1 277
Subscribers
No data24 hours
-37 days
+1330 days
Posts Archive
1 277
Repost from አልፋና ዖሜጋ የንጽጽርና የትምህርት መገኛ አደባባይ (አዖተ)
🔥 ሁሉም ነገር ሲዘጋጋ ፤ ያኔ ብዙ ነገሮችን ከአጠገባችን ስናጣ ፤ ዛሬ እንደቀልድ አይተን የምናልፋቸውን ሁሉንም ጠቃሚ ነገሮች ነገ ማግኘት በፈለግን ሰዓትና ሁኔታ እንደፈለግናቸው ማግኘት ሳንችል ስንቀር ሁላችንም የሚቆጨን የሚጨንቀን የሚጠበን ይሆናል!!!
💥 ምንጭ፦ የማቴዎስ ወንጌል ፳፭ ፥ ፩–፲፫ [ይነበብ]
🌄 ሐምሌ ፳፪ | ፳፻፲፰ ዓ.ም
🌄 አልፋና ዖሜጋ ዘተዋሕዶ
🌄 የአባቶች ድካም... #ያስፈርዳል!!!
1 277
Repost from አልፋና ዖሜጋ የንጽጽርና የትምህርት መገኛ አደባባይ (አዖተ)
ከኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን በተለያዩ ጊዜያት የተሰጡ መግለጫዎች
16/04/2016 ዓ.ም
1 277
በጃፓን ኩማሞቶ በሬክተር ስኬል 7.1 የመሬት መንቀጥቀጥ ተከሰተ
በጃፓን ደቡባዊ የኪዩሹ ደሴት በሚገኘው ኩማሞቶ ግዛት ዛሬ የደረሰው ኃይለኛ የመሬት መንቀጥቀጥ በሰዎች ሕይወት፣ በመሠረተ ልማት እና በኢንዱስትሪ ተቋማት ላይ ከፍተኛ ጉዳት አስከትሏል።
የመጀመሪያ ግምገማዎች መንቀጥቀጡ በ6.8 እስከ 7.1 ማግኒትዩድ መካከል መለካቱን ያሳያሉ፤ ባለሥልጣናት የመጨረሻ ሳይንሳዊ ግምገማ እየተጠበቀ መሆኑን ገልጸዋል።
ከአደጋው በኋላ በካሺማ ከተማ የሚገኘው «ኢዮን ሞል ኩማሞቶ» ውስጥ ከባድ ፍንዳታ ተከስቶ የሕንፃው ክፍል በመፍረሱ በርካታ ሰዎች በፍርስራሹ ስር መቀራቸው ተገልጿል።
እስካሁን ከ20 እስከ 30 የሚደርሱ ሰራተኞች የጠፉ ሲሆን፣ የእሳት አደጋ እና የነፍስ አድን ቡድኖች የማዳን ሥራ እያካሄዱ ነው። ፍንዳታው ከጋዝ መፍሰስ ጋር ሊያያዝ እንደሚችል ጥርጣሬ ቢኖርም፣ ባለሥልጣናት መንስኤውን እያጣሩ ነው።
በሌላ በኩል፣ በአካባቢው በሚገኝ የወረቀት ፋብሪካ ውስጥ የነበሩ በርካታ ሰራተኞች ያሉበት እስካሁን አልታወቀም።
በባቡር መስመሮች፣ በድልድዮች እና በመንገዶች ላይም ከፍተኛ ጉዳት ደርሷል፤ የባቡር አገልግሎት ተቋርጧል፣ አንዳንድ ባቡሮችም ከሐዲድ ወጥተዋል። በአካባቢው የአየር ማረፊያም ለጊዜው ተዘግቷል።
የኃይል አቅርቦት በአስር ሺዎች ቤቶች ተቋርጧል፤ ከ60 በላይ የተከታታይ ንዝረቶች በመመዝገባቸውም ተጨማሪ የመሬት መንሸራተት እና የሕንፃ መውደቅ አደጋ ስለሚኖር ህዝቡ ከተጎዱ ሕንፃዎች እንዲርቅ ጥሪ ቀርቧ
1 277
🔥 ☝️☝️☝️☝️☝️
"...እሳቶች ከተነሱ የማይጠፉ ፤ አውሎ ነፋስ አዘል ሆነው ብዙ ከተሞችን ያወድማሉ።''
