የአገልጋይ ብርሃኑ ገፅ
Open in Telegram
ይህ የአገልጋይ ብርሃኑ ገፅ ነው።ዓላማዬ የተለያዩ መፅሐፍ ቅዱሳዊ ትምህርቶችን ማካፈልና ማድረስ ሲሆን ምክሮችን፥አባባሎችን፥ፀሎቶችንና ትዝብቶቼን የማካፍልም ይሆናል።የሰራዊት ጌታ እግዚአብሔር ወደ ልቤ ያመጣውንና የተናገረኝንም እፅፋለሁ።ትውልዱን ወደ ኢየሱስ የሚያስጠጋውን የትኛውንም ነገር የምፅፍበት ገፄ ነው።በማንበብና ሼር በማድረግ ከአገልግሎቴ ጎን ይቁሙ።0984005562.
Show more447
Subscribers
+224 hours
+87 days
+3030 days
Posts Archive
❤️የእለቱ መልእክት❤️
06/12/12 የምሕረት ዓመት
#አዎ_በዚህ_ጊዜም_ይባላል!!
🗣በብርሃኑ ታምራት
👉ኢትዮጵያ አሁን ደህና አይደለችም።ምንም ደግ ነገር እየሰማን አይደለም።በሽታው አሳሳቢ ነው።የፖለቲካው ሁኔታም ሰላም ይነሳል።ስለ ግድባችን ያለው ፈተና፥የተላለፈው ምርጫ፥ያለው የእርስ በእርስ ግጭት ልብ ሰባሪ ነው።እነዚህን ተከትሎ ርሀቡና ስደቱ ያስለቅሳል።የዓለም መጨረሻ በሚመስል መከራ ውስጥ እያለፍን ነው።ግን በዚህ ጊዜም አንድ ነገር ይባላል።እርሱም፦ #በጌታ_ደስ_ይበላችሁ_ደግሜ_እላለሁ_ደስ_ይበላችሁ።
👉ሐዋርያው ጳውሎስ በጌታ ደስ ይበላችሁ ያለው ከዚህ በከፋ ሁኔታ ውስጥ አገሩ እሥራኤልና አማኞች በሚያልፉበት ጊዜ ነው።እርሱም ታስሮ ሞቱን እየተጠባበቀ በጌታ ደስ ይበላችሁ አለ።አዎ በዚህ ጊዜም ይባላል።የምንወዳት ሀገር ታማም፥የምናፈቅረውንና የምንወደውን ሰው አጥተንም አዎ በዚህ ጊዜም ይባላል።በጌታ ደስ ይበላችሁ።
#ለምን_በጌታ_ደስ_እንደሰታለን?
፩፦ብቻውን እርሱ ኢየሱስ የአማኞች ደስታ ነውና።
፪፦ምንም ነገር ከእርሱ ቁጥጥር ውጭ አይደለምና።
፬፦ ይፈርዳልና።
፭፦ ሁሉን ያያልና።
፮፦ ቢዘገይም ይመጣልና።
፯፦ እንደገና እንስቃለን፥በጎውን ዘመን ያመጣልናልና።በጌታ ደስ ይበላችሁ።
❤️አያልፉም የተባሉት ጊዜያት አልፈዋል።ምድርን ያንቀጠቀጡ ኃያላን ወድቀዋል።ስለእነርሱ ሲሰማ ሰው ሁሉ ሚሸበርላቸው ነገስታት በአደባባይ ተሰቅለዋል።ሕፃናትን ያለ አባት ያስቀሩ ጦርነቶች፥ሰውን እንደ ቅጠል ያረገፉ ወረርሽኞች፤እንዴት ያልፉ ይሆን የተባሉ የጭንቅ ቀኖች አልፈዋል።ዛሬም ይሄ ቀን ያልፋል።
👉ለኢትዮጵያና ለኢትዮጵያውያን የሚያስብ አምላክ በሰማይ አለ።ግፈኞችን የሚገድል፤ትእቢተኞችን የሚያዋርድ፤የፖለቲካን እንቆቅልሽ የሚፈታ፤የፈሰሰን ደም ሁሉ ሳይበቀል የማይተው፤የድሃ አደጎች አባት፤ተከራካሪ ለሌላቸው ጠበቃ የሆነው ስለእኛ የሚገደው እግዚአብሔር አለ።በጌታ ደስ ይበላችሁ።
👉ክርስቲያኖች በጌታ ተፅናኑ።ከእርሱም ባገኛችሁት መፅናናት ሌሎችን አፅናኑ።እግዚአብሔርን እንጂ ችግርና መከራን አታግዝፉ።እግዚአብሔር ከሁሉ በላይ ነው።#ያያል #ይሰማል #ይመረምራል #ይፈርዳል።
መዝሙር 11
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
⁴ እግዚአብሔር በተቀደሰው መቅደሱ ነው፤ እግዚአብሔር፥ ዙፋኑ በሰማይ ነው፤ #ዓይኖቹ_ወደ_ድሃ_ይመለከታሉ፥ #ቅንድቦቹም_የሰው_ልጆችን_ይመረምራሉ።
⁵ #እግዚአብሔር_ጻድቅንና_ኅጥእን_ይመረምራል፤ ዓመፃን የወደዳት ግን ነፍሱን ጠልቶአል።
⁶ ወጥመድ በኅጥኣን ላይ ያዘንባል እሳትና ዲን ዐውሎ ነፋስም የጽዋቸው እድል ፈንታ ነው።
ለሌሎች ያካፍሉት።።።
ፔጁን ይቀላቀሉ።።።
👇👇👇👇👇
https://telegram.me/preac
❤️የእለቱ መልእክት❤️
27/11/2012 ዓ/ም
#የትናንቱን_ነው_ማየት
🗣በብርሃኑ ታምራት
👉አንድ ወዳጅ ነበረኝ።ምሥጢረኛዬም ነበር።እርሱም እኔን ከመውደዱ የተነሳ ለእኔ የሚጠቅመኝን እርሱ ጋ ያለን ሀሳብ፥ገንዘብና ጊዜውን አይሰስትም።እኔም ለእርሱ እንደዛው ነኝ።ግን አንድ ቀን በጓደኝነታችን መሀል ነፋስ ገባና በጣም አስቀየመኝ።እኛ ቤት ይመጣ ነበርና መምጣቱን አቆመ።እኔም አላገኘውም።ከዛ እናቴ፦ "ምነው ጓደኛህ ጠፋ" ብላ ጠየቀችኝ።እኔም "አስቀይሞኝ ተጣልተናል" አልኳት።እናቴም፦ "ኧረ ልጄ ጥሩ አልሰራህም፤የትናንቱን ነው እንጂ ማየት" አለችኝ።እኔም ለጊዜው ባልሰማትም፤እየቆየ ግን ምክሯን ተቀብዬ ራሴ ፈልጌ ሄጄ ታረቅን።እውነት ነው ዛሬ ተጣልተናል፤የዛሬው ጥላችን ግን ትናንትን አስረስቶኛል።ግን የዛሬውን ጠብ የሻረውና ጓደኝነታችን እስከዛሬ ያስቀጠለው ትናንትን ማየታችን ነበር።
👉ትናንት ሀዘናችሁን ተጋርቶ ያፅናናችሁን፤ጉድለታችሁን አይቶ የሞላላችሁን፤ብቸኝነታችሁን ያስረሳችሁን፤ትናንት ከጎናችሁ የነበረውን ሰው በአንድ ቀን ጥፋትና ጥል ያን ሁሉ ፍቅርና መተሳሰብ አፈር አታልብሱት።የትናንት ደግነቱን ለዛሬ ጥፋቱ ስንቅ አድርጋችሁ ቁጠሩ።
👉ጓደኞቻችሁን በይቅርታ መልሳችሁ የራሳችሁ አድርጓቸው።ከተደረገባችሁ ነገር ይልቅ ለተደረገላችሁ ነገር ዋጋ ስጡ።
👉እናንተም ትናንት የረዳችሁን ያገዛችሁን ዛሬ ግን በችግር ያለን ሰው አትርሱት።ውለታ ቢስ አትሁኑ።ዛሬ ደግሞ እርሱ የእናንተ እርዳታ ያስፈልገዋል።ትናንት ከጎናችሁ ነበረ ዛሬ ደግሞ እናንተ ከጎኑ ቁሙ።
👉የትናንቱን አስባችሁ የዛሬን ጥል በይቅርታ ፍቱት።እውነትና ምሕረት ከእናንተ አይራቅ።
“ወዳጅህንና የአባትህን ወዳጅ አትተው፤ በመከራህም ቀን ወደ ወንድምህ ቤት አትግባ፤ የቀረበ ወዳጅ ከራቀ ወንድም ይሻላል።”
— ምሳሌ 27፥10
👉እባክዎን ያለን ጊዜ አጭር ስለሆነ በደል መቁጠር ትተን፤ያለፈውን በይቅርታ ዘግተን በፍቅር እንፈወስ።
ሼር ያደርጉት ዘንድ ይጠየቃሉ🙇♂
ፔጁን ይቀላቀሉ።
👇👇👇👇
https://telegram.me/preac
👉እግዚአብሔርን እመኑት እርሱ አይዋሽም።
👉ይጠብቃችኋል ከእርሱ በላይ ኃይለኛ የለም።
👉ያፅናናችኋል እንደ እርሱ የሚያውቅላችሁ የለም።
👉ይወዳችኋል ልጁን ስለእናንተ ለሞት አሳልፎ ሰጥቶታል።
👉ይሳሳላችኋል ዛሬም ሀዘናችሁ ሀዘኑ ነው።
👉ይደግፋችኋል ክንዱ አስተማማኝ ነው።…………ያሕዌ ትልቅ ነው።
️የእለቱ መልእክት❤️
16/10/2012 ዓ/ም
#የክርስቶስ_የደሙ_እዳ_አለባችሁና_ክፈሉ!!
🗣በብርሃኑ ታምራት(የተተወለት)
👉ክርስትና ከእዳ ነፃ የወጣንበትና ወደ ሌላኛው እዳ የገባንበት ነው።ከዲያብሎስ አገዛዝ ነፃ ብንወጣም ነፃ መውጣታችን ግን ለእግዚአብሔር ለመገዛት ነው።ጌታ ነው የቀየርነው።ያለ ክርስቶስ የሆኑትን የሚገዛቸው ሰይጣን ነው።የዚህ ዓለም ገዢ መባሉም ለዚ ነውና።በክርስቶስ የሆኑት ደግሞ እግዚአብሔርን እንደ ልጅ በክብር፥ እንደ ባርያ በፍቅር ይገዙታለል።እስራኤላውያንን ነፃ ይወጡ ዘንድ ያሕዌ የተዋጋላቸው በኃይል ሳይሆን በፍቅር ለእርሱ እንዲገዙና እንዲያገለግሉ ነው።
👉እርግጥ የክርስቶስን የደሙን ዋጋ መክፈል ማንም አይችልም።ግን በደሙ የዳነና የተፈወሰ ብሎም ዋጋ የተከፈለለት ሰው ሦስት እዳዎች አሉበት።
#የመጀመሪያው_እዳ_በክርስቶስ_ለያሕዌ_ክብር_መኖር
🙏የሞተውና የተነሳው ማንም ለራሱ እንዳይኖር ነው።እግዚአብሔር ምን ደስ ያሰኘዋል? እግዚአብሔርን የሚያከብር ሕይወት የትኛው ነው? ለእግዚአብሔር ተለይቼ በቅድስና የምኖረው እንዴት ነው? የእግዚአብሔር ሀሳብና ፈቃድ ምንድነው? አካሄዴ፥ኑሮዬ፥ንግግሬ፥ሀሳቤ፥ተግባሬ እግዚአብሔርን ያከብረዋልን? መንፈስ ቅዱስን እንዳላሳዝን ምን ላድርግ? እያልን እግዚአብሔርን የማስደሰትና የማክበር እዳ አለብን።
"በዋጋ ተገዝታችኋልና ለራሳችሁ አይደላችሁም፤ ስለዚህ በሥጋችሁ እግዚአብሔርን አክብሩ።" 1ቆሮ.6:19
"በሕይወትም ያሉት ስለ እነርሱ ለሞተውና ለተነሣው እንጂ ወደ ፊት ለራሳቸው እንዳይኖሩ ስለ ሁሉ ሞተ።" 2ቆሮ.5:15
" #ከእኛ_አንድ_ስንኳ_ለራሱ_የሚኖር_የለምና፥ #ለራሱም_የሚሞት_የለም፤" ሮሜ.14:5
#2ኛው_እዳ_በክርስቶስ_የፍቅር_እዳ
❤️ክርስቲያን ማንንም አይጠላም።በመስቀሉ ሥራ የዳነ አማኝ ሁሉን አፍቃሪ ነው።ወንድሙን ይወዳል።ለአሳዳጆቹ ይፀልያል።ክፉን በክፉ አይመልስም።ከማንም ጋር ሂሳብ ተሳስቦ መልካም አይሆንም።ለመመስገንና ለከንቱ ውዳሴ ብሎ ምንም አያደርግም።ከማንም ከፍቅር በቀር እዳ የሌለብን ነፃ የወጣን ቅዱስ ሕዝብ ነን።የደሙ እዳ አለብን።እርሱም በፍቅር መመላለስ ነው።
"#እርስ_በርሳችሁ_ከመዋደድ_በቀር_ለማንም_ዕዳ_አይኑርባችሁ፥ ሌላውን የሚወድ ሕግን ፈጽሞታልና።" ሮሜ.13:8
"ፍቅር ለባልንጀራው ክፉ አያደርግም፤ ስለዚህ ፍቅር የሕግ ፍጻሜ ነው።"ሮሜ.13:10
#3ኛው_እዳ_በክርስቶስ_ይቅር_የማለት_እዳ
✝ክርስቲያን ብዙ የተተወለትና ብዙ የተደረገለት ነው።ይቅር የተባለ ይቅርታን ያውቃል።ይቅር የማይሉ ይቅር አልተባሉም።እንደዚ ጎድቶኝማ ይቅር አልለውም የሚሉ ጌታ በመስቀሉ ሥራ ብዙ እንደተወላቸው የዘነጉ አመፀኞች ናቸው።ይቅር የማለት መብት የለንም ግዴታ እንጂ።ስናጠፋ ይቅርታ መጠየቅ፥ስንበደል ይቅር የማለት ግዴታ አለብን።
👉አንዳንድ ሰዎች ይቅርታ ሲጠየቁ "ይቅር ለእግዚአብሔር" ይላሉ።ስህተት ነው።ይቅር ምትለው ለእግዚአብሔር ብለህ ሳይሆን ለራስህ ብለህ ነው።ሌሎች ደግሞ ይቅር ለእግዚአብሔር ማለታቸው እግዚአብሔር ይበቀለልኝ ማለታቸው ነው።ይቅር ማለት በደልን አለመቁጠር እንጂ በእጅ አዙር የበደለንን በእግዚአብሔር ማስቀጣት አይደለም።
👉ይቅር በሉ።ይቅርታ ጠይቁ።በይቅርታ ተፈወሱ።የይቅርታ እዳችሁን ክፈሉ።
📖 "እርስ በርሳችሁ ትዕግሥትን አድርጉ፥ ማንም በባልንጀራው ላይ የሚነቅፈው ነገር ካለው፥ #ይቅር_ተባባሉ፤ #ክርስቶስ_ይቅር_እንዳላችሁ እናንተ ደግሞ እንዲሁ አድርጉ" ቆላስ.3:13
📖 "ለሰዎች ግን ኃጢአታቸውን ይቅር ባትሉ፥ አባታችሁም ኃጢአታችሁን ይቅር አይላችሁም።" ማቴ.6:15
👉የምክርን ቃል ስለታገሳቹህና እዳችሁን ስለምትከፍሉ ክብሩ ለጌታ ይሁን።።።
እባክዎን ሼር ያርጉት።
ፔጁን ይቀላቀሉ
👇👇👇👇
https://telegram.me/preac
❤️የእለቱ መልእክት❤️
11/10/2012 ዓ/ም
#ሰው_ግን_ፀባዩ_እንዲ_የሚቀያየረው_ምን_ሆኖ_ነው?
