የአገልጋይ ብርሃኑ ገፅ
Open in Telegram
ይህ የአገልጋይ ብርሃኑ ገፅ ነው።ዓላማዬ የተለያዩ መፅሐፍ ቅዱሳዊ ትምህርቶችን ማካፈልና ማድረስ ሲሆን ምክሮችን፥አባባሎችን፥ፀሎቶችንና ትዝብቶቼን የማካፍልም ይሆናል።የሰራዊት ጌታ እግዚአብሔር ወደ ልቤ ያመጣውንና የተናገረኝንም እፅፋለሁ።ትውልዱን ወደ ኢየሱስ የሚያስጠጋውን የትኛውንም ነገር የምፅፍበት ገፄ ነው።በማንበብና ሼር በማድረግ ከአገልግሎቴ ጎን ይቁሙ።0984005562.
Show more447
Subscribers
+224 hours
+87 days
+3030 days
Posts Archive
ታሪኬ ይሄ ነው፦
1ኛ ጢሞቴዎስ 1 (አዲሱ መ.ት)
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
¹⁵ ‘ #ክርስቶስ_ኢየሱስ_ኀጢአተኞችን_ለማዳን_ወደ_ዓለም_መጣ’ የሚለው ቃል እውነተኛና ሰው ሁሉ ሊቀበለው የሚገባ ነው፤ #ከኀጢአተኞችም_ዋና_እኔ_ነኝ።
¹⁶ ነገር ግን ክርስቶስ ኢየሱስ በእርሱ ለሚያምኑና #የዘላለምን_ሕይወት_ለሚቀበሉ_ወሰን_የሌለው #ትዕግሥቱን_ከኀጢአተኞች_ዋና_በሆንሁት_በእኔ #እንደ_ምሳሌ_አድርጎ_ያሳይ_ዘንድ_ምሕረትን_አገኘሁ።
✝✝✝ኪዳነ ምሕረት ማን ናት?✝✝✝
👉👉ይቅርታ ኦርቶዶክሳውያን ወንድም እህቶቼ የኪዳነ ምሕረት ነገር ትንሽ ግር ስላሰኘኝ ነው መጠየቄ።ምኑ ግራ አጋባህ? አትሉኝም?
👉👉ኪዳነ ምሕረት ማለት ቀጥተኛ ትርጉሙ የምሕረት ኪዳን ማለት ነው።ታዲያ የምሕረት ኪዳን መባል የሚገባው ሰው አለን? ለሰውስ ሆነ ለመልአክ እንዲህ ዓይነት ስም ለመስጠት መነሻ የሚሆን የመፅሐፍ ቅዱስ ሀሳብስ አለን? ከሌለ ከየት መጣ?
👉👉ኪዳነ ምሕረት ማለት ድንግል ማርያም ናት።ኪዳነ ምሕረት የተባለችው የእምርልሻለሁ ቃል ኪዳን ስለገባላት ነው ከተባለስ <<የእምርልሃለሁ፡የእምርልሻለሁ>> ቃልኪዳን ያልተቀበለ ማን አለ? ለአርሴማ፣ለክርስቶስ ሠምራ፣ለተክለሃይማኖትስ ተብሎ የለም እንዴ እንደትረካችሁ፤ ታዲያ እነርሱስ ለምን ኪዳነ ምሕረቶች አልተባሉም??
👉👉ፍጥረት ሁሉ ሚድነው በድንግል ማርያም ኪዳን ከሆነ ጌታ ኢየሱስን መላክ አብ ለምን ፈለገ? ስምሽን የጠራ ይድናል የሚል ቃል ኪዳን እግዚአብሔር የሰጣት የኢየሱስን ስም የጠራ ይድናል ያለውን ረስቶት ነው? ወይስ የኢየሱስን ስም መጥራት በቂ አይደለሞ? ሮሜ 10:13
👉👉በምልጃዋ ከሆነ ሰው የሚድነው እግዚአብሔር በልጄ በኢየሱስ የሚያምን የዘላለም ሕይወት ያገኛል ለምን አለን? ጌታስ ለምን ተሠቀለ?
👉👉በድንግል ማርያም ስም የተማፀነ ፀሎቱ ይሰማል እግዚአብሔር ካለ ኢየሱስ በስሜ ምትለምኑትን አደርገዋለሁ ያለው ለምንድነው? ወይስ ስሙ በቂ ስላልሆነ የእርሷን ስም ጨምሩ ያለበት ያላየነው ቦታ ይኖር ይሆን?
👉👉ኢየሱስ እንደተስፋው ቃል የተወለደ ምሕረት ያገኘንበት የኪዳን ልጅ ከሆነ ኪዳነ ምሕረት መባል ያለበት እርሱ አይደለምን?
