en
Feedback
የአገልጋይ ብርሃኑ ገፅ

የአገልጋይ ብርሃኑ ገፅ

Open in Telegram

ይህ የአገልጋይ ብርሃኑ ገፅ ነው።ዓላማዬ የተለያዩ መፅሐፍ ቅዱሳዊ ትምህርቶችን ማካፈልና ማድረስ ሲሆን ምክሮችን፥አባባሎችን፥ፀሎቶችንና ትዝብቶቼን የማካፍልም ይሆናል።የሰራዊት ጌታ እግዚአብሔር ወደ ልቤ ያመጣውንና የተናገረኝንም እፅፋለሁ።ትውልዱን ወደ ኢየሱስ የሚያስጠጋውን የትኛውንም ነገር የምፅፍበት ገፄ ነው።በማንበብና ሼር በማድረግ ከአገልግሎቴ ጎን ይቁሙ።0984005562.

Show more
447
Subscribers
+224 hours
+87 days
+3030 days
Posts Archive
. ኢየሱስ ክርስቶስ ከሌለህ ፓስተር ታምራት ሃይሌ | Live 🕑-5:08Min◦💾-4.7MB ▷ @yedestaye_elilta ◁ ▷ @yedestaye_elilta△Join Us△

#የጴንጤዎች_ኢየሱስ 23-11-2013 የምህረት ዓመት 🗣 አገልጋይ ብርሃኑ ዘኢየሱስ 👉ጊዜውን በትክክል አላስታውስም።ግን በእድሜም በሃይማኖት እውቀት ገና ልጅ በነበርኩበት እንዲህ ሆነ።ከእናቴ ጋር ጎንደር ጃንተከል ፊት ለፊት በሚገኝ "አደባባይ ኢየሱስ ቤተክርስቲያን" በተባለ ጥንታዊ ቤተክርስቲያን በኩል እያለፍን ነበር።ለመሳለም በተጠጋን ጊዜ በቤተክርስቲያኑ በር በትልቁ የተፃፈው ፅሁፍ ጋር መፋጠጤ አልቀረም።እኔ ቤተክርስቲያኑን የማውቀው በልበ ብርሃን ምእመናን መጥሪያ "ባለ እግዚአብሔር" በሚል ነበር።ባለ እግዚአብሔር ያልነው "በዐለ እግዚአብሔር" የሚለውን ነበር።እናም ትልቁ ፅሁፍ "አደባባይ ኢየሱስ ቤተክርስቲያን" ይላል።እናም እኔ በልጅነት ስሜት ቁጣ ሞላብኝ።እንዴት ይሄን የኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን ኢየሱስ ቤተክርስቲያን ይሉታል ብዬ ተቆጣሁ።ምክንያቱም በልጅነት እኛ ምናውቀው "ኢየሱስ" የጴንጤዎች "እግዚአብሔር ወይም ክርስቶስ" የእኛ እንደሆነ ነው።ከጥቂት ዓመታት በኋላ ግን በዛው ቤተክርስቲያን በስብከት አገልጋይ ሆንኩ። 👉ኢየሱስ ስሙ እንደ ልብ በማይጠራበትና የጴንጤ ነው በተባልንበት ጊዜ እንኳን ሳይቀር ስሙን ደጋግሜ መስማቴ አልቀረም።የቄስ ትምህርት ቤት ገብቼ ንባብና የቃል ትምህርት ስማርም "መልክአ ኢየሱስ" ከሚባል ፀሎት ጋር መተዋወቄና በቃሌ ይዤ ማነብነቤ አልቀረም።በቤተክርስቲያኒቱ ትምህርት እየበሰልኩ ስመጣ የተለያዩ መፃሕፍትንም ሳነብ ምእመናንና ኢየሱስ እንጂ ቤተክርስቲያኒቱና ኢየሱስ ማይተዋወቁ እንግዶች አልሆኑብኝም። 👉የሆነ ሆኖ በቤተክርስቲያኒቱ ስኖር ስለ ጌታ ኢየሱስ ሲሰበክ፥ስለ እርሱ በኩራት ሲወራ መስማት መመኘቴ አልቀረም።ስሙን ደጋግሞ መጥራት ማያስጠረጠርበትንና እንደ ተሐድሶ ማያስቆጥርበትን ጊዜ እናፍቅ ነበር።እናም ሁሌ በጴንጤዎች እቀና ነበር። 👉ሁሌም ጴንጤዎች ተሰብስበው በነፃነት የሥጋ ለባሽን ሁሉ ፀሎት ወደሚሰማው ወደ ኢየሱስ ይፀልያሉ እንጂ የተሸመደደ ፀሎት፥የተፃፈ ንባብ የላቸውም።በቃልም ይሁን በሥራ የሚያደርጉትን ሁሉ በኢየሱስ ስም ያደርጋሉ።ወሬያቸው ስብከታቸው መዝሙራቸው ሁሉ ዙፋኑን ከበው እንደሚያገለግሉት ቅዱሳን መላእክት ኢየሱስ ኢየሱስ ማለት ብቻ ነው። 👉ስለ ቅዱሳን አባቶችና እናቶች ቢያወሩና ቢተርኩም ማሰሪያቸው ኢየሱስ የታረደው በግ ነበር። 👉ነቢያትን በነቢያትም ስም፤ሐዋርያትን በሐዋርያት ስም፤ፃድቃንን በፃድቃን ስም ቢቀበሉም እነርሱን የተቀበሏቸው ኢየሱስን ለመቀበል ቅድመ ሁኔታ ስለነበር ነው።የትኛውም ቅዱስና ፃድቅ ሰው ክርስቶስ ኢየሱስን እንዲጋርዱ አይፈቅዱም። 👉በሃይማኖት በጅምላ እንደማይዳን ኦርቶዶክስ ብታስተምርም የሚኖሩበት ጴንጤዎች ናቸው።እናም በግል ከጌታ ጋር ይገናኛሉ።ክብሩን ይጠሙታል።ከእንባ ጋር ፊቱን ይፈልጋሉ። 👉ሰብኬ ሰብኬ ፀልዬ ፀልዬ የነፍሴ ድርቀት ሲሰማኝ እንዲህ ብዬ መፀለዬን አስታውሳለሁ "ጌታ ሆይ አንዴ እንደ ጴንጤዎች ፍቅርህን ቀምሼ ላልቅስና ወደ ሃይማኖቴ መልሰኝ"።ፀሎቴ ከልቤ ናፍቆትና ጥማት ነበር። 👉በመጨረሻ ግን ጌታ ጴንጤ አላደረገኝም።ኦርቶዶክስነትንም አልሰጠኝም።የራሱ አደረገኝ።ራሱን ገለጠልኝ።ሞቶልኛልና ሊወርሰኝ ተገባው። 🙏ኢየሱስ የማልቀይርህ ሃይማኖቴ፤የማላፍርብህ ትምህርቴ ነህ።ብቻህን ንገስ።ክብርን ሁሉ ጠቅልለህ ውሰድ።አሜን አሜን። ❤️ኢየሱስ ክርስቶስ ከሌለው ሃይማኖት በራሱ ገዳይ ነው!!