🗣በብርሃኑ ታምራት(ምሕረት የበዛለት)
👉ብዙ ጊዜ እኛ ሀበሾች ስሜትን መግለፅ ላይ ደካሞች ነን።በትክክል ሚሰማንን ማንገልፅበት ዋነኛውም ምክንያት ስሜታችንን ከሚረዳው ይልቅ የሚያወራብን ስለሚበዛ ዝምታን እንመርጣለን።ደግሞም እውነት ነው።ወዳጄ ብለህ ምሥጢር ስትነግረው እርሱም ሌላ ወዳጅ አለውና ለማንም እንዳትናገር ብሎ ይናገርብሃል።ያኛውም እንደዛ።ከዚ ሁሉ ከውስጥ ሕመሞቻችን ጋር መቀመጡን እንመርጣለን።
👉እኔ ዛሬ የማስተላልፍላችሁ መልእክት ስለእናንተም ስለሌሎችም ስሜት ጥሩ መረዳት እንድትይዙ ሕይወት ካስተማረኝና ካማከርኩት ለእናንተ ለማካፈል ነው።ቢያንስ ይሄን መልእክት ካነበባችሁ በኋላ ሰውን መርዳት ባትችሉ እንኳን መረዳት ትችላላችሁ፤መረዳት ባትችሉ እንኳን ሌላ ችግር አትሆኑባቸውም።ያኔ እኛም ስሜታችን ሚረዳ ካልሆነ ችግር ማይሆንብን ሰው እናገኝ ይሆናል።
👉የጓደኞቻችንና የወዳጆቻችንን ስሜት መለዋወጥን መረዳት፦
🖌ሁሌም ምናወራውና ምንቀራረበው ሰው ጋር ባለን ግንኙነት የስሜት መለዋወጥ ያጋጥማል።እናም ስሜታቸው ሲለዋወጥ 😡ይነጫነጩብናል፥😶ወሬ ያሳጥሩብናል፥🙄ቶሎ ይሰላቻሉ፥🤐ብቻቸውን መሆን ይፈልጋሉ(ወይ ይጠፉብናል፥ ወይ ስልክም ወይ ቴክስትም አይመልሱም)፥👤ፕሮፋይል ፒክቸራቸውን ቶሎ ቶሎ ይቀያይራሉ ወይ ያነሳሉ፥😳በቀላል ቀልድና ንግግር ቶሎ ይቆጣሉ ይናደዱብናል፥ያኮርፉናል፥እልፍ ሲልም ይሰድቡናል፥ጨከን ብሎ ሲመጣም ይቦልኩናል።በዚ ጊዜ እኛ ምን ተፈጠረ ምን ሆኑ ብሎ ሰዎችን ከመረዳት ይልቅ፤ አይ ሰው ብለን መታዘብና መጣላት ነው ሚቀድመን።ግን ሰው ከመሬት ተነስቶ ስሜቱ እንዲ ሊቀያየር አይችልም።በርግጥ ፀባይና ሥርአት የለሽ፥ ሰው ሚንቁ ባልንጀሮቻችንን ደግ ነገር ከእነሱ አንጠብቅምና ስለእነርሱ እያወራሁ አይደለም።እውነተኞች ወዳጆቻችን፥ቤተሰቦቻችንና የእኛ ምንላቸው ሰዎች ግን በቅንነት ድርጊታቸውን ልናይ ይገባል።
#የወዳጆቻችን_እንደዛ_መሆንና_የስሜት_መለዋወጥ_መንስኤዎች_ምንድናቸው_ስንል፦
💔በሚወዱትና በሚያምኑት ሰው ተከድተው ይሆናል፥🖤በራስ አለመተማመን በሚባል ማንም በማያውቅላቸው በሽታ ተጠቅተው ይሆናል፥🤧የእውነት አሟቸው ሊሆን ይችላል(ራስ ምታት፥ጨጓራ ወዘተ)፥😡ከሆነ ሰው ጋር ተጣልተው ይሆናል ያገኘናቸው፥😭ገንዘብ ማጣታቸውና መቸገራቸውም ስሜታቸውን ይለዋውጠዋል፥👥በጓደኛቸው፥በፍቅረኛቸው ወይም በቤተሰቦቻቸው ጫና በዝቶባቸው ሳለ ይሆናል የደወልናላቸው ወይ የፃፍንላቸው ወይም ያገኘናቸው፥🤦♀🤦ባለፈ ጉዳት ፀፀት ውስጥ እያለፉ ይሆናል፥🤷♀🤷♂ወይ የእናንተ አቀራረብና አወራር አድካሚ ሆኖባቸው ይሆናል፥🐒ስሜቴን ሚረዳኝ ሰው የለኝም በሚል እምነት ላይ ሳሉ ይሆናል የመጣንባቸው፥😔ከቤተሰብ የታመመ ሰው መኖሩ ወይም ቤተሰብ መሃል ባለ ጠብ ተጨንቀው ሳለ ይሆናል የመጣንባቸው፥🥀🍂አንዳንዶች ደግሞ ከሚያፈቅሩት ፍቅረኛቸው ጋር ተለያይተው ሳለ ይሆናል ያገኘናቸው።………#በእነዚህና_በመሳሰሉት_ችግሮችና_ሁኔታዎች_የሚያልፍ_ሰው_ለምን_ፀባዩ_አይቀያየር?_ለምን_ስሜቱ_አይለዋወጥ?
🌚🌝አንዳንድ ሰዎች በሳቅ የሚደብቁት ሕመም አለባቸው።አንዳንዶች በሃይማኖት፥አንዳንዶች በክርክር፥አንዳንዶች በማውራት ብቻ፥አንዳንዶች በመሳቅ በመጫወት ሚደብቁት ችግርና ሕመም አለባቸው።ጊዜው እኔ ወይ እገሌ ጤነኛና ሕመም የለሽ የሆንበት ሳይሆን እርስ በእርስ ምንተካከምበት ጊዜ እንደሆነ አምናለሁ።እንረዳዳ።እንተጋገዝ።ኩርፊያና ጥሉን ያዝ እናርገው።ከውስጥ የሆነ የስሜት መረዳዳትና መተጋገዝ በፍቅር ሆነን እናምጣ።ውስጥ ውስጡን በብቸኝነት፥ውስጥ ውስጡን ተደብቆ በማልቀስ፥ውስጥ ውስጡን ለማን ላውራው በሚያስብል ችግር፥ሕመምና ጉዳት የሚያልፍ ብዙ ሰው አለ።መፍትሔ ባንሆን ችግር አንሁን።እውነተኛ መተሳሰብና ፍቅር ሕመምንና ጉዳትን ሁሉ በክርስቶስ ኢየሱስ ስም ይፈውሰዋል።
"በመጨረሻው ሁላችሁ በአንድ ልብ ሁኑ፥ #የሌላው_መከራ_ለእናንተ_እንደሚሆን_አድርጉ፥ እንደ ወንድሞች ተዋደዱ፥ ርኅሩኆችና ትሑታን ሁኑ፤ ክፉን በክፉ ፈንታ ወይም ስድብን በስድብ ፈንታ አትመልሱ በዚህ ፈንታ ባርኩ እንጂ፥ በረከትን ልትወርሱ #ለዚህ_ተጠርታችኋልና።" 1ጴጥ.3:8-9
እባክዎን ለሌሎች ሼር ያርጉት።
ፔጁን ይቀላቀሉ
👇👇👇👇
https://telegram.me/preac
❤️የእለቱ ድንቅ መልእክት❤️
07/10/2012 ዓ/ም
#ትምህርተ_ሥላሴን_እንዴት_መረዳት_እችላለሁ?
