1 262
المشتركون
+124 ساعات
+87 أيام
+3630 أيام
أرشيف المشاركات
1 262
📌 እንግዲህ ስማ የአዳም ዘር!
ዛሬ ከጸባኦት በወጣው ውሳኔ መሠረት ከአብርሃሙ ሥላሴ በተሰጠ ጥብቅ ውሳኔና ትዕዛዝ መሠረት እኛም ይቺን ውሳኔና ትዕዛዝ እንዲች ብለን የማናልፋት እናንተም ቀይ መስመር እንደምትሉት የሆነ ነው ውሳኔና ትዕዛዙን መሠረት አድርገን ይኸው እንገልጽላቹሃለን ዓለም ሰምታም አይታም ወደ ማታውቀው ፍጹም መጠረግ በእሳት ወላፈን መበላት መውደም መክሰም ትሄድ ዘንድ የመጨረሻው መለከት ተነፍቷል።
⚡️ በኢትዮጵያ የዓለም ብርሃናዊ መንግሥት በቀን 21/10/2017 ዓ:ም ከሰተጠው
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን
ትምህርት አዘል መግለጫ
እና
የመጨረሻው መጨረሻ
የውሳኔ እና የፍርድ ቃል ከሚለው መግለጫ ላይ የተወሰደ።
1 262
በቬንዙዌላው አደጋ የሟቾች ብዛት 235፣ የተጎጂዎች 4,300 ደረሰ
በቬንዙዌላ ዋና ከተማ ካራካስ አቅራቢያ በደረሱ ሁለት ተከታታይ ከባድ የመሬት መንቀጥቀጦች የሞቱ ሰዎች ቁጭር 235 ሲደርስ፣ 4,300 ተጎድተዋል።
በካራከስ እና በአቅራቢያው በሚገኛው የባሕር ዳርቻ ከተማ ላጉኣራ በሕንፃዎች ፍርስራሽ የተቀበሩ ሰዎች ለእርዳታ ሲጣሩ ይሰማሉ።
በአደጋው በርካታ ሰዎች ሞተዋል ተብሎ ሲገመት፤ ሌሎች ደግሞ ቤት አልባ ወይንም በተጎዱ እና ለአደጋ በተጋለጡ ሕንፃዎች ውስጥ ከመቆየት ይልቅ መንገድ ላይ መሆንን መርጠዋል።
አደጋው የደረሰው ዕረቡ ዕለት ቬንዙዌላ ብሔራዊ በዓል እያከበረች በነበረችበት ጊዜ ነው። ይህም ማለት አደጋው የደረሰው ከወትሮ በተለየ በርካታ ሰዎች ቤት ውስጥ እያሉ ነበር።
የቬንዙዌላ ብሔራዊ ምክር ቤት ፕሬዝዳንት ሆርሄ ሮድሪጉዝ የአገሪቱ ጊዜያዊ ፕሬዝዳንት ዴልሲ ሮድሪጌዝ አስቸኳይ ጊዜ ካወጁ በኋላ የሟቾች ቁጥር መጨመሩን አስታውቀዋል።
1 262
አውሮፓ በሙቀት እየተቃጠለች ነው!
