880
Subscribers
No data24 hours
-27 days
-2630 days
Posts Archive
ሰላም እንዴት ናችሁ?
ጨፌ የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርት ቤት በ2016ዓም ተማሪዎችን በማታው መርሃ ግብር ተቀብሎ ለማስተማር በምዝገባ ላይ ይገኛል።
በዚህም መሠረት እሰጣለሁ እስካሁን የተመዘገቡ ተማሪዎች ትምህርት ለማስጀመር በቂ በመሆኑ ነገ ሐሙስ በቀን 01/02/2016ዓም ትምህርት መስጠት የምንጀምር መሆኑን እናሳውቃለን።
የትምህርት ሚኒስትሩ ብርሃኑ ነጋ (ፕ/ር) ካነሷቸው ነጥቦች፦
በተፈጥሮ ሳይንስ መስክ 200 ተማሪዎች ከ600 በላይ ውጤት አምጥተዋል፡፡
በማህበራዊ ሳይንስ መስክ 15 ተማሪዎች ብቻ ከ500 በላይ ውጤት አምጥተዋል፡፡
በተፈጥሮ ሳይንስ ከፍተኛው ውጤት 649 ሲሆን በአዲስ አበባ የልደታ ክሩዝ ትምህርት ቤት ተማሪ ናት፡፡
በማህበራዊ ሳይንስ ከፍተኛው ውጤት 533 ሲሆን የደብረ ማርቆስ አዳሪ ትምህርት ቤት ተማሪ ነው፡፡
በከተማ ደረጃ
አዲስ አበባ፣
ሀረሪ እና
ድሬዳዋ የተሻለ አፈጻጸም ያሳዩ ከተሞች ናቸው፡፡
👉ግማሽ ያህሉ ትምህርት ቤቶች ምንም ተማሪ አላሳለፉም
የዘንድሮውን የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ካስፈተኑ 3,106 ትምህርት ቤቶች መካከል 42.8 በመቶ የሚሆኑት አንድም ተማሪ አለማሳለፋቸውን የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ዛሬ በሰጡት መግለጫ ይፋ አድርገዋል።
Repost from Natnael Mekonnen
ትምህርት ሚኒስቴር በ2015 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ውጤት ዙሪያ መግለጫ ይሰጣል።
ሚኒስቴሩ ነገ መስከረም 28/2016 ዓ.ም ከቀኑ 5:30 ጀምሮ የ2015 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ፈተና ውጤትን በተመለከተ በሚኒስቴሩ የመሰብሰቢያ አዳራሽ ጋዜጣዊ መግለጫ ይሰጣል።
በሚኒስቴሩ የህዝብ ግንኙነትና ኮሚዩኒኬሽን ሥራ አስፈፃሚ አመለወርቅ ህዝቅኤል ተፈርሞ ለተለያዩ የመገናኛ ብዙሃን ደብዳቤ ተልኳል።
ቲክቫህ ዩኒቨርሲቲ (@tikvahuniversity) ለመገናኛ ብዙሃን የተላከውን ደብዳቤ ትክክለኛነት #አረጋግጧል።
በሐምሌ 2015 ዓ.ም መጨረሻ በሁለት ዙር የተሰጠውን የ2015 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ፈተና ከ 840 ሺህ በላይ ተፈታኞች መውሰዳቸው ይታወሳል።
More Tikvah Ethiopia University 👇
https://t.me/+RYD_4tbNBwRoKR2h
ከክልል የመጣችሁ እና ከ6ኛ ክፍል ወደ 7ኛ ክፍል ያለፋችሁ ተማሪዎች። መመዝገብ የሚቻለው የመግቢያ ፈተና ስትፈተኑ ብቻ ነው።
በዚህም መሰረት ባለፈው መስከረም 8 ቀን ፈተና ተሰጥቶ ነበር። አሁንም በተለያዬ ምክንያት ከዛ ወዲህ የመጣችሁ ተማሪዎች ካላችሁ ድጋሚ መፈተን እንድትችሉ በቀን 22/01/2016ዓም እስከ 4:00 ብቻ ትምህርት ቤት በአካል ቀርባችሁ እንድታሳውቁን(እንድትመዘገቡ)
Repost from Addis Ketema Education Office
ለሁሉም ትምህርት በቶች፡-
1) ከክልል መጥተው የ6ኛ ክፍል ፈተና ወስደው ውጤት ያልመጣለቸው ተማሪዎች ስም ዝርዝራቸውን እስከ ነገ 4፡00 በተመቻችሁ መንገድ እንድታደርሱን፡፡
2) ያልተፈተኑ 6ኛ ክፍል ተማርዎች በሁለተኛ ዙሪ ስለሚፈተኑ ስምዝርዝራቸውን እስከ ነገ 4፡00 በተመቻችሁ መንገድ እንድታደርሱን፡፡
#ማስታወቂያ
የድህረ ምረቃ ትምህርት መግቢያ ፈተና ምዝገባና ፈተና ጊዜ ተራዝሟል።
የድህረ ምረቃ ትምህርት መግቢያ ፈተና (Graduate Admission Test) ከመስከረም 28-30/2016 ዓ.ም ጀምሮ በመንግስት ዩኒቨርስቲዎች ይሰጣል።
በመሆኑም የድህረምረቃ ተማሪዎች ከመስከረም 21-25/2016 ዓ.ም በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ፖርታል https://portal.aau.edu.et በመጠቀም እንድትመዘገቡ እንገልጻለን ።
BEEKSIISA
BARNOOTA GALGALA ILAALCHISEE SIRNA BARNOOTA AFAAN OROMOON.