⚡️ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት -5 ገጽ-29* ተፃፈ 21/01/2004ዓ.ም
1 277
በፈረንሳይ እና በስፔን የደረሰዉ ሰደድ እሳት ተባብሶ መቀጠሉ ተነገረ
በፈረንሳይ እና በስፔን የሚነደው የሰደድ እሳት ቃጠሎ አሁንም እየቀጠለ ይገኛል፡፡በፈረንሳይ እሳት አሁን ከቦርዶ ከተማ ዳርቻ 15 ኪ.ሜ ርቀት ላይ ብቻ ይገኛል።በጂሮንድ ክልል 220,000 የሚገመቱ ሰዎች አካባቢያቸዉን ለቀዉ ለመዉጣት ተገደዋል፣ 42,000 ሄክታር ያህል መሬት ሲቃጠል 240 ቤቶችም ወድመዋል።
በስፔን ከዋና ከተማዋ ማድሪድ በስተ ምዕራብ 50 ኪ.ሜ ርቀት ላይ የእሳት ቃጠሉለፐ እንደቀጠለ ይገኛል፡፡ ወደ 105,000 የሚጠጉ ሰዎች በሰደድ እሳቱ ተፈናቅለዋል፣ በማድሪድ፣ በአቪላ እና በቶሌዶ ክልሎች በተነሳው የእሳት ቃጠሎ 77,000 ሄክታር አካባቢ ተጎድቷል።እሳቱ በፍጥነት እንዲሰራጭ እና በከፍተኛ ሁኔታ እንዲቃጠል የሚያስችል ሞቃታማ እና ደረቅ የአየር ሁኔታ እየተፈጠረ ነው ሲሉ የአየር ንብረት ባለሙያዎች ተናግረዋል፡፡
1 277
ከሔዋን ጀምሮ በተሰጠው ሥነ ተፈጥሮና ፍርድ፣ ሴቶች በሐልዮ፣ በነቢብ፣ በገቢር በፍትወት ይጠመዳሉ። ኋላም በጋብቻ ለአንድ ወንድ ይኾናሉ። ድንግልናን ያጣሉ። በሕማም ይፀንሳሉ ፣ በሕማም ይወልዳሉ፣ ከ ፲፭ ዓመት በኋላ ተፈትሖ ማሕፀን አለባቸው። ቢወልዱም ባይወልዱም በየወሩ የወር ግዳጅ ከነሕመሙ አለባቸው። በድሮ ቋንቋ አደፍ ያያሉ ይባላል። በዛሬው ግን አበባ ተብሎአል። እንግዲኽ ይኽ ሁሉ በእመቤታችን የለም። እግዚአብሔር ከዚህ ሁሉ ጠብቋታል አድኗታል። ከመርገመ ሥጋ ከመርገመ ነፍስ ጠብቋታል። እላይ የዘረዘርነው ኹሉ በአምላክ ፍርድ የጸና ስለኾነ በሴቶች ላይ የማይለወጥ ያልተለወጠ ግዳጅ ነው። በእመቤታችን ግን ይኽ ሁሉ የለም። ለምን? ቢሉ ምክንያቱ መልአኩ " ቡርክት አንቲ እምአንስት" ብሎ እንደመሰከረ ከሴቶች ተለይታ የተባረከች ናትና ፣ እንከን ለሌለው ደስታ የተፈጠረች ናትና፣ ጸጋን ኹሉ የተሞላች ናትና ፣ እግዚአብሔር ከእርሷ ጋር ነውና፣ እናቱ ልትሆን፣ ማደሪያው ልትሆን ፣ መቅደሱ ዙፋኑ ልትኾን ቅድስተ ቅዱሳን አድርጎ ፈጥሮአታልና። ለምን? የሚል ጥያቄ የሚገባበት አይደለም። ሥልጣኑ ፣ ሥራው ገንዘቡ ነው። እግዚአብሔር ቅዱስ ነው ፣ ዙፋኑም ቅዱስ ነው።
" እግዚአብሔርሰ ይነብር ዲበ መንበሩ ቅዱስ።" "እግዚአብሔር በቅዱስ ዙፋኑ ላይ ይኖራል" ተብሎ ተጽፎአል። ( መዝ.፵፮:፰) እሱ ቅዱስ ነው እናቱም ቅድስት ናት።
ሊቀ ሊቃውንት አያሌው ታምሩ።
1 277
