880
Subscribers
No data24 hours
-27 days
-2630 days
Posts Archive
+9
በቀን 18/08/2024 የጨፌ ቅድመ መደበኛና አንደኛ ደረጃ ት/ቤት ከ6ኛ/7ኛ/8ኛክፍል አንደኛ የወጡ ተማሪዎች በኢትዮጵያአየር መንገድ ያደረጉት ጉብኝት ይህንን ።
Repost from N/a
ቀን 08/08/2016ዓም
በጨፌ ቅድመ አንደኛ እና የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርት ቤት ውስጥ ለ17 የሚሆኑ ተማሪዎች በጣም ውብ እና ማራኪ የሆነ የደብተር መያዣ ቦርሳ በእርዳታ ተሰጠ።
እርዳታውን የሰጡት አቶ አስናቀ እና ኒው ኢሊት ትምህርት ቤት የሚማር ተማሪ ልጃቸው ናቸው።
የቦርሳዎቹ ጠቅላላ ግምታዊ ዋጋም 34000ብር የሚገመት እንደሆነ ማወቅ ተችሏል።
ይህ ተግባርም ወደፊት በአቶ አስናቀ እና በሌሎችም ለጋሽ አካላት አማካኝነት ተጠናክሮ የሚቀጥልበትን ሁኔታ እያመቻቸን መቀጠል እንዳለብን የትምህርት ቤቱ ርዕሰ መምህር እና የማኔጅመንት አባላት ተስማምተዋል።
በመላው አለም እና ትምህርት ቤታችን ለምትገኙ የአስልምና እምነት ተከታዮች በሙሉ እንኳን ለ1445ኛው የኢድ አልፈጥር በዓል በሠላም አደረሳችሁ!
ኢድ ሙባረክ‼️
Hordoftoota amantaa Islaamaa Mana barumsaa keenyaa fi Addunyaa mara irratti argamtan baga Ayyaana Sooma hiikaa(Iid Al Faxirii) 1445 ffaan nagaan isin gahe!
Eid Mubaarak‼️
Repost from 𝙱𝚄𝙻𝙱𝚄𝙻𝙰 𝙽𝙴𝚆𝚂⏰
የዒድ አል ፊጥር በዓል ረቡዕ ይከበራል‼️
ዛሬ ጨረቃ ባለመታየቷ ነገ ረመዷን 30 ሆኖ ዒድ አል ፊጥር በዓል ደግሞ #እሮብ ሚያዝያ 2 እንደሚከበር ይፋ ተደርጓል ።
ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች በሙሉ ከወዲሁ እንኳን ለ1445ኛ የዒድ አል ፊጥር በዓል በሰላም አደረሳቹ ለማለት እንወዳለን ።
ኢድ ሙባረክ🙏🤩
@BBN_info
ቀን 24/07/2016
በጨፌ ትምህርት ቤት የታላቁን ህዳሴ ግድብ የተጀመረበትን 13ኛ ዓመት ክብረ በዓል ምክንያት በማድረግ የአካል ብቃት እንቅስቃሴ ተካሔደ።
መጋቢት 24/2016ዓም " በህብረት ችለናል" በሚል መሪ ቃል ዕለቱ ይታወሳል።
1.ዐረፍተ ነገር ሲዋቀር ሁለት ሐረጓችን በውስጡ ይይዛል።
2.የዐረፍተ ነገሩ ባለቤት ስማዊ ሐረግ ይባላል።
3.አንድ አንቀፅ ሁለት ዋና ዋና ሐሳቦችን ሊይዙ ይችላሉ።
4.አንቀፅ አነስተኛ የፅሑፍ ክፍል ነው።
5.ጠዋት ሲንገናኝ "እንደምን አመሻችሁ" በማለት ሰላምታ እንለዋወጣለን።
6.ጅብ
7.መፅሐፍ
8.ላም
9.እንደምን አደሩ?
10.ዐረፍተ ነገር
ሀ/የቤት እንሰሳት
ለ/የመማሪያ መሳሪያ
ሐ/የዱር እንስሳት
መ/ሁለት ሐረጓችን በዉስጡ ይይዛል
ሠ/ለአክብሮት የሚሰጥ ሰላምታ
11.ጫልቱ ሄደች።የዐረፍተ ነገሩ ባለቤት____ነዉ።
ሀ/ሄደ ለ/ጫልቱ ሐ/ሄደች መ/ሁሉም
12.ተማሪዎቹ ተጫወቱ።የዐረፍተ ነገሩ መቋጫ/ግስ/____ነው።
ሀ/ተጫወቱ ለ/ተማሪ ሐ/ተማሪዎች መ/ሁሉም
13.ዐረፍተ ነገር የሚመሰረተው ከ___ነው።
ሀ/ከቃላት ስብስብ ለ/ከሐረጋት ቅንጅት ሐ/ከአንቀፅ መ/ሀ እና ለ መልስ ነው
14.አንቀፅ ምንድን ነው?
ሀ/ከዐረፍተ ነገር ይመሠረታል ለ/አንድ ሀሳብ ብቻ ይይዛል
ሐ/አነስተኛ የፅሁፍ ክፍል ነው መ/ሁሉም መልስ ይሆናል
15.ከሰው ጋር ተላምዶ ቤት ውስጥ የምኖሩ እንስሳት__ይባላሉ።
ሀ/የዱር እንስሳት ለ/የዱር አውሬ ሐ/የቤት እንስሳት መ/መልስ አልተሰጠም
1.የ"ጠ" ሆሄ ባለ ሶስት እግር ፍደል ነው።
2.ከ"ጠ" ቀጥሎ የሚመጣው ፊደል የ"ጢ" ፊደል ነው።
3."ጫማ" የሚለው ቃል ከ"ጨ" የፊደል ዘር የተመሰረተ ነው።
4.በ"ሕ" ሆሄ "ሒሳብ" የሚለውን ቃል ሊንመሰርት እንችላለን።
5."ሖድ" የሚለው ቃል ከ"ሖ" ፊደል የተመሠረተ ነው።
6.ከሚከተሉት ውስጥ ከ"ጠ" የፊደል ዘሮች የተመሠረተው የቱ ነው?