“ነገር ግን ገና ኃጢአተኞች ሳለን ክርስቶስ ስለ እኛ ሞቶአልና እግዚአብሔር ለእኛ ያለውን የራሱን ፍቅር ያስረዳል።” — ሮሜ 5፥8

❤️የእለቱ መልእክት❤️ 15-11-2013 የምሕረት ዓመት #እየሄዳችሁ_ጠብቁት 🗣በብርሃኑ (ምሕረት የበዛለት) 👉አንድ ጓደኛ ነበረኝ።አብረን በመንገድ እየሄድን በየመሀሉ የሚያውቀው ሰው እየገጠመው ለሰላምታ ይቆማል።እናም እኔ ራቅ ብዬ ቆሜ እጠብቀው ነበር።በኋላ ግን በነገሩ መሰላቸት ስለጀመርኩ ቆሜ መጠበቄን ትቼ " #እየሄድኩ_መጠበቅ"ን መረጥኩ።ቆሜ ስጠብቀው በጣም የቆየ ይመስለኛል።እየሄድኩ ስጠብቀው ግን እየሮጠም ቢሆን ይደርስብኛል እኔም መጠበቄ አይታወቀኝም።ግን ለሕይወቴ አንድ ነገር ቀረልኝ፦ " #እየሄዱ_መጠበቅ"። 👉እግዚአብሔርን በጠየቃችሁት ጉዳይ ላይ እየሄዳችሁ ጠብቁት።እየሰራችሁ የፀሎታችሁን መልስ ጠብቁ።እያገላገላችሁ መልሱን ጠብቁ።ሳትቆሙ ጠብቁት። 👉እግዚአብሔር የሚሰራበት የራሱ ጊዜ አለው።ከጊዜው በፊት ምንም አያደርግም።ይሄ ጌታ የዘገየ የሚመስለን በእኛ ጊዜ ስላልመጣ ነው።ደግሞም በእኛ ጊዜ አይመጣም።ለዛ ነው ጌታ ኢየሱስ እናቱን ድንግል ማርያምን "ጊዜዬ ገና አልደረሰም" ሲላት የሰማነው።እርሱ እንዲሰራ በተጠየቀበት ሰአት አይሰራም።በእርሱ ጊዜ ነው ሥራውን የሚሰራው። 👉ስለዚህ እግዚአብሔርን እየሄዳችሁ ጠብቁት።ፀሎታችሁ እስኪመለስላችሁም ድረስ ምንም ነገር አታቁሙ።እናንተም አትቁሙ።እግዚአብሔርን ቆሜ እጠብቀዋለሁ የሚልን እንባቆምን ብትጠይቁት ""በፅናት እጠብቀዋለሁ" ማለቴ እንጂ ሳልንቀሳቀስ ሥራና አገልግሎት አቁሜ የጌታን መልስ እጠብቃለሁ ማለቴ አይደለም" ይላችኋል። 👉 #እየሄዳችሁ_ጠብቁት።። 📖“እግዚአብሔርን በመተማመን የሚጠባበቁ ግን ኃይላቸውን ያድሳሉ፤ እንደ ንስር በክንፍ ይወጣሉ፤ ይሮጣሉ፥ አይታክቱም፤ ይሄዳሉ፥ አይደክሙም።” — ኢሳይያስ 40፥31

❤️የእለቱ መልእክት❤️ 03-10-2013 የምሕረት ዓመት #ማንን_ላማክር? 🗣 በብርሃኑ ታምራት 👉ሕይወትን ቀላል እንዲሆን ከሚያደርጉልን ነገሮች ውስጥ ዋነኛው #ከትክክለኛው_ምንጭ_ትክክለኛ_ምክር_ማግኘት ነው።መካሪ ከተገኘ ሕይወት ቀላል ነው። 👉መስቀለኛ መንገድ ላይ ቆመን "የትኛውን መንገድ መርጠን ብንሄድ ካሰብንበት እንደርስ ይሆን?" ብለን ግራ የተጋባንበት ሁኔታ ብዙ ጊዜ ገጥሞናል።ወደፊትም ሊገጥመን ይችላል።እናም መንገድ የሚያሳዩንን አማካሪዎች መፈለጋችን አይቀሬ ነው። 👉ማንን ላማክር? ብለን ከጉዳያችን በላይ መካሪ ማግኘቱ አስጨናቂ ይሆንብናል።በመካሪ ፍለጋ ከምንጨነቅባቸው ምክንያቶች አንዱ "ምሥጢራችንን ይይዝልን ይሆን?" የሚለው ሲሆን ሁለተኛው ምክንያት ደግሞ ጉዳዩን አግዝፈን በማየት መፍትሄ እንደማናገኝበት ያሰብን ጊዜ ነው።አማካሪ የምንፈልግባቸው በጣም ብዙ ጉዳዮች ይኖራሉ።ከእነዚህም ውስጥ፦ መንፈሳዊ ሕይወት፤ትዳርና ልጅ አስተዳደግ፤ጭንቀትና ድብርት፤ንግድ፤ከሕግ ጋር የተያያዙ የተለያዩ ጉዳዮችን እንደ ምሳሌ ማንሳት እንችላለን። 👉በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ትክክለኛና ፀፀት የሌለበትን ውሳኔ ለመወሰን አማካሪ ያስፈልጋል።ይሄንም የሚያምን ሰው አስተዋይ ነው።ታዲያ ማንን እናማክር? 👉ከዚህ በታች የምዘረዝራቸውን ምንጮች እንደ አማካሪ ልንጠቀምባቸው እንችላለን፦ ፩፦ #ትክክለኛ_ሰዎችን፦ ምክርን የምንፈልግባቸው ጉዳዮች ምንድን ናቸው? #ምክር_የምንፈልግበት_ጉዳይ_ልናማክረው_የሚገባውን_ሰው_ይጠቁመናል።ለምሳሌ፦ በመንፈሳዊ ሕይወታችን ማደግና መለወጥ በምንፈልግበት ጊዜ ከሆነ አማካሪ የምንፈልገው፤ ሊያማክረን የሚገባው መንፈሳዊ ሰውና ምሥጢራችን እንደሚይዝልን ያመንበት አገልጋይ መሆን አለበት።የሕግ ጉዳይ ከሆነ ከዘርፉ ጋር በተገናኘ በቂ እውቀትና ልምድ ያለው ሰው መሆን አለበት።ንግድና ሌሎች ጉዳዮችም እንዲሁ ወደ ትክክለኛው የምክር ምንጭ የሚጠቁሙን ናቸው።ትክክለኛ አማካሪ ካላገኘን የተሳሳተ ውሳኔን እንወስናለን።ውሳኔያችንም ብዙ ዋጋ የሚያስከፍለን ሊሆን ይችላል።ለምሳሌ፦ አንድ ፍቅር የያዘው ወጣት አንድን ደብተራን ቢያማክር ምን ሊመክረው ይችላል? ግልፅ ነው።መስተፋቅር መፍትሄ እንደሆነ ነው ሊመክረውና ሊያሳምነው የሚችለው።አያችሁ #ትክክለኛን_አማካሪ_አለማግኘት_የተሳሳተ_ውሳኔ_እንድንወስን_ያደርገናል። 👉ትክክለኛ አማካሪ ባለማግኘት የተጎዱ ሁለት ሰዎችን ላስታውሳችሁ፦ 👉እህቱን አፍቅሮ የነበረው አምኖንና የሕዝቡን ቁጣ የቀሰቀሰው የሮብአም ታሪክ ተጠቃሽ ናቸው።አምኖን ሕይወቱን ሮብአም ከግማሽ በላይ መንግስቱንና ሕዝቡን አጥቶበታል።(ታሪኩን እናንተ አንብቡት።2ሳሙ.13 እና 1ነገ.12) ስለዚህ ትክክለኛ ሰው አግኝተን እናማክር። ፪፦ #መፅሐፍ_ቅዱስን፦ መፅሐፍ ቅዱስ የእግዚአብሔር ምክር መፅሐፍ ነው።በሚያስፈልገን ጉዳይ ላይ በቂ ምክሮችን እናገኝበታለን።ጳውሎስም "የእግዚአብሔር መንፈስ ያለበት መፅሐፍ ሁሉ…በፅድቅም ላለው ምክር ደግሞ ይጠቅማል" 2ጢሞ.3:16 ብሏል። 👉ስለዚህ ፅድቅና ሰላም እንዲሁም እረፍት የሚገኝበት ምክር ከተለያዩ ታሪኮችና ትንቢቶች ጋር በመፅሐፍ ቅዱስ ውስጥ ይገኛል።ጥልቅ የሆነ ምክሩን፤ልብ አሳራፊ ሀሳቡን እንድናገኝ መፅሐፍ ቅዱሳችንን እናንብብ። ፫፦ #መፃሕፍትን፦ የተለያዩ ርእሰ ጉዳዮች ላይ መሠረት ያደረጉ ብዙ መፃሕፍት ሞልተዋል።እናም ከእነዚህ መፃሕፍት ምክሮችን መቀበል እንችላለን።መፃሕፍት የማይሰሙን ግን የሚመክሩን መሪዎች ናቸው።በመንፈሳዊ ሕይወት ጉዳይ ላይ፤በትዳርና በልጅ አስተዳደግ ጉዳይ፤ሰውን ብናማክር ምሥጢሬን ያወጣብኛል በምንልባቸው ጉዳዮች ሁሉ ሳይቀር የተፃፉ መፃሕፍትን ማንበብ ሌላኛው አማራጭ ነው። ፬፦ #የተለያዩ_ድረገፆችና_ማህበራዊ_ሚዲያዎችን፦ ብዙ ጊዜ ማህበራዊ ሚዲያዎችን የምንጠቀመው ለወሬና ለመዝናናት ብቻ ነው።ሆኖም በጣም ብዙ አስተማሪ ድረገፆችና ማህበራዊ ሚዲያዎች አሉ።እናም የምንፈልገውን ጉዳይ ላይ ሰርች በማድረግ ተጠቀሙበት። 🗣ትክክለኛ አማካሪዎችን በመጠቀም ሕይወትን ቀላል እናድርግ። 👉ትክክለኛ ናቸው ብላችሁ የሰው አማካሪ ባትፈልጉ በጉዳዩ ላይ የተፃፉ ጤነኛ መፃሕፍትን ተጠቀሙ ከሁሉ በላይ ግን መፅሐፍ ቅዱሳችሁን ተጠቀሙበት። 📖“ምክር ሲጓደል ዕቅድ ይፋለሳል፤ በብዙ አማካሪዎች ግን ይሳካል።” — ምሳሌ 15፥22 (አዲሱ መ.ት) 📖“ጦርነት ለመግጠም መልካም ምክር፣ ድል ለማድረግም ብዙ አማካሪዎች ያስፈልጋሉ።” — ምሳሌ 24፥6 (አዲሱ መ.ት)

