የአገልጋይ ብርሃኑ ገፅ
Open in Telegram
ይህ የአገልጋይ ብርሃኑ ገፅ ነው።ዓላማዬ የተለያዩ መፅሐፍ ቅዱሳዊ ትምህርቶችን ማካፈልና ማድረስ ሲሆን ምክሮችን፥አባባሎችን፥ፀሎቶችንና ትዝብቶቼን የማካፍልም ይሆናል።የሰራዊት ጌታ እግዚአብሔር ወደ ልቤ ያመጣውንና የተናገረኝንም እፅፋለሁ።ትውልዱን ወደ ኢየሱስ የሚያስጠጋውን የትኛውንም ነገር የምፅፍበት ገፄ ነው።በማንበብና ሼር በማድረግ ከአገልግሎቴ ጎን ይቁሙ።0984005562.
Show more447
Subscribers
+224 hours
+87 days
+3030 days
Posts Archive
#ወደ_ኦርቶዶክስ_ተመልሰናል_ባዮቹ_የሕይወት_ታሪክ"
🗣በአገልጋይ ብርሃኑ እይታ
👉አንዲት ጥንቸል አንድን ጣፋጭ ፍሬ በዛፉ ላይ አይታ ቆርጣ ለመብላት መዝለል ጀመረች።ብትዘል ብትዘል ችላ ቆርጣ ልትበላ አልቻለችም።ከዛ ጥንቸሏም በንዴት፦ "እንደውም ትቼዋለሁ አልበሰለም" አለች ይባላል።😂
👉እኛ ተሐድሶ ነን አሉ።ኅብረት መሠረቱ።መዝሙር አወጡ።አዳራሽ ተከራዩ።ሰው ለመሰብሰብ ሞከሩ።የቻሉትን አገልጋይና ዘማሪ ሰብስበው ደሞዝ እየከፈሉ ለማገልገል ሞከሩ።በየሀገራቱ እየዞሩ በገንዘብ ኃይል አጥቢያ ተከሉ።"እገሌ ዓለም አቀፍ ቤተክርስቲያን" የሚል የቸርች ፈቃድ ሁሉ አወጡ።የመንፈስ ቅዱስን የፀጋ ሥጦታ መቃወምና ድንዛዜውን አበዙት።የፀጋ ሥጦታን የሚቀበሉትን ሰዎች "በሲኖዶሳቸው" አውግዘው አባረሩ።ግን ብዙ ሰው ጥሏቸው መውጣትና ጴንጤ መሆን ጀመረባቸው።አንዳንድ አገልጋዮችም ወደ ኦርቶዶክስ ተመልሰው "እነርሱ እኮ እንዲህ ናቸው" እያሉ ሲመሰክሩባቸው።"ከእኛ የወጡትና ወደ ጨለማ የተመለሱት ምንሰፍርላቸው ቀለብ እንደሌለ ስንነግራቸው ነው እንጂ አምነውበት አይደለም" ብለው መልስ ሰጡ።አንዳንድ አገልጋዮች ደግሞ ወደ ወንጌላውያን አብያተክርስቲያናትና ወደ ሌሎች ኅብረት ሄዱባቸው።ብቻቸውን ጣሩ ደከሙ።በአንዴ የሚሰበሰው ያ ሕዝብ ቁጥሩ ወደ 10 ወረደ።ብሎ ብሎ ተዘጋና አረፈው።
👉🙈አሁን ዜማና ማርሽ ቀየሩና ሊበሉትን ያልቻሉትን ፍሬ "አልበሰለም" ትተነዋል አሉ።ወደነበራችሁበት ተመለሱና እከፍላለሁ የሚልም ተገኘ።እህህ ስፖንሰር ከተገኘማ አሉ፤ልባቸው ገንዘቡና እልካቸው ላይ ቢሆንም ቅሉ "ተመልሰናል" አሉን።
👉🙈በቲቪም ሊመጡ ነው አሉ።ይሄ ሁሉ እግዚአብሔርን አምነው ሳይሆን አንድ ሰውን አምነው፤ኑሮን ፈርተው፤ካፈርን አይመልሰን ብለው ነውና ፀሎት እንጂ ምክር አይመልሳቸውም።
😂👉ኦርቶዶክሳውያን ምናቸው ሞኝ ነው በቅርቡ የቅሌታቸውን ዋጋ ይሰጡአቸዋል።እድሜ "ለቅዱሳኖች ማኅበር"።
👉ይሄው ነው።።።።።።
📖“እነሆ፥ ድንግል ትፀንሳለች፥ ወንድ ልጅም #ትወልዳለች፥ ስሙንም አማኑኤል ብላ ትጠራዋለች።”
— ኢሳይያስ 7፥14
📖“ሕፃን #ተወልዶልናልና፥ ወንድ ልጅም ተሰጥቶናልና፤ አለቅነትም በጫንቃው ላይ ይሆናል፤ ስሙም ድንቅ መካር፥ ኃያል አምላክ፥ የዘላለም አባት፥ የሰላም አለቃ ተብሎ ይጠራል።”
— ኢሳይያስ 9፥6
እስኪ ልዩነቱን ያስተዋለ?