በአውሮፓ ምድር ላይ ከባድና አለቅጥ የናረ የሙቀት ማዕበል መከሰቱን ተከትሎ የሰዎች ሕይወት እያለፈ፣ ትምህርት ቤቶች እየተዘጉና መደበኛ የዕለት ተዕለት እንቅስቃሴዎች ሙሉ በሙሉ እየተስተጓጎሉ ይገኛሉ።
ፈረንሳይ፣ ጣሊያን፣ ስፔንና ጀርመንን ጨምሮ በበርካታ አገራት ሙቀቱ የከፋ ጉዳት እያደረሰ ሲሆን፤ በጀርመን የሙቀቱ መጠን 38 ዲግሪ ሴልሲየስ ደርሷል።
ይህ ከፍተኛ ሙቀት የኤሌክትሪክ ኃይል ማስተላለፊያዎችን፣ አስፋልቶችንና የሕንፃ ግድግዳዎችን ጭምር እያቀለጠ ሲሆን፣ የባቡር ትራንስፖርት ድርጅቶችም ተጓዦች ጉዟቸውን እንዲሰርዙና የትኬት ገንዘባቸውን እንዲመልሱ እያደረጉ ነው።
ከ300 ሚሊዮን በላይ የሚሆነው የአውሮፓ ሕዝብ በዚህ አስከፊ ሙቀት ውስጥ እየተሰቃየ ይገኛል።
1 262
በቬንዙዌላ የመሬት መንቀጥቀጥ የሟቾች ቁጥር 164 ደረሰ
በቬንዙዌላ መዲና ካራካስ እና ሳን ፌሊፔ አቅራቢያ ረቡዕ ዕለት የተከሰቱ የ7.2 እና 7.5 ማግኒትዩድ ከፍተኛ የመሬት መንቀጥቀጦች በሀገሪቱ ላይ ከባድ ውድመት አስከትለዋል።
በደረሰው አደጋ የሟቾች ቁጥር 164 የደረሰ ሲሆን፣ ቢያንስ 971 ሰዎች ደግሞ ከባድና ቀላል የአካል ጉዳት ደርሶባቸዋል።
1 262
+1
በቬንዝዌላ በሪክተር ስኬል 7.2 እና 7.5 የተመዘገበ የመሬት መንቀጥቀጥ ተከሰተ‼️
በቬኔዝዌላ ዋና ከተማ ካራካስ በ39 ሰከንዶች ልዩነት ብቻ የተመዘገቡ 7.2 እና 7.5 በሪክተር ስኬል የነበራቸው ሁለት ኃይለኛ የመሬት መንቀጥቀጦች ከባድ ጉዳት መድረሱ ተገልጿል።
በሀገሪቱ የአደጋ ጊዜ አዋጅ አውጃለች። እስካሁን ይፋ በተደረገው የ32 ሰዎች ህይወት ማለፉ ሲገለጽ 700 ሰዎች ላይ ጉዳት መድረሱን የሀገሪቱ ፕረዚዳንት ዴልሲ ሮድሪጌዝ አስታውቀዋል።
በአደጋው ሳቢያ የማይኬቲያ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ላይ መዋቅራዊ ጉዳት በመድረሱ ለአገልግሎት መስጠት ሲያቆም በረራዎችም ተሰርዘዋል።
1 262
በአህጉረ አውሮፓ የተከሰተው ከባድ የሙቀት ማዕበል ቢያንስ 18 ሰዎችን ለሞት መዳረጉ ተሰምቷል። ፈረንሳይ፣ ስፔን፣ ብሪታንያ እና ጣሊያንን ጨምሮ በርካታ ሀገራትን ያጠቃው ይህ ከባድ ሙቀት፣ በብዙ ከተሞች ከዚህ ቀደም ያልተሰስተዋለ ከፍተኛ የሙቀት መጠን አስመዝግቧል።
በፈረንሳይ ብቻ 18 ሰዎች ሕይወታቸውን ያጡ ሲሆን፣ ከእነዚህም መካከል በደቡብ ምስራቅ የሀገሪቱ ክፍል በሚገኝ አካባቢ በሞቃት መኪና ውስጥ የነበሩ የ2 እና የ4 ዓመት ሕፃናት ይገኙበታል። የአደጋ ጊዜ ምላሽ ሰጪ ቡድኖች ሕፃናቱን ለማዳን ጥረት ቢያደርጉም ሕይወታቸውን ማትረፍ እንዳልቻሉ ሮይተርስ በዘገባው አመላክቷል።
በተጨማሪም በቦርዶ ክልል ከ80 እስከ 95 ዓመት ዕድሜ ያላቸው ሦስት አዛውንቶች በሙቀቱ ሳቢያ በተከሰቱ የጤና ችግሮች ምክንያት መሞታቸው ታውቋል። ሰዎች ከሙቀቱ ለማምለጥ ወደ ወንዞችና የመዋኛ ቦታዎች በመሄዳቸውም የ13 ሰዎች ሕይወት በሞትና በመስጠም አደጋ ማለፉም ተገልጿል።