❤️የእለቱ መልእክት❤️ 02-10-2013 የምሕረት ዓመት #እንዴት_ቻልከው? 🗣በብርሃኑ ታምራት(ምሕረት የበዛለት) 👉በአንድ ሰው አስቸጋሪ ባሕርይ የተማረረ ሰው ሲፀልይ ፦ "ጌታ ሆይ ይህን ሰው ግን እንዴት ቻልከው? " አለ።ጌታም፦ "አንተን እንደቻልኩት" አለው።እግዚአብሔርን ተመሳሳይ ጥያቄ እናንተም እንደ ሰውዬው ብትጠይቁ የእግዚአብሔር መልስም ተመሳሳይ ነው።እግዚአብሔር የሚያኖረን ችሎንና ታግሶን ነው። 👉ሁሌም እኛ ሰዎች ራሳችንን ያዋደድን ግብዞች ነን።አፋችንን ሞልተን "ፍፁም ፃድቅ ነኝ" እንዳንል የሕሊናችን ክስ ስለማይፈቅድልን እንጂ ብዙ ጊዜ ፍርዳችንና ወሬያችን እንደ ፃድቅ ሰው ነው።እኛ ኃጢአት ስንሰራ "የሥጋ ድካም" ብለን እንጠራዋለን።ሌሎች ኃጢአት ሲሰሩ "ድፍረትና እግዚአብሔርን አለመፍራት" ነው።እናም ስለሌሎች በደል ስናስብ "ፍርዱን" ስለ እኛ በደል ስናስብ ግን "ምሕረቱን" እንለምናለን።ታዲያ ከዚህ በላይ ግብዝነት ከየት ይመጣል? 👉እግዚአብሔር ትእግስቱ ሰፊ ነው።ጴጥሮስም፦ "የጌታችንም ትእግስት መዳናችሁ እንደሆነ ቁጠሩ" ይላል(2ጴጥ.3:15)። #እየኖርን_ያለነው_በሚያኖር_መልካም_ሥራ_ሳይሆን_በሚያኖር_የእግዚአብሔር_ትእግስት_ነው።እነ እገሌን እግዚአብሔር እንዴት ቻላቸው ካላችሁ እናንተን እንደቻለ ነው የቻላቸው።እናንተን የታገሰ ነው የታገሰኝ።እኔን የታገሰ ጌታ ነው የታገሳችሁ። 👉በመልካም ሥራ እየተጋደልኩ ነው ብላችሁ የምታስቡ ቤተሰቦቼ "ሥራችሁን አትቁጠሩ"።ስለፀለይኩ ተቀበልኩ፤ስለለመንኩት ሰጠኝ፤ስለታመንኩለት ሾመኝ፤ስለቅንነቴ ጌታ ተቀበለኝ እያላችሁ አትመፃደቁ። 👉እግዚአብሔር የሰጠንን ሰጠን ለጋሽ ስለሆነ ነው።እግዚአብሔር የሚጠብቀን አባት ስለሆነ፤የተቀበለን በምሕረቱ ባለጠጋ ስለሆነ ነው።ክርስቶስ ኢየሱስ ስለ እኛ በተቀበለው መከራ እየኖርን ነው። 👉ትከሻው ሰፊ፤ምሕረቱ ብዙ፤ትእግስቱ ትልቅ፥ፍቅሩ ጥልቅ ስለሆነ ችሎናል። #ክፉዎችን_ዐመፀኞችን_በደለኞችን_የቻለው_እኛን_እንደቻለው_ነው። 👉በሕይወታችሁ ተአምራቱን ስታዩ፤ሥጦታው ሲበዛላችሁ፤ነገር ሁሉ ሲስተካከልላችሁ ለእግዚአብሔር ምሕረት እውቅና ስጡ እንጂ አንድም ሥራችሁን በፊቱ አትጥቀሱ። 👉 ስትበረቱ፥ስትፀልዩ፥ስትፆሙ፥ቃል ስታጠኑ፥ስታገለግሉ፥በቅድስና ስትመላለሱ የእነዚህ ተግባራት መብዛት ምሕረቱን አያስረሱአችሁ።በፊቱ ሰማይ እንኳን ንፁህ አይደለምና በትእቢት እንዳትወድቁ፤በደከመውም እንዳትፈርዱ ለራሳችሁ ተጠንቀቁ። ከመዝሙረኛው ከዳዊት ጋር እንዲህ ብለን እንፀልይ፦ “ #ሰው_ሆኖ_በፊትህ_ጻድቅ_የለምና፣ #ባሪያህን_ወደ ፍርድ_አታቅርበው።” — መዝሙር 143፥2 (አዲሱ መ.ት). ❤️እንዲህም ብላችሁ እግዚአብሔርን አመስግኑ፦ መዝሙር 103 (አዲሱ መ.ት) ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ⁸ እግዚአብሔር መሓሪና ይቅር ባይ፣ ለቍጣ የዘገየ፣ ፍቅሩም የበዛ ነው። ⁹ እርሱ ሁል ጊዜ በደልን አይከታተልም፤ ለዘላለምም አይቈጣም። ¹⁰ እንደ ኀጢአታችን አልመለሰልንም፤ እንደ በደላችንም አልከፈለንም። ❤️እንዲህም ብላችሁ ተደነቁ፦ “እግዚአብሔር ሆይ፤ ኀጢአትን ብትቈጣጠር፣ ጌታ ሆይ፤ ማን ሊቆም ይችላል?” — መዝሙር 130፥3 (አዲሱ መ.ት)