በደቡባዊ ምዕራብ ፈረንሳይ የተቀሰቀሰው የሰደድ እሳት በከፍተኛ ሁኔታ እየተስፋፋ መምጣቱን ተከትሎ ባለስልጣናት ነዋሪዎችን ከአካባቢው ማስለቀቅ መጀመራቸውን አስታወቁ። በተለይ ቦርዶ ከተማ አቅራቢያ የተጠናከረውን ሰደድ እሳቱን ለመቆጣጠር በሚደረገው ጥረት የሀገሪቱ ጦር ወደ አካባቢው መሰማራቱ ተሰምቷል። የእሳቱ ኃይል እየጨመረ መምጣቱን ተከትሎ በጭስ መታፈን የሚያስከትለውን አደጋ ለመቋቋም የሀገሪቱ መንግስት ከ 1.5 ሚሊዮን በላይ የፊት ጭንብሎች ወደ አካባቢው መላኩ ተገልጿል።
የጅሮንድ ክልል አስተዳደር የቦርዶ አውሮፕላን ማደሪያ የሚገኝበትን ጨምሮ በሦስት የምዕራባዊ የከተማ ዳርቻዎች የሚኖሩ ነዋሪዎች በአስቸኳይ አካባቢውን ለቀው እንዲወጡ አዟል። በዚህም ምክንያት ቀደም ሲል በአካባቢው ከተፈናቀሉት 141,000 ሰዎች በተጨማሪ፣ በአጠቃላይ በፈረንሳይ እና በስፔን ከ200,000 በላይ ሰዎች ከቀያቸው ለመፈናቀል ተገደዋል ነው የተባለው።
የፈረንሳይ ጠቅላይ ሚኒስትር ሴባስቲያን ለኮርኑ እንዳሉት «የእሳቱ ኃይል እጅግ ከመበርታቱ የተነሳ የራሱን የንፋስ አቅጣጫ እስከመፍጠር ደርሷል»። ዋናው ትኩረታችን «የሰዎችን ሕይወት መታደግ» ነው ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፣ ነዋሪዎች የተሰጣቸውን የደህንነትና የመልቀቂያ ትዕዛዝ ያለማወላወል እንዲተገብሩም አሳስበዋል።
በአደጋው በርካታ የእሳት አደጋ ሠራተኞች ለጉዳት የተዳረጉ ቢሆንም እስካሁን የሰው ሕይወት ማለፉ አልተረጋገጠም። አደጋው በከፍተኛ ሙቀትና በአየር ንብረት ለውጥ ምክንያት የተከሰተ መሆኑን የገለጠው የፈረንሳይ ዜና አገልግሎት በድንገተኛነቱና በፍጥነቱ ለአሳት አደጋ ተከላዮች ብርቱ ፈተና መሆኑን አመልክቷል።
1 277
Repost from አልፋና ዖሜጋ የንጽጽርና የትምህርት መገኛ አደባባይ (አዖተ)
በትግራይ ክልል የተከሰተ የከፋ የአየር ሁኔታ የሕይወትና የንብረት ጉዳት አድረሰ
በማዕከላዊ ዞን ቀይሕ ተኽሊ እና አሕፈሮም ወረዳዎች በጣለው ከባድ በረዶ አዘል ዝናብ የአንድ ሕፃን ሕይወት ያለፈ ሲሆን በአዝእርት፣ በመስኖ እና በአትክልት ላይ ከፍተኛ ጉዳት ወድቋል።
በሌላ በኩል ደግሞ የክልሉ እርሻና ተፈጥሮ ጥበቃ ቢሮ እንደገለጸው፣ በክልሉ ከሚገኙ 600 ቀበሌዎች ውስጥ 176 ቀበሌዎች እስካሁን ምንም ዓይነት የክረምት ዝናብ አላገኙም።
በአንዳንድ አካባቢዎች የጣለው ከመጠን ያለፈ ዝናብ ጉዳት እያደረሰ ባለበት ሁኔታ፣ በሌሎች አካባቢዎች ያለው የዝናብ እጥረት በእርሻና በምርት ላይ ከፍተኛ ስጋት ደቅኗል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
1 277
+2
አሳዛኝ መረጃ!
