880
Subscribers
No data24 hours
-27 days
-2630 days
Posts Archive
Repost from Addis Ababa Education Bureau
በፈረንሳይ ፓሪስ የተከናወነውና በርካታ ሃገራት አባል በሆኑበት የዓለም የትምህርት ቤት ምገባ ጥምረት (School Meal Global Coalition) መድረክ ላይ ከተማችን አዲስ አበባ በሌሎች ሃገራት ልምድ የሚቀሰምባት ሆና በመመረጧ ትልቅ ኩራት ተሰምቶናል::
(ቀን 11/2/2016 ዓ.ም) የትምህርት ቤት ምገባ ፕሮግራም ተጠቃሚ የሆኑ የአንደኛ ደረጃ ተማሪዎች ያሳዩት አበረታች ውጤት ፣ በምግብ እጥረት ምክንያት ከትምህርት ገበታ የሚቀር ተማሪ ቁጥር መቀነስ ፣ በምገባ ፕሮግራሙ ለእናቶች የተፈጠረው የስራ እድል ፣ ፕሮግራሙ ከከተማ ግብርና ጋር ማጣመር በመቻሉ እና የምገባ ማዕከል አቋቁማ በዘላቂነት ፕሮግራሙን በመምራት አዲስ አበባ ላሳየችው አርአያ የሚሆን ስራ ሌሎች ሃገራት ልምድ ሊወስዱባት እንደሚገባ በመድረኩ ላይ ተነስቷል።በቀጣይም ፕሮግራሙ የትውልድ ግንባታ አካል አድርገን ይበልጥ እያጠናከርን የምንሄድ ይሆናል::
ከንቲባ አዳነች አቤቤ
መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያዎቹን ይጫኑ!
You Tube: https://www.youtube.com/watch?v=TWkBGoeYCNQ...
TikTok፡- tiktok.com/@aaeducationbureau
Telegram ፡ https://t.me/wwwAddisAbabaeducationbureau
Twitter ፡ https://twitter.com/aacaebc
Face book: https://www.facebook.com/aacityeducationcommunication
Blog: - http://www.aacaebc.wordpress.com/
Website: - aaceb.gov.et
Email;- aacaebc@gmail.com
Instagram: - https://www.instagram.com/aaeb/
ቀን 11/02/2016ዓም
ጨፌ አፀደ ህፃናት እና የመጀመሪያ መካከለኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ዛሬው ዕለት ከተማሪ ወላጆች ጋር ውይይት ተደረገ።
በውይይቱ ወቅት የተከናወኑ ተግባራት
የ2015ዓም የተማሪዎች ውጤት ትንተና, የ2016ዓም መሪ ዕቅድ, የትምህርት ቤቱን ራዕይ ተልዕኮና እሴት ማስፀደቅ, የተማሪዎችን መተዳደሪያ ደንብ ማስፀደቅ, የወተመህ 2015ዓም ሪፖርት, የወተመህ የ2016 ዕቅድ, በክረምት ወራት በወተመህ የተሰሩ ተግባራት, የወተመህ ፋይናንስ ሪፖርት እና የክፍል ወተመህ ማስመረጥ ስራ ተከናውኗል።
በዕለቱም የተማሪ ወላጆች መምህራን ርዕሳነ መምህራን የወመህ ተወካዮች እና የወረዳ 3 ትምህርት ፅ/ቤት ሃላፊ ተገኝተዋል።
ሁሉም በየዘርፋቸው ገንቢ ሃሳቦችን በማንሳት ወደፊት በጋራ በምንሰራቸው ስራዎች ላይ የጋራ መግባባት ላይ በመድረስ ፕሮግራሙን አጠናቀናል።
ጨፌ አፀደ ህፃናትና የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርት ቤት የ2015 ዓም የተማሪዎች ወጤት ትንተና እና የ2016ዓመ መሪ ዕቅድ ትውውቅ በቀን 09/02/2016ዓም ከጠቅላላ መምህራን እና ሰራተኞች ጋር አካሔደ።
ለጨፌ አፀደ ህፃናት እና የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርት ቤት የተማሪ ወላጆች በሙሉ በመጪው ዕሁድ ማለትም በቀን 11/02/2016ዓም ያለፈውን ዓመት የትምህርት ስራ ውጤት ገምግመን ለ2016ዓም ደግሞ በጋራ የምንሰራበትን ዕቅድ ዙሪያ ውይይት ስለምናደርግ በተጠቀሰው ዕለት ከጠዋቱ 2:30 ጀምሮ በትምህርት ቤቱ አዳራሽ እንድትገኙ ስንል ጠርተንዎታል።