❤የእለቱ መልእክት️ ❤️ 01-10-2013 የምሕረት ዓመት #በእግዚአብሔር_ሀሳብ_መሞላት 👉መዝሙር አንድ ላይ የተመሰረተ 🗣በብርሃኑ 👉መፅሐፍ ቅዱስ ስለ ታላላቅ ተቃራኒ ነገሮች የሚያስተምር መፅሐፍ ነው።ሰው ደግሞ በሁለት ተቃራኒ ነገሮች መሀል መኖር የሚችል ፍጡር ነው።ሆኖም በእግዚአብሔር ዘንድ በሁለት ተቃራኒ ነገሮች ውስጥ መኖር ተቀባይነት የለውም።ብርሃንና ጨለማ፤ቅድስናና ርኩሰት፤ማመንና አለማመን(ጥርጣሬ)፤ፃድቅና ኃጥእ፤ጣኦትና የጌታ መቅደስ፤ክርስቶስና ቤልሆር ምንም መጋጠም የላቸውም።ሩቅ ለሩቅ ሆነው የማይደራረሱ ናቸው። 👉ሰው በወደቀና በተበላሸ ዓለም በመኖሩ ምክንያት በዓለም ተውጦ የኃጢአተኛን ኑሮ ለመኖር ይገደዳል።በክርስቶስ ኢየሱስ ስናምን ግን የኃጢአት አስገዳጅነት፤የሞት ኃይል ይሰበራል።ሆኖም #ሁልጊዜ_ሰው_አእምሮውን_በእግዚአብሔር_ሀሳብ_መሙላት_እስካልቻለ_ድረስ_በዓለም_ሀሳብ_የመሞላት_እድሉ_ከፍተኛ ነው። 👉አንዱ ዘማሪ በመዝሙር አንድ ላይ ሁለት ሰዎችን ያነፃፅራል።ኃጥኡንና ፃድቁን ሰው።የሁለቱንም ኑሮና ፍፃሜ ግልፅ አድርጎ ያስቀምጣል። 👉 #ኃጥኡ፦ ክፉ #ምክር አለው።በዚህ ክፉ ምክሩም ብዙዎች እንዲሄዱለት ያግባባል።ብቻው አይጠፋም።ይልቁን አጥፍቶ ጠፊ ነው።የእግዚአብሔርን መንገድ ስለተወ ብዙዎችን አታሎ የሚወስድበት የአመፅ #መንገድ አለው።መንፈሳዊ ነገር በመንፈስ የሚመረመር በመሆኑ ለዚህ ሰው መንፈሳዊነት ሞኝነት ነው።ስለሆነም ሲገስፁት ይጣላል።ሲመክሩት ያፌዛል።በመንገዱ በሀሳቡ በኑሮው እግዚአብሔር የለም።በመጨረሻም የኑሮው ምርጫ ውጤቱም እንዲህ ይሆናል።ጌታ መንገዱን ያጠፋዋል።ምክሩን ያፈርሰዋል።ፍሬ አልባ ያደርገዋል።ነፋስ ጠርጎ እንደሚወስደው ትቢያ ፍፃሚው እንዲሁ ባዶነት ይሆናል። 👉 #ፃድቁ ግን በኃጢአተኛው ድንኳን አያድርም።በወንበሩም አይቀመጥም።በመንገዱም አይሄድም።የነፍሱን ነፍስ፤የሕይወቱን ጌታ ድምፅ ይከተላል።ሕጉንም በቀንና በሌሊት ያስባል።የእግዚአብሔር ሀሳብ ሀሳቡን እንዲገዛ ይፈቅዳል።ስለዚህ የፈቃዱን እውቀት ይሞላል።ለእግዚአብሔርና ለእግዚአብሔር ለሆነው ነገር ሁሉ ትጋትና ጥማት አለው።በፍፃሜውም እግዚአብሔር ይፈርድለታል።ፍሬያማ ያደርገዋል።ስጋት በሌለበት ደስታ ይሞላዋል። ❤️ስለዚህ እንደ ፃድቅ ሰው በእግዚአብሔር ሀሳብ እንሞላ።ቃሉንም በቀንና በሌሊት እንብላ።መፅሐፍ ቅዱሳችሁን አንሱት።

#ድንግል_ማርያም_ጥንተ_አብሶ_ነበረባትን? 🗣በብርሃኑ(ምሕረት የበዛለት) 👉በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን ሁለት ዓይነት አስተምህሮ እንዳለ ባለፈው ፅሁፌ ገልጨላችሁ ነበር።እነዚህም፦ አንፅሓ እና ዐቀባ የሚባሉ ናቸው።አንፅሓ የሚባሉት ነበረባት በመልአኩ ብሥራት ጊዜ ነፃች ሲሉ ዐቀባዎች ግን ከእናቷ ማኅፀን ጀምሮ ከጥንተ አብሶ ተጠብቃለች የሚሉ ናቸው። 👉አልነበረባትም ለሚሉ ሰዎች የተወሰኑ ጥያቄዎችን ልጠይቅና ነበረባት ግን ነፅታለች የሚሉ አባቶችን ሀሳብ አቀርባለሁ። 1- ድንግል ማርያም የአዳም ልጅ አይደለችምን? ከሆነችስ ያለ ልዩነት "በአንዱ አለመታዘዝ ብዙዎች ኃጢአተኞች ሆኑ" የሚለው ቃል እንዴት አይመለከታትም? 2- የጌታ መሞትና ማዳን እርስዋን የማይመለከት ነውን? ጌታ ለእርስዋም ካልሞተ "መድኃኒቴ" ለምን አለችው? 3- እርስዋን ጥንተ አብሶ ካለባት እናቷ ያለ ጥንተ አብሶ እንድትወለድ ካደረገ ክርስቶስስ ጥንተ አብሶ ካለባት እናቱ ንፁህ ሆኖ መወለድ አይችልምን? #ወደ_ኦርቶዶክሳውያኑ_ሊቃውንት_ልለፍ፦ 1- ብፁእ ወቅዱስ አቡነ ጳውሎስ በመመረቂያ ፅሁፋቸው እንዲህ አሉ፦ "እንደ ኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን ድንግል ማርያም ለእግዚአብሔር የመታዘዝና የእምነት አርኣያና ምሳሌ ናት።በሁለት ወገን ድንግል ናት።በሥጋም በነፍስም።#የተፀነሰችው_ያለ_ጥንተ_አብሶ ወይም #ከጥንተ_አብሶ_ነፃ_ናት" #ባንልም ቅሉ ቅድስተ ቅዱሳን ንፅህት በእግዚአብሔር የማዳን ሥራና በሥጋዌው ሱታፌ ያላት ናት።" ወልታ ፅድቅ.ገፅ.192-193 2- መጋቤ ብሉይ ሰይፈ ሥላሴ ዮሐንስ የተባሉ ሊቅ በ "መሰረተ ሃይማኖትና የካህናት ተልእኮ" በሚለው መፅሐፋቸው ገፅ.29 ላይ፦ "አንዳንዶች እመቤታችን አድፎ የነበረው የአዳም ጠባይ ወይም #ጥንተ_አብሶ_እንደሌለባት_ያስተምራሉ፤ነገር ግን ይሄ ትምህርት በኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያናችን #ተቀባይነት_የለውም።ምክንያቱም እመቤታችን ከኢያቄም ከሐና በሕጋዊ ሩካቤ የተገኘች ናት። #ካሣ_የማያሳስፈልጋትም_ሳትሆን_ክርስቶስ_በደሙ_ከዋጃቸው_ካሣም_ከተከፈለላቸው_ወገን_ናት፤ሆኖም እንደ አዳምና ሔዋን የምኞት የመናገርና የገቢር ኃጢአት ፈፅሞ የለባትም።" ብለዋል። 3- አሥራት ገብረማርያም በትምህርተ መለኮት መፅሐፋቸው #1983ቱ እትም ገፅ.96 ላይ ፦ "በኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን እምነት መሰረት በሉቃ.1:38 ላይ የመልአኩን ብሥራት ተቀብላ "እነሆኝ የጌታ ባሪያ እንደ ቃልህ ይሁንልኝ" ብላ እምነቷን በእግዚአብሔር ላይ ባሳረፈች ጊዜ ጌታን ከመውለዷ በፊት መንፈስ ቅዱስ እመቤታችንን ቀድሶና #አንፅቶ_የጥንቱን_የአዳምን_ኃጢአት አስወግዶላታል።……በሌላ በኩል ደግሞ የቀድሞው የአዳም ኃጢአት የሚወረሰው በወንድ ዘር አማካኝነት ልጅ በሚወለድበት ጊዜ ከአባት ወደ ልጅ በመሆኑና ጌታ ግን የተወለደው መንፈስ ቅዱስ #የጥንቱን_ኃጢአት_ካስወገደላት ከእናት ብቻ ስለሆነ ሲወርድ ሲዋረድ የመጣውን የጥንቱን የአዳም ኃጢአት አልወረሰም።" 4- በመጨረሻም ብፁእ ወቅዱስ አቡነ ሺኖዳ ያሉትን ልጠቀስና ልጨርስ፦ "የግብፅ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን መንፈስ ቅዱስ የድንግልን አበሳ(ከጥንተ አብሶ) #ክርስቶስን_በፀነሰች_ጊዜ_እንደነፃች_ታምናለች።ይኸውም ቅዱስ ገብርኤል "መንፈስ ቅዱስ ወደ አንቺ ይመጣል፤የልኡል ኃይልም ይፀልልሻል፥ከአንቺም የሚወለደው ቅዱሱ የእግዚአብሔር ልጅ ይባላል" ባላት ጊዜ ነው።…#ከኃጢአቱ_በመንፈስ ቅዱስ_መንፃቷ ከእሷ የተወለደውን ጌታ ያለ ጥንተ አብሶ እንዲወለድ አደረገው።የእርሷን መፀነስ ተመልክቶ ግን እናቷ እንደ ማንኛውም ሰው ነው የፀነሰቻት፤ስለዚህ ነው ድንግል "መንፈሴ በአምላኬና በመድኃኒቴ ሀሴት ታደርጋለች" ያለችው።ለዚህ ነው ቤተክርስቲያን ወንድሞቻችን ካቶሊካውያን ድንግል ያለ ጥንተ አብሶ ተፀነሰች ከሚሉት እምነት ጋር የማትስማማው።" ወልታ ፅድቅ.ገፅ.188 5- ምሥራቃውያን ኦርቶዶክሶች ደግሞ እንዲህ ይላሉ፦ "እመቤታችን ያለ ጥንተ አብሶ ተፀንሳለች(አልነበረባትም) ብሎ ያስተማረ አባት አልሰማንም።" ሻሎም!!! https://telegram.me/preac