አገዛዙ በመካነሰላም አባይ ድልድይ አከባቢ በምትገኘው ቅድስት አርሴማ ገዳም ላይ በፈፀመው ዘግናኝ የድሮን ጥቃት በርካታ መናኒያን ተገደሉ!
የብልፅግናው አገዛዝ በመካነሰላም አባይ ድልድይ አከባቢ በምትገኘው ቅድስት አርሴማ ገዳም ላይ ዛሬ ሐምሌ 15/2018 ዓ/ም ማርፈጃውን በፈፀመው የድሮን ጥቃት በርካታ የገዳሙ መነኮሳት ሕይወታቸው ማለፉን መረብ ሚዲያ ለማረጋገጥ ችሏል።
በርካታ ደናግላን መነኮሳትም ለከባድ ጉዳት ተዳርገዋል፡ የገዳሙ ንብረቶችም ወድመዋል።
1 277
📌 የታዘዙ የቅጣት ዓይነቶች ከዚህ በፊት በመልእክቶቹም የተጠቀሱ ቢሆንም ዛሬም ደግሜ ላነሳቸው ግድ ይለኛል፡፡
በ አገራችን ----- እጅግ ከባድ ቋጥኝንና ሕንጻን ነቅሎ የሚወስድ አውሎ ነፋስ ፤ከባድ የመሬት ነውጥና እሳተ ገሞራ ፤
👉ከባድ ርሀብና ችጋር ፤
ተሰምተው የማያውቁ እንደ ሰደድ እሳት የሚዘምቱ ገዳይ በሽታዎች፤
ጎርፍ ፤ የርስ በእርስ መተላለቅ ፤ከባድ በረዶ ፤ የዘር ፍጅት
፤ከባድ የገንዘብ ቀውስ-----
➕ ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን ኢትዮጵያ የዓለሙ ገዢ መልእክት 8ገጽ 47
በቀን 21/4/2011 ዓ፡ም የተጻፈ፡፡
1 277
Repost from ራዕይ ዮሐንስ 20 የንፅፅር ቻናል
+2
የዝናብ እጥረት በጃንአሞራ‼️
በጃናሞራ ወረዳ በድርቅ ምክንያት ከ19 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት ሳይዘራ ቀረ፤ ከ96 ሺህ በላይ ዜጎች ለችግር ተጋልጠዋል‼️
በአማራ ክልል ሰሜን ጎንደር ዞን በሚገኘው የጃናሞራ ወረዳ፣ በዘንድሮው የመኸር እርሻ ወቅት ባጋጠመው ከፍተኛ የዝናብ እጥረት ምክንያት ከባድ ድርቅ እየገጠመው መሆኑን የወረዳው ኮሙኒኬሽን ጽሕፈት ቤት አስታውቋል።
በወረዳው ከሚገኙት 36 የገጠር ቀበሌዎች መካከል በ19ኙ ቀበሌዎች እስከ አሁን ድረስ ምንም ዓይነት ዝናብ ባለመጣሉ፣ አርሶ አደሩ ማሳውን አርሶና አዘጋጅቶ ቢጠብቅም ዘሩን መሬት ላይ ማሳረፍ አልቻለም።የወረዳው ግብርና ጽሕፈት ቤት ምክትል ኃላፊ አቶ መልስ አደላድለው እንደገለጹት፣ ዝናብ ባለመጣሉ ምክንያት ከ19 ሺህ 4 መቶ ሄክታር በላይ መሬት ሳይዘራ "ጦሙን አድሯል"።