እግዚአብሔር ወደ ገሃነም የሚወረውረው ኃጢአተኞችን እንጂ ኃጢአትን አይደለም።ገሃነምም ገሃነም የሆነው እግዚአብሔር በገሃነም ስለሌለ ሳይሆን ገሃነም ገሃነም የሆነው የእግዚአብሔርን ቁጣ ስለተሞላ ነው።ይሄ ነው የመፅሐፍ ቅዱሱ እግዚአብሔር።
Paul Washer
#መመረጥና_የመመረጥ_ስሜት
🗣በአገልጋይ ብርሃኑ
15/01/2014 የምሕረት ዓመት
❤️እኔ የሰውን ፈቃድ በማይቃወም መመረጥ አምናለሁ።እግዚአብሔር የመረጣቸውና የተመረጡ የሚመስላቸው የሚለያዩት በሕይወት ነው።
👉እግዚአብሔር እንደመረጠህ ምታውቀው በልብህ ውስጥ እርሱን መፍራት ካስቀመጥልህ ነው።እግዚአብሔር እንደመረጠህ ምታውቀው በልብህ ትሁት ስትሆን ነው።
👉ቃሉ የሕይወትህ መመሪያ፤እውነቱ መመኪያ ከሆነልህ በቃ ተመርጠሃል።ተቀድሻለሁ ብለህ አስሬ እየለፈፍክ የቅድስና ትምህርትና የቅድስና ሕይወት ከጠላህ እንደተመረጥክ ብታውጅም እንኳን እውነተኛ ክርስቲያን ቀርቶ ክርስቶስ አያውቅህም።
👉የንስሐ ፀሎት ላንተ ጊዜ ያለፈበት ከሆነ፤መንፈስ ቅዱስን በማሳዘንህ የማታዝን ከሆነ፤ባለመፀለይህ፥ቃል ባለማጥናትህ፥ባለመቀደስህ፥በመዋሸትህ ማትወቀስ ከሆነ ላንተ መርዶ አለኝ።አልተመረጥክም።
❤️የተመረጡት ድነዋል፥እየዳኑም ነው፤ይድናሉም።የተመረጡት ፀድቀዋል፤በቅድስና ይኖራሉ፤ይከብራሉ።
✝ሃይማኖት እንደማያድን ሃይማኖተኞችም ያውቃሉ።ሃይማኖት ክርስቶስን ከማወቅህ በፊት ርእስህ ነበር።ክርስቶስን ስታውቅ ግን ዋናው አጀንዳህ የእግዚአብሔር መንግስት ይሆናል።ጉዳይህ ከእግዚአብሔር መንግስት መስፋት ጋር እንጂ ከሃይማኖት ጋር ካልሆነ በቃ ተመርጠሃል።
🍇አብ የተከለው አይነቀልም።
📖ሕግ ነቢያት ወንጌል ክርስቶስን አስተማሩ።ዮሐ.5:37
✡የአጥቢያ ኮከብ ሳይፈጠር ከእርሱ የተወለደ የአብ ሕሊናው ፍፁም ቃለ እግዚአብሔር ኢየሱስ ነው።መዝ.110:3
❤️ከአብና ከመንፈስ ቅዱስ ጋር በሥራ ሁሉ ያለና ሁሉን የፈጠረ፤ሰውን የሠራ ኢየሱስ ነው።ዘፍጥ.1:1-2"26
👨🦳በአበው አለቆች ዘንድ የአበው አለቃ ኢየሱስ ነው።ሕግን በመሥራት ጊዜም ሕግን የሠራ ኢየሱስ ነው።መዝ.78:1:8
👑ካህናት የሚሾም ሊቀ ካህናት ነው።ነገሥታትንም የሚገዛ ኢየሱስ ነው።በነቢያት አድሮ የሚናገር ኢየሱስ ነው።በመላእክት ላይ ንጉሥ እርሱ ነው።ራእይ.1:5-6፤5:9-10
👉በሰው ባሕርይ ሰው የሆነ ኢየሱስ ነው።ከአብ የተወለደ እውነተኛ አምላክ፤የዘለዓለም ንጉሥ ኢየሱስ ነው።1ጢሞ.1:17፤ዕብ.1:2
👉ኖኅን የጠበቀው ኢየሱስ ነው።አብርሃምን የመራው፤ከይስሐቅ ጋር የታሠረ፤ከያእቆብ ጋር እንግዳ የሆነ፤ከዮሴፍ ጋር የተሸጠ ኢየሱስ ነው።ዘፍጥ.8:18፤2ጴጥ.2:5፤ዘፍጥ.12:1-7፤22:1-15፤28:1-20፤37:26-28
👉በሙሴ አድሮ ሕዝቡን የመራ፤ሕግን የሠራላቸው፤ለኢያሱ ርስትን የሰጠው፤በእርሱም አድሮ ለእሥራኤል ልጆች ያወረሳቸው ኢየሱስ ነው።ዘፀ.3:14፤መዝ.77:20፤ሥራ.7:34-45፤ኢያሱ.3:14
📖በዳዊት አድሮ ትንቢት የተናገረ፤በነቢያት አድሮ ሕዝቡን ያስተማረ ኢየሱስ ብቻ ነው።ከቅድስት ድንግልም ሰው የሆነ እርሱ ነው።መዝ.72:6፤ኢሳ.9:6፤ሉቃ.1:26-56
🙏በቤተልሔም ተወለደ።በጨርቅ ተጠቀለለ።በበረት ተጣለ።ከብት ጠባቆች አዩት፤መላእክት አመሰገኑት፤ሰብአ ሰገል ሰገዱለት።ሉቃ.2:1-20፤ማቴ.2:1-12
👉ዮሐንስ ገለጠው።በዮርዳኖስ አጠመቀው።በገዳም ተፈተነ።እርሱም የባሕርይ አምላክ እንደሆነ ታወቀ።ዮሐ.1:29፤ማቴ.3:13-16፤4:1-11
💒ሐዋርያትን ወደ እርሱ ሰበሰበ።ወንጌልን አስተማረ።ድውያንን ፈወሰ።አንካሶችን እንዲሄዱ አደረገ።ለምፃሞችን አነፃ።የእውራንን ዐይን አበራ።ሙታንን አሥነሳ።ማቴ.4:12-25፤ዮሐ.11:1-45
🗣በምኵራብ ሲያስተምር ታዬ።ሕዝቡ ግን አላመኑበትም።ይሁዳ አሳልፎ ሰጠው።የካህናት አለቆችም ተቀበሉት።ዮሐ.7:37-53፤8:20-59፤10:23-42፤ማር.14:43-47
✝በሥጋ ተሰቀለ፥በመስቀል ላይም ተቸነከረ፤ሞተ፤ተገነዘ፤ተቀበረ፤ከሙታንም ተለይቶ ተነሣ።መዝ.22:16፤78:65፤1ጴጥ.2:24፤ማቴ.28:5፤ዮሐ.19:16-42
👉የሙታን ትንሣኤያቸው፤ፈርሰው በስብሰው የነበሩትን የሚያድናቸው፤በጨለማ ላሉ ብርሃናቸው፤የተማረኩትን የሚመልሳቸው፤የጠፉትን የሚመራቸው፤ለተጨነቁት አምባ መጠጊያቸው ኢየሱስ ነው።መዝ.32:6፤36:9፤85:1፤91:2፤ሉቃ.15:23-32፤1ቆሮ.15:42-44፤1ጴጥ.3:20