#ጥንተ_አብሶ(Original Sin) #ምንድን_ነው? 🗣በብርሃኑ(ምሕረት የበዛለት) 👉ጥንተ አብሶ ስንል #አዳምና_ሔዋን_በሰሩት_ኃጢአት_ያለ_ውስጣዊ_ተጠያቂነት ማለት ነው። 👉እንደ ኤርትራ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ያሉ በጣምጥቂቶች ካልሆኑ በቀር ሁሉም አብያተ ክርስቲያናት በሚባል ደረጃ "ሁሉም ሰው ከአዳምና ከሔዋን የውርስ ኃጢአት አለበት" ብለው ያምናሉ። 👉የውርስ ኃጢአት ወይም ጥንተ አብሶ ለኃጢአት ከሚሰጡ ትርጉሞች አንዱ ነው እንጂ ብቸኛ የኃጢአት ትርጉም አይደለም።ስለዚህ ኃጢአት ምንድን ነው የሚለውን መፅሐፍ ቅዱሳዊ ትርጉም እንይ። #ኃጢአት_ምንድን_ነው? 1- ኃጢአት የሚለው ቃል #በእብራይስጥ ቻታህ(chattah) ኢላማን መሳት፤ከመንገድ መውጣት ማለት ሲሆን ከእግዚአብሔር መንገድ መውጣት፤የእግዚአብሔርን ሀሳብ መሳት ወይም ከእግዚአብሔር ሀሳብ በተቃራኒው መቆምን ያመለክታል። 2- ኃጢአት በግሪኩ ደግሞ ሐማርትያ (Hamartia) የአዲስ ኪዳን ፀሀፊዎች ይሄን ቃል የተጠቀሙት ኃጢአት ሰብአዊ ተፈጥሮ(sinful nature) ለመግለፅ የተጠቀሙበት ሲሆን ይሄንን ቃልበአዲስ ኪዳን 174 ጊዜ ተጠቅመውታል።ቀጥተኛ ትርጉሙ ግን ከእብራይስጡ ጋር ተመሳሳይ ነው። 👉ስለዚህ ኃጢአት ማለት፦ የእግዚአብሔርን ሕግ መጣስና መተላለፍ፤በጎውን እያወቁ አለማድረግ፤አለመታዘዝና አምላክ ላይ ማመፅ ማለት ነው።(1ዮሐ.3:4፤ያእ.4:17፤ያእ.2:9) #የውርስ_ኃጢአት( #ጥንተ_አብሶ) #ሰው_ሁሉ_አለበትን? 👉መፅሐፍ ቅዱስ ይሄን ጉዳይ በማያሻማ ሁኔታ አስቀምጦልናል።ሁላችንም የአዳም ልጆች በመሆናችን የአዳም ኃጢአትና የኃጢአቱ ውጤት ወራሾች ነን።ይሄም የሆነው አዳም ኃጢአቱን ሲሰራ በአዳም ወገብ(ዘር ሆነን) የመኖራችን ጉዳይ ተካፋይ እንድንሆን ያደርገናል።ሐዋርያው ጳውሎስም፦ "“ስለዚህ ምክንያት #ኃጢአት_በአንድ_ሰው_ወደ_ዓለም_ገባ #በኃጢአትም_ሞት፥ እንደዚሁም ሁሉ ኃጢአትን ስላደረጉ ሞት ለሰው ሁሉ ደረሰ፤” — ሮሜ 5፥12 በማለት ኃጢአቱ ከነውጤቱ እንደደረሰብን ፅፎልናል።አክሎም፦ “ #ሁሉ_በአዳም_እንደሚሞቱ #እንዲሁ #ሁሉ_በክርስቶስ_ደግሞ_ሕያዋን_ይሆናሉና።” — 1ኛ ቆሮንቶስ 15፥22 ብሏል። 👉መጀመሪያ አዳምና ሔዋን በእግዚአብሔር መልክና ምሳሌ በፅድቅና በቅድስና ተፈጠሩ።በኃጢአት ከወደቁ በኋላ ግን የሚወልዷቸው ልጆች እንደ እግዚአብሔር ምሳሌ ፃድቅና ቅዱስ ሳይሆኑ እንደ ወላጆቻቸው ኃጢአተኛና ጎስቋላ ሆነው በእነርሱ መልክ ተወለዱ።ስለዚህ የአዳም ዘር ሆኖ የወላጆቹን ኃጢአትና የኃጢአት ውጤት ማምለጥ የሚችል የለም።ዘፍጥ.5:1-3 👉ከፍጥረታችን የቁጣ ልጆች ነን(ኤፌ.2:1-3) በዓመፃ ተፀንሰን፤በኃጢአት ተወለድን(መዝ.51:5) የልባችን የኃጢአት ዝንባሌ ኃጢአተኛ ሆነን የመወለዳችን ምስክር ነው(ኤር.17:9፤ማቴ.15:18-19.ሮሜ.7:23) ሮሜ 3 ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ²² … #ልዩነት_የለምና፤ ²³ #ሁሉ ኃጢአትን ሠርተዋልና የእግዚአብሔርም ክብር ጎድሎአቸዋል 🛑ድንግል ማርያምስ ጥንተ አብሶ ነበረባትን? ክርስቶስስ ከእርስዋ ሥጋና ደም ተካፍሏልን? ከተካፈለስ የጥንተ አብሶ ነገር እንዴት ይታያል? ይቀጥላል……… https://telegram.me/preac