የሙቀት ማዕበሉ በበርካታ ከተሞች አዳዲስ የሙቀት ክብረ ወሰኖችን አስመዝግቧል፤ በዚህም፣ በፈረንሳይ የወይን ምርት ማዕከል በሆነችው ቦርዶ፣ የሙቀት መጠኑ 41.9 ዲግሪ ሴልሺየስ ደርሷል። በዚያው በፈረንሳይ ፖይቲየርስ፣ 41.2 ዲግሪ ሴልሺየስ ተመዝግቧል። በስፔን ሰሜናዊ ከተማ ሳን ሴባስቲያን፣ የሙቀት መጠኑ 40 ዲግሪ ሴልሺየስ ደርሷል።
የብሪታንያ የአየር ትንቢያ ተቋም በዚህ ሳምንት የሰኔ ወር የሙቀት ክብረ ወሰን ሊሰበር እንደሚችል ያስጠነቀቀ ሲሆን፣ በአንዳንድ አካባቢዎች የሙቀት መጠኑ እስከ 39 ዲግሪ ሴልሺየስ ሊደርስ እንደሚችል አመልክቷል። ጣሊያን በበኩሏ ለ12 ከተሞች ከፍተኛው የአደጋ ደረጃ የሆነው የቀይ የሙቀት ማስጠንቀቂያ ታውጇል።
1 262
በአህጉረ አውሮፓ የተከሰተው ከባድ የሙቀት ማዕበል ቢያንስ 18 ሰዎችን ለሞት መዳረጉ ተሰምቷል። ፈረንሳይ፣ ስፔን፣ ብሪታንያ እና ጣሊያንን ጨምሮ በርካታ ሀገራትን ያጠቃው ይህ ከባድ ሙቀት፣ በብዙ ከተሞች ከዚህ ቀደም ያልተሰስተዋለ ከፍተኛ የሙቀት መጠን አስመዝግቧል።
በፈረንሳይ ብቻ 18 ሰዎች ሕይወታቸውን ያጡ ሲሆን፣ ከእነዚህም መካከል በደቡብ ምስራቅ የሀገሪቱ ክፍል በሚገኝ አካባቢ በሞቃት መኪና ውስጥ የነበሩ የ2 እና የ4 ዓመት ሕፃናት ይገኙበታል። የአደጋ ጊዜ ምላሽ ሰጪ ቡድኖች ሕፃናቱን ለማዳን ጥረት ቢያደርጉም ሕይወታቸውን ማትረፍ እንዳልቻሉ ሮይተርስ በዘገባው አመላክቷል።
በተጨማሪም በቦርዶ ክልል ከ80 እስከ 95 ዓመት ዕድሜ ያላቸው ሦስት አዛውንቶች በሙቀቱ ሳቢያ በተከሰቱ የጤና ችግሮች ምክንያት መሞታቸው ታውቋል። ሰዎች ከሙቀቱ ለማምለጥ ወደ ወንዞችና የመዋኛ ቦታዎች በመሄዳቸውም የ13 ሰዎች ሕይወት በሞትና በመስጠም አደጋ ማለፉም ተገልጿል።
የሙቀት ማዕበሉ በበርካታ ከተሞች አዳዲስ የሙቀት ክብረ ወሰኖችን አስመዝግቧል፤ በዚህም፣ በፈረንሳይ የወይን ምርት ማዕከል በሆነችው ቦርዶ፣ የሙቀት መጠኑ 41.9 ዲግሪ ሴልሺየስ ደርሷል። በዚያው በፈረንሳይ ፖይቲየርስ፣ 41.2 ዲግሪ ሴልሺየስ ተመዝግቧል። በስፔን ሰሜናዊ ከተማ ሳን ሴባስቲያን፣ የሙቀት መጠኑ 40 ዲግሪ ሴልሺየስ ደርሷል።
የብሪታንያ የአየር ትንቢያ ተቋም በዚህ ሳምንት የሰኔ ወር የሙቀት ክብረ ወሰን ሊሰበር እንደሚችል ያስጠነቀቀ ሲሆን፣ በአንዳንድ አካባቢዎች የሙቀት መጠኑ እስከ 39 ዲግሪ ሴልሺየስ ሊደርስ እንደሚችል አመልክቷል። ጣሊያን በበኩሏ ለ12 ከተሞች ከፍተኛው የአደጋ ደረጃ የሆነው የቀይ የሙቀት ማስጠንቀቂያ ታውጇል።
1 262
ሚልክያስ 4 ፥ 1--6
1፤ እነሆ፥ እንደ ምድጃ እሳት የሚነድድ ቀን ይመጣል፤ ትዕቢተኞችና ኃጢአትን የሚሠሩ ሁሉ ገለባ ይሆናሉ፤ የሚመጣውም ቀን ያቃጥላቸዋል፥ ሥርንና ቅርንጫፍንም አይተውላቸውም፥ ይላል የሠራዊት ጌታ እግዚአብሔር።