🗣በብርሃኑ ታምራት(ምሕረት
👉👉ልብ ወለድ ባልሆነውና የእኔን መዳን አለመዳን በሚወስነው የሥላሴ ትምህርት አምናለሁ።#ማንኛውም_ሰው_አማኝ_ነኝ_ቢል_በሥላሴ_ግን_ባያምን_የገሃነም_ሲሳይ_ከመሆን_አያመልጥም።
👉አብ፥ወልድና መንፈስ ቅዱስ አንድ አምላክ።በስም፥በአካል፥በግብርና በኩነት ሦስት ናቸው።በመለኮት፥በአገዛዝ፥በሥልጣን፥በፈቃድና በእግዚአብሔርነት አንድ ናቸው።
👉አንድነታቸው ሦስትነታቸውን አይቃወምም፥አይጠቀልልም።ሦስትነታቸው አንድነታቸውን አይቃወምም፤አይከፋፍልም።አንድ ሲሆኑ ሦስት፥ሦስት ሲሆኑ አንድ ናቸው።
👉አብ ወልድን ወልዶታልና ለዘላለም አባቱ ነው።ወልድ ከአብ ተወልዶአልና ለዘላለም ልጅ ነው።መንፈስ ቅዱስ ከአብ ሰርፆአልና ለዘላለም ሕይወታቸው ነው።
👉ያለመለያየት ያቅዳሉ፥ይናገራሉ፥ያደርጋሉ።አብ፥ወልድና መንፈስ ቅዱስ ለዘላለም አንድም ሦስትም ናቸው።ሦስቱም በአብ ልብነት ያስባሉ፥በወልድ ቃልነት ይናገራሉ፥በመንፈስ ቅዱስ እስትንፋስነት ሕያው ሆነው ይኖራሉ።
👉የሥላሴን ምሥጢር መረዳት ዘንድ እነዚህን ነጥቦች አስታውሱ፦
#1_የእምነታችሁን_መሰረት_ቃሉን_አድርጉ፦
📖(ሮሜ.10:17፤ኢሳ.34:16፤1ጴጥ.4:11፤ገላ.1:8-9፤መዝ.87:6)
🖌🖍 እግዚአብሔር ራሱን በቃሉ ገልጦአል።ከቃሉ የተሻለ መረጃና ማስረጃ ከየትም አይመጣም።እግዚአብሔር እንዲ ነኝ ብሎ ነግሮናል።ስለሥላሴ ቃሉ በግልጥ ይናገራል።ከቃሉ ወደ ቀኝም ወደ ግራም ሳትሉ ከሰማችሁ የሥላሴ ትምህርት የተገለጠና የተብራራ እውነት ነው።አብና ኢየሱስ የተለያዩ አካላት ናቸው አይልምን? 2ዮሐ.1:3 መንፈስ ቅዱስ አካል ያለውና እግዚአብሔር አይደለምን? ኢሳ.48:16፤የሐዋ.5:3-4
🖌🖍ቃሉን ሳትቀንሱ ሳትጨምሩ በሙሉ ልባችሁ ብታምኑ የሥላሴ ትምህርት ግልፅ ነው።ሰው የሥላሴን ትምህርት በሎጂክ ለመረዳት ሲጥር ይስታል።
#2_ስለእግዚአብሔር_ሙሉ_ለሙሉ_ልታውቁ_እንደማትችሉ_እወቁ፦
📖(1ቆሮ.13:9፤1ነገ.8:27፤ኢዮብ.11:7-9)
🖌🖍እንኳን ስለፈጣሪ ስለፍጥረት ማናውቀው ብዙ ነገር አለ።ሌላውን ተውትና ስለራሳችሁ ተፈጥሮ በቅጡ ታውቃላችሁ? ሰው ራሱን እንደማያውቅ ማስረጃው ስለሰው ተፈጥሮ የሚሰጠው የተለያየ ትምህርት ነው።አንዱ ሰው ሥጋ ብቻ ነው፥ ሌላኛው ሰው ሥጋና ነፍስ አለው፥ሌላኛ ሰው የሰው ሁለንተና መንፈስ፥ነፍስና ሥጋ ነው ወዘተ።አስተውሉ ሰው ውስብስብ ፍጥረት ሆኖ እንዲ ካለያየ ያሕዌን አውቄ እጨርሳለሁ አትበሉ።
❤️የተገለጠው ለእኛ ነው።ምሥጢሩና ያልተገለጠው ግን ለአምላካችን ሚተው ነው።
👉አብ ወልድን ወልዶታል።ግን እንዴት እንደወለደው ልናውቅ አንችልም።የሥላሴን አለመቀዳደምና በሕልውና መገናዘብ አድንቀን ምናልፈው እንጂ ምናብራራው ነገር አይደለም።ግን ቃሉ አብ ወልድን ቢወልደውም አይበልጠውም።ዮሐ.10:30 እኩል አምልኮ ይቀበላሉ።ራእይ.5:13
👉ከሰማይ ይልቅ ከፍ ያለውን፥ከሲኦል ይልቅ ጥልቅ የሆነውን ሥላሴን ማን ሊያውቀው ይችላል?
#3_እግዚአብሔር_ራሱን_ካልገለጠ_በቀር_በምርምርና_በመላምት_ልታውቁት_አትችሉም፦
📖(ማቴ.11:25-27፤ገላ.1:15:16፤1ቆሮ.1:21፤ኤፌ.1:17፤ዮሐ.17:25፤.1ቆሮ.2:10፤ሮሜ.11:33)
👉በኪሎ ብንመዝነው ሰው ከ3 ኪሎ በማይበልጠው ጭንቅላቱ የዘላለሙን ሥላሴ ተመራምሮ ሊደርስበት አይችልም።በትህትና ሆኖ ግን አንተ ያው አንተ ነህ ራስህን ግለጥልኝ ለሚል አብ ራሱ ራሱንም ልጁንም መንፈስ ቅዱስንም ያብራራልናል።በተረፈ በትእቢት ተነፍታችሁ ለማወቅ ብትሞክሩ ወይ እብድ ወይ መናፍቅ ከመሆን ማንም አይመልሳችሁም።
👉አብን ያየ የለም፥ልጁን ግን ተርኮታል።ኢየሱስን ማንም አያውቀውም፤አብ ልጁን ገልጦልናል።መንፈስ ቅዱስን ማንም አያውቀውም፥ኢየሱስ ግን ለደቀመዛሙርቱ አብራርቶታል።ዛሬም እንዲሁ ነው።በሰማይ የሚኖረው አብ ካልገለጠላችሁ በቀር ምንም ልታውቁ አትችሉም።
#4_በእምነት_ብቻ_የምንቀበለው_መሆኑን_ማወቅ_አለባችሁ፦
👉እምነት በ5ቱ የስሜት ሕዋሳት ምናረጋግጠው ጉዳይ አይደለም።በእምነት እንጂ በማየት አንመላለስም።የተፃፈውን እናምነዋለን።ድንግል ያለወንድ ዘር መውለዷ፥አባት ልጁን አለመብለጡ፥በዘመን አለመቀዳደማቸውን በእምነት ምንቀበለው እንጂ ተመራምረን እንዴት እንደሆነ ተረድተን ምናስረዳበት ነገር አይደለም።አብ፥ወልድና መንፈስ ቅዱስ አንድ አምላክ ብለን እናምናለን።ሥላሴ ከምክንያታዊነት በላይ ነው።ሥላሴ ከምርምር በላይ ነው።ሥላሴ ደኅንነትን የሚወስን እምነትና እውነት ነው።እናምናለን እንመሰክራለን።
#5_ምሥጢር_ነው፦
📖(1ቆሮ.2:7፤1ቆሮ.4:1፤ኤፌ.3:1-6)
👉አንዳንዶች በሥላሴ ቢያምኑም ምሥጢር መባሉን አይስማሙበትም።አለመስማማታቸው ግን ምሥጢር መሆኑን አያስቀረውም።ዋናው በሥላሴ ማመናቸው ነው።ሐዋርያትም ራሳቸውን የእግዚአብሔር ምሥጢር መጋቢዎች አድርገው ራሳቸውን ይቆጥሩ ነበር።1ቆሮ.4:1
👉ምሥጢር ማለት ሁሉም ሰው የማያውቀው ነገር ነው።አንዳንዶች ምሥጢር ማለት ገመና ይመስላቸዋል።ግን ምሥጢር በጎም ይሁን ክፉ ነገር የተደበቀ ነገር ነው።የተደበቀ ማለት ግን ከሁሉም ሰው እንጂ ከቅርብ ወዳጅና ከራስ ሰው ሚደበቅ ምሥጢር የለም።የሥላሴ ትምህርትም፦
🖌በሁሉ ዘንድ አይታወቅምና ምሥጢር ነው፦1.ቆሮ.2:7-8
🖌ለሚጠፉት ሰዎች ተከድኖባቸዋልና ምሥጢር ነው፦ 2ቆሮ.4:3
🖌ለሚወዱት ለሚወዳቸው ለወዳጆቹ ሐዋርያትና ነቢያት እንዲሁም ለእኛ ለአማኞች ብቻ ገልጦልናልና ምሥጢር ነው፦ ዮሐ.15:15፤ቆላስ.1:26፤ኤፌ.3:5-6
❤️ስለዚህ እነዚህን አምስት ነጥቦች እንደ ፍሬም ተጠቅማችሁ ተማሩበት አስተምሩበት።ስለ ሥላሴ አስተምሩ።ስለሥላሴ ስበኩ።
✝ከሥላሴ በቀር አላመልክም።ክብር ለሥላሴ ይሁን።
🕎አብ ወልድ መንፈስ ቅዱስ አንድ አምላክ አሜን።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
✡እባክዎን ሼር ያርጉት።
ፔጁን ይቀላቀሉ
👇👇👇👇
https://telegram.me/preac
❤️የእለቱ መልእክት❤️
02/10/2012 ዓ/ም
😭"#ምነው_ፈተናዬ_በዛ……#መች_ነው_የሚያበቃው?"😭
🗣በብርሃኑ ታምራት(ምሕረት የተደረገለት)
#ሕይወትን_ፈተና_በፈተና_የሚያረጉ_ሰባቱን_መንገዶች_ያውቋቸዋልን?
👉ይሄን ምክር የምትካፈሉ ሁላችሁም እነዚህን መንገዶች በጥንቃቄ አንብቡልኝ።ይወስዳል መንገድ፤ይመልሳል መንገድ።እነዚህን 7 መንገዶች እየተከሉ "አቤቱ ወደ ፈተና አታግባኝ" አያዋጣም።ወደ ፈተና መግቢያ መንገዱን ይዘነው አቤቱ ወደ ፈተና አታግባኝ ምን የሚሉት ፀሎት ነው።
👉#እነዚህን_7_መንገዶች_መከተል_ወደ_ፈተና_እንድትገቡ_ብቻ_ሳይሆን_ከፈተናው_እንዳትወጡም_ይረዱአችኋል።ከገቡማ ቶሎ አለመውጣት ጥሩ ነው።
👉እነዚህ 7 መንገዶች እኔን ጨምሮ ብዙዎቻችንን በፈተና አዙሪት ውስጥ እንድንመላለስ ያደረጉና እንባችንን፥ጭንቃችንን ያበዙ፥እንቅልፍ የከለከሉና የጌታን መንፈስ እንድናሳዝነው ያስደረጉን ናቸው።ኃይልና ሞገስ አልባ ሆነን እንድንሸነፍ አድርገውናል።
#ወደ_ፈተና_መግቢያ_7_አዋጭ_መንገዶች
#1_አለመፀለይ፦
🙏የማትፀልዩ ከሆናችሁ የትኛውም ነገራችሁ ለፈተና የተጋለጠ ነው።አገልግሎታችሁ፥ትዳራችሁ፥ጤናችሁ፥ሥራችሁ፥ወዳጅነታችሁ፥አለኝ የምትሉትና የምትፈልጉት ሁሉ በሰይጣን ኢላማ ውስጥ ይገባል።ስትፀልዩ ኃይልን ትቀበላላችሁ።ፈተናው አያልፍባችሁም፥ይልቁን ታልፉታላችሁ።የሚፀልይ ሰው የመለኮት ጥበቃ ይበዛለታል።ስለዚህ ወደ ፈተና መግባት የምትፈልጉ ሁላችሁም እንዳትፀልዩ።
"#ወደ_ፈተና_እንዳትገቡ_ትጉና_ጸልዩ፤ መንፈስስ ተዘጋጅታለች ሥጋ ግን ደካማ ነው ።" ማቴ.26:41
#2_መታበይ፦