#ጥንተ_አብሶ_በአብያተ_ክርስቲያናት 🗣በብርሃኑ (ምሕረት የበዛለት) 👉ሰሞኑን የአንዲትን ጋዜጠኛ ንግግር ተከትሎ ሁሉም በየእምነቱ ስለ "ጥንተ አብሶ" የሚያውቀውንና የተረዳውን ሲል ተመልክቻለሁ።እንደው በደፈናው የጌታችን እናት ማርያም ርእስ ሆና ጥንተ አብሶ አለባት የለባትም ተባለ እንጂ የሰው ልጆችም ጥንተ አብሶ በየአብያተ ክርስቲያናቱ አከራካሪ ጉዳይ ነው። #ጥንተ_አብሶ የሚለው ቃል ትርጉም #የመጀመሪያው_በደል ማለት ሲሆን ጥሬ ቃሉ።በእንግሊዝኛ በተፃፉ መዛግብት ተለዋዋጭ ቃላትን እናገኛለን።አዳማዊ በደል(Adamic Guilt)፤የውርስ ኃጢአት(Hereditary Sin)፤የቀደመው ኃጢአት(Original Sin)፤የቀደምት ወላጆቻችን ኃጢአት(Ancestral Sin) የሚሉ ተጨማሪ መጠሪያዎችን እናገኛለን። 👉ዞሮ ዞሮ ጥንተ አብሶ(Original Sin) ስንል አዳምና ሔዋን በሰሩት ኃጢአት ያለ ውስጣዊ ተጠያቂነት ማለት ነው። 👉አንዳንድ አብያተ ክርስቲያናት ከአዳምና ሔዋን ኃጢአት ሳይሆን የኃጢአቱን ውጤት መርገሙንና ፍዳውን እንጂ ኃጢአቱን አልወረስንም ብለው ያምናሉ ያስተምራሉ።*የኤርትራ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን* እናም ጥንተ አብሶ በማለት ፈንታ የአዳምና ሔዋን ኃጢአት ይላሉ።ውጤቱ እንጂ ኃጢአቱ አይተላለፍም ለማለት። 👉 #የግብፅና_የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን እንዲሁም ወንጌላውያን ደግሞ ከአዳምና ከሔዋን በደል ተሳታፊዎች ስለሆንን ኃጢአቱንም ውጤቱንም ወርሰናል ይላሉ።ኃጢአትና ውጤቱን ወርሰናል ቢሉም ወደ ትምህርቱ ሲገባ ጥቂት መለያየቶች ደግሞ እናገኛለን።ለምሳሌ፦ በጌታችን እናት በማርያም ከጥንተ አብሶ ነፃ መሆንና አለመሆን ልዩነቶች አሉ። 👉 #የግብፅ_ቤተ_ክርስቲያን መልአኩ ገብርኤል ሲያበስራትና ፈቃደኛ ስትሆን ነፃች እንጂ #እንደ_ማንኛውም_ሰው_ጥንተ_አብሶ_ነበረባት ብለው ያምናሉ። 👉 #በኢትዮጵያን_ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን ግን 2 ዓይነት አመለካከት ነው ያለው። 1-አንፅሓና 2-አቀባ የሚባሉ። #አንፅሓ የሚሉ ሰዎች እንደ ግብፃውያን እምነት ጥንተ አብሶ ነበረባት በመልአኩ ብሥራት ነፃች።የሚሉ ናቸው። #አቀባ የሚሉ ደግሞ ድንግል ማርያም ሲጀመርም ለእናትነት የተመረጠች በመሆኗ ጠበቃት እንጂ አላነፃትም ይላሉ። 👉ወደ #ወንጌላውያን ስንመጣ ደግሞ ድንግል ማርያም ጥንተ አብሶ ነበረባት ጌታን ከወለደችውም በኋላ አልነፃችም።የነፃችው በደሙ መፍሰስ ቆይቶ ነው ይላሉ።እና ካልነፃች ሴት እንዴት ሥጋና ደም ተካፈለ ሲባሉ #ለሁለት ጎራ ይከፈላሉ።እናም፦ 👉 ከእርስዋ ምንም አልተካፈለም የሚሉና 👉ከእርስዋ አንዲት ዘር(እንቁላሉን) ብቻ በማንፃት ተዋሃደ እንጂ እርስዋን አላነፃትም የሚሉ። 👉የኃጢአትን ምንነት መረዳት መዳንን መረዳት ነውና ስለኃጢአት በቂ መፅሐፍ ቅዱሳዊ እውቀት ያስፈልጋል። 👉መፅሐፍ ቅዱስ ግን ምን ይላል? ድንግል ማርያምስ ጥንተ አብሶ ነበረባትን? ይቀጥላል…… https://telegram.me/preac

❤️የእለቱ መልእክት❤️ 09/04/2013 የምሕረት ዓመት #ከብቸኝነት_ስሜት_እንዴት_ልላቀቅ? 🗣በብርሃኑ(ምሕረት የበዛለት) 👉 በሰው ተከበን ብቸኝነት ሲሰማን ራሳችንን ብዙ ጊዜ እናገኘዋለን። 👉ብቻችንን ልንሆንበት የምንችልባቸው ጊዜዎች ብዙ ናቸው።ፈልገንም ሳንፈልግም ብቻችንን እንሆናለን። #ብቻችንን #መሆናችን #ግን #ሲያድግ #ብቸኞች #እንሆናለን። 👉በሰው መከበብ፤የሚወዱንና የሚያፈቅሩን ሰዎች መብዛት፤ከቤተሰብ ጋር መኖር፤ሶሻል ሚዲያን መጠቀም ከብቸኝነት ስሜት አያድኑንም። 👉 የብቸኝነት ስሜት ሕይወት የሚያበላሽ ግን ሁሉም ሰው የሚፈተንበት ችግር ነው። #የብቸኝነት #ስሜት #ሁሉም #ሰው #ይሰማዋል። #የሚለያየው #ድግግሞሹና #ቆይታው #ነው። 👉 #በብቸኝነት_ስሜት_የሚሰቃይ_ሰው_እነዚህ_ምልክቶችን_ያሳያል፦ 🖍 ሰዎች ሁሉ ከጀርባው ስለእርሱ የሚያወሩና የሚያሙት ይመስለዋል። 🖍 ግንኙነትን ይሸሻል።ፍቅረኛ መያዝ፥ጓደኝነትን መመሥረትና ከሰው መቅረብ አይፈልግም።የብቸኝነት ስሜቱ መጎዳትን ያሳየዋልና ይሸሻል። 🖍 ተማሪ ከሆነ ከተማሪዎች መነጠል፤በዙሪያው ካሉ ሰዎች መነጠልና ለብቻው መሆን። 🖍 ሰዎች ሊያገኙት ፈልገው ስልክ ሲደውሉለት አለማንሳትና መዝጋት። 🖍 በሱሶችና በተለያዩ ነገሮች ለመደበቅ መሞከር። 🗣ከላይ የተዘረዘሩት ምልክቶች በብቸኝነት ስሜት የሚሰቃዩ ሰዎች መገለጫዎች ናቸው። 👉 #ከብቸኝነት_ስሜት_ለመዳን_ምን_ላድርግ? 🖍 ሊያማክራችሁ የሚችል ሰው ፈልጉ።ችግራችሁን በመንገር፤ትክክለኛ ስሜታችሁን በመግለፅ የምክር እገዛ ፈልጉ።ይህ የመሸነፍ ምልክት ሳይሆን ራስን ለማዳን የሚወሰድ እርምጃ ነው። 🖍 ከተለያዩ ሰዎች ጋር መርጣችሁ፤ መልእክቶችን ተለዋወጡ፤ተደዋወሉ፤ሰው አግኙ። 🖍 ሰዎች ወደሚበዙበት ቦታዎች ወጣ በሉ።ጤናማና ለኃጢአት የማያጋልጡ መዝናኛዎችን ተጠቀሙ።ከሰው ጋር ተቀላቀሉ። 🖍 ማህበራዊ ሕይወት ላይ ንቁ ተሳታፊ ሁኑ።የታመመ ጠይቁ፤የታሰረ ጎብኙ፤በሰው ደስታ ተደሰቱ፤ሀዘናቸውን ተጋሩ። 🖍❤️ ከምንምና ከማንም በላይ ግን ብቻችሁን በማይተዋችሁ እግዚአብሔር ተማመኑ።ሰዎች መውደድ ብቻ ሳይሆን መጥላትም ይችላሉ።ጌታ ግን መቼም ቢሆን አይጠላችሁም። 👉ሰዎች በእናንተ ደክመው ይተውአችኋል።ጌታ ግን መቼም አይተዋችሁም።ተፅናኑ ተፅናኑ ተፅናኑ ተፅናኑ ተፅናኑ። ❤️ከብቸኝነት ሕይወት ጌታ ኢየሱስ ነፃ ያወጣችኋል። "የሚያፅናናኝ ልቤን ሚደግፈው ብቻዬን አይደለሁም አብ ከእኔ ጋር ነው" እነዚህን ቃላት አሰላስሉ፦ ❤️" እነሆ፥ #እያንዳንዳችሁ #ወደ #ቤት #የምትበታተኑበት #እኔንም #ለብቻዬ #የምትተዉበት #ሰዓት #ይመጣል፥ አሁንም ደርሶአል፤ #ነገር #ግን #አብ #ከእኔ #ጋር #ስለ #ሆነ #ብቻዬን #አይደለሁም።" (የዮሐንስ ወንጌል 16:32) ❤️ (የሐዋርያት ሥራ ምዕ. 2) ---------- 25፤ #ጌታን #ሁልጊዜ #በፊቴ #አየሁት፥ #እንዳልታወክ #በቀኜ #ነውና። 26፤ #ስለዚህ #ልቤን #ደስ #አለው፥ #ልሳኔም #ሐሤት #አደረገ፥ #ደግሞም #ሥጋዬ #በተስፋ #ያድራል፤ 27፤ #ነፍሴን #በሲኦል #አትተዋትምና፥ #ብቸኛ #አትሁኑ።