በዚህም ሳቢያ ከ96 ሺህ በላይ የአካባቢው ዜጎች ለከፍተኛ ችግር እንደሚጋለጡ ኃላፊው አሳስበዋል። በሌሎች የቀሩት የወረዳው ቀበሌዎችም ቢሆን ዝናቡ እጅግ ዘግይቶ መዝነቡን ጠቁመዋል።በድርቁ ክፉኛ ከተጎዱት አካባቢዎች መካከል በተለይ የበየዳ እና የሰሃላ ሰየምት ወረዳዎችን የሚያዋስኑት ቀበሌዎች በከፍተኛ ሁኔታ ተጠቂ መሆናቸው ታውቋል።የዋሰል ቀበሌ ነዋሪ የሆኑ አርሶ አደሮች በሰጡት አስተያየት፣ በአሁኑ ወቅት አካባቢው አረንጓዴ ለብሶ እሸት የሚበላበትና ተራሮች በጉም የሚሸፈኑበት ወቅት ቢሆንም፣ በተቃራኒው ግን እጅግ ከባድ ሙቀትና ፀሐይ ነግሦ አካባቢው በድርቅ መጎዳቱን ይናገራሉ።
ዝናብ ይጥላል በሚል ተስፋ በደረቁ መሬት ላይ የተዘራው ዘርም ሳይበቅል የውኃ ሽታ ሆኖ ቀርቷል።
1 277
📌 እኛ ከእንግዲህ ድርሻችንን ተወጥተናል።
እግዚአብሔር ያዘዘንን ገልጸናል። አድርሰናል።
ግዳጃችንን ተወጥተናል።
እንግዲህ ወገኖቼ እዳ የለብንም።
የፍቅር እዳ የለብንም።
የታዘዝንበትም እዳ የለብንም።
ሁሉንም ነገር በጊዜውና በሰአቱ በዚህ ክፉ ሰአት ውስጥ ሁሉ
ሊደርስ ወደ ሚገባው ሁሉ አድርሰናል ማለት ነው።
ከእንግዲህ በየበዓታችን ሆነን መጪውን የእግዚአብሔርን እርምጃ ማየት ብቻነው።
ኖህ በመርከቡ አይደል! የተካተተው?
አዎ እኛም በእምነት መርከባችን ተካተን ውጤቱን መከታተል ብቻ ነው።
መቼም ለምታስተውሉ አለም ወዴት እየሄደች እንደሆነ ግልጽ እያየን ስለሆነ
ምንም ድብቅም ስለሌለ።
ከእንግዲህ ለአዳም ዘር አስተዋሽ አያስፈልገውም ።ፍርዱ ሁሉ ከደጁ ነው።
የቁጣው እሳት ሲያጠልመው ሲለበልበው ሲያቀልጠው ያኔ የእግዚአብሔር ፍርድ ነውና ይገበዋል።በ ፍርዱም ይካተታል።
እኛ ደግሞ እግዚአብሔርንን እያመሰገንን በየበዓታችን መቀመጥ ነው።
እኛ የኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን ቤተሰቦች
ልንበረታ ይገባል
ከነበረን የእምነት ጥንካሬ ልንላላ አይገባም።እውነትን ከተረዱ በኋላ ወደ ኃላላ በሚያፈገፍግ ነፍስ እኔ ደስ አልሰኝም አዝናለሁ ነው የሚለው ቸሩ መድኃኔዓለም ስለዚህ ይህንን ቃል እያስታወሳችሁ በጀመራችሁበት መንፈሳዊ ጥንካሬ ተመላለሱ።ምንም አይነት ፈተና ቢገጥማችሁ ምንም አይነት ችግር ቢታይ በእምነት እለፉት እንጂ ከእምነታችሁ አትጉደሉ።