👉የቤተክርስቲያን ሙሽራዋ፤ያመኑትን የሚጠብቃቸው፤ኪሩቤልን የፈጠረ፤አምላክነቱን የሚያገለግሉ ሠራዊተ መላእክትን የሚመራቸው፤ከእውነተኛ አምላክ የተወለደ እውነተኛ አምላክ፤ከእግዚአብሔር አብ የተወለደ ወልድ ኢየሱስ ክርስቶስ የዘላለም ገዥ ነው።መዝ.104:4፤ኤፌ.5:32፤1ጢሞ.1:17፤ራእይ.19:7-9
ሄሬኔዎስ
❤️የሙታን ትንሣኤያቸው፤ፈርሰው በስብሰው የነበሩትን የሚያድናቸው ፤በጨለማ ላሉ ብርሃናቸው፤የተማረኩትን የሚመልሳቸው፤የጠፉትን የሚመራቸው፤ለተጨነቁት አምባ መጠጊያቸው #ኢየሱስ ነው።❤️
ሄሬኔዎስ.🙏
❤️የሰባኪው ሙግት ስለወንጌል❤️
05/01/2014 የምሕረት ዓመት
#ስለታዳጊው_እግዚአብሔርና_ወንጌልን_ስለመስበክ_ዮሐንስ_አፈወርቅ_እንዳስተማረው
👉(በክፍል ሁለት እግዚአብሔር ሰውን ሁሉ እንደሚወድና መንግስቱን ለሰው እንዳዘጋጀው አይተን ነበር።ከዛ የቀጠለ ስለሆነ ስለዚህ ብሎ ይጀምራል።
ይሄን መልእክት ምታነቡ ሰዎች መልእክቱን እባካችሁ ለራሳችሁ ብላችሁ ስሙት።ዮሐንስ ቀጠለና እንዲህ አለ……)
👉ስለዚህ እግዚአብሔር እንደዚህ እጅግ ሰውን የሚወድ፥ደግና ቸር ነውና ስለራሳችንም ኾነ ስለወንድሞቻችን መዳን በደንብ ልናስተውል ይገባናል።ለራሳችን ብቻ ሳይኾን ለወንድሞቻችን መዳን የምናስብ ወደ እውነት ይመጡ ዘንድም አስፈላጊውን ኹሉ የምናደርግ ስንኾን ጥቅሙ ለራሳችን ነው።ለሌሎች ሰዎች የምናደርገው በጎ ሥራም ኾነ ጥንቃቄ መልሶ ለራሳችን ጥቅም እንደኾነ ታውቁ ዘንድ ከወደዳችሁ በእግዚአብሔር ስም የሚናገረውን የመፅሐፍ ቅዱስ ፀሐፊ አድምጡት፥ እንዲህ ያለውን፦ "የከበረውን ከተዋረደው ለይቶ የሚያመጣ ቢኖር እርሱ እንደ አፌ ይኾናል"/ኤር.15:19/።ምን ማለት ነው? "ወንድሙን ከስሕተት ወደ እውነት የሚያመጣ፤ኃጢአት ይሠራ የነበረን ሰው የፅድቅን ሥራ እንዲያደርግ የሚመራ ሰው ምንም እንኳን በፍጥረቱ ሰው ቢሆንም እኔን ይመስላል" ሲል ነው።
🛑 #አስታውሱ፦ እግዚአብሔር(ወልድ) ምንም አምላክ ቢሆንም፥ ሥጋን ለብሶ የመጣው ስለሰው ዘር መዳን እንጂ ለሌላ ለምንም ዓላማ አይደለም።ባሕርያችንን የነሣው(የተዋሐደው)፤ከኃጢአት በቀር ሰው የሚቀበለውን መከራ ታግሶ የተቀበለው፤ንፁሐ ባሕርይ ሆኖ ሳለ የመስቀልን ሞት የሞተው እኛን ከኃጢአት እስራት፤ከመርገም ከቁራኝነት ለማዳን ካልኾነ ለምንድነው? ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስም አሰምቶ ያስተማረው ይህን ነው፤እንዲህ ሲል"““በዕንጨት ላይ የሚሰቀል ሁሉ የተረገመ ነው” ተብሎ ስለ ተጻፈ፣ ክርስቶስ ስለ እኛ ርግማን ሆኖ ከሕግ ርግማን ዋጅቶናል፤”/ገላትያ 3፥13/.
❤️ታዲያ እርሱ ባሕርዩ የማይመረመር አምላክ ሆኖ ሳለ ከታላቅ ፍቅሩ የተነሣና ስለ እኛ መዳን ሲል ከኃጢአት በቀር የእኛ የኾነውን ኹሉ ሳይፀየፍ ከተቀበለ፤ከዲያብሎስ መንጋጋ እናስጥላቸው ዘንድ፤የእውነት መንገድንም እናሳያቸው ዘንድ የእኛ አካል ለሆኑት ለወንድሞቻችን እንዲህ የማንሆንበት ምን ምክንያት አለን?
📖ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ/ዘፍጥረት ትርጓሜ/ድርሳን ፫/ገፅ ፷፫-፷፬/
❤️ጥንታዊ መፅሐፍ ቅዱሳዊ ስብከት❤️
04/01/2014 የምሕረት ዓመት
#እግዚአብሔር_ለሰው_ስላዘጋጀው_መዳን_ቅዱስ_ዮሐንስ_አፈወርቅ_ያስተማረው_ትምህርት
ክፍል ሁለት
(🗣ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ይሄን ትምህርት ያስተማረው በ388 ዓ/ም ነበር።በእግዚአብሔር ሕልውና ለማያምኑት እንትጋላቸው ምክንያቱም የእግዚአብሔር ሐሳብ ሁሉም ሰው እንዲድን ነው ካለ በኋላ እግዚአብሔር ለሰው ስላዘጋጀው መዳን እንዲህ ብሎ አስተማረ።)
🛑ተመልከቱ! ፍጥረታትን ኹሉ የፈጠራቸው፥እኛንም ካለመኖር ወደ መኖር ያመጣን፥ እንዲያድነን፥ ከስህተት ሁሉ ጠብቆም ርስቱንና መንግስቱን እንዲያወርሰን እንጂ እንድንጠፋ ወይም እሳቱ ለማይጠፋው ትሉ ለማያንቀላፋው ለምረረ ገሀነም አይደለም።ይህቺን መንግስቱን እንኳን ያዘጋጀልን እኛ ወደዚህ ምድር ከመጣን በኋላ አይደለም።ከመምጣታችን በፊት ነው እንጂ/ማቴ.25:34/።
👉እንግዲህ የእግዚአብሔር ፍቅሩ እንደምን ከቃላት እንደሚያልፍ ገና ፍጥረታት ሳይፈጠሩ፥የሰው ልጆች ራሳቸው እንኳን ካለ መኖር ወደ መኖር ሳይመጡ ርስቱን መንግስቱን ማዘጋጀቱ ለእኛ ያለው ሐሳብ እንደምን እንደማይመረመር ሰው ሁሉ ይድን ዘንድ እንደሆነም ታስተውላላችሁን?