🧟♂ባላችሁ መንፈሳዊነት፥ባላችሁ ሀብት፥ጤና፥ትዳር፥ሥራ መመካትና መታበይ ራስን ለፈተና ማጋለጥ ነው።መታበይ በግልፅ ከአምላክ ጋር መጣላት ነው።ኃይል ያሳጣናል።ስለዚህ ወደ ፈተና ለመግባት ባላችሁ እውቀትና መንፈሳዊነት እንዲሁም አለኝ በምትሉት ማንኛውም ነገር ተመኩ።ያኔ በቀላሉ ወደ ፈተና ትገባላችሁ።መግባት ብቻ አይደለም።ቶሎ አትወጡም።
"#ትሕትናን_እንደ_ልብስ_ታጠቁ፥ #እግዚአብሔር_ትዕቢተኞችን_ይቃወማልና፥ #ለትሑታን_ግን_ጸጋን_ይሰጣል።" 1ጴጥ.5:5
#3_መፍረድ፦
⚖በሌሎች ድክመት፥ውድቀት፥ኃጢአት መፍረድ በፈረድንበት ሰው ኃጢአት ራስን ለፈተና ማጋለጥ ነው።#መፍረድ_እኔ_ብሆን_አላደርገውም_ማለት_ነውና ያሕዌ ኃይሉን ከእኛ ይወስድና ብቻችንን ስለምንሆን በቀላሉ ወደ ፈተና እንገባለን።በፈተናውም በደንብ እንወድቃለን።ስለዚህ ከፈተና አዙሪት ለመግባት ብሎም ላለመውጣት በሰው ፍረዱ።
" #ስለዚህም_በጨለማ_የተሰወረውን_ደግሞ_ወደ_ብርሃን_የሚያወጣ_የልብንም_ምክር_የሚገልጥ_ጌታ_እስኪመጣ_ድረስ_ጊዜው_ሳይደርስ_አንዳች_አትፍረዱ፤ በዚያን ጊዜም ለእያንዳንዱ ምስጋናው ከእግዚአብሔር ዘንድ ይሆናል።" 1ቆሮ. 4:5
#4_የድፍረት_ኃጢአት፦
👉 በስህተትም በድፍረትም ይሰራ ኃጢአት ኃጢአት ነው።ሆኖም የድፍረት ኃጢአት ለሰይጣን ቅርብ መሆን ነውና በቀላሉ ላንወጣ ወደ ሩቁ የፈተና ሸለቆ ይወረውረናል።
"#የድፍረት_ኃጢአት_እንዳይገዛኝ_ባሪያህን_ጠብቅ፤ #የዚያን_ጊዜ_ፍጹም_እሆናለሁ፥ #ከታላቁም_ኃጢአት_እነጻለሁ።" መዝ.19:13
#5_አለመምረጥ፦
👉ሕይወት በምርጫ የተሞላች ናት።እያንዳንዱ ምርጫችን ለፈተና የማጋለጥ እድሉ ሰፊ ነው።ጓደኞቻችሁን፥የትዳር አጋራችሁን፥የምታነቡትን፥የምታዩትን፥የምትሰሙትን፥የምታወሩትን፥የምትውሉበትን፥የምትበሉትን፥የምታስቡትን አስተውላችሁ ምረጡ።ሁሉ የኔ ነው ማለትና ምርጫን አለመጠንቀቅ ዋጋ ያስከፍላችኋል።
"በቀረውስ፥ ወንድሞች ሆይ፥ #እውነተኛ_የሆነውን_ነገር_ሁሉ፥ #ጭምትነት_ያለበትን_ነገር_ሁሉ፥ #ጽድቅ_የሆነውን_ነገር_ሁሉ፥ #ንጹሕ_የሆነውን_ነገር_ሁሉ፥ #ፍቅር_ያለበትን_ነገር_ሁሉ፥ #መልካም_ወሬ_ያለበትን_ነገር_ሁሉ፥ በጎነት ቢሆን ምስጋናም ቢሆን፥ #እነዚህን_አስቡ"
#6_ሁሉን_ማመን፦
👉 ዜናውን፥ሁኔታውን፥ሕልምና ቅዠታችሁን፥የጠላትን ወሬና ዛቻ፥ሰውን ሁሉ ማመን ወደ ፈተና ያስገባችኋል።#አጉል_እምነት_ሌሊታችንን_ያረዝመዋል።ሁሉን አትመኑ።ወደ ፈተና ለመግባት ግን ሁሉን እመኑ።
" #የዋህ_ቃልን_ሁሉ_ያምናል፤ #ብልህ_ግን_አካሄዱን_ይመለከታል።" ምሳ.14:15
#7_ከቃሉ_መራቅ፦
👉የመንፈስ ሰይፍ የሆነውን የያሕዌን ቃል ያልያዘ ሰው ያለ ትጥቅ የዘመተ ሞኝ ወታደር ነው።ለሰይጣን ሽንገላ፥ለሕይወት ፈተና፥ለሟርተኞች ድግምት ዓይነተኛና መለኛ መድኃኒት ቃሉ ብቻ ነው።ወደ ፈተና ለመግባትና አወዳደቃችሁ እንዲከፋ ቃሉን ራቁት።
" የዲያብሎስን ሽንገላ ትቃወሙ ዘንድ……የመዳንንም ራስ ቁር #የመንፈስንም_ሰይፍ_ያዙ_እርሱም_የእግዚአብሔር_ቃል_ነው"
"#አንተን_እንዳልበድል፥ #ቃልህን_በልቤ_ሰወርሁ" መዝ.119:11
👉ምነው ፈተናዬ በዛ ያልነው በእርግጠኝነት በ7ቱ መንገድ እየተጓዝን ስለሆነ ነው።ሰባቱን ትታቹህ ከሰባቱ በአንዱ ብቻ ራሱ መገኘት ሕይወትን ፈተና ያደርጋታል።
እባክዎን ሼር ያርጉትና አንድን ሰው ከፈተና ይታደጉት።
ፔጁን ይቀላቀሉ
👇👇👇👇
https://telegram.me/preac
❤️የእለቱ መልእክት❤️
30/09/2012 ዓ/ም
#የውዴ_ድምፅ
🗣በብርሃኑ ታምራት(ምሕረት የተደረገለት)
👉 ኢየሱስ የጠፋሁትን ፈልጎ መጥቶ አገኘኝ።ፊት ለፊቴም ቁጭ ብሎ ያናግረኝ ጀመር።ሰው የናቀኝን እኔን ፤ኃያላን የሚገዙለት ኢየሱስ እያናገረኝ ነው።ንግግሩን የጀመረው <<ልትድን ትወዳለህን?>>በማለት ነበር።እኔም <<መዳን እወዳለሁ፤ግን አንተ እኮ ፃድቅ ፈራጅ ነህ።ከኃጢአተኞች ዋና የሆንኩትን እኔን እንዴት ይቅር ትለኛለህ??>> አልኩት።ጌታ ኢየሱስም ፈገግ ብሎ፦<<ልጄ ሆይ፦የሰራሁልህን ሥራ በማመንህ ብቻ ልትድን ትችላለህ>>አለኝ።እኔ ግን ማመን አልቻልኩም።አምኜ ብቻ እንዴት እድናለሁ? አልኩ በልቤ።ኢየሱስም የልቤን አውቆ፦<<አይዞህ ልጄ እመን ብቻ እንጂ አትፍራ፤አዝኜልሀለሁ፤ራርቼልሀለሁ፤ባፈሰስኩልህ ደም ንፃ>>አለኝ።ውስጤ በሀሴት ሲሞላ ታወቀኝ፤አንድ ከባድ ሸክም ከላዬ ላይ ተነሳ።ልጁ አደረገኝ፤አሁን እኔ የእርሱ ነኝ።እርሱም የእኔ ነው።የወደደኝን ወደድኩት።
✝ #ኢየሱስ_በማስቀጠል_እንዲህ አለኝ፦
❤️❤️መስቀልህን ተሸክመህ ተከተለኝ፤
❤️❤️እንደሞትኩልህ ኑርልኝ፤
❤️❤️የሰጠውህን አደራ ፈፅም፤
❤️❤️ስለእኔ ክብር ክብርህን ጣል፤
❤️❤️ሳይግገባህ ወድጄሃለሁና ጠላትህን ውደድ፤
❤️❤️ ለደስታህ እንዳነባሁ አንተም ላዘኑት ድረስ
❤️❤️ ጉብኝቴ እንዲበዛልህ የባዘኑትን ሰብስብ
❤️❤️ ሕይወቴን ሰጥቼሀለሁና ያለህን አካፍል
❤️❤️ እኔ ብቻ ትልቅ ነኝና አትታበይ(አትኩራ)
❤️❤️ ይመራህ ዘንድ መንፈሴን ሰጥቼሃለሁና ድምፁን ስማ፤ምሪቱን ተከተል
❤️❤️ ቃሌን ጠብቅ
❤️❤️ ኃጢአትህ ለሞት አብቅቶኛልና ኃጢአትን ተፀየፍ
❤️❤️ ወንድምህን ውደድ
❤️❤️ ሁሉን ለክብሬ አድርግ
❤️❤️ ስመጣ እስክወስድህ ፅና በርታ፤አይዞህ>> አለኝ።
👉 ጌታ ኢየሱስ በዐይኔ ፊት ተሰወረ።ያ ማራኪ ድምፁ ግን አሁንም በጆሮዬ አለ።ማፅናናቱ ከበበኝ።ትዛዙ ያነቃኛል።እንዴት እርሱን እንድመስል እንደሚወድ በትዛዙ ውስጥ ይሰማኛል።
👉 ውዴ ኢየሱስ ናልኝ።አጠገቤ ሆነህ ሁሌ አውራኝ።ከከንፈሮችህ ሞገስ ይፍፈሳል።ድምፅህን አብዛልኝ።አቅሜ እርሱ ነውና።
#እነሆ_የውዴ_ድምፅ_በተራሮች_ላይ_እየዘለለ_፤ #በኮረብቶችም_ላይ_እየተወረወረ_ሲመጣ_ይሰማኛል። መኃ.2:8
እባክዎን ሼር ያርጉት።
ፔጁን ይቀላቀሉ
👇👇👇👇👇
https://telegram.me/preac
❤️የእለቱ መልእክት❤️
23/09/2012 ዓ/ም
#በቦታው_ስንሆን_አይመስለንም
🗣በብርሃኑ ታምራት
👉ልጅ እያለሁ አንድ የዲቁናና የመፅሀፍ ቅዱስ መምህር ነበሩኝ።ፆም እንድለማመድ በጣም ነበር ሚያበረታቱኝ።እናም አንድ ቀን ፁም ብለውኝ እኔ ግን ልጅ ስለነበርኩ ያን ፆም አልቻልኩም ነበር።እናም ሄጄ የኔታ አልኳቸው።"አቤት ልጄ" "የኔታ ፆሙን አልቻልኩም ልብላ" አልኳቸው። "ምነው" አሉኝ።"እየራበኝ ነው" አልኳቸው።የኔታም ፈገግ ብለው፦ "ልጄ ሳትራብ እንዴት ትፆማለህ?" ብለው ጠየቁኝ።እኔም ሳልራብ መፆም መፈለጌ ለራሴ ገርሞኝ ታገስኩት።ሰአቱ ሲደርስ የቀረበልኝ ሚያጠግበኝ አይመስለኝም ነበር።ስጠግብ ደግሞ የወጥ ሺታ እስክጠላ ድረስ ሚርበኝ አይመስለኝም ነበር።ሲርበኝ የጥጋብ ስሜት ምን እንደሆነ ማስታወስ አልችልም።ስጠግብ ርሀብን እረሳለሁ።
👉እያወቅን ግን በቦታው ስንሆን ምንረሳው ነገር አለ።
👉ወጣት ስንሆን ምንሞት አይመስለንም።ስናጣ ምናገኝ አይመስለንም።ስናገኝ ደግሞ ምናጣ አይመስለንም።ግን ሕይወት የራሷ አዙሪት አላት።ያጣ ያገኛል።ያገኘም ያጣል።የተዋደደ ይጣላል።የተጣላም እንደገና ይዋደዳል።ግን በቦታው ስንሆን አይመስለንም።
👉በምንወደው ሰው የተከዳን ቀን ሰው ሁሉ እኩል ከሀዲ ይመስለናል።ያኔ በቦታው ስንሆን ሰው አይታመንም።ፍቅር በፍቅር የሆን ቀን ደግሞ ሰው የራሱ ችግር ስላለበት ነው እንጂ ታማኝ ሞልቶ እንላለን።በቦታው ስንሆን አይመስለንም።
👉ታመን ስንሰቃይ ፈውስ ያለን፥እንደገና ምንቆም አይመስለንም።ጤነኛ ስንሆን ደግሞ ምንታመም አይመስለንም።
👉ሰዎች የተቀበሉን ቀን ሚቃወሙን አይመስለንም።ሰው የተቃወመን ቀን ደግሞ የሚቀበለን ያለን አይመስለንም።የጥቂት ሰዎችን ጥላቻ አይተን ሕዝቡ ሁሉ የጠላን፥የሚወደን እንደሌለ ያሰብንበት ጊዜ ብዙ ነው።