ሀ/ጡት ለ/ጣሳ ሐ/ጥጥ መ/ሁሉም
7.ከሚከተሉት ውስጥ ከ"ጨ" የፊደል ዘሮች የተመሠረተው የቱ ነው?
ሀ/ሒሳብ ለ/ጨው ሐ/ጠላ መ/ሕዝብ
8.ከዚህ በታች ከተሰጡት ውስጥ በ"ሐ" የፊደል ዘሮች የተመሠረተው የቱ ነው?
ሀ/ጨወታ ለ/ጠመኔ ሐ/ጥጥ መ/ሔደ
9.እያንዳንዳቸው የ"ጠ" ፣ የ"ጨ" እና የ"ሐ" ሆሄያት ስንት ዝሪያ አላቸው?
ሀ/አስር ለ/ሰባት ሐ/ስድስት መ/ዜጠኝ
10.የ"ጠ" ፣ የ"ጨ" እና የ"ሐ" ሆሄያት ባለ ስንት እግር ሆሄያት ናቸው።
ሀ/ሶስት ለ/አምስት ሐ/ስምንት መ/ሁለት
እባካችሁ አንብባችሁ ሼር አድርጉት‼️
ከዛሬ ጀምሮ እስከ መጭው ማክሰኞ በአዲስ አበባ ከሚያጋጥመው ከፍተኛ የፀሀይ ጨረር የተነሳ ከቀኑ ከ5:00—10:00 ጥንቃቄ እንደሚያስፈልግ መረጃዎች ያመለክታሉ። መረጃው ዛሬ March 17/2024 አዲስ አበባ የፀሀዩ ሁኔታ የአልትራ ቫዮሌት ጨረር በከፍተኛ ሁኔታ እንደሚረጭ የሚያመለክት ሲሆን የነገውን ትኩረት ሰጥቶታል። አልትራ ቫዮሌት ጨረር በተለይ ቆዳና ስነ ተዋልዶ ላይ ጥንቃቄ ካልተደረገ ጎጂ ነው። መለኪያው 12 ከደረሰ ደሞ በጣም ከፍተኛ ደረጃ ላይ ነው። መረጃው እንደሚያመለክተው አራቱ ቀናት በተከታታይ 12 ነው። ባለሙያዎች እንደሚሉት መፍትሄው በጠራራ ሰዓት አንድም በቤት(በሱቅ) ውስጥ መቀመጥ፣ ለእንቅስቃሴ ጥላ እንደሚገባ ይመክራሉ።
11 is already extreme! Becareful family! Don't expose children to the sun .
12 is extremely high
ሰላም እንደምን አላችሁ
ከዚህ በታች ስማቸው የተዘረዘሩት የ6ኛ እና 8ኛ ክፍል የሚኒስትሪ ፈተና ተፈታኝ ተማሪዎች ፎቶ የሌላቸው ስለሆነ እስከ ነገ 06/07/2016ዓ.ም ድረስ እንዲያመጡ ትነግሯቸው ዘንድ ትብብራችሁን እየጠየቅን ይህ ካልሆነ ግን ት/ቤቱ ሀላፊነቱን የማይወስድ መሆኑን እነገልፃለን።
Repost from N/a
ቀን 04/07/2016ዓም
የልምድ ልውውጥ ተካሔደ
በጨፌ ቅድመ አንደኛ ; አንደኛ ደረጃ እና መካከለኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ውስጥ የልምድ ልውውጥ በዛሬው ዕለት ተካሔደ።
የልምድ ልውውጡን ያዘጋጁት የጨፌ ክላስተር አስተባባሪ እና ሱፐርቫይዘሮች ከወረዳ 03 ትምህርት ፅ/ቤት ጋር በመተባበር ነው።
በፕሮግራሙ ላይ በለሚ ኩራ ክ/ከተማ በሻሌ ክላስተር አስተባባሪ ሱፐርቫይዘር ሀይለስላሴ ደምሴ, የወረዳ 03 ት /ፅ/ቤት ሱፐርቫይዘር እና ባለሙያዎች; በወረዳ 03 ስር ያሉ የግል እና የመንግስት ትምህርት በቶች ርዕሳነ መምህራን እና ባለሙያዎች ተሳትፈዋል።
የተከናወኑ ተግባራት
_ የመማር ማስተማር ስራውን በክፍል ውስጥ በመግባት ምልከታ ተደርጓል።
_ ቤተ ሙከራ; ቤተ መፃህፍት, የትምህርት ማበልፀጊያ ማዕከል, የተማሪዎች ክሊኒክ, የምገባ አዳራሽ እና ምገባ ስርዓቱን ምልከታ ተደርጓል።
- የከተማ ግብርና እየተተገበረ ያለበትን ሁኔታም ምልከታ ተካሒዷል።
በመቀጠልም በመስክ ምልከታ በታዩት ጉዳዮች ዙሪያ ውይይት ተካሒዷል። በውይይቱ ላይም ወደፊት ተቀናጅተን በጋራ መስራት የምንችልባቸውን ገንቢ ሃሳቦች ተነስተዋል።