ይቀጥላል……
📖ምንጭ፦ የኦሪት ዘፍጥረት ትርጓሜ/ድርሳን ፫/ገፅ ፷፫/
❤የእለቱ መልእክት❤️
03/01/2014 የምሕረት ዓመት
️#ለሚጠፉ_ሰዎች_ግድ_ሊለን_እንደሚገባ_ቅዱስ_ዮሐንስ_አፈወርቅ_ካስተማረው
ክፍል አንድ
(👉ይህ አሁን ማካፍላችሁ ጥንታዊ ትምህርት ነው።ግን በዚህ ዘመንም ኃላፊነታችንን ለዘነጋን ሰዎች የሚያነቃ ነው ብዬ አምናለሁና ተባረኩበት።
👉ይህ መልእክት ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ በ388 ዓ/ም ካስተማረው ትምህርት የተወሰደ ነው፤እግዚአብሔር ፍጥረተ ዓለሙን በቃሉ ብቻ ከምንም ቢፈጥራቸውም ፍጥረት ራሱን በራሱ አስገኘ የሚሉ ቁስ አካላውያንን ልበ እውሮች ቢላቸውም ቅሉ ክርስቲያን ላላመነ ልበ እውርም ቢሆን ስላለበት ኃላፊነት እንዲህ ብሎ አስተማረ)
👉ልባቸው እውር ለሆኑ ሰዎች የሚታየውንና የተገለጠውን ለማስረዳት የምንደክመው ለምንድን ነው? ቢሆንም የመፅሐፍ ቅዱስን ትምህርት ለእነዚህ ሰዎች መናገራችንን፤በተቻለን አቅምም ከወደቁበት የስህተት ማጥ ለማውጣትና ወደ እውነትም እንመራቸው ዘንድ ትጋታችንን አናቋርጥ።ምንም እንኳን በስህተት ጎዳና ቢሆኑም እንደ እኛ ሰዎች ናቸውና አስፈላጊውን እንክብካቤ ሁሉ ልናደርግላቸው ይገባል።ግራ ባናጋባቸውና በታላቅ ትጋት ሆነን አስፈላጊውን መፍትሔ ብንሰጣቸው ቀስ በቀስ ወደ ጤናማ ጎዳና ሊመጡ ይችላሉ።ልብ በሉ! #እግዚአብሔር_ሰዎችን_ከማዳን_ውጪ_ሌላ_ምንም_ዓላማ_የለውም።ቅዱስ ጳውሎስም ይህን እንደዚህ ብሎ ግልፅ አድርጎልናል፦ "ሰዎች ሁሉ ይድኑ ዘንድ፤እውነትንም ያውቋት ዘንድ እርሱ (እግዚአብሔር) ይወዳል/1ጢሞ.2:4/።ዳግመኛም ራሱ እግዚአብሔር እንዲህ ብሎአል፦ "የኃጥኡን ሞት አልፈቅድም፤ከክፉ መንገዱ ይመለስና በሕይወት ይኖር ዘንድ ነው እንጂ" /ሕዝ.18:23/።
ይቀጥላል………
📖የኦሪት ዘፍጥረት ትርጓሜ/ድርሳን ፫/ገፅ 62-63/
❤️የዓመቱ መጨረሻ መልእክቴ❤️
ጳጉሜን 5/2013 የምሕረት ዓመት
#ለ2014_እንዲህ_ብናቅድስ፦
🗣አገልጋይ ብርሃኑ ታምራት
👉ሰላም ለእናንተ ይሁን! በምሕረቱ የጠበቀንና ወደ 2014 በሕይወት ያሸጋገረን አምላክ ያሕዌ የተባረከ ይሁን።ያልጠፋነው ከእግዚአብሔር ምሕረት የተነሣ ነው።
👉እግዚአብሔር በእኛና ለእኛ የዘላለም እቅድና ሀሳብ አለው።በሰው ልብ ብዙ ሀሳብ ቢኖርም የእግዚአብሔር ሀሳብ ነው የሚፈፀመው።ከእግዚአብሔር በታች እንደ ብርሃን ልጆች እቅድን እናቅዳለን።ስለዚህም፦እግዚአብሔር ቢፈቅድና በሕይወት ብንኖር ለ2014 እንዲህ ብናቅድስ፦
#1 መፅሐፍ ቅዱስን አንብቤ እጨርሳለሁ ስለዚህ ከመስከረም አንድ እጀምራለሁ።
#2 ቋሚ የፀሎት ሰአት መድቤ ቢያንስ በቀን ሁለቴ በአምላኬ ፊት እሆናለሁ።
#3 በተደጋጋሚ ምወድቅበት ኃጢአት ላይ የፀሎትና የምክርም እገዛ በማግኘት በጌታ ፀጋ አሸንፈዋለሁ።
#4 ………በክፍት ቦታው ቁጥር በማስቀመጥ ለእነዚህን ያህል ሰዎች ወንጌልን እመሰክራለሁ።ከመሰከርኩላቸው ሰዎች ቢያንስ ይሄን ያህሉ እንዲድኑ እተጋለሁ።
#5 በቤተክርስቲያን አባልነት ያልተያዛችሁ ደግሞ በዚህ ዓመት ለቃሉ እውነት ወደ ምታደላ ቤተክርስቲያን አባል እሆናለሁ።በአሥራቴም እታመናለሁ።በሉ።
#6 ቢያንስ በሳምንት አንድ ቀን በፆምና በፀሎት እጋደላለሁ
#7 ………በክፍት ቦታው ቁጥር በመሙላት።እነዚህን ያህል መፃሕፍትን አነባለሁ።
#8 ድሆችንና የተቸገሩትን ከማገኘው ነገር ላይ አስባለሁ።
#9 ቤተክርስቲያኔ ባወጣችው እቅድና ባዘጋጀችልኝ ፕሮግራም ሁሉ በንቃት እካፈላለሁ
#10 በመጨረሻ ሲንግሎች ፍቅረኛ ያዙ፤በቂ የመጠናናት ጊዜ የወሰዳችሁ ተጋቡ፥የተጋባችሁ ውለዱ……የልባችሁን መሻት ይፈፅምላችሁ……ስለትዳር በማሰብ ግን ልባችሁ አይክበድባችሁ።ሉቃ.21:34
👉ማቀድ ከእቅዳችን ይበልጣል።
📖ኤፌሶን 5
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
¹⁶ ቀኖቹ ክፉዎች ናቸውና ዘመኑን ዋጁ።
¹⁷ ስለዚህ የጌታ ፈቃድ ምን እንደ ሆነ አስተውሉ እንጂ ሞኞች አትሁኑ።
❤️መልካም አዲስ ዓመት።
❤️የእለቱ መልእክት❤️
29/12/2013 የምሕረት ዓመት
#ኧረ_በመፅሐፍ_ቅዱስ_አምላክ
🗣በአገልጋይ ብርሃኑ የኢየሱስ
👉የሆነ ጊዜ አንድ አገልጋይ ያደረገውን ኢንተርቪው እየተከታተልኩ ነበር።አገልጋዩ በዘመናችን ስሙ በዝና የመነሳቱን ያህል በክፉም ይነሳል።እናም ጠያቂው "ስምህ በተደጋጋሚ ሲነሳና ሲጠፋ አያለሁና ምክንያቱ ምንድነው ትላለህ?" ብሎ ይጠይቀዋል።አገልጋዩም፦ "መፅሐፍ ምን እንደሚል ታውቃለህ?…እግዚአብሔር እንሳስትን ከፈጠራቸው በኋላ ስም እንዲያወጣላቸው ያመጣቸው ግን ወደ አዳም ነው…እናም ይሄው ከዛን ጊዜ ጀምሮ ሰው ስም እንዳወጣ ነው" በማለት መለሰ።በአገልጋዩ መልስ መሳቄም መገረሜም ማዘኔም አልቀረም።
👉የሳኩት የሰማው ሁሉ የሚያምነው ስለሚመስለው ሞኝነቱ ነው ያሳቀኝ።የተገረምኩት የአዳም ለእንስሳት ስም ማውጣት ከእርሱ ስም መጥፋት ጋር ለማገናኘት መዳከሩ ለራሱ ስድብ መሆኑን እንዴት አልተረዳውም ብዬ ነው።አዳም ለእንስሳት ስም አወጣ።የአዳም ልጆች እርሱ ጋ ሲደርሱ ለእንስሳ ስም አወጡ ማለቱ ነው ወይስ ምንድን ነው ሀሀሀ።ብቻ ገርሞኛል።ያሳዘነኝ ግን የመፅሐፍ ቅዱስ ሀሳቦችንና ጥቅሶችን እየጠመዘዙ ሰዎች ወደ ሚፈልጉት ሀሳብ ሚቀይሩት እስከመቼ ነው ብዬ ነው።
👉መፅሐፍ ቅዱስ ባለቤት የለውም ማለት ነው? እንደፈለገው ማንም ተነስቶ በጥቅስና በቃላት መጫወት ይችላል ማለት ነው? ኧረ በመፅሐፍ ቅዱስ አምላክ…ትንሽ እንኳን እንፍራ።የጥቅስም ጡር አለው።
👉የራሱን ትምህርት የሚደግፍ ከመሰለው አውዱንም ግሪኩንም እንይ ይልና የእርሱ ትምህርትን የሚቃወም ቃል ግን ሲጠቅሱበት አውዱና ግሪኩ አትበሉብኝ ባይ ነው።
🛑መፅሐፍ ቅዱስ ሰዋዊም መለኮታዊም ባህርይ አለው።በሰዋዊ ባሕርይው የፀሀፊውንና የተፃፈላቸውን ሰዎች ወቅታዊ ሁኔታ መረዳትን ማስቀደም ይገባል።በመለኮታዊ ባሕርዩውም በሰው ቋንቋ የተፃፈውን የመለኮት ቃል ለመተርጎምና ለመረዳት የመንፈስ ቅዱስን እገዛ በፀሎት መጠየቅን ይሻል።መፅሐፍ ቅዱስን ከማንበብና ከማነብነብ ወደ ማጥናት፤ከማጥናትም ወደ ትክክለኛው ሥነ አፈታት እንጠጋ።እንጠንቀቅ ምክሬ ነው።ተባረኩልኝ።
👉📖2ኛ ጴጥሮስ 1 (አዲሱ መ.ት)
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
²⁰ ከሁሉ አስቀድሞ ይህን ልታውቁ ይገባችኋል፤ በመጽሐፍ ያለው የትንቢት ቃል ሁሉ ማንም ሰው በገዛ ራሱ መንገድ የሚተረጒመው አይደለም፤
²¹ ምክንያቱም ትንቢት ከእግዚአብሔር የተላኩ ሰዎች በመንፈስ ቅዱስ ተመርተው ተናገሩት እንጂ ከቶ በሰው ፈቃድ የመጣ አይደለም።
❤️የእለቱ መልእክት❤️
27/12/2013 የምሕረት ዓመት
#ሁለት_ፅንፎች_በቤተክርስቲያን
🗣በአገልጋይ ብርሃኑ የኢየሱስ