👉በልዩ ልዩ የሀዘን ሸለቆ ምታልፉ ወገኖቼ አሁን በሀዘኑ ቦታ ስለሆናችሁ ምትፅናኑ፥እንደገና መሳቅ ምትችሉ አይመስላችሁ ይሆናል።ግን እንደገና ትፅናናላችሁ፥ትስቃላችሁ።ስብርብሬ ወጦአል ልቤ አይፈወስም በምንልበት ሁኔታ ውስጥ ስንገኝ ምናገግም አይመስለንም።ግን የማይነጋ ሌሊት የለም።ሕይወት ይቀጥላል።
👉አሁን ደግሞ ጊዜያችሁ ሆኖላችሁ፥በለስ ቀንቷችሁ ደስ የተሰኛችሁ ከቀኑ 11:00 ሰአት በኋላ ምሽት ይመጣልና አትታበዩ።ሳይመሽ ቀንህን አታድንቅ ይላሉ ነጮች።ስትጠግቡ ማይርባችሁ፥ስትደሰቱ ማታዝኑ፥ስትገናኙ ማትጣሉ፥ስትዋደዱ ማትለያዩ እየመሰላችሁ ለምድር ለሰማይ አስቸጋሪ አፍለኛ አትሁኑ።እስከ ቀኑ 11:59 ድረስ ስለ ቀኑ ምንም ማለት አይቻልም።በቦታው ስንሆን ባይመስለንም እውነታው ይሄ ነው።
👉እኛ ሀዘንም ሆነ ደስታ የማንችል ደካሞች ስለሆንን እንዲ ብላችሁ ፀልዩ፦ ጌታ ሆይ እኔ እንኳን ሀዘንን ደስታን ምችልበት አቅም የሌለኝ ደካማ ነኝ።በመንፈስ ቅዱስ ኃይል ሁሉንም የምችልበትን አቅምና ፀጋ ስጠኝ፤ በኢየሱስ ስም አሜን።
👉አሁን ባለንበት ሁኔታ የስደተኞች ሰቆቃ፥የእርስ በእርስ ግጭቱ፥ የኮሮና ቫይረስ ስርጭት ሚቆም አይመስልም።በቦታው ስንሆን አይመስለንም።ግን ሁሉም ያበቃል።የማይነጋ ሌሊት የለም።
እግዚአብሔር አዋቂ ነው አዋቂ ነው
ሥራችንን ይመዝናል
ዋጋችንን ይተምናል
ከፋኝ ብለን አናጉረምርም ስለሁሉ እናመስግነው
ደላኝ ብለን አንታበይ እግዚአብሔር አዋቂ ነው
📖📖📖📖📖📖📖📖📖📖
(ወደ ፊልጵስዩስ ሰዎች ምዕ. 4)
----------
12፤ መዋረድንም አውቃለሁ መብዛትንም አውቃለሁ፤ በእያንዳንዱ ነገር በነገርም ሁሉ መጥገብንና መራብንም መብዛትንና መጉደልን ተምሬአለሁ።
13፤ ኃይልን በሚሰጠኝ በክርስቶስ ሁሉን እችላለሁ።
📖📖📖📖📖📖📖📖
(መጽሐፈ ምሳሌ ምዕ. 30)
----------
7፤ ሁለትን ነገር ከአንተ እሻለሁ፥ ሳልሞትም አትከልክለኝ፤
8፤ ከንቱነትንና ሐሰተኛነትን ከእኔ አርቃቸው፤ ድኅነትንና ባለጠግነትን አትስጠኝ፤ ነገር ግን የሚያስፈልገኝን እንጀራ ስጠኝ፥
9፤ እንዳልጠግብ እንዳልክድህም። እግዚአብሔርስ ማን ነው? እንዳልል፤ ድሀም እንዳልሆን እንዳልሰርቅም፥ በአምላኬም ስም በሐሰት እንዳልምል።
እባክዎን ሼር ያርጉት።
ፔጁን ይቀላቀሉ
👇👇👇👇
https://telegram.me/preac
❤️የእለቱ መልእክት❤️
21/09/2012 ዓ/ም
#መፅሀፍ_ቅዱስን_የማንበብ_8ቱ_ጉዳቶች
🗣በብርሃኑ ታምራት(ምሕረት የተደረገለት)
(እድሜያችሁ ከ18 ዓመት በታች የሆናችሁና ችኩሎች እባካችሁ አታንብቡት)
👉ብዙ ሰዎች መፅሀፍ ቅዱስን ማንበብ ይጠቅማል ይላሉ።እናም ያነባሉ።ግን ይሄ መፅሀፍ "ጉድ" ሲሰራቸው አይተናል።እኔ ለጊዜው ምክርን በትህትና ለሚቀበሉ እንዲ እመክራለሁ።ሚሰማ ይስማኝ።ጥቅሙ ለራሱ ነው።ለጊዜው ስምንቱን ጉዳቱን ብቻ እዘረዝራለሁ።ተከተሉኝ።
#1_ፈሪ_ያደርጋችኋል፦
👉እንደ ልብ ስታደርጉት የነበረውን ኃጢአት ያስተዋችኋል።ደፋርና ዓይና አውጣ የነበራችሁትን ሰውን ምታፍሩ፤እግዚአብሔርን ምትፈሩ ያረጋችኋልና ተውት አታንብቡት።ከሞት በኋላ ሕይወትና ለፍርድ መቅረብ እንዳለ ነግሮ ሕይወታችሁን እግዚአብሔርን በመፍራት እንድትኖሩ ያረጋችኋል።እግዚአብሔርን ፈሪ ስለምትሆኑ አታንብቡት።ምትበሉትን ብትመርጡ አንሷችሁ፤ምትናገሩትን ለምን ትመርጣላችሁ? ይሄ መፅሀፍ ጉደኛው ስለምትናገሩት ከንቱ ነገር ሳይቀር ትጠየቃላችሁ ብሎ እርፍ።ስሙኝና አታንብቡት።
#2_ውሸታችሁን_ያስጥላችኋል፦
👉 የኔ ነው ያላችሁትን፤ዘመናት ያስቆጠረውን፤ከእናት ከአባት የወረሳችሁትን ውሸት ቢያስጥላችሁስ? እባካችሁ አታንብቡት።የተከበረ ውሸታችንንማ በመፅሀፍ ቅዱስ መነጠቅ የለብንም።ጎበዝ ይሄን እውነት እውነት ሚናገር መፅሀፍ አታንብቡት።ተናግሬያለሁ።ከባለቤቱ ሚያውቅ ቡዳ ነው እንደሚባለው።ከአባቶች በላይ ራሱ አዋቂ ነኝ ይላል።ሆ ደፋር።አባቶችና የሥነ መለኮት ምሁራን እንዲሁም አንዳንድ የመፅሀፍ ቅዱስ አሳታሚዎች እርሱን እናርመዋለን ብላችሁ ቃል እየተካችሁ ከምትደክሙ።መፅሀፍ ቅዱስን የማንበብን ጉዳት አስጠኑን።ከዛ ለማን ብለን እናነባለን።
#3_የፅድቅ_ባሪያ_ያረጋችኋል፦
👉 ማነው ባሪያ መሆን ሚፈልግ? ይሄን መፅሀፍ አንብባችሁ እንደልማድችሁ መዋሸት፥ማመንዘር፥መክዳት፥ማጭበርበር አትችሉም።አስቡት እስኪ።እንዴት ሳትዋሹ ትኖራላችሁ? በሉ በሉ ይሄን የፅድቅ ባሪያ ሚያረጋችሁን፥ቅድስና እያለማመደ ከለመዳችሁት የሕይወት አይነት ሚያወጣችሁን ይሄን መፅሀፍ እንዳትነኩት።ሰምታችኋል።እንኳን ልታነቡት እንዳትነኩት።
#4_ራሳችሁን_ላይ_አተኩሩ_ይለናል፦
👉ወንድሞቼና እህቶቼ እኛ የለመድነው ሰው መገምገምና በሰው መፍረድ።እስኪ ምን ይሁን ብለን ነው ራሳችን ላይ ምናተኩረው? እኛ በሰው መፍረዱ ተመችቶናል።ይሄ መፅሀፍ ግን ለፍርድ ምትቀርቡት በግል ነው፥በግላችሁ ባረጋችሁት ነገር ነው ምትጠየቁት እያለ ጨቅጭቆ ሊገለን ነው።ከሰማችሁኝ አታንብቡት።
#5_መሸወዳችሁ_ቢገባችሁስ?፦
👉 ሰይጣን የበላባችሁን ጊዜ፥ጉልበትና ገንዘብ እንድታውቁ አርጎ ጉድ ይሰራችኋል።ተናግሬያለሁ በኋላ፤የሃይማኖት መሪዎች ራሱ ምን ብለው እንደሸወዷችሁ አውቃችሁ ከምትናደዱ፤ባታነቡትስ? ምክሬን ስሙ ይሄን ጉደኛ መፅሀፍ አንብባችሁ ከምትነቁ፤ ጎመን በጤና ብላችሁ ስትሸወዱ ብትኖሩ ይሻላችኋል።ሆ እንዳታነቡት።
#6_ኢየሱስ_ኢየሱስ_ቢያስብላችሁስ? ፦
👉እኔ መፅሀፍ ቅዱስ አንብቦ ኢየሱስ ኢየሱስ ያላለ አላየሁም።ለስንቱ ስንዘምር የኖርነውን፥ለስንቱ ምንሰግደውን ሰዎች ሊያስተወን ነው እንዴ ይሄ ደፋር።በሉ ሺ ጌቶቻችንን አስጥሎ አንድ ጌታ ሚያስተምረውን ይሄን መፅሀፍ እንዳታነቡት።እነርሱ ምን አሉን።አንተ መፅሀፍ ነቅቼብሃለሁ።ሳነብህ ታያለህ ደግሞ።
#7_ልክ_ልኬን_ለምን_እነገራለሁ፦
👉 ለሰው እንደ መንፈሳዊ ሰው ታይቼ፤ተከብሬ ምኖረውን ልክ ልኬን እየነገረ ሚያሸማቅቀኝን መፅሀፍማ አላነብም።እናንተም እንዳታነቡት።ሌባውን ሌባ፤ ርኩሱን ርኩስ፤ፃድቁን ፃድቅ የማለት አባዜ የተጠናወተውን ይሄን መፅሀፍ እንዳታነቡ።ቀጥሎ ደግሞ እኮ ንስሐ ግቡ ይላል።ጎበዝ ባይነበብስ?
#8_ለሰው_ሰው_ሁኑ_እያለ_ያስጨንቀናል፦
👉ያዘነ አፅናና፥የታመመና የታሰረ ጎብኝ፥ፍርድ ተጓደለ፥ደሃ ተበደለ በል ይላል።መፅሀፉን አታንብቡ ራስወዳድነታችሁን ያስተዋችኋል።ግዴለም አታንብቡት ራስወዳድነታችሁ ያዋጣችኋል።ቢበዛ ያሕዌ ቢፈርድባችሁ ነው።እንዳታነቡት ብያለሁ።
👉👉ብዙ ጉዳቶች አሉት በጠቅላላው።የማውቀውን ጉዳቶቹን ሁሉ ብነግራችሁ ተናዳችሁበት ልታቃጥሉት ሁሉ ትችላላችሁ።በአጭሩ ግን መፅሀፉን አታንብቡት።አንብባችሁት አጥፍታችኋል ብሎ ቢገስፃችሁስ? ታጠፋላችሁ ብሎ ቀድሞ ቢመክራችሁስ? ኃጢአተኝነታችሁን ነግሮ ንስሐ ግቡ ቢላችሁስ? ዓይናችሁን ከምድራዊ ነገር ላይ አስነስቶ ሰማይ ላይ ቢተክለውስ? ኢየሱስን አሲዞ ጣኦቶቻችሁን ቢያሰብራችሁስ? ኧረ እንዳታነቡት።
👉👉ደብተራዎች፥ጠንቋዮች፥ሀሰተኛ ነቢያቶችና ሀሰተኛ አስተማሪዎች፥መናፍቃን ይሄ ሕዝብ ይሄን መፅሀፍ ከማንበቡ በፊት አዚም አርጉበት።ካልሆነ ጉዳችሁ ነው ሚፈላው።
👉ይሄን ምክሬን እባካችሁ ለሌሎችም ሼር አርጉት።
ጨረስኩ።
ፔጁን ይቀላቀሉ
👇👇👇👇
https://telegram.me/preac
❤️የእለቱ መልእክት❤️
19/09/2012 ዓ/ም
#ባለጉዳይ_ብቻ_አትሁኑ
🗣በብርሃኑ ታምራት(ምሕረት የተደረገለት)
👉ብዙ አማኞች ባለጉዳይ ናቸው።አገልጋይ ለነርሱ የነርሱ ጉዳይ አስፈፃሚ ሲሆን የያሕዌ ቤት ደግሞ መሥሪያ ቤት ሆኗል።
💔ክርስቲያን ባለጉዳይ ብቻ ሲሆን እንደማየት አሳዛኝ ነገር የለም።
#ባለጉዳይ_ክርስቲያኖች_ምን_ይፈልጋሉ?
