይንቀሳቀሳል ማለት ነው። ይህ ጥናትን መሰረት ያደረገ ማስረጃ ከኳስ ውጪ የሚደረግ እንቅስቃሴ ብዙ መስራት የሚጠይቅ መሆኑን ያስረዳል። ታዲያ እንደ አሰልጣኝ ገብረመድህን ሃይሌ አስተያየት የኢትዮጵያ ተጨዋቾች ከተጋጣሚያቸው ኳስ ለመንጠቅ ብቁ እንዳልነበሩ አልያም ብዙ ስራ በሚጠይቀው ከኳስ ውጭ በነበራቸው እንቅስቀሴ ደካማ እንደነበሩ ነገረውናል። እንዲህ አይነት ችግሮች የሚከሰቱት ምን ሲገጥም ነው የሚለውን ስንመለከት በአካል ብቃት ረገድ ብቁ ካለመሆን ጋር የሚያያዝ ሲሆን ይህ ደግሞ የስነ ልቦና ውድቀትን ያመጣል ከዚያም የትኩረት ማነስ ይከተላል። የአንድ ቡድን ተጨዋቾች በአካል ብቃት በኩል ብልጫ ከተወሰደባቸው ተጋጣሚያቸውን ለማሸነፍ የሚያስችላቸውን ሃይል ያጣሉ። ስለዚህ በሃገራችን እግር ኳስ ብዙ ትኩረት የማይሰጠው አካል ብቃት ከኳስ ጋርም ሆነ ከኳስ ውጪ በሚደረግ እንቅስቃሴ እጅግ አስፈላጊ መሆኑን የተማርንበት ነው። ከምንም በላይ ደግሞ በአንድ ወቅት "የአካል ብቃት ባለሞያ የግድ አይደለም " ላሉት ለአሰልጣኝ ገብረመድህን ሃይሌ ትልቅ ትምህርት ሰጥቶ ያለፈ ጨዋታ እንደነበር ምንም ጥርጥር የለውም። እንዲህ አይነቱ ክፍተት ለመፈጠሩ ተጠያቂነቱ (ሃጢያታችሁን እያበዛሁት አይደለም በተለይ አሰልጣኞች) ከአሰልጣኞች ባሻገር የክለብ አደረጃጀት ጉዳይ ሲነሳ እጅ እጅ የሚላቸውን የክለብ አመራሮችንም ይመለከታል።
446
14
No text...
335
15
የታክቲክ ሰሌዳ፦ "ቀጥተኛ ጨዋታ መጫወቴን አላቆምም"....ገብረመድህን ሃይሌ.... #ቀጥተኛ ጨዋታ ማለት ምን ማለት ነው...? አሰልጣኝ ገብረመድህን ሃይሌ የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድኑ ከጊኒ ጋር ያደረጋቸውን ሁለት ጨዋታዎች አስመልክቶ ዛሬ ከጋዜጠኞች ጋር ቆይታ አድርገዋል። አሰልጣኙ ከጋዜጠኞች ለቀረቡላቸው በርካታ ጥያቄዎች መለስ በሰጡበት ወቅት "ቀጥተኛ ጨዋታ መጫወታቸውን እንደሚቀጥሉበት ተናግረዋል። አሰልጣኙ ብሄራዊ ቡድኑን በመሩባቸው ጨዋታዎች ቡድኑ ቀጥተኛ ጨዋታ ይጫወት ነበር.....? ከሆነስ ውጤታማ ነበር ወይ የሚለውን ለግዜ እናቆየውና ቀጥተኛ ጨዋታ ማለት ምን ማለት ነው የሚለውን እንመልከት። ቀጥተኛ direct play ጨዋታ ማለት በረጅም ኳስ ማለትም ከተከላካይ ለአጥቂ በሚጣል ኳስ ማጥቃት ብቻ መስሎን የቆየን ብዙዎች ነን። ሆኖም ቀጥተኛ ጨዋታ ማለት ቶሎ ቶሎ ወደ ተጋጣሚ የግብ ክልል የሚደረስበት የጨዋታ ስልት ሲሆን እሱም በዋናነት በሁለት መንገድ ሊከናወን ይችላል። አንደኛ ከላይ እንደጠቀስኩት ከተከላካይ ክፍል በቀጥታ ለአጥቂዎች ወደ ተጋጣሚ የግብ ክልል በሚጣል ኳስ መድረስ ሲሆን.... ሁለተኛው ደግሞ በፈጣን፣ ቀጥተኛ እንዲሁም ብዙ አጭር ቅብብሎሽ በማድረግ በፍጥነት ወደ ተጋጣሚ የግብ ክልል በመሄድ የሚከወን ነው። ፈጣንና ቀጥተኛና አጭር ቅብብሎሽ የተጋጣሚ ቡድን ሳይደራጅ ለማጥቃት የሚመች የማጥቂያ ስልት ሆኖ በዚህ አጨዋወት ሂደት ውስጥ የኋሊት ቅብብሎሽ እምብዛም ቦታ የማይሰጠው ሊሆን ይችላል። እርግጥ ነው Possession (indirect play) አጨዋወት ከማጥቃትም ሆነ ከመከላከል ጋር በተያያዘ ሰፊ ጥቅሞች ቢኖሩትም የአሰልጣኝ ገብረ መድህን ሃይሌ ምርጫ ግን ቀጥተኛ ጨዋታ ነው። ይህ የእሳቸው የጨዋታ መንገድ ስለሆነ ምርጫቸውን መጋፋት ባንችልም አንድ የምጠይቀው ጥያቄ ግን የትኛውን ቀጥተኛ ጨዋታ ነው የሚከተሉት....? #በረጅም ኳስ መጫወት #በአጭር ቅብብሎሽ....? # ወይስ ድብልቅ ቀጥተኛ ጨዋታ መከተል...ይህን ነው ግልፅ ያላደረጉት.....
427
16
No text...
355
17
“ ሦስት ፣ አራት ክለቦች የክፍያ ስርዓት መርያውን ለመጣስ ሲሞክሩ አግኝተናል”- መቶ ዓለቃ ፈቃደ ማሞ... የፕሪምየር ሊጉ አክሲዮን ማህበር በአዲሱ የክፍያ ስርዓት አፈፃፀም ሂደት ዙርያ በፕሬዝደንቱ አማካኝነት ለጋዜጠኞች ምላሽ ሰጥተዋል። በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ አክስዮን ማህበር 6ተኛ መደበኛ ጠቅላላ ጉባኤ ባሳለፍነው ቅዳሜ በሃያት ሬጀንሲ ሆቴል መካሄዱ ተከትሎ ለሚዲያ አካላት ጋዜጣዊ መግለጫ በዛሬው ዕለት በቤስት ዌስተርን ፕሪሚየር ዳይናስቲ ሆቴል እየሰጡ ይገኛል። እየተሰጠ ባለው ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ ከሚዲያ አካላት ከተነሱ ጥያቄዎች መካከል የአዲስ በወጣው የክፍያ ስነ ሥርዓት አፈፃፀሙ እንዴት አገኛቹሁት ? የምትፈልጉትን ቁጥጥር አድርጋቸዋል ወይ አተገባበሩ ላይ የተለያዩ ቅሬታዎች በተወሰኑ ክለቦች እየተነሳ ይገኛል በሚል ለተነሳው ጥያቄ መቶ አለቃ ፍቃደ ማሞ ምላሽ ሲሰጡ “ በጉባኤው ላይ ከተነሱ ሦስት ዋና ዋና ጉዳዮች መካከል አንዱ የክፍያ ሥርዓቱ አፈፃፀም በተመለከተ ነበር። በዚህ የክፍያ ስነ ሥርዓት መመርያ ዙርያ ሁለት አንኳር ጥያቄዎች ተነስተዋል።” ያሉት መቶ ዓለቃ ፈቃደ “አንደኛው እኛ በቅንነት ብዙ መረጃ ሠጥተን ነገር ግን ተግባራዊ ባለመደረጉ ክለባችን ተጎድቷል። በዚህም የ2017 ውድድር መውረድም፣ ሻምፒዮን የሚሆን ክለብ መኖር የለበትም።” የሚል ሲሆን “ሁለተኛ ደግሞ በቅንነት ያቀረብነው የተጫዋቾች ደሞዝ የተጣራው እንዲቀርብ ፈልገን የነበረ ቢሆንም ያልተጣራ መቅረቡ ተገቢ አይደለም።”