👉ምንም መልካም ነገር ሲለጠጥ ክፉን ነገር ይወልዳል።ነጭ የደም ሴሎቻችን በሽታን የሚከላከሉንን ናቸው።ከመጠን ሲያልፍ ግን ነጭ የደም ሴል በሽታ ከመከላከል በሽታ ወደ መሆን ይለወጣል።በአዲስ ኪዳን አማኞችም ዘንድ የሚለጠጡ ነገሮች እየበዙ ከመጡ ቆዩ።
👉በአማኞች ዘንድ እየተለጠጡ ከመጡና በሽታ ወደ መሆን እያደጉ የመጡት አሳቦችና አስተምህሮዎች መካከል፦ የእግዚአብሔር ልጅነታችን፥በክርስቶስ የሆንነውና ያገኘነው በረከቶቻችን፥ፀጋ፥ነፃነት የሚሉት ይገኙበታል።
🛑አንዳንዱ አማኝ በሰይጣን ክስ አንገቱን ደፍቶ እንደ ባሪያ በእግዚአብሔር ቤት ይኖራል።አንዳንዱ የእግዚአብሔር ልጅ የሆነው ከፈቃዱ በእምነት በመወለድ እንደሆነ ሳያውቅ ልጅነቱን ለጥጦት የኢየሱስ እኩያ ካልሆንኩ ይላል።
🛑አንዳንዱ በክርስቶስ የሆነለትንና በክርስቶስ የተደረገውን ረስቶ የሆነውን ገና ለመሆን ይጋደላል።አንዳንዱ ደግሞ በክርስቶስ የሆነውንና የተደረገውን ብቻ በመለጠጥ ከእግዚአብሔር ጥገኝነት እንደተላቀቀ ትንሽዬ አምላክ ራሱን ይቆጥራል።
🛑አንዳንዱ በፀጋ ድኛለሁ ብሎ ከሕግ በታች ሲኖር ሕጉን ለመጠበቅና ለማስጠበቅ ይጋደላል።ሌላኛው በፀጋ አንዴ ድኛለሁ ደኅንነቴንም አላጣም ብሎ ስንፍናና ኃጢአት ቤት ሰርተውበታል።
❤️ከራሱና ከእግዚአብሔር ቃል ጋር የታረቀ ትውልድ ተነስቶ ማየት እግዚአብሔር ይፈልጋል።ከተፃፈው ሳናልፍ፤እግዚአብሔርን በመውደድና በመፍራት ለክርስቶስ ወንጌል የተለየን እንሁን!!!
👉📖“እንግዲህ ወንድሞች ሆይ፤ ለእናንተ ጥቅም ብዬ በዚህ ጒዳይ እኔን ራሴንና አጵሎስን ምሳሌ አድርጌ አቅርቤላችኋለሁ፤ ይህንም ያደረግሁት፣ “ከተጻፈው አትለፍ” የሚለውን ከእኛ እንድትማሩ ነው። ስለዚህ አንዱን ሰው ከሌላው አብልጣችሁ አትመኩበት።”
— 1ኛ ቆሮንቶስ 4፥6 (አዲሱ መ.ት)
❤️የእለቱ መልእክት❤️
15/12/2013 የምሕረት ዓመት
#ዳርቻ_ሥፍርና_ቁጥር
🗣በአገልጋይ ብርሃኑ ዘኢየሱስ
👉እግዚአብሔር ራሱ መኖሪያ ነው እንጂ እርሱ መኖሪያ የለውም።ለዘመኑ ጥንት፥ለመንግስቱም ፍፃሜ የለውም።እርሱ በማይቆጠር ዘመን፥በማይወሰን ቦታ ይኖራል።እግዚአብሔር ትልቅ ነው።ማስተዋሉም አይመረመርም።የሐዋ.7:48-50፤ኢዮብ.36:26
👉ታዲያ ይሄ ትልቁ እግዚአብሔር ለፍጥረተ ዓለሙ ሁሉ ዳርቻን አበጅቶአል።ሰማይን በስንዝሩ ለክቶታል።ውኆችን በእፍኙ ሰፍሮአቸዋል።ተራሮችንና ኮረብቶችንም በሚዛኑ መዝኖአቸዋል።ከዋክብትን ቆጥሮአቸዋል በየስማቸውም ይጠራቸዋል።ለባሕር፥ለውቅያኖስና ለሀይቆች ወሰንን አበጅቶላቸዋል።ኢሳ.40:12፤ኢዮብ.38:8-11
👉ገደብ አልባ ትልቅ፤በዘመናት የሸመገለ አልፋ ዖሜጋ እግዚአብሔር ብቻ ነው።ዳን.7:9
👉በምድር ላለ ለየትኛውም አስቸጋሪም ሆነ ደስታን የሚሰጡ የሚባሉ ነገሮች ላይ ሁሉ ገደብን አስቀምጧል።ዛሬ የምታዩት ነገ አይኖርም።ዛሬ የሌለውም ነገ ይመጣል።ሆኖም ምንም ይምጣ ምን ገደብ አበጅቶለታል።
👉ሀዘናችን ገደብ አለው።ጦርነቱም መጨረሻ አለው።አስቸጋሪ ሁኔታዎችም ዳርቻ አላቸው።ያልተሰፈረና ያልተቆጠረ ምንም ነገር የለም።
❤️በእግዚአብሔር ታመኑ።በማዳኑ ተደገፉ።መልካም ነገር ሲገጥማችሁ በመከራ ያሉትን ባላችሁ ነገር አስቧቸው።ክፉ ቀን ሲገጥማችሁ አሳላፊውንና አሳራፊውን መድኃኔዓለምን አስቡ።
🙏የጌታ ማፅናናት ይብዛላችሁ!!!
❤️የእለቱ መልእክት❤️
09/12/2013 የምሕረት ዓመት
#የእግዚአብሔር_ፀጋ_ሦስቱ_አሠራሮች_ምንድን_ናቸው?
