210 395Subscribers
+29024 hours
+1 7407 days
+8 18630 days
- Subscribers
- Post coverage
- ER - engagement ratio
Data loading in progress...
Subscriber growth rate
Data loading in progress...
🏆🏆 ፒኤስጂ ሻምፒዮን ሆኗል 🏆🏆
የፈረንሳይ ሊግን በሰባ ነጥቦች እየመራ የሚገኘው ፒኤስጂ ተከታዩ ሞናኮ በኦሎምፒክ ሊዮን መሸነፉን ተከትሎ የሊጉ አሸናፊ መሆኑን አረጋግጧል።
ፒኤስጂ ሶስት የሊግ ጨዋታዎች እየቀሩት ከወዲሁ የፈረንሳይ ሊግ አሸናፊ መሆን ችለዋል።
ለሶስተኛ ተከታታይ አመታት የሊጉ ሻምፒዮን የሆነው ፒኤስጂ ባለፉት አስር አመታት ስምንት ጊዜ ሊጉን አሸንፈዋል።
ፒኤስጂ በታሪካቸው አስራ ሁለተኛ የፈረንሳይ ሊግ ዋንጫቸውን ማሳካት ችለዋል።
@tikvahethsport @kidusyoftahe
👍 132👎 25❤ 16🎉 12😁 9👏 4🤩 2🔥 1
" ዛሬ እድለኞች ነበርን " ጋርዲዮላ
የማንችስተር ሲቲው ዋና አሰልጣኝ ፔፕ ጋርዲዮላ ቡድናቸው ኖቲንግሃም ፎረስትን ባሸነፈበት ጨዋታ እድለኛ እንደነበር ከጨዋታው በኋላ ገልጸዋል።
እነሱ በጣም ከባድ ተጋጣሚ ነበሩ በፈጣን ተጨዋቾቻቸው ተጭነው ተጫውተዋል ብዙ ግቦችንም ስተዋል ዛሬ እድለኛ ነበርን በጣም ጥሩ ድል ነው ያስመዘገብነው።"በማለት ፔፕ ጋርዲዮላ ተናግረዋል።
@tikvahethsport @kidusyoftahe
👍 154❤ 26😁 20👎 15🥰 6👏 1🤬 1
የኤደርሰን ጉዳት ቀላል ላይሆን እንደሚችል ተገለፀ !
ብራዚላዊው የማንችስተር ሲቲ ግብ ጠባቂ ኤደርሰን በዛሬው የኖቲንግሀም ጨዋታ ያጋጠመው ጉዳት ከባድ ሊሆን እንደሚችል አሰልጣኝ ፔፕ ጋርዲዮላ ጠቁመዋል።
ኤደርሰን በጨዋታው ተቀይሮ ለመውጣት መገደዱ የሚታወስ ሲሆን አሰልጣኝ ፔፕ ጋርዲዮላም ስለ ጉዳቱ መጠን ተጠይቀው " ጥሩ አይመስልም " ሲሉ መልሰዋል።
ግብ ጠባቂው በሚቀጥሉት ቀናት የህክምና ምርመራ ያደርጋል ተብሎ ይጠበቃል።
@tikvahethsport @kidusyoftahe
😢 79😁 38👍 30❤ 8👎 3
" ወሳኙ ሶስት ነጥብ ማግኘታችን ነው " ሀላንድ
የማንችስተር ሲቲው የፊት መስመር አጥቂ ኤርሊንግ ሀላንድ አስፈላጊው ነገር ቡድናቸው በዛሬው ጨዋታ ያሳየው አቋም ሳይሆን ሶስት ነጥቡ መሆኑን ገልጿል።
" በጣም አስፈላጊ ድል ነው ያስመዘገብነው ሜዳ ላይ ያደረግነው ነገር ለውጥ አያመጣም ጉዳዩ ስለማሸነፍ ነው ሶስት ነጥቡን አግኝተናል አሁን ስለ ቀጣይ ጨዋታ ማሰብ እንጀምራለን።"ሲል ሀላንድ ተናግሯል።
@tikvahethsport @kidusyoftahe
👍 216👎 50❤ 33😁 6🔥 5🤬 4
ናፖሊ ከሮማ ነጥብ ተጋርተዋል !