የሚል ጥያቄ ቀርቦ እንደነበር ገለፀዋል። ማብሪራያቸውን ሲቀጥሉ ይህን የፋይናስ ስርዓት ዝም ብለን ያወጡት አለመሆኑ እና ጥናት ተደርጎበት እንደሆነ ያብራሩት ፕሬዝደንቱ ብዙ ክለቦች ተግባራዊ ለማድረግ ሲፎካክሩ ቢቆዩም ሐምሌ ወር ሲመጣ ግን አብዛኛዎቹ ባይባልም ሦስት አራት ክለቦች የክፍያ ሥርዓቱ ጥሰው አግኝተናል ብለዋል። መመርያውን ጣሱ ስለተባሉ ክለቦች ሲያስረዱም “ለምን እነዚህ ክለቦች ህጉን ጣሱ ቢባል ለኪሳቸው አስበው መመርያውን የጣሱ አሉ ይሄን ለመናገር አልፈራም በግልፅ ነው የምናገረው። ለምሳሌ ከቅዱስ ጊዮርጊስ ይጫወት የነበረ አንድ የውጭ ሀገር ተጫዋች ሦስት መቶ ሰማንያ ሺህ ብር ያገኝ የነበረ ተጫዋች መቻል ሲገባ መቶ ሺህ ብር መከፈሉ በግልፅ መመርያው መጣሱን ማሳያ ነው። ሌሎች ብዙ መረጃዎች ይዘናል። የቀድሞ ክለባቸው የሚሰጣቸውን ከፍተኛ ብር አንቀበልም ብለው በአነስተኛ ክፍያ ሌላ ክለብ የሄዱ አሉ ። በአጠቃላይ መረጃዎች እየተሰባሰቡ እየተጠናከሩ ይገኛል። የተዋቀረው ኮሚቴ ጉዳዮን እየመረመረ ነው በጊዜ ሂደት መፍትሄ ያገኛል። ምንም በማያወላውል ሁኔታ እርምጃ እንወስዳለን የጊዜ ሁኔታ ነው። ይህን ላረጋግጥላቹ እፈልጋለው።” ብለዋል። በመጨረሻም በክረምቱ ከተረደጉ ዝውውሮች ውስጥ 25 ተጫዋቾች ጥርጣሬ ውስጥ ገብተው ስማቸው እና ማስረጃዎችን አጠናክሮ ለመርመር ለኮሚቴው ስማቸው ስለመተላለፉ አንስተዋል። መረጃው የሶከር ኢትዮጵያ ነው
458
18
No text...
310
19
አዲስ አበባ ዩንቨርስቲ የአቋም ለውጥ አድርጓል.... በ2017 የውድድር አመት በከፍተኛ ሊግ ከሚወዳደሩ ቡድኖች መካከል አንዱ ይሆናል ተብሎ ሲጠበቅ የነበረው የአዲስ አበባ ዩንቨርስቲ እግር ኳስ ቡድ
አዲስ አበባ ዩንቨርስቲ የአቋም ለውጥ አድርጓል.... በ2017 የውድድር አመት በከፍተኛ ሊግ ከሚወዳደሩ ቡድኖች መካከል አንዱ ይሆናል ተብሎ ሲጠበቅ የነበረው የአዲስ አበባ ዩንቨርስቲ እግር ኳስ ቡድን ከሰሞኑን በውድድሩ እንደማይሳተፍ መግለፁ ይታወቃል። ሆኖም ግን ዛሬ Sport 52 ባገኘችው መረጃ መሠረት ቡድኑ የሚወዳደር ሲሆን በዛሬው እለት የሚጠበቅበትን ክፍያ ፈፅሞ መመዝገቡን ለማረጋገጥ ችለናል። የቡድኑ ህልውና እንዲቀጥል በማደረግ የዩኒቨርሲቲው ከፍተኛ አመራሮችና የተማሪዎች ዲን ጽ/ቤት ያደረጉት አስተዋፅኦ ከፍተኛ መሆኑን አውቀናል።
397
20
https://youtu.be/HBMfzEOLbEs?si=dzbC4sJRygVg-aGP
364