🗣በፀጋው አገልጋይ የሆነ ብርሃኑ
❤️የእግዚአብሔርን ፀጋ የመሰለ ተወዳዳሪ ርእስ አዲስ ኪዳን የለውም።የሆነው ሁሉ የሆነው በእግዚአብሔር ፀጋ ነው።ሕይወት፥ ድነት፥ አገልግሎት፤ ፥መንፈሳዊ ሥጦታዎች ሁሉ የእግዚአብሔር ፀጋ ውጤት ናቸው።የእግዚአብሔር ፀጋ ለእኛ የበዛው በክርስቶስ ኢየሱስ አማካኝነት ነው። #ፀጋ_የሰጪውን_ለጋስነት_ብቻ_መሠረት_ያደረገ_ሥጦታ_ነው።ከእግዚአብሔር የተቀበልነው ሁሉ በነፃና ለሥጦታው ተገቢ ሰዎች ባልሆንበት ጊዜ ነው።
❤️አንዱ የእግዚአብሔር ፀጋ ሦስት አሠራሮች አሉት።እነርሱም፦
#1_የሚያድን_ነው፦
👉 ከጨለማው ሥልጣን የምናመልጠው በእግዚአብሔር ፀጋ ነው።ፀጋው በእምነት አማካኝነት ከኃጢአት፥ከሞትና ከኩነኔ ያድነናል።ቃሉም ሰዎችን ሁሉ የሚያድን የእግዚአብሔር ፀጋ ተገልጧል ይላል።ቲቶ.2:11።ሕግ የሚኮንን ሲሆን ፀጋ ግን ያድናል።ሁሉም አማኝ ከፀጋ በታች እንጂ ከሕግ በታች አይደለም።ስለዚህ በክርስቶስ ኢየሱስ ላሉት አሁን ኩነኔ የለባቸውም።ሮሜ.8:1 በሚያድነው በሚያስመልጠው የእግዚአብሔር ፀጋ አምናችሁ ዳኑ እንጂ በሕግ የራሳችሁን ፅድቅ ለማቆም በከንቱ አትድከሙ።
📖“ #ጸጋው_በእምነት_አድኖአችኋልና፤ ይህም የእግዚአብሔር ስጦታ ነው እንጂ ከእናንተ አይደለም፤”
— ኤፌሶን 2፥8
#2_አስተማሪ_ነው፦
👉የእግዚአብሔር ፀጋ ካዳነን በኋላ አይተወንም።ታላቅ ወንድማችንን እንድንመስል ያስተምረናል እንጂ።የዳንበት ያው ፀጋ መምህራችን ነው።መምህራችን ጳውሎስ አደራ የሰጠን ለፀጋው ቃል ነው።የማይሳሳት፥እንከን አልባ ነው የእግዚአብሔር ፀጋ።ተደገፉበት።
📖“ይህም ጸጋ በኀጢአት መኖርንና ዓለማዊ ምኞትን ክደን፣ በአሁኑ ዘመን ራሳችንን በመግዛት በጽድቅ፣ #በእውነተኛ_መንፈሳዊ_ሕይወት_እንድንኖር_ያስተምረናል፤”
— ቲቶ 2፥12 (አዲሱ መ.ት)
#3_ረዳት_ነው ፦
👉የእግዚአብሔር ፀጋ ካዳነን በኋላ መሪና አስተማሪ መሆኑ ብቻ ሳይበቃው ይረዳናል።አቅም ይሰጠናል።ሕግ ያዝሃል እንጂ ኃይል አይሰጥህም።ፀጋ ግን ያዝህ ያስተምርህና አቅም ይሰጥሃል።ብቻ እኛ በእምነት ወደ ፀጋው ዙፋን በእምነት እንቅረብ።
📖“እንግዲህ ምሕረትን እንድንቀበል #በሚያስፈልገንም_ጊዜ_የሚረዳንን_ጸጋ እንድናገኝ ወደ ጸጋው ዙፋን በእምነት እንቅረብ።”
— ዕብራውያን 4፥16
👉ይሄ ነው የፀጋው ክብር፤ይሄ ነው የፀጋው ብዛት።የፀጋው ክብር ይመስገን።አሜን።።
❤️የእለቱ መልእክት❤️
03-12-2013 የምሕረት ዓመት
#ስለ_ወንጌል_ያሉብን_ሦስት_ኃላፊነቶች_ምንድን_ናቸው?
🗣በአገልጋይ ብርሃኑ ዘኢየሱስ
❤️ወንጌል የምሥራች ነው።ከዘፍጥረት እስከ ራእይ ያሉት መፃሕፍት ወንጌል ተብለው ይጠራሉ። ምክንያቱም መፃሕፍት ሁሉ የሚናገሩት ስለ አብ አንድያ ልጅ ስለ ኢየሱስ ነውና።ወንጌል ስለ ኢየሱስ ነው።እናም እኛ ክርስቲያኖች ስለ ወንጌል ሦስት የታወቁ ኃላፊነቶች አሉብን።እነርሱም፦
#1ኛ_በወንጌል_ማመን_ነው።
👉በወንጌል በፍፁም ልባችን ስናምን እንድናለን።ለራሳችን ማምለጥና ጥቅም በወንጌል ማመን አለብን።"““ጊዜው ደርሶአል፤ የእግዚአብሔር መንግሥት ቀርባለች፤ ንስሓ ግቡ፤ በወንጌልም እመኑ” እያለ ይሰብክ ነበር።”
— ማርቆስ 1፥15 (አዲሱ መ.ት)
ጊዜው ደርሶአል።የእግዚአብሔር መንግስትም ቀርባለች ስለዚህ በወንጌል ማመን አለብን።እግዚአብሔርን ሰምተው፥ራሳቸውን ክደው፥ኢየሱስን የሕይወታቸው ጌታ አድርገው በወንጌል ያመኑ ሁሉ ይድናሉ።
#2ኛ_ወንጌልን_መስበክ፦