በጣልያን ሴርያ የሰላሳ አራተኛ ሳምንት መርሐ ግብር ናፖሊ ከሮማ ጋር ያደረጉትን ጨዋታ 2 ለ 2 በሆነ አቻ ውጤት አጠናቀዋል።
የናፖሊን ግቦች ቪክቶር ኦሲሜን እና ማትያስ ኦሊቬራ ከመረብ ሲያሳርፉ ለሮማ ፓብሎ ዲባላ እና ታሚ አብረሀም አስቆጥረዋል።
ናይጄሪያዊው አጥቂ ቪክቶር ኦሲሜን በውድድር አመቱ ያስቆጠራቸውን የሊግ ግቦች አስራ አራት ማድረስ ችሏል።
የሊግ ደረጃቸው ምን ይመስላል ?
5️⃣ ሮማ :- 59 ነጥብ
8️⃣ ናፖሊ :- 50 ነጥብ
ቀጣይ ጨዋታ ምን ይመስላል ?
ሰኞ - ዩዲኒዜ ከ ናፖሊ
እሁድ - ሮማ ከ ጁቬንቱስ
@tikvahethsport @kidusyoftahe
👍 61❤ 1
ማንችስተር ሲቲ ወሳኝ ድል አሳክቷል !
በእንግሊዝ ፕርሚየር ሊግ የሰላሳ አምስተኛ ሳምንት መርሐ ግብር ማንችስተር ሲቲ ከኖቲንግሃም ፎረስት ጋር ያደረጉትን ጨዋታ 2 ለ 0 በሆነ ውጤት ማሸነፍ ችለዋል።
የማንችስተር ሲቲን የማሸነፊያ ግቦች ኤርሊንግ ሀላንድ እና ጆስኮ ግቫርዲዮል ከመረብ ማሳረፍ ችለዋል።
ኖርዊያዊው የፊት መስመር ተጨዋች ኤርሊንግ ሀላንድ በውድድር አመቱ ያስቆጠራቸውን የሊግ ግቦች ሀያ አንድ ማድረስ ችሏል።
ኬቨን ዴብሮይን በ2024 ባደረጋቸው አስራ ዘጠኝ ጨዋታዎች ሀያ የግብ አስተዋፅኦ ማድረግ ችሏል።
በሊጉ ደረጃ ሰንጠረዥ ስንተኛ ናቸው ?
2️⃣ ማንችስተር ሲቲ :- 79 ነጥብ
1️⃣7️⃣ ብራይተን :- 26 ነጥብ
ቀጣይ ጨዋታቸው ምን ይመስላል ?
ቅዳሜ - ሼፍልድ ዩናይትድ ከ ኖቲንግሃም
ቅዳሜ - ማንችስተር ሲቲ ከ ዎልቭስ
@tikvahethsport @kidusyoftahe
👍 310👎 73❤ 19🔥 12😁 12🥰 8🤔 5🤬 3🤩 2
90+3 ' ኖቲንግሀም 0 - 2 ማንችስተር ሲቲ
⚽ ግቫርዲዮል
⚽ ሀላንድ
@tikvahethsport @kidusyoftahe
👍 54👎 19🔥 12❤ 7
80 ' ኖቲንግሀም 0 - 2 ማንችስተር ሲቲ
⚽ ግቫርዲዮል
⚽ ሀላንድ
@tikvahethsport @kidusyoftahe
🔥 94👎 46👍 27🤬 22❤ 11😁 10🥰 4
63 ' ኖቲንግሀም 0 - 2 ማንችስተር ሲቲ
⚽ ግቫርዲዮል
@tikvahethsport @kidusyoftahe
👏 148👎 76❤ 32👍 22🤬 17😁 13🔥 11