2፤ ነገር ግን ስሜን ለምትፈሩት ለእናንተ የጽድቅ ፀሐይ ትወጣላችኋለች፥ ፈውስም በክንፎችዋ ውስጥ ይሆናል፤ እናንተም ትወጣላችሁ፥ እንደ ሰባም እምቦሳ ትፈነጫላችሁ።
3፤ በምሠራበት ቀን በደለኞች ከእግራችሁ ጫማ በታች አመድ ይሆናሉና እናንተ ትረግጡአቸዋላችሁ፥ ይላል የሠራዊት ጌታ እግዚአብሔር።
4፤ ለእስራኤል ሁሉ ሥርዓትንና ፍርድን አድርጌ በኮሬብ ያዘዝሁትን የባሪያዬን የሙሴን ሕግ አስቡ።
5፤ እነሆ፥ ታላቁና የሚያስፈራው የእግዚአብሔር ቀን ሳይመጣ ነቢዩን ኤልያስን እልክላችኋለሁ።
6፤ መጥቼም ምድርን በእርግማን እንዳልመታ እርሱ የአባቶችን ልብ ወደ ልጆች፥ የልጆችንም ልብ ወደ አባቶች ይመልሳል።
1 262
+1
በፈረንሳይ ከሚገኙት 96 ግዛቶች መካከል በ49ኙ ከፍተኛ የሙቀት ማዕበል ተመዘገበ
በፈረንሳይ ከሚገኙት 96 ክልሎች አርባ ዘጠኙ ቀይ ደረጃ ያለዉ ከባ የሙቀት ማስጠንቀቂያ ተሰጥቷል፡፡ ሀገሪቱ በከፍተኛ የሙቀት ማዕበል የተነሳ ዜጎቿ እንዲጠነቀቁ ማሳሰቢያ አዉጥታለች፡፡ ከ40 ዲግሪ ሴንቲ ግሬድ በላይ ከፍተኛ ሙቀት ሰኞ እለት በምዕራብ ፈረንሳይ ተመዝግቧል፡፡ በቦርዶ ውስጥ 43 ዲግሪ ሴንቲ ግሬድ መመዝገቡን የአየር ሁኔታ ትንበያ ባለሙያዎች አስታዉቀዋል፡፡
ሰኞ እለት 845 ትምህርት ቤቶች የተዘጉ ሲሆን 1,800 ተማሪዎች ቀድሞ ትምህርታቸውን እንዲጨርሱ መደረጉን የፈረንሳይ ትምህርት ሚኒስቴር አስታዉቋል።በደርዘን የሚቆጠሩ ሌሎች ክልሎች በብርቱካናማ ማስጠንቀቂያ ውስጥ ይገኛሉ፣ በአጠቃላይ 63 ሚሊዮን ሰዎች በመላው አገሪቱ በከባድ ሙቀት የተነሳ ተጎድተዋል።
በደቡብ ምዕራብ ጂሮንዴ ክልል፣ የአካባቢው ባለስልጣናት እሁድ እለት እንዳስታወቁት ከ80 እስከ 95 ዓመት የሆናቸው ሶስት ሰዎች በከባድ ሙቀት የተነሳ መሞታቸውን ገልጸዋል፡፡ የፈረንሳይ የጤና ሚኒስትር ስቴፋኒ ርስት ለፈረንሳዩ የህዝብ ብሮድካስቲንግ ቲቪ 1 እንደተናገሩት በሞቃታማ የአየር ጠባይ ወቅት " በርካታ ሰዎች ይሰቃያሉ" እናም ሰዎች ዘመዶቻቸውን እና ጎረቤቶቻቸውን "በቅርብ እንዲከታተሉ" ጥሪ አቅርበዋል።በምዕራቡ የባህር ዳርቻ በጣም ሞቃታማው የሙቀት መጠን ሲጠበቅ፣ በተቀረው የፈረንሳይ ክፍል ከ36 እስከ 40 ዲግሬ ሴንቲግሬድ የሚደርስ ከፍተኛ የሙቀት መጠን እንደሚኖር ይጠበቃል ሲል ሜትዮ ፈረንሳይ አስታዉቋል።
Via_dagu
1 262
የሕወሓት ታጣቂዎች በአፋር ክልል ድንገተኛ የሞርታር ጥቃት መፈፀማቸው ተሰማ
ጊዜያዊ አስተዳደሩን በማፍረስ በትግራይ መጠነ ሰፊ የግዳጅ ወታደራዊ አፈሳ እየፈጸመ የሚገኘው ሕወሓት፤ በትናንትናው እለት በአፋር ክልል ዞን 2 መጋሌ ወረዳ የሞርታር ጥቃት መፈጸሙን አንዳፍታ ሚዲያ ዘግቧል፡፡
ሆርን ፍሪኩዌንሲ የተሰኘ ድህረ ገጽ በበኩሉ፣ ጥቃቱ የተከፈተው የአፋር ጸጥታ ኃይሎች በሰፈሩበት አካባቢ እንደሆነ ዘግቧል፡፡