👉ለብዙ ሰዎች መስበክ የመድረክ ሥራ ነው።ለአንዳንዶች ደግሞ የአገልጋዮች ድርሻ ብቻ ነው።ነገር ጌታ ኢየሱስ ይሄንን ተልእኮ የሰጠው ለአማኞች ሁሉ ነው።ማቴ.28:18-20 አማኞች የዓለም ብርሃን የምድር ጨው ናቸው።ማቴ.5:13:16 በጴጥሮስ መፅሐፍ ደግሞ የጠራንን የእርሱን በጎነት ልንናገር እንደተመረጥን ይናገራል።1ጴጥ.2:9።ጳውሎስ ያለ ሰባኪ ሰዎች ማመንና መዳን ስለማይችሉ መስበክ እንዳለብን ፅፎአል።ሮሜ.10:13-17።ወንጌልን አለመስበክ ከበሽተኛ መድኃኒትን እንደመደበቅ ይቆጠራል።በወንጌል የማያፍር ወንጌልን ይሰብካል።ሮሜ.1:16 ጌታ ኢየሱስ እንዲህ ብሎአል፦በሰዎች ሁሉ ፊት የሚመሰክርልኝ እኔ ደግሞ በአባቴና በመላእክት ፊት እመሰክርለታለሁ።እንመስክር።ማቴ.10:32-33
#3ኛ_ወንጌልን_መጠበቅ(ምካቴ)፦
👉ወንጌል አንድ ነው።ይሄን አንዱን ወንጌል ግን ሊያጣምሙ ሊበርዙ የሚፈልጉ ሀሰተኞች ግን በየጊዜው ይነሳሉ።እናም እኛ አማኞች ለወንጌል እውነት በምካቴ እምነት መቆም አለብን።ለሀሰተኞች መልስ ለመስጠት ዘወትር መዘጋጀት አለብን።በአዲስ ኪዳን ካሉት 27ት መፃሕፍት ከግማሹ በላይ የተፃፉት ወንጌልን ከብረዛና ከስህተት ትምህርት ለመጠበቅና ለሀሰተኞች ምላሽ ለመስጠት ነው።ወንጌልን ከነሙሉ መሠረታዊ እውነቱና ትምህርቱ በደንብ እንረዳው።ተረድተንም እንጠብቀው።ምንጠብቀውም መሠረታዊ ትምህርቶችን በማስተማርና ግንዛቤ በመፍጠር ለስህተት ትምህርቶችም ምላሽ በመስጠት ነው።ሮሜ.16:17-18፤ገላ.1:6-9፤2ቆሮ.11:3-4፥13-15፤2ጴጥ.3:16-18፤1ጴጥ.3:15
❤️እነዚህን ሦስት አይቀሬ ኃላፊነቶቻችንን በጌታ ፀጋ እንወጣ።ወንጌልን እንመነው፥እንስበከው፥እንጠብቀው።በነገር ሁሉ የጌታ ፀጋ ከእናንተ ጋር ይሁን!!!
እባክዎን ለሌሎች ያካፍሉት።
#ተቀባይነትን_ለማግኘት
29-11-2013 የምሕረት ዓመት
🗣በብርሃኑ ዘኢየሱስ
👉ብዙዎቻችንን አንድ የሚያደርገን ፍላጎት ይመስለኛል።ማንኛችንም ቢሆን ተቀባይነት እንፈልጋለን።ምናልባት መጠኑ ሊለያይ ይችል ይሆናል እንጂ።አይ ተቀባይነትን አልፈልግም የሚል ሰው እንኳን "ተቀባይነትን የማይፈልግ ሰው" አድርገን እንድንቀበለው ይፈልጋል።
✝አንድ እውነት ግን ማወቅ አለብን።ተቀባይነት ማግኘትን ከራሳችን በላይ ልንቀበለውና ልንፈልገው አይገባም።ከራሳችን በላይ ተቀባይነትን ስንፈልግ ራሳችንን እናጣዋለን።
☠ሰዎች እንዲቀበሉን አብዝተን የምንፈልግ ከሆነ የራሳችንን ስሜት በሰዎች ስሜት፤ፍላጎታችንንም በፍላጎታቸው እንተካዋለን።ከዛም የሰው ባሪያ እንሆናለን።
🤝ብዙዎችን የሚያስማማ ሀሳብ እየፈለግን እናቀነቅነዋለን።አንዳንዴም ከፍ ሲል በሰው ሁሉ ፊት ተቀባይነት ላለማጣት ክርስቶስን እስከመሸሸግ ይደረሳል።
🤙ሰዎች እንደ አራዳ እንዲቀበሉን ጠጪ፥ተዝናኚ፥አጫሽ መሆን ያሳፍራል።ሰዎች ሥርአት እንዳለው ሰው እንዲቀበሉንም ቸርች ተመላላሽ መሆን ልክ አይደለም።ፕሮግራም ተካፋይ ከመሆን ኅብረት የሚያደርግ ሰው ነው መሆን የሚገባውና።
👩❤️👨በሚወዱትና በሚያፈቅሩት ሰው ተቀባይነት ለማግኘት ያኛው ሰው የሚወደውን ማድረግ፥ትክክለኛ ስሜትን መደበቅ፥መዋሸት፥ያለው ሰው መስሎ ለመታየት በብድር መሽቀርቀር፥በማያስቀው በፍቅረኛ ቀልድ መንፈር የተቀባይነት ጥማት በሽታ ነው።ራስን መቀበል ከዛ ራስን መስጠት ነው ፍቅር።ይሄን ስላችሁ ልክ ያልሆነ መተው ያለብንን ነገር አንተው ማለቴ አይደለም።ራስን ትቶ፥ራስን ገድሎ ግን የፍቅረኛ አሽከር መሆን ፍቅር አይደለም።
🗣📖በምእመናን ተቀባይነት ለማግኘት ጥማት ያለበት ሰው ስሜት እያነበበ፥የአየር ሁኔታውን እያነበበ ይሰብካል።አገልጋይ ጊዜው በሚጠይቀው ነገር ላይ ተመስርቶ አማኞች የሚያስፈልጋቸውን ትክክለኛ የጌታ ሀሳብ የሚመግብ ነው።
🔴ቤተሰቦቼ ተቀባይነትን ማግኘት መፈለግ ጤነኛ ስሜት ነው።ከመጠኑ እንዳያልፍና ራሳችንን እንዳያሳጣን ግን እንጠንቀቅ።ጲላጦስ በሕዝቡ ያለውን ተቀባይነት ለማስቀጠል ንፁሁን ኢየሱስን እጁን ታጥቦ ፈርዶበታል።የተቀባይነት ጥማት ሕይወትን ያስገድላል።ሕሊና ያሸጣል።እውነት ላይ ያስዋሻል።እንጠንቀቅ።
“ጲላጦስም የሕዝቡን ፈቃድ ሊያደርግ ወዶ በርባንን ፈታላቸው፥ ኢየሱስንም ገርፎ እንዲሰቀል አሳልፎ ሰጠ።”
— ማርቆስ 15፥15