#በአዳም #ውስጥ #ወይስ #በክርስቶስ #ውስጥ #ነህ? Are You In Adam Or In Christ? 🗣ብርሃኑ(ምሕረት የበዛለት) 👉አዳም የሰው ዘር በሙሉ አባት ነው።እርሱ ቀድሞ በእግዚአብሔር መልክ ቢፈጠርም የእግዚአብሔርን ኪዳን በማፍረሱ ምክንያት ከእርሱ የሚወለዱ ሁሉ እርሱን የሚመስሉ ሆኑ።ዘፍጥ.1:26==ዘፍጥ.5:1-3 ✍አንተ በአዳም ውስጥ ነህ? ወይስ በክርስቶስ ውስጥ ነህ? 👇👇👇👇👇👇 👉ከሁለቱ ውጭ መሆን አትችልም።ወይ በአዳም ውስጥ ነህ ወይም በክርስቶስ ውስጥ ነህ።በአዳም ውስጥ ለመሆን ማመንም መካድም አይጠበቅብህም።ሰው ሁሉ በአዳም ውስጥ ነው።በክርስቶስ ውስጥ ለመሆን ግን በክርስቶስ የማመን ግዴታ አለብህ።ማመን ብቻ። 👉አዳም አትብላ የተባለውን ሲበላ ነበርክን? አልነበርክም ግን የእርሱ ልጅ በመሆንህ ብቻ እርሱ የሆነበት ኩነኔ ሆኖብሃል።በአካል ባትኖርም ወገቡ ውስጥ ነበርክ።ዘሩ ነበርክ።በእርሱ ውስጥ ሆነህ አብረህ ያሕዌ ላይ አምፀሃል። 👉ክርስቶስ ሲሰቀል ነበርክ? አልነበርክም።ክርስቶስ ሕግን ሁሉ ፈፅሞ አብን ሲያከብር ነበርክ? አልነበርክም።በእርሱ ካመንክ ግን ውስጡ ነበርክ።ሲሰቀል አብረህ ተሰቅለሃል።ሲታዘዝ አብረህ ታዘሃል።አብን ሲያከብር አንተም ውስጡ ነበርክና አብን አክብረሃል።አሁን በአብ ቀኝ በሰማይ በክርስቶስ ውስጥ ነህ።በክርስቶስ ተሰውረሃል።ኩነኔ የለብህም።ፍፁም ፃድቅ ነህ።አንተ የማይጠፋው የክርስቶስ ዘር ነህ። 😱“…… ነፍሱን ስለ ኃጢአት መሥዋዕት ካደረገ በኋላ #ዘሩን #ያያል፥” — ኢሳይያስ 53፥10 ❤️በአዳም አለመታዘዝ ኃጢአተኛ ነህ።በክርስቶስ መታዘዝ ፃድቅ ነህ። ❤️በአዳም ከፍጥረትህ የቁጣ ልጅ ነህ።በክርስቶስ ምሕረት የገነነልህ የያሕዌ ልጅ ነህ። ✝በክርስቶስ ውስጥ ሁን።በእርሱ ተሰወርና ከቁጣው አምልጥ። ሮሜ 5 ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ¹⁴ ………፤ #አዳም #ይመጣ #ዘንድ #ላለው #ለእርሱ #አምሳሉ #ነውና። “#በአንዱም #በደል #ሞት በአንዱ በኩል #ከነገሠ፥ ይልቁን #የጸጋን #ብዛትና #የጽድቅን #ስጦታ #ብዛት የሚቀበሉ #በአንዱ #በኢየሱስ ክርስቶስ በኩል #በሕይወት #ይነግሣሉ።” — ሮሜ 5፥17 ፔጁን ይቀላቀሉ 👇👇👇👇👇 https://telegram.me/preac

❤️የእለቱ መልእክት❤️ 03/01/2013 የምሕረት ዓመት #ራስን_መጉዳት 🗣በብርሃኑ ታምራት(ምህረት የበዛለት) 👉❤️ከሁለት ዓመት በፊት ነው።አንዲት በጣም የተጨነቀች እህት በየቀኑ የፀሎትና የምክር እገዛ ትጠይቀኝ ነበር።ጭንቀቷ እስኪያስጨንቀኝና ምላት ሁሉ እስኪጠፋኝ ድረስ እረበሽ ነበር።ከፍቅረኛዋ ጋር ተለያይተዋል።……"ካለሱ መኖር አልችልም።እንዲታረቀኝ ፀልይልኝ።ወይ ማድረግ ያለብኝን ምከረኝ" የሁልጊዜ ጥያቄዋ ነው።ልጂቱ በጣም ቆንጆ ናት።ግን የምታልፍበት ሁኔታ እያጠቆራት፥እየከሳች መጣች።አብረን ሆነን እንዲታረቁ ወደ አብ ፀሎት ሳደርስ በጣም ታለቅስ ነበር።ጨነቀኝ።በመጨረሻ እንዲህ አልኳት፦…… "እባክሽ እህቴ ስሚኝ፦ ያሕዌ ፀሎታችንን ሰምቶአል ትታረቃላችሁ፥ ግን ራስሽን እየጎዳሽ ነው፤ራስሽን እየጣልሽና ጤና እያጣሽ ነው፤ያሕዌ ልጁን ሲያመጣው አንቺ ግን ጤና አጥተሽ ትጠብቂዋለሽ፥ለራስዋ ያልሆነችን ሴት ለእኔ ትሆነኛለች ብሎ የሚያገባሽ ይመስልሻል? ያሕዌን እመኚው፤ሐና ከፀለየች በኋላ ዳግመኛ ፊቷ ላይ ሀዘን እንዳልታየ እንዲሁ አንቺም በእምነት በርቺ እባክሽን" አልኳት።እርስዋም በረታች።አሁን ታርቀው አብረው ናቸው። 👉ተመልከቱ ወዳጆቼ፦ አንድ ነገር ይሳካላችሁ ዘንድ ራሳችሁን ማጣትና ማሳቃየት የለባችሁም።ስኬቱ ሲመጣ እናንተ ለዛ ስኬት የማትበቁ ትሆናላችሁና!! ✍ሀብታም ለመሆን እረፍት ለሰውነታችሁ፥መልካም ምግብ ለሆዳችሁ፥ጊዜ ለወዳጆቻችሁ ከልክላችሁ ሀብቱ ሲመጣ ጤናም ሰውም አይኖራችሁም። ✍ጥያቄያችሁ እስኪመለስ፤የልባችሁ እስኪደርስ በእምነት መፀለይ እንጂ ራስን ማስጨነቅ፥ራስን መጉዳት ከምትፈልጉት ነገር ራስን ማራቅ ነው።እናንተ ደህና ስትሆኑ ነው ሀብትም ትዳርም ልጅም አገልግሎትም ሊኖር ሚችለው። 👉እናም ማድረግ ያለባችሁን እያደረጋችሁ፤በበራ ፊት፤እምነት በተሞላ ልብ አምላካችሁን ጠብቁት። 📖1ኛ ሳሙኤል 1 ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ¹⁰ እርስዋም በልብዋ ትመረር ነበር፥ በእግዚአብሔር ፊት ጸለየች፥ ጽኑ ልቅሶም አለቀሰች። … ¹⁸ ……ሴቲቱም መንገድዋን ሄደች፤ በላችም፥ #ፊትዋም #ከእንግዲህ_ወዲያ_አዘንተኛ_መስሎ_አልታየም። አንዲት የተጨነቀች ነፍስ ታርፍበት ዘንድ እባክዎን ሼር ያድርጉት። ፔጁን ይቀላቀሉ 👇👇👇👇👇 https://telegram.me/preac