#1_እግዚአብሔርን_ለጉዳይ፦
👉 እግዚአብሔርን የሚፈልጉት ልጅ እስኪሰጥ፤ትዳር እስኪሰጥ፤ፈውስ እስኪያመጣ፤በሀብት እስኪባርክ ብቻ ነው።ከእግዚአብሔር ጋር በጥቅም የሚተሳሰሩ አማኞች ናቸው።እግዚአብሔርን የሚፈልጉት ጉድለታቸውን እንዲሞላና እነርሱ ያልቻሉትን ጉዳይ እንዲፈፅምላቸው ብቻ ነው።ሲፀልዩ እንኳን የማይችሉትንና ያቃታቸው ነገር ሲገጥማቸው ብቻ ነው።የእግዚአብሔርን እንጂ እግዚአብሔርን አይፈልጉትም።እውነተኛ አማኞች ግን ከእግዚአብሔር ጋር የተሳሰሩት በአባትና በልጅነት ነው።ችግር አያቀራርባቸውም፤ምቾት አያለያያቸውም።
" እግዚአብሔርም ለእስራኤል ቤት እንዲህ ይላልና። #እኔን_ፈልጉ፥ በሕይወትም ትኖራላችሁ፤ "
(ትንቢተ አሞጽ 5:4)
#2_አገልጋይን_ለጉዳይ፦
👉 ባለጉዳይ ክርስቲያኖች አገልጋዩን አይፈልጉትም።የአገልግለን ጥያቄ ይጠይቁታል እንጂ ምን ትበላለህ ብለው አይጠይቁትም።እንደውም አንዳንዶቹ አገልጋይ ተመጋቢ ሁሉ አይመስላቸውም።ያስፀልያሉ፤ይጠይቃሉ፤ያደንቃሉ፥ይገለገላሉ።ግን ወደ ሕይወቱ ገባ ብለው ጓዳውን አያዩም።እውነተኛ አገልጋይ ተረስቶ የሰውም የመላእክትም መጫወቻ ቢሆን እንኳን የጠራው አይጥለውም።ግን መንፈሳዊን ነገር ከአገልጋዩ እያጨዱ፤ሥጋዊን ነገር ለአገልጋይ የማይዘሩ እዳ አለባቸው።
(1ኛ ወደ ቆሮንቶስ ሰዎች ምዕ. 4)
----------
8፤ አሁን ጠግባችኋል፤ አሁንስ ባለ ጠጎች ሆናችኋል፤ ያለ እኛ ነግሣችኋል፤ እኛ ደግሞ ከእናንተ ጋር እንድንነግሥ ብትነግሡ መልካም ይሆን ነበር።
9፤ ለዓለም ለመላእክትም ለሰዎችም መጫወቻ ሆነናልና፤ እግዚአብሔር እኛን ሐዋርያቱን ሞት እንደ ተፈረደባቸው ሰዎች ከሁሉ ይልቅ የኋለኞች እንዳደረገን ይመስለኛልና።
#3_አገልግሎትን_ለጉዳይ፦
👉 አገልጋዩ አገልግሎትን ለጥቅሙ፥ለነገ ሕይወቱ መስተካከል፥ለገንዘብ ብሎ በጉዳይ ሲያገለግል እንደማየት ልብ ሰባሪ ነገር የለም።አገልግሎት ለክብራችን ሳይሆን ለክብሩ ነው።ለማገልገል እንጂ ለመገልገል አልተጠራንም።ባለጉዳይ አንሁን።የአገልጋይ ትልቁ ጉዳዩ የእግዚአብሔር ክብር፤የሰው ልጅ መዳን ነው።ያሕዌ ሚከፍለንን ብድራት እያሰብን እናገልግል።
(የማቴዎስ ወንጌል ምዕ. 10)
----------
7፤ ሄዳችሁም። መንግሥተ ሰማያት ቀርባለች ብላችሁ ስበኩ።
8፤ ድውዮችን ፈውሱ፤ ሙታንን አስነሡ፤ ለምጻሞችን አንጹ፤ አጋንንትን አውጡ፤ #በከንቱ_ተቀበላችሁ፥ #በከንቱ_ስጡ።
#4_ጓደኝነትን_ለጉዳይ፦
👉ባለጉዳይ ክርስቲያኖች የልብ ጓደኛ የላቸውም።በሆነ ነገር ያግዘናል ከሚሉት ሰው ሥር አይጠፉም።ጓደኛ ሲሆኑ ሊያስፈፅሙት ላለው ጉዳይ አቅደው ነው።የድሃ ጓደኛ የላቸውም እንዲኖራቸውም አይፈልጉም።ከማን ምን እንደሚጠቀሙ እንጂ እነርሱ ምን እንደሚጠቅሙ አያስቡም።በመጨረሻም የቀረባቸውን ሰው ከተጠቀሙበት በኋላ ይተውታል ወይም ይክዱታል።ከነዚ ባለጉዳይ ክርስቲያኖች ጋር የተወዳጀ ሰው የልብ ስብራት ይገጥመዋል።እውነተኛ አማኞች ግን ከሁሉ ጋር በሰላም ይኖራሉ።ምን እንደሚጠቅሙ እንጂ ምን እንደሚጠቀሙ አያሰሉም።
(ወደ ፊልጵስዩስ ሰዎች ምዕ. 2)
----------
3፤ ለወገኔ ይጠቅማል በማለት ወይም በከንቱ ውዳሴ ምክንያት አንድ እንኳ አታድርጉ፥ ነገር ግን እያንዳንዱ ባልንጀራው ከራሱ ይልቅ እንዲሻል በትሕትና ይቍጠር፤
4፤ #እያንዳንዱ_ለራሱ_የሚጠቅመውን_አይመልከት፥ #ለባልንጀራው_ደግሞ_እንጂ።
#5_ትዳርን_ለጉዳይ፦
👉ባለጉዳይ ክርስቲያኖች ትዳር ሲይዙም ምን አለው? ምን አላት? እንጂ እግዚአብሔር አለው? እግዚአብሔር አላት? አይሉም።ወደ ውጭ ለመሄድ፤ኑሮን ለመቀየር ነው ትዳሩ የተፈለገው።ተፋቅረውና ተፈቃቅደው ድሃ እንኳን ቢሆኑ አብረን ሰርተን እንለወጣለን ማለት ፋሽኑ ሳያልፍበት አልቀረም።አብዛኛው የትዳር ትስስር የጥቅምና የጉዳይ ሆኗል።
❤️ተወዳጅ ሆይ አንተ ግን ባለጉዳይ ብቻ አትሁን።ሕይወትህ ለእግዚአብሔር ክብር፤ለሰው ጥቅም የተዋጀ ይሁን።እግዚአብሔርንና ሰዎችን ራሳቸውን ፈልጋቸው።እነርሱ ከተገኙ ከእነርሱ የሆነው አያመልጥህምና።
እባክዎን ሼር ያርጉት።
ፔጁን ይቀላቀሉ
👇👇👇👇
https://telegram.me/preac
❤️የእለቱ መልእክት❤️
11/09/2012 ዓ/ም
#ምርጫ_ብሎ_ዝም…… #ኧረ_ምንድነው_ጉዱ?
🗣በብርሃኑ ታምራት(Justified Sinner)
👼👼👼👼👼👼👼👼👼
👉👉ለራስ ሲቆርሱ እንደ ሚባለው ምርጥ ምርጡን ለእኛ ነው ምናስበው።የትዳር አጋር ስንፈልግ መስፈርታችን ለእኛ የሚመቸንን ነው።ማንም ሰው ያልተማረ፥ደሃ፥መልከ ጥፉ፥ሱሰኛ፥ቅናተኛ፥ተጨቃጫቂ ወይ ተደባዳቢ፥ሌባ አገባለሁ ብሎ መስፈርት አያወጣም።አውጥቶም ይሄ ነው መስፈርቴ ቢል አፋፍሶ አማኑኤል ከመውሰድ ውጭ አማራጭ ያለ አይመስለኝም።በመስፈርቱ መሰረትም ቢያገባ የምንለው የማሽሟጠጫ ቃል……"ምርጫ ብሎ ዝም……ኧረ ምንድነው ጉዱ" ነው የምንለው።እህታችን ወይ ወንድማችን ከሆነ ደግሞ ጥረን ግረን ምናፋታው ይመስለኛል።
👼👼👼👼👼👼👼👼
አንዳንዶች ደግሞ ምርጫ አብዝተው ምራጭ ላይ ይወድቃሉ።በፊት ቀይ ካልሆነ እንዳላለች አሁን ዋናው ልቡ ነው፤ ልቡ ይቅላ ትላለች።የተማረች ካልሆነች ሲል እንዳልነበር አግብቼ አስተምራታለሁ ይላል።ሰው ራስ ወዳድ ነውና ምርጥ ምርጡን ለራሱ ቢመርጥ አይገርምም።ሚገርመው ተቃራኒውን ሲመርጥ ነው።
🙆♂🙆♂🙆♂🙆♂🙆♂🙆♂🙆♂🙆♂
የእግዚአብሔር ምርጫ ግን አማኑኤል እንደ ወሰዳችሁት ሰው ነው።
🙇🙇♀🙇🙇♀🙇🙇♀🙇
በፊት ጌታን አገኘሁት እል ነበር።ለካ የጠፋሁት እኔ ነበርኩ።ያገኘኝ ደግሞ እርሱ ነው።
👉ጳውሎስ ጉዴን እስኪነግረኝ ድረስ ቅን ሰለነበርኩ ጌታ ረዳኝም እል ነበር።
#እስኪ_በጌታ_የሆኑት_እነማን_እንደሆኑ_እንያቸው፦
#ጥበብ_የሌላቸው፦ በጌታ የሆኑት በጥበባቸው የታወቁ የባቢሎን(የዓለም) ሰዎች አይደሉም።
#ደካሞች፦ ሮጠው የሚቀድሙ፥ታግለው የሚጥሉ፥ወርውረው የሚያርቁ ኃያላንን አልመረጠም።
#የባላባት_ልጆች_ያልሆኑትን፦ ዛሬ የኔ ዘር ነው ምርጥ ዘር በምንባባልበት ጊዜ እንኳን፤የባላባት ዘር ጌታ አይመርጥም።ዘርህ ከእሥራኤል ይመዘዝ ከጀርመን፤ የጀግና ዘር ሁን የሃይማኖተኛ፤የባላባት ዘር ብሎ ምርጫ የለም።
#ሞኞችን፦ የሳይንስ ሊቅና ምሁር፥ተመራማሪና አጥኚ ብሎ መስፈርት ሰማይ የለውም።ሞኞችን ነው የሰበሰበው።
#የተናቁትን፦ በማህበረሰቡ የተከበረ፥ተቀባይነት ያለው ብሎ ነገር የለም።የተናቁትን የመረጠው ግን ምን ሊሆኑት ነው?
#ኃጢአተኞችን፦ በቅንነቱ፥በመልካም ሥራው ማን ተመረጠ?እግዚአብሔርን በመፍራቱና በፀሎት ሕይወቱ ማን ተጠራ?
❤️ወዳጆቼ ሆይ አያችሁ እነማን እንደነበራችሁ? ጌታን መርጣችሁት ሳይሆን መርጧችሁ ነው።ጌታ የጠራችሁ ባላችሁ ነገር ሳይሆን ለሚሰጣችሁ ፀጋና ሕይወት ነው።አስፈልጋችሁት ሳይሆን ፈልጓችሁ ነው።ወዳችሁት ሳይሆን ወዷችሁ ነው።ለመንግስቱ ሥራ ከእናንተ መዋጮ ፈልጎ ሊጠቀምባችሁ ሳይሆን በመንግስቱ የልኡላን ቤተሰብ ሊያረጋችሁ ነው የጠራችሁ።
👉👉ደካማ፥ ያልተማረ፥የተናቀ፥ድሀ፥ ኃጢአተኛና ሞኝ በምኑ ይመካል።ጌታ ባልዳነና ወንጌልን ባልተረዳ ሰው ስትፈርዱ ሲያይ ያዝናል።ጌታ አብርቶላችሁ እንጂ የወንጌሉን ምሥጢር ደርሳችሁበት አይደለም።
👉👉ጌታ ኃይሉ በድካም ይፈፀማልና።ክብሩን ሁሉ እርሱ ለመውሰድ ስለሚፈልግ ይህን አደረገ።ትምክህታችን ባለን ነገር ነው እንዳንል ለጌታ በጌታ ፊት ምን አለን?
👉👉በትህትናና በምሥጋና ለትውልዱ ወንጌል ስበኩ እንጂ አትታበዩ።በጌታ የሆንነው የማንጠቅም ኃጢአተኞች ነን ብለን አምነን ነው።
#እነዚህን_ቃላት_አሰላስሉ፦
📖📖📖📖📖📖📖📖📖📖
(1ኛ ወደ ቆሮንቶስ ሰዎች ምዕ. 1)
----------
26፤ ወንድሞች ሆይ፥ መጠራታችሁን ተመልከቱ፤ እንደ ሰው ጥበብ ጥበበኞች የሆኑ ብዙዎች፥ ኀያላን የሆኑ ብዙዎች፥ ባላባቶች የሆኑ ብዙዎች አልተጠሩም።
27፤ ነገር ግን እግዚአብሔር ጥበበኞችን እንዲያሳፍር የዓለምን ሞኝ ነገር መረጠ፤ ብርቱንም ነገር እንዲያሳፍር እግዚአብሔር የዓለምን ደካማ ነገር መረጠ፤
28፤ እግዚአብሔርም የሆነውን ነገር እንዲያጠፋ የዓለምን ምናምንቴ ነገር የተናቀውንም ነገር ያልሆነውንም ነገር መረጠ፥
29፤ #ሥጋን_የለበሰ_ሁሉ_በእግዚአብሔር_ፊት_እንዳይመካ።
30-31፤ ነገር ግን። የሚመካ በእግዚአብሔር ይመካ ተብሎ እንደ ተጻፈው ይሆን ዘንድ፥ ከእግዚአብሔር ዘንድ ጥበብና ጽድቅ ቅድስናም ቤዛነትም በተደረገልን በክርስቶስ ኢየሱስ የሆናችሁ ከእርሱ ነው።
📖📖📖📖📖📖📖📖📖
(1ኛ ወደ ጢሞቴዎስ ምዕ. 1)
----------
15፤ ኃጢአተኞችን ሊያድን ክርስቶስ ኢየሱስ ወደ ዓለም መጣ የሚለው ቃል የታመነና ሁሉ እንዲቀበሉት የተገባ ነው፤ ከኃጢአተኞችም ዋና እኔ ነኝ፤
16፤ ስለዚህ ግን፥ የዘላለምን ሕይወት ለማግኘት በእርሱ ያምኑ ዘንድ ላላቸው ሰዎች ምሳሌ እንድሆን፥ ኢየሱስ ክርስቶስ ዋና በምሆን በእኔ ላይ ትዕግስቱን ሁሉ ያሳይ ዘንድ፥ ምህረትን አገኘሁ።
17፤ ብቻውን አምላክ ለሚሆን ለማይጠፋው ለማይታየውም ለዘመናት ንጉሥ ምስጋናና ክብር እስከ ዘላለም ድረስ ይሁን፤ አሜን።
እባክዎን ሼር ያርጉት።።
ፔጁን ይቀላቀሉ
👇👇👇👇👇
https://telegram.me/preac
❤️የእለቱ መልእክት❤️
09/09/2012 ዓ/ም
#እግዚአብሔር_የማያድግ_ልጅ_አይወልድም!!