የጉዳቱ መጠን በግልጽ ባይታወቅም፣ ድርጊቱ በአካባቢው ማህበረሰቦች ዘንድ ድንጋጤ መፍጠሩን ነዋሪዎች ገልጸዋል።
1 262
በፍሎሪዳ በተቀሰቀሰ አስከፊ የሰደድ እሳት ሳቢያ ዋና ዋና አውራ ጎዳናዎች ተዘጉ
እሑድ ሰኔ 14 ቀን 2018 ዓ.ም የወጡ ዘገባዎች እንደሚያመለክቱት፤ በአሜሪካ ፍሎሪዳ ግዛት ማያሚ ከተማ በስተምዕራብ በተቀሰቀሰ አስከፊ የሰደድ እሳት ሳቢያ ወደ 90 ካሬ ኪሎ ሜትር የሚጠጋ መሬት ወድሟል።
በመብረቅ ጥቃት የተቀሰቀሰውና በግዛቱ ባለው ከፍተኛ ድርቅ የገነፈለው ይህ እሳት ጥቅጥቅ ያለ ጥቁር ጭስ በመፍጠሩ ዋና ዋና አውራ ጎዳናዎች እንዲዘጉ ተደርገዋል።
የነፍስ አድን ሠራተኞች እሳቱን ለመቆጣጠር በሄሊኮፕተሮች ውሃ ከመጣል ባለፈ፤ እሳቱ ወደ ሌላ ስፍራ እንዳይዛመት ሆን ብለው የቁጥቋጦዎችን መንገድ የማቃጠል (backfire) ስልትን እየተጠቀሙ ይገኛሉ።
ባለሥልጣናት የአየር ጥራት መበላሸቱን ተከትሎ በአካባቢው የሚኖሩ ዜጎች በቤታቸው ውስጥ እንዲቆዩ አሳስበዋል።
1 262
+1
በትግራይ ላዕላይ ፀለምቲ ወረዳ በደረሰ የጎርፍ አደጋ የ5 ሕፃናት ሕይወት አለፈ
በትግራይ ክልል ላዕላይ ፀለምቲ ወረዳ ሜዳ ጣቢያ ሰኔ 11 ቀን 2018 ዓ.ም ለረጅም ሰዓታት የጣለውን ከባድ ዝናብ ተከትሎ በተከሰተ የጎርፍ አደጋ የአምስት ሕፃናት ሕይወት ማለፉን የፀለምቲ ልማት ማኅበር አስታወቀ።
በአደጋው ከሕፃናቱ ሞት በተጨማሪ ከ20 በላይ ከብቶች፣ ከ50 በላይ ፍየሎችና 10 ያህል አህዮች በጎርፍ ተወስደው መሞታቸውን ማኅበሩ ገልጿል።
ማኅበሩ ባወጣው የሐዘን መግለጫ፥ ማኅበረሰቡ በጦርነት ጠባሳና በመንግሥት አገልግሎቶች እጥረት ውስጥ በሚገኝበት ወቅት ይህ ተጨማሪ የተፈጥሮ አደጋ መከሰቱ ልብ ሰባሪ መሆኑን ጠቅሶ ለተጎጂ ቤተሰቦች መጽናናትን ተመኝቷል።
መላው ሕዝብ ከጎርፍ አደጋ አስፈላጊውን ጥንቃቄ እንዲያደርግና የሚመለከታቸው አካላትም የቅድመ-ማስጠንቀቂያ መረጃዎችን በወቅቱ ለሕዝቡ እንዲያደርሱ ማኅበሩ ጥሪ አቅርቧል።
1 262
📌ትላንት በአንድ በሽታ በአንድ ይህ ኮቪድ በሚባል የታመሰውና ግራ የገባው ዓለም ኢኮኖሚውም በዚህ ምክንያት ደቆ ባዶ የሆነበት ዓለም ትርምስምሳቸውን ያወጣቸው አንድ በሽታ አንድ የአንድ በሽታ ገጽታ ነበር ፡፡
አሁን ደሞ ከበፊቱም የከፋ እጅግ የከፋ የበሽታዎች አይነት የተፈጥሮ አደጋዎች እጅግ በዝተው ከሰባት እጥፍ በላይም እየጨመሩ እንደሚመጡ ዛሬም ለሁሉም ሰሚና ጠፊ ሁሉ ትውልድ ግልፅ ሊሆንለት ይገባል፡፡
እግዚአብሔር ያለውን ሳይፈጽም የሚቆም ነገር የለም፡፡የተናገረው ሳይፈጸም ሳይከናወን የሚቀር ነገር የለም ፡፡ወረፋውን ነው የሚጠብቀው ወገኖቼ ምንም የሚቀር ነገር የለም፡፡
🇨🇬 በቀን 9 /12/2014 ዓ፡ም ከተለቀቀው፡፡
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን
የሉቃስ ወንጌል ትምህርት ክፍል ሁለት ላይ ለግንዛቤ ያህል የተወሰደ፡፡