2013 ዓ/ም ሁሌም ተመሳሳይ ነገር እያደረግን፤በአሮጌው አስተሳሰብ ሆነን አዲስ ነገር ማንጠብቅበት ዓመት ይሁንልን!!! መልካም 2013 ዓመት!!!

❤️የእለቱ መልእክት❤️ 17/12/2012 የምሕረት ዓመት #የመሠጠት_መርህ 🗣በብርሃኑ ታምራት ✍ከታወቀ ዩኒቨርስቲ ስለተማርክ አዋቂ አትሆንም።ከግል ትምህርት ቤት የተማሩም ከመንግስት ት/ቤት ከተማሩ የተሻለ የአእምሮ ብልህነት(IQ) የላቸውም።ከታወቀ ምሁር እውቀትን ለመካፈል የተሰበሰቡ ሁሉ የምሁሩን እውቀት አያገኙትም።ልዩነቱ ያለው ትምህርት ቤቱና መምህሩ ጋ ሳይሆን የተማሪው መሠጠት ላይ ነው። ❤️የቅዱስ ጳውሎስ የሥጋ ልጆች እንኳን ብንሆን እንደ ጳውሎስ አንሆንም። ✍በአባቶቻችንና በእኛ መካከል ከፍተኛ ልዩነት አለ።የቅድስና ሕይወታቸው፥እግዚአብሔርን መፍራታቸው፥እምነታቸው፥የፀሎት ሕይወታቸው፥ከሰማይ በሚቀበሉት ሞገስና ጉብኝት ከእኛ እጅጉን ይልቃሉ።አባቶቻችን ነቢያትና ሐዋርያት እግዚአብሔር አምላካቸው ተብሎ ሲጠራ በእነርሱ እየኮራ ነው።እግዚአብሔር እኔ እኮ የአብርሃም አምላክ ነኝ ማለቱን ሳነብ ያሕዌ በአብርሃም እንደ ኮራው በእኔ የሚኮራው መች ነው እላለሁ፤እንባ ይተናነቀኛል።አባቶቼን ሳይ ራሴን እንቀዋለሁ፥የኢየሱስን ደም አስቤ ግን እፅናናለሁ። 🙏አባቶቻችን እንደ እኛ ፍጡራን ናቸው።በአባቶቻችንና በእኛ መካከል የሰውነት ልዩነት የለም።እንደ እኛ ሰው ናቸው።ይደክማሉ፤ ይራባሉ፤ይበላሉ ይጠጣሉ።ኃጢአት ሰርተዋል፥ንስሐም ገብተዋል። 👉በእኛና በአባቶቻችን መካከል ያለው ከፍተኛው ልዩነት መሠጠት(Self giving) ነው።አባቶቻችን ቁርጠኞችና የተሰጡ ነበሩ።እንደ እኛ ቸልተኞችና ሰነፎች አይደሉም።በአጋጣሚና ሲመቻቸው ሲመቻቸው አይፀልዩም።የታወቀና ቋሚ የፀሎት ሰአት ነበራቸው።መፅሐፍ ቅዱስንም ድንገት የገለጡትንና ያገኙትን ቃል አንብበው ዛሬ ያሕዌ ተናገረኝ አይሉም።በፀሎት ጥያቄያቸውን አቅርበው፤በቃሉ በኩል መልስ ያገኙ ነበር።ሰይጣንን አይፈሩም፤ግን ደግሞ አይንቁትም።ሁልጊዜ የያሕዌን ፊት ይፈልጋሉ።ቃሉን ያሰላስላሉ።ይፆማሉ።ሁልጊዜ መፅሐፍቅዱስን ሲያጠኑና ሲያነቡ ለመታዘዝ ነው።ከእውቀታቸው ይልቅ እምነታቸው ትልቅ ነው።እግዚአብሔር ያዘዛቸውን በፀጋው ተደግፈው ያለምንም ቅሬታና ጥያቄ ይፈፅሙታል።ለሞተላቸው ለመኖር ይጋደላሉ።አባቶቻችን የተሠጡ ነበሩ።አባቶቻችን ቁርጠኞች ነበሩ። 👉ተወዳጆች ሆይ በእኛና በአባቶቻችን መካከል ያለው ልዩነት መሠጠት ብቻ ነው።የእነርሱ አምላክ የእኛም አምላክ ነው።እነርሱ ልጆች እኛ ባሪያዎች አይደለንም።እኛም የእግዚአብሔር ልጆች ነን።አባቶችም እኛም አንዱን መንፈስ ነው የጠጣነው።የተወለድነው ከእግዚአብሔር ነው።ተወልዶ ብልጫ፤አንክሶ ሩጫ የለም።ስለዚህ በመሠጠት መርህ አባቶቻችንን እንምሰል። ❤️ላመንበት ነገር ራሳችንን እንስጥ።ጠንክረን ቃሉን እናጥና።ሳናቋርጥ እንፀልይ።ስለሁሉ እግዚአብሔርን በክርስቶስ እናመስግን።ያሕዌን እንታዘዘው።እንፁም።ሕይወታችንን፥ጊዜያችንን መንፈስ ቅዱስ እንዲወርሰው እንፍቀድለት።ስናሾፍ ስንቀልድ ጊዜው አይሂድ። 🙏የመሠጠት መርህ ዋናው የሕይወት መርህ ነው።በመሠጠት መርህ ስንመላለስ እግዚአብሔርን በሚያከብር ሕይወት እንገለጣለን።እምነታችን ይጨምራል።ሰማይ በእኛ አንፃር የተከፈተ ይሆናል። የመሠጠት መርህ።።።።።።። 🙇‍♂እነዚህን ቃላት አሰላስሉ፦ 📖ልመካ ብወድስ ሞኝ አልሆንም፥ እውነትን እላለሁና፤ ነገር ግን #ማንም_ከሚያይ_ከእኔም_ከሚሰማ #የምበልጥ_አድርጎ_እንዳይቆጥረኝ_ትቼአለሁ። 2ቆሮ.12:6 📖#ኤልያስ_እንደ_እኛ_የሆነ_ሰው_ነበረ፥ …… ያእቆብ.5:17-18 📖“አንተ ግን #ትምህርቴንና_አካሄዴን_አሳቤንም_እምነቴንም_ትዕግሥቴንም_ፍቅሬንም_መጽናቴንም_ስደቴንም_መከራዬንም_ተከተልህ፤” — 2ኛ ጢሞቴዎስ 3፥10 እባክዎን ለሌሎች ሼር ያድርጉት። ፔጁን ይቀላቀሉ 👇👇👇👇 https://telegram.me/preac

የእለቱ መልእክት