🗣በብርሃኑ ታምራት(Justified Sinner)
👉👉አማኞች የእግዚአብሔር ልጆች ናቸው።የእግዚአብሔር ልጆች መሆናቸውንም መንፈስ ቅዱስ ከመንፈሳቸው ጋር ሆኖ ይመሰክርላቸዋል።እግዚአብሔር ልጆቹን የወለደው በክርስቶስ የቀራንዮ ምጥና ቤዛነት በኩል ነው።
👉👉እግዚአብሔር ወልዶ አይጥልም።ወልዶ ያሳድጋል እንጂ።ልጆቹም የእግዚአብሔር ዘር በውስጣቸው አለና።መርሁን ተከትለው ለማደግና ታላቅ ወንድማቸውን ኢየሱስን ተከትለው ለማደግ ፈቃደኞች ናቸው።
🙌የማያድግ ልጅ እግዚአብሔር ወልዶ አያውቅም።ስለዚህ እግዚአብሔር ለልጆቹ ባስቀመጠው መርህ መሰረት ወደ ክርስቶስ እንደግ።
☝️☝️በመንፈሳዊ ሕይወቴ ለማደግ ምን ላድርግ? ለሚል እነዚህን አስር መርሆዎች ለጊዜው አቅርቤያለሁ።
#10ሩ_መርሆዎች
#1_ማደጋችን_ወደ_ክርስቶስ_መሆኑን_መረዳት፦
🌿🌿🌿🎋🌿☘🍀
👉ብዙ ክርስቲያኖች አገልጋዮቻቸውንና መንፈሳዊ አባቶቻቸውን ከመሰሉ ክርስትናውን የቋጩት ይመስላቸዋል።ግን እኛ ማደግ ያለብን ወደ ክርስቶስ እንጂ ወደ አገልጋዮቻችን አይሁን።የልጁን መልክ እንድንመስል ሰማይ አስቀድሞ ወስኖታልና።ሀዋርያት፥ነቢያት፥አስተማሪዎች፥መጋቢዎችና ወንጌላውያን የተሰጡን እኛን ወደ ክርስቶስ ለማሳደግ ነው።ስለዚህ ክርስቶስን መምሰል ደግሞ የእድሜ ልክ መንፈሳዊ ተግባርና የማያቋርጥ እድገት መሆኑን ተረዱ።ኤፌ.4:11-13
🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿
#2_ቃሉን_በየቀኑ_ማጥናት፦
🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿
👉👉አማኝ እድገቱ የሚወሰነው ከቃሉ ጋር እንዳለው ትስስር ነው።ቃሉን በየቀኑ ማንበብና ማጥናት አለብን።ስትንቀሳቀሱ መፅሀፍ ቅዱሳችሁን ይዛችሁ ተንቀሳቀሱ።ቤተክርስቲያን ስትሄዱም መፅሀፍቅዱሳችሁን ይዛችሁ ሂዱ።ከሃያ አራት ሰአት ውስጥ ቢያንስ አንድ ሰአት ለቃሉ መድቡ።ቃሉን አንብቡ፥አሰላስሉ፥ተናገሩት፥አካፍሉት።መዝ.119:15-17
🍀🍀🍀🍀🍀🍀🍀🍀
#3_ሳታቋርጡ_ፀልዩ፦
🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿
👉👉የማይፀልይ ክርስቲያን በፍፁም አያድግም።ከእግዚአብሔር ጋር ኅብረት ምናደርግበትና የመንፈስቅዱስን ኃይል የምንቀበልበት ዋነኛ መንገድ ፀሎት ነው።ስለማጠር ስለመርዘሙ፥ስለምትፀልዩበትና ቦታና ሁኔታ ሳትጨነቁ አባታችሁን ሁሌ አውሩት።ስትፀልዩ ታድጋላችሁ።።1ተሰ.5:17-18
🍀🍀🍀🍀🍀🍀🍀
#4_ኅብረት_ማድረግ፦
🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿
👉👉በመንፈሳዊ ሕይወት ለማደግ ከወንድሞች ጋር ኅብረት ማድረግ በጣም ወሳኝ ነው።ግለኝነትን ቃሉ በጭራሽ አይደግፍም።ዋናው መዳኔ ነው።ጌታን በቤቴ አመልካለሁ የምትሉ የዋህ ወንድሞቼና እህቶቼ በቃሉ ላይ አታምፁ።ኅብረት አርጉ።ካልሆነ አታድጉም።መዝ.133:1
🍀🍀🍀🍀🍀🍀
#5_ጓደኛ_መምረጥ፦
☘☘☘☘☘☘☘☘
👉👉ለመንፈሳዊ እድገታችን እንቅፋትም ሆነ ለውጥ ጓደኞቻችን ትልቁን ሚና ይጫወታሉ።ጓደኞቻችሁን ምረጡ።ለማደግ ጉጉት የሌለባቸው፥በኃጢአት ልምምድ ውስጥ በድፍረት ከሚያልፉ ጓደኞቻችሁ ራቁ።አርአያ ባይሆኗችሁ እንኳ እንቅፋት ማይሆኗችሁን ምረጡ።ይሉኝታን አስወግዱ።1ቆሮ.15:33
🍀🍀🍀🍀🍀🍀🍀🍀
#6_ቃሉን_መማር፦
☘☘☘☘☘☘☘
👉👉በትምህርት እመኑ።ባገኛችሁት የመማር እድል ሁሉ ተማሩ።ጤነኛ የመፅሀፍ ቅዱስ አስተማሪዎች የሚያስተምሩትን ትምህርት ተከታተሉ።ቤተክርስቲያናችሁ በምታዘጋጀው የትምህርት ፕሮግራም ሁሉ ተሳተፉ።መሰረታዊውን የክርስትና ትምህርት ጥንቅቅ አርጋችሁ ተማሩ።ያኔ ታድጋላችሁ።ኢሳ.54:13
🍀🍀🍀🍀🍀🍀🍀🍀
#7_አንባቢ_መሆን፦
🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿
👉👉መንፈሳዊ ሕይወታችሁን ሊያበለፅጉ ሚችሉ መንፈሳዊ መፅሀፍትን አንብቡ።1ጢሞ.4:13
🍀🍀🍀🍀🍀🍀🍀
#8_ለብቻችሁ_የፆምና_የፀሎት_ጊዜ_መውሰድ፦
🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿
👉👉መባከን አታብዙ።በግላችሁ ደግሞ የፆምና የፀሎት ጊዜ ውሰዱ።ቢያንስ በሳምንት አንድ ቀን የፆም ፀሎት ቀን ውሰዱ።ስልካችሁን አጥፍታችሁ።ከሶሻል ሚድያ ርቃችሁ።በጌታ ፊት በፆም በፀሎት ሁኑ።ለውጡን ታያላችሁ።ማቴ.6:6፤ማቴ.6:16-18
🍀🍀🍀🍀🍀🍀🍀🍀
#9_በቤተክርስቲያን_መታቀፍ፦
🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿
👉👉ቃራሚና ዟሪ አትሁኑ።በአንድ ቤተክርስቲያን ታቀፉ።ለዛች ቤተክርስቲያንም በአገልግሎት፥በፕሮግራም፥በአሥራት በኩራት ታማኝ ሁኑ።ያኔ በመንፈሳዊ ሕይወታችሁ ሚመጣውን ለውጥ ማመን አትችሉም።የሐዋ.2:41
🍀🍀🍀🍀🍀🍀🍀🍀
#10_ለውጣችሁ_ላይ_ማተኮር፦
🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿
👉👉ብዙዎች በጌታ ቤት ይህን ያህል ዓመት ቆይቻለሁ ብለው እድሜ ይቆጥራሉ።እናንተ ግን ለውጥ ቁጠሩ።ለውጥ ላይ አተኩሩ።ውጤት ላይ አተኩሩ።ለውጣችሁን ተከታተሉ።በሕይወት፥በእውቀት ምን ለውጥ አመጣሁ? እረፍት አገኘሁ ወይ በሉ።2ጴጥ.1:5-10
#በመጨረሻም፦
" #እነዚህ_ነገሮች_ለእናንተ_ሆነው_ቢበዙ፥ #በጌታችን_በኢየሱስ_ክርስቶስ_እውቀት_ሥራ_ፈቶችና_ፍሬ_ቢሶች_እንዳትሆኑ_ያደርጉአችኋልና፤"
(2ኛ የጴጥሮስ መልእክት 1:8).
እባክዎን ለሌሎችም ያካፍሉት።
ፔጁን ይቀላቀሉ
👇👇👇👇👇
https://telegram.me/preac
❤️የእለቱ መልእክት❤️
07/09/2012 ዓ/ም
#ሳይቆጣጠራችሁ_ተቆጣጠሩት።
🗣በብርሃኑ ታምራት(Justified Sinner)
👅አንደበት እሳት ነው።የፍጥረትን ሩጫ ያቃጥላል።መፅሀፍ ቅዱስ ምላስን ትንሽ ብልት ብትሆንም ዓመፀኛ ዓለም ናት ይላታል።አንደበት አንድ ጣእም የሚሰጥ የውሃ ምንጭ እንዲሆን ቃሉ ያበረታታናል።ያእ.3:10-11
🙊🙊ብዙዎች ያኔ እንዲ ባላልኩ ነበር ብለው ይፀፀታሉ።ያፀፀታቸውን ያን ንግግራቸውን ግን መመለስ እንደማይችሉ ያውቁታል።
🙅♀🙅የምትናገሩትን ከመናገራቹህ በፊት ተቆጣጠሩት።ከተናገራችሁ በኋላ ግን ንግግራችሁ ይቆጣጠራችኋል።ንግግራችሁን ሁሌ መቆጣጠር ቢኖርባችሁም በተለየ ሁኔታ ግን በነዚ ወቅቶች አብዝታችሁ ተቆጣጠሩት።።
#ንግግራችሁን_መቆጣጠር_ያለባችሁ_ሦስት_አሳሳች_ወቅቶች፦
#1_በተናደዳችሁና_በተቆጣቹህ_ጊዜ፦
😡😡ንዴትና ቁጣ በጭራሽ የእግዚአብሔርን ፅድቅ አይሰራም።በንዴት ጊዜ ዝምታ በጣም ጥሩ መፍትሄ ነው።ሴቶች ሆይ ባላችሁ ወይም ፍቅረኛችሁ በተናደደና በተቆጣ ጊዜ ለብቻው እንዲሆን ጊዜ ስጡት።ካልሆነ ፍንጣሪው ለሌላ እስኪተርፍ ሚፈነዳ ነገር ከአፉ ሊወጣ ይችላል።ወንዶች በዝምታቸው፥ሴቶች በእንባቸውና በማውራታቸው ነውና ንዴቱ ሚወጣው ለዛ ነው ሴቶች ሆይ ማለቴ።
😡😡በተናደዳችሁና በተቆጣችሁ ጊዜ #ስልክ _አታውሩ፥#መልእክት_አትፃፃፉ_ወይም_አትፃፉ፥#አትከራከሩ ወይም #አትወያዩ።ምክንያቱም በንዴት ጊዜ ራሳችንና ንግግራችንን የመቆጣጠር እድላችን በጣም ያነሰ ነው።ለይቅርታ ሚቸግር ነገር እንዳንናገርና የሰው ልብ እንዳንሰብር ዝምታን እንምረጥ።ንዴቱና ቁጣው ሲያልፍ ሁሉም ይደርሳል።የተናደደም ባልንጀራችሁ ተውኝ አሁን ሲላችሁ ተውትና ሲበርድለት አናግሩት።ንዴት ደግ ነገር አያናግርምና በሀገራችን "ከተናግሮ አናጋሪ ጠብቀኝ" ይባላል።ተናግረው ያቆሰሉን ቀን እኛም ትግስት አጠን ክፉ እንናገራለንና።
📖📖📖📖📖📖📖
(የያዕቆብ መልእክት ምዕ. 1)
----------
19፤ ስለዚህ፥ የተወደዳችሁ ወንድሞቼ ሆይ፥ #ሰው_ሁሉ_ለመስማት_የፈጠነ_ለመናገርም_የዘገየ_ለቍጣም_የዘገየ_ይሁን፤
20፤ #የሰው_ቍጣ_የእግዚአብሔርን_ጽድቅ_አይሠራምና።
📖📖📖📖📖📖📖📖📖
#2_በጣም_ደስ_ባላችሁ_ጊዜ፦
🙊🙊ሰው ንግግሩን በጣም መቆጣጠር ካለበት ሁኔታዎች አንዱ የደስታ ቀን ነው።ሰው ደስ ባለው ሰአት ቃል ይገባል።ደስተኛ ነውና የገባውን ቃል እንደሚፈፅመው ነው ሚያውቀው።አንዳንዶች እንደውም በደስታ፥በሞቅታ ቃል ገብተው ማይወጡበት ነገር ውስጥ ገብተዋል።ነፍሴን እንኳን እሰጥሃለሁ/እሰጥሻለሁ የሚያባብል የደስታ ቀን አለ።ግን ቃል ገብታችሁ በቃላችሁ ከመያዛችሁ በፊት ንግግራችሁን ተቆጣጠሩት።ቃል ከገባችሁ በኋላ የሚቆጣጠራችሁ ቃላችሁ ነውና።
📖📖📖📖📖📖📖📖📖
(የማቴዎስ ወንጌል ምዕ. 14)
----------
8፤ እርስዋም በእናትዋ ተመክራ። የመጥምቁን የዮሐንስን ራስ በዚህ በወጭት ስጠኝ አለችው።
9፤ ንጉሡም አዘነ፥ ነገር ግን #ስለ_መሐላው_ከእርሱም_ጋር_ተቀምጠው_ስላሉት_ሰዎች_እንዲሰጡአት_አዘዘ፤
📖📖📖📖📖📖📖📖📖📖
(የማቴዎስ ወንጌል ምዕ. 26)
----------
34፤ ኢየሱስ። እውነት እልሃለሁ፥ በዚች ሌሊት ዶሮ ሳይጮኽ ሦስት ጊዜ ትክደኛለህ አለው።
35፤ ጴጥሮስ። ከአንተ ጋር መሞት እንኳ የሚያስፈልገኝ ቢሆን፥ ከቶ አልክድህም አለው። ደቀ መዛሙርቱ ሁሉ ደግሞ እንደዚሁ አሉ።
📖📖📖📖📖📖📖📖📖
#3_በተማረርን_ጊዜ፦
💔💔ሕይወትን የሚያጎመዝዝ፥መኖርን እንድንጠላ ሚያደርግ ፈተና ሊያገኘን ይችላል።በዚ ጊዜ ዝምታን መምረጥ ብልህነት ነው።ከሰው ከነፍሱ ምሬት በጎ ነገር አይፈልቅም።ፈጣሪን መሳደብ፥መንግስትን መክሰስ፥ቤተሰቦቻችን መውቀስ፤አጋሮቻችን ማጥላላት ከወዴት ይመጣሉ? የሚመጡት ከነፍስ ምሬት ነው።ሰው ሲማረር እርሱ ብቻ ፃድቅ የሆነ ይመስለውና "አምላኬ ምን በደልኩህ?" ይላል።ይራገማል፥ይሳደባል፥ያጥላላል፥ይተቻል፥ያማርራል።እናም ተወዳጆች ለሚያልፍ የነፍስ ምሬት ከአፋችን ከወጣ በኋላ ማንቆጣጠረውን ነገር እንዳንናገር እንጠንቀቅ።
📖📖📖📖📖📖📖📖
(መዝሙረ ዳዊት ምዕ. 10)
----------
10፤ ድሀ ይዋረዳል፥ ይጐብጣል፤ በኃያላኑም እጅግ ይወድቃል።
11፤ በልቡም ይላል። #እግዚአብሔር_ረስቶኛል፤ #ፈጽሞም_እንዳያይ_ፊቱን_ሰወረ።
📖📖📖📖📖📖📖📖📖📖
(ሰቆቃው ኤርምያስ ምዕ. 3)
----------
27፤ ሰው በታናሽነቱ ቀንበር ቢሸከም መልካም ነው።
. . .