1 262
በኮንጎ በኢቦላ የሟቾች ቁጥር 232 ደረሰ
በዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ በኢቦላ ወረርሽኝ ህይወታቸው ያለፈ ሰዎች ቁጥር 232 መድረሱን የሀገሪቱ መንግስትን ዋቢ በማድረግ አርቢሲ ዘግቧል።
እንደ መረጃው ገለጻ ከሆነ በሀገሪቱ ቫይረሱ በምርመራ የተገኘባቸው ሰዎች አጠቃላይ ቁጥር ወደ 896 አድጓል።
ሰኔ 11 ቀን በወጣው የቅርብ ጊዜ ሪፖርት መሠረት፣ በአንድ ቀን ውስጥ ብቻ 21 አዳዲስ የኢቦላ ታማሚዎች የተመዘገቡ ሲሆን የስድስት ሰዎች ህይወት ማለፉም ተረጋግጧል።
ወረርሽኙን ለመቆጣጠር ከፍተኛ ጥረት እየተደረገ ቢሆንም የበሽታው መባባስ ስጋት ፈጥሯል።
1 262
+3
◦●●●◦
በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ፨
~❴ ሰኔ ፲፪/12 ❵~
በዚህች ቀን፦
● የከበረ የመላእክት አለቃ #ቅዱስ_ሚካኤል በነገዱ ውስጥ በመላእክት ሁሉ ላይ በብዙ ክብር የተሾመበት መታሰቢያው የሚከበርበት በዓል እና #ቅዱስ_ባህራንን የረዳበት ዕለት ነው፡፡
● ዳግመኛም በዚህች ቀን #ቅድስት_አፎምያ የዕረፍቷ መታሰቢያ ሆነ፣
● የተባረከና የተመሰገነ የኢትዮጵያ ንጉሥ #ቅዱስ_ላሊበላ የዕረፍቱ መታሰቢያ ሆነ፣
● የእስክንድርያው ሊቀ ጳጳሳት #አባ_ዮስጦስ ዐረፈ፣
● ስልሳ ሰባተኛ የሆነው የእስክንድርያ ሊቀ ጳጳሳት #አባ_ቄርሎስ ዐረፈ።
1 262
Repost from ራዕይ ዮሐንስ 20 የንፅፅር ቻናል
የኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን ቤተሰባችን እጅግ ድንቅ ምስክርነት
ከቅድስት ሀገር ኢትዮጵያ = ቤሩት ሊባኖስ
በ 10/10/2018 ዓ.ም የተለቀቀ
1 262
Repost from ራዕይ ዮሐንስ 20 የንፅፅር ቻናል
የኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን ቤተሰባችን ወለተ ጻድቅ እና የአንድ መንፈሳዊ እህታችን እጅግ ድንቅ ምስክርነት
ከቅድስት ሀገር ኢትዮጵያ = ባህር ዳር
በ 10/10/2018 ዓ.ም የተለቀቀ
1 262
Repost from ራዕይ ዮሐንስ 20 የንፅፅር ቻናል
የኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን ቤተሰባችን ያልሆነው ወንድማችን (በመንፈስ ግን ከኛው ጋር ያለ)ገብረሥላሴ እጅግ ድንቅ ምስክርነት
ከቅድስት ሀገር ኢትዮጵያ = ቢቸና
በ 10/10/2018 ዓ.ም የተለቀቀ
1 262
Repost from ራዕይ ዮሐንስ 20 የንፅፅር ቻናል
የኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን ቤተሰባችን እጅግ ድንቅ ምስክርነት
ከቅድስት ሀገር ኢትዮጵያ
በ 10/10/2018 ዓ.ም የተለቀቀ
متاح الآن! بحث تيليغرام 2025 — أهم رؤى العام 