⚡️ለአለም መንግሥታት እና ሕዝብ ይደርሱ ዘንድ በቀን 7/5/2016 ዓ,ም ከኢትዮጵያ የዓለም ብርሃናዊ መንሥት ከተጻፉት ደብዳቤች መካከል
በንባብ ከተላለፈው ክፍል 1 መግቢያ እና ማብራሪያ ላይ የተወሰደ።
1 277
አሜሪካ የኢራንን ድልድዮች ማጥቃት ጀመረች‼️
አሜሪካ የኢራንን ዋና ድልድዮች እንዲሁም የውሃ ማጣሪያ ተቋሟት ላይ ጥቃት በመፈፀም ጉዳት አድርሳለች።
1 277
በርካታ የአሜሪካ ወታደሮች ተጎዱ‼️
ኢራን ጆርዳን በሚገኘው የአሜሪካ የጦር ቤዝ ላይ በፈፀመችው የሚሳኤል ጥቃት በርካታ ወታደሮች መጎዳታቸውን የአሜሪካ ባለስልጣናት እንዳረጋገጡለት ነገር ግን ቁጥሮቹን ለመግለፅ ፈቃደኛ እንዳልሆኑ CBS ዘግቧል።
አሜሪካ እና ኢራን ከባድ የተኩስ ልውውጥ ውስጥ ሲሆኑ አሜሪካ የኢራንን መሰረተ ልማት እና ድልድዮችን እያጠቃች ትገኛለች።
የኢራን ዋና የኤሌክትሪክ መስመር ጉዳት ያስተናገደ ሲሆን የቴህራን ዜጎች ኤሌክትሪክ ቆጥበው እንዲጠቀሙ ኢራን ለዜጎቿ መልዕክት አስተላልፋለች።
ኢራን በባህሬን እና ኩዬት የሚሳኤል ጥቃቷን የቀጠለች ሲሆን ኩዬት ለኢራን ጥቃት ምላሽ ለመስጠት ማቀዷን በመግለፅ ለዜጎቿ የጥንቃቄ መልዕክት አስተላልፋለች።
1 277
viral | በቻይና ፔንግሹዊ ግዛት የተከሰተ የመሬት መንሸራተት ቤቶችን በማፈራረስ ነዋሪዎችን ፍርስራሽ ውስጥ ቀበረ
በመሬት መንሸራተቱ ሳቢያ ነዋሪዎች በፍርስራሾች ሥር ተቀብረው መቅረታቸውን የሚገልጹ መረጃዎችን ተከትሎ የድንገተኛ አደጋ የነፍስ አድን ቡድኖች በአካባቢው መሰማራታቸው ተዘግቧል።
1 277
Repost from አልፋና ዖሜጋ የንጽጽርና የትምህርት መገኛ አደባባይ (አዖተ)
🔥🔥🔥የአምኃ ኢየሱስ ገብረ ዮሐንስ ቁጥር ፯ መደበኛ ትምህርታዊ የጽሑፍ መልእክት እና አዋጅ ነው። 👉 ክፍል 1
1 277
🔥🔥🔥የአምኃ ኢየሱስ ገብረ ዮሐንስ ቁጥር ፯ መደበኛ ትምህርታዊ የጽሑፍ መልእክት እና አዋጅ ነው።
ሐምሌ ፯ ፪ሺ ፲፰ ዓ ም ዕለተ ማክሰኞ።
በPDF ለማንበብ 👇👇👇
1 277
“ሲነቅፉአችሁና ሲያሳድዱአችሁ በእኔም ምክንያት ክፉውን ሁሉ በውሸት ሲናገሩባችሁ ብፁዓን ናችሁ።
12: ዋጋችሁ በሰማያት ታላቅ ነውና ደስ ይበላችሁ፥ ሐሴትም አድርጉ፤ ከእናንተ በፊት የነበሩትን ነቢያትን እንዲሁ አሳድደዋቸዋልና።ማቴ 5፥11-12