29፤ ተስፋ የሆነው እንደ ሆነ #አፉን_በአፈር_ውስጥ_ያኑር።
ያሕዌ በነገር ሁሉ ማስተዋልን ይስጠን።።።
እባክዎን ለሌሎች ያካፍሉት።
@preac
❤️የእለቱ መልእክት❤️
05/09/2012 ዓ/ም
#በነገ_መመካት_እና_ነገን_መፍራት
🗣በብርሃኑ ታምራት(Justified Sinner)
👉የሕይወታችን ሦስቱ ገፅታዎቻችን ትናንት ያሳለፍነው ታሪካችን፥ዛሬ እየኖርነው ያለው ቀናችንና ነገ ምንናፍቀው ተስፋችን ናቸው።ዛሬ ላይ ሆኖ በትናንት ሚፀፀት፥ዛሬ ላይ ሆኖ ነገን የሚፈራ ሞልቶአል።እንዲሁ ደግሞ ዛሬ ላይ ሆኖ በትናንቱ ጀብድ ሚኮፈስ፥ዛሬ ላይ ሆኖ በነገ ሚመካም ብዙ ነው።
👉ነገ ለአንዳንዶች ኩራትን፥ለአንዳንዶች ፍርሃትን አዝሎአል።ስለ ነገ ሲያስቡ የሚመኩ፥ስለ ነገ ሲያስቡ የሚታወኩ ሰዎች እንደ ቃሉ ኖሮአቸውን ቢያስተውሉ መልካም ነው።
#የመጀመሪያዎቹ_ሰዎች፦ #በነገ_ሚመኩ
🙊🙈ለእነዚህ ሰዎች ሁሉ ነገራቸው ያለው ነገ ውስጥ ነው።ትዳራቸው፥ጤናቸው፥ሀብታምነታቸው፥ታዋቂነታቸው፥ደስተኝነታቸው፥ለጠላት ለወዳጅ አሳየዋለሁ የሚሉት ነገር ሁሉ ያለው ነገ ውስጥ ነው።በነገ እርግጠኞችና ተስፈኞች ናቸው።እናም ከዚህ ትምክህታቸው የተነሳ ካሁኑ ማውራት ይጀምራሉ።በነገራችን ላይ ስለነጋቸው የሚያወሩ ሰዎች አብዛኞቹ አይሳካላቸውም።ገና ነገና ያሰቡት ነገር እጃቸው ሳይገባ ሰው ከፍና ዝቅ ሚያደርጉም ብዙ ናቸው።ነገ ገና እጃቸው ሳይገባ ትምህርት የሚያቋርጡ፥ሥራ የሚለቁ ሁሉ አሉ።ስለ ነገ ምንም አሉታዊ ነገር ማሰብ ስለማይፈልጉ መጠንቀቅ፥ገንዘብ መቆጠብና ዝም ማለት አይችሉም።ነገ በሺዎች የሚቆጠር ገንዘብ ስለሚያገኙ ዛሬ በመቶዎች ያላቸው ገንዘብ ያጠፏታል።ነገ ውጭ ስለሚሄዱ ዛሬ ደፋ ቀና ሚለውን ደሃ ያጥላላሉ።
👉ነገ ግን አያስመካም።ነገ አያኮራም።ነገ በፈጣሪ እጅ እንጂ በእኛ ፈቃድ ውስጥ የለም።ነገ ምን እንደሚፈጠር አይታወቅምና፤በነገ አትመኩ።ነገ እንደማያስመካ ኮሮና መጦ እቅዳቹህን ያዘገየባቹህ፥ሰርጋቹህን ያሰረዘባቹህ፥ከአገር እንዳትወጡ የከለከላቹህ፥የገንዘብ አቅማቹህን አዳክሞ እቅድ ያስቀየራቹህ ምስክሮች ናቹህ።በነገ አትመኩ።ዛሬን ኑሩ በልኩ።
❤️ቃሉ እንዲህ ይላል፦ " #ቀን_የሚያመጣውን_ምን_እንደ_ሆነ_አታውቅምና_ነገ_በሚሆነው_አትመካ። "
(መጽሐፈ ምሳሌ 27:1)
#ሁለተኛዎቹ_ሰዎች፦ #በነገ_ሚታወኩ
😳😳የአንዳንዶች የነገ ፍርሃትማ ከቃል በላይ ነው።የሚቆዝሙት አምላካቹህ ሞቶአል የተባሉ ያህል ነው።ምንም ተስፋ አይታያቸውም።ሚታያቸው ባዶአቸውን ሲቀሩ፥ሰው ሁሉ ሲርቃቸው፥ደሃ ሲሆኑ፥ሲታመሙ ወይ ሲሞቱ ነው።ሳላገባ ቆሜ መቅረቴ ነው።ሰው መቼም አይወጣልኝም።ምንም ብሰራ አያልፍልኝም።ከዚህ ሁሉ ጌታ ቢገድለኝ እገላገል ነበር ብለው ሁሌ ለራሳቸው ይነግሩታል።ለነሱ መቸገር፥ማጣት፥መከዳትና መጠላት የዓለም መጨረሻ ነው።ጭንቀታቸው ማባሪያ የለውም።በነገ ፍርሃትና መታወክ ዛሬን ያበላሻሉ።
👉ግን አምላክ ያለው አይታወክም።አይፈራም።ሕይወታችን በእርሱ እጅ ናት።ዛሬ አብሮን ያለው ነገም ፍቅሩ ማይቀንሰው ታማኙ ኢየሱስ ነው።ነገን አትፍሩት።በነገ አትታወኩ።በእግዚአብሔር ታመኑ።እግዚአብሔር ያውቃል ብላቹህ ዛሬን በትጋትና በደስታ አሳልፉት።#ዛሬ_ምትዘሩትን_ነው_ነገ_ምታጭዱት_ዘራቹህ_ላይ_ተጠንቀቁ።
" #ነገ_ለራሱ_ይጨነቃልና_ለነገ_አትጨነቁ፤ #ለቀኑ_ክፋቱ_ይበቃዋል።
"
(የማቴዎስ ወንጌል 6:34)
ሚዛናዊ እንድንሆን ጌታ ያግዘን።ያሕዌ በነገር ሁሉ ማስተዋልን ይስጣቹህ።
እባክዎን ለሌሎች ያካፍሉት።
ፔጁን ይቀላቀሉ
👇👇👇👇
https://telegram.me/preac
❤️የእለቱ መልእክት❤️
24/05/2012 ዓ/ም
#አስቸጋሪውን_የመከራ_ጊዜ_ማነው_ሚሻገረው?
🗣በብርሃኑ ታምራት
👉 ዛሬ በዓለማችን በተከሰተው የኮሮና በሽታ ወረርሽኝ ምክንያት ሁሉም ሰው ጭንቀት ላይ ነው።ካደጉ አገራት እስከ ታዳጊ አገራት ድረስ አቅማቸው ተዳክሟል።
👉 ይሄ የጭንቅ ቀን ያላሳሰበው የሰው ዘር የለም።በጣም አስገራሚው ነገር ደግሞ የኃጢአት እንቅስቃሴ በተገታበት ልክ የፅድቅ እንቅስቃሴም ተገትቶታል።ጭፈራ ቤት ተዘጋ ብሎ ተመስገን ያለው ሰው፤ ቸርች መዘጋቱን አይቶስ ምን አለ?
👉 የሁሉም ሰው ጥያቄ ይሄ ወረርሽኝ መች ነው ሚያበቃው? መች ነው እንደ ቀድሞው መውጣት መግባት፤ያሰብነውን ለማሳካት ምንችለው? የሚለው ነው።
👉 ኮሮና ከምድራችን ላይ መጠረጉ አይቀርም።ይጠፋል።ጌታ ጣልቃ ይገባል።ኮሮና ያልፋል።ግን እነማንስ አብረውት ያልፋሉ? እነማንንስ ያልፋቸዋል?
👉ይሄን ክፉ የመከራ ጊዜ የሚቋቋሙትና የሚያልፉት አማኞች ናቸው።
👉 መቅሰፍት ወደ ቤትህ አይገባም በሚለው ጌታ ጥበቃ የሚተማመን ያልፈዋል።
👉ቅዱሳን አባቶቻችን የአንበሳን አፍ የዘጉት፥እሳቱን ያጠፉት፥የሰይፉን ስለት የተጋፈጡት በእግዚአብሔር ልጅ በኢየሱስ ላይ ባላቸው እምነት ነው።
👉እግዚአብሔርን እንዲህ በሉት፦ አንተ መታመኛዬ ነህ።ከክፉም ሁሉ ትጠብቀኛለህ።የኔ ጠባቂ እግዚአብሔር አትተኛም አታንቀላፋም።ከሞት ጣር ትጠብቀኛለህ።
👉 ልባችሁ አይታወክ አይፍራም።መሆን ያለበት ሁሉ ይሆናል።የእግዚአብሔር ጥበቃ ከእናንተ እንደማይለያቹህ እመኑ።
👉አሻጋሪው ያሻግራችኋል።አሳላፊው ያሳልፋችኋል።ይህን ክፉ ጊዜ ተሻግራቹህ በድል ከሚዘምሩት፤የእግዚአብሔርን ስም በክብር ከሚያውጁት ውስጥ ትሆናላቹህ።
👉እኔ ዛሬ እነግራችኋለሁ፦ በኢየሱስ ለምታምኑ ለሁላቹህ የፅድቅ ፀሐይ ይወጣላችኋል።
🕊እነዚህን የኪዳን ቃላት አሰላስሉ፦
🗣" ልባችሁ አይታወክ፤ በእግዚአብሔር እመኑ፥ በእኔም ደግሞ እመኑ።"
(የዮሐንስ ወንጌል 14:1)
🗣
" በእኔ ተማምኖአልና አስጥለዋለሁ፤ ስሜንም አውቆአልና እጋርደዋለሁ።"
(መዝሙረ ዳዊት 91:14)
ፔጁን ይቀላቀሉ
👇👇👇👇👇
@preac
https://telegram.me/preac