Manni barumsaa caffee sadarkaa 1ffaa bara barnootaa 2015 kutaa 3ffaa;5ffaa fi 7ffaa barsiisaa turuun ni beekama.Yaa ta'u malee bara barnootaa 2016 sadarkaa daree hundaa jechuun kutaa tokkoo jalqabee hanga kutaa 8ffaa barsiisuuf guyyaa galmee 15/01/2016 kan jalqabu ta'uu beektanii akka galmooftan manni barumsaa ergaa isaa ni dabarsa. Yeroo galmee sa'aatii 10:30 irraa jalqabee galmaa'uu kan dandeechan ta'uu isin beeksiisna.
Repost from N/a
ጨፌ አፀደ ህፃናት እና የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርት ቤት የተማሪዎች ደብተር ድጋፍ ተደረገለት።
ድጋፉን ያደረጉት የኢትዮጵያ አየር መንገድ ከአዲስ አበባ ከተማ አሰተዳደር ከንቲባ ፅ/ቤት እና የተማሪዎች ምገባ ኤጀንሲ ጋር በመተባበር ነው።
በድጋፍ ርክክቡ ወቅትም የአየር መንገድ አመራር አካላት, የከንቲባ ፅ/ቤት ተወካይ, የምገባ ኤጀንሲ ሃላፊዎች, የለሚ ኩራ ክ/ከተማ ት/ጽ/ቤት ሃላፊ, የወረዳ 03 ት/ጽ/ቤት ሃላፊ እና የጨፌ ትምህርት ቤት ርዕሳነ መምህራን እና መምህራን እንዲሁም የተማሪ ወላጅ ተወካዮችና ተማሪዎችም ተገኝተዋል።
ድጋፉን ያበረከቱ የአየር መንገድ ተወካዮችም ለ4000ተማሪዎች በድምሩ 48000 ደብተር ገቢ ተደርጓል። በተጨማሪም አየር መንገድ ለ970 የቅድመ መደበኛ ተማሪዎች የመጀመሪያ ሴሚስተር የምግብ ወጪን ለአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ምገባ ኤጀንሲ ገቢ እንዳደረጉም ገልፀዋል።
ቀን 04/01/2016ዓም
ለጨፌ ቅድመ መጂሪያ እና የመጀመሪያ መካከለኛ ትምህርት ቤት የተማሪ ወላጆች በሙሉ:-
የ2016ዓም የትምህርት ዘመን ትምህርት የሚጀምረው ሰኞ መሆኑ ይታወቃል። በዚህም መሠረት በመማር ማስተማር ዙሪያ አስቀድሞ ከሁሉም የትምህርት ባለሙያዎች ጋር መወያዬት አስፈላጊ ሆኖ ስለተገኘ ውይይት እየተደረገ ይገኛል።
ስለሆነም ነገ ቅዳሜ በ05/01/2016ዓም ጨፌ ትምህርት ቤት ውስጥ ጠዋት 2:30 ላይ ተገኝታችሁ የውይይቱ ተሳታፊ እንድትሆኑ ስንል እናሳስባለን።
ቀን 04/01/2016ዓ.ም
ሰላም እንዴት ሰነበታችሁ?
የ2016ዓም የትምህርት ዘመን ትምህርት የሚጀምረው ሰኞ በ07/01/2016ዓም መሆኑ ይታወቃል።
በዚህም መሠረት ትምህርት ቤታችን ጨፌ አፀደ ህፃናትና የመጀመሪያ መካከለኛ ትምህርት ቤት በዕለቱ ትምህርት የምንጀምር ይሆናል።
መጨናነቅ እንዳይፈጠር የትምህርት አጀማመር ሁኔታም እንደሚከተለው ይሆናል።
1. ሰኞ በ07/01/2016ዓም ከ5ኛ _ 8ኛ ክፍል ያሉ ተማሪዎች።
2. ማክሰኞ በ08/01/2016ዓም ኬጅ2,ኬጂ3, ኦ ክፍል እና ከ2ኛ እስከ 4ኛ ክፍል ያሉ ተማሪዎች
3. ረቡዕ በ09/01/2016ዓም ኬጂ1 እና 1ኛ ክፍል ተማሪዎች።
በዚህ ፕሮግራም መሰረት እንድትስተናገዱ ስንል እንገልፃለን።
ምናልባትም በምዝገባ ወቅት ስማችሁ የተደገመ ተማሪዎች 4ኛ፣6ኛ፣7ና8ኛ ክፍል አካባቢ ስላለ የሚስተካከል ይሆናል ነገር ግን የስም፣ የእድሜና ሌሎች ስህተቶች ካሉ ግን ነገ አርብ የመጨረሻ ምዝገባም ጭምር መሆኑን እናሳውቃለን።