👉👉ለአብርሃምና ለዘሩም የተስፋው ቃል ተነገረ። ስለ ብዙዎች እንደሚነገር። ለዘሮቹም አይልም፤ ስለ አንድ እንደሚነገር ግን። ለዘርህም ይላል፥ እርሱም ክርስቶስ።
ወደ ገላትያ ሰዎች 3 : 16
❓እባካችሁ የኪዳነ ምሕረትን በዓል ምታከብሩ ሰዎች ጥያቄዬን መልሱ።❓
ፔጁን ይቀላቀሉ
👇👇👇👇
https://t.me/preac/256
❤️የእለቱ መልእክት❤️
#የሰውና_የመላእክት_መጫወቻ_የሆኑ_አገልጋዮች (3)
🗣በአገልጋይ ብርሃኑ ታምራት
4_አገልጋዮችን_ማሳደድ፦
👉 ሐዋርያው ተቀባይነት እንዳያገኝ የሚሰሩ፤ከሰው ልብ አገልጋይን የሚያሳዱ ነበሩ።አሁን ቸርቹ ተተክሏል።የሚያስፈልጋቸው ሁሉ አላቸው።መሪ አላቸው።በጀት አላቸው።ጳውሎስ ጉዳያቸው አይደለም።ጭራሽ በሌሎች አማኞችም ሆነ በቤተክርስቲያን ተቀባይነት እንዳይኖረው ይሰራሉ።ምን ዓይነት ጭካኔ ነው ይሄ? ጳውሎስ ግን እንዲህ አለ፦
📖1ኛ ቆሮንቶስ 4
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
⁸ አሁን ጠግባችኋል፤ አሁንስ ባለ ጠጎች ሆናችኋል፤ ያለ እኛ ነግሣችኋል፤ እኛ ደግሞ ከእናንተ ጋር እንድንነግሥ ብትነግሡ መልካም ይሆን ነበር።
⁹ #ለዓለም_ለመላእክትም_ለሰዎችም_መጫወቻ_ሆነናልና፤ እግዚአብሔር እኛን ሐዋርያቱን ሞት እንደ ተፈረደባቸው ሰዎች #ከሁሉ_ይልቅ_የኋለኞች_እንዳደረገን ይመስለኛልና።
👉ከአገልጋዮቻችሁ ጋር ብትከብሩ፤ከአገልጋዮቻችሁ ጋር ብትደሰቱ መልካም በሆነ ነበር።ግን አልሆነም።የልብ ስብራቱን ጥግ እንዲህ በማለት ነበር የገለፀው፦
📖1ኛ ቆሮንቶስ 4
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
¹⁰ #እኛ_ስለ_ክርስቶስ_ሞኞች_ነን እናንተ ግን በክርስቶስ ልባሞች ናችሁ፤ እኛ ደካሞች ነን እናንተ ግን ኃይለኞች ናችሁ፤ እናንተ የከበራችሁ ናችሁ እኛ ግን የተዋረድን ነን።
¹¹ እስከዚህ ሰዓት ድረስ #እንራባለን፥ #እንጠማለን፥ #እንራቆታለን፥ #እንጐሰማለን፥ #እንንከራተታለን፥
¹² በገዛ እጃችን #እየሠራን እንደክማለን፤ #ሲሰድቡን እንመርቃለን፥ #ሲያሳድዱን እንታገሣለን፥ #ክፉ_ሲናገሩን እንማልዳለን፤
¹³ #እስከ_አሁን_ድረስ_የዓለም_ጥራጊ_የሁሉም_ጉድፍ_ሆነናል።
👉ማጠቃለያ፦
❤️እውነተኛ አገልጋይ ቢመቸውም ባይመቸውም፤በብዙ ውርደትም በብዙ ክብርም መልእክቱን ሳይለውጥ ያገለግላል።አማኞች ግን ከሰይጣንና ከዓለም ጋር ሆነው በአገልጋዮች እንዳይጫወቱ ሊጠነቀቁና ኃላፊነታቸው ሊወጡ ይገባል።አገልጋዩን ባይረዱት እንኳን ስሙን ባያጠፉት፤ባይደግፉት እንኳን ቢያንስ ባይገፉት፤ባይወዱት እንኳን ሰው እንዲጠላው ባይሰሩ የእግዚአብሔርን መንግስት አይዋጉም ብዬ አምናለሁ።
❤️የእለቱ መልእክት❤️
#የሰውና_የመላእክት_መጫወቻ_የሆኑ_አገልጋዮች (2)
🗣በአገልጋይ ብርሃኑ ታምራት
3_የአገልጋዮችን_ስም_ማጥፋት፦
👉 ሐዋርያ ሊሆን የተጠራውንና መንፈሳዊ አባታቸውን ሐዋርያ አይደለም ብሎ ስም ከማጥፋት በላይ ምን ልብን የሚሰብር ነገር አለ።እንዲያድጉ ብዙ የደከመላቸውን ሰውና አጥቶ ትንሽ ስለረዱት ብቻ "ገንዘብ ይወዳል፤ያገለገለን ለገንዘብ ብሎ ነው" ከማለት በላይ አስደንጋጭ ነገር ይኖር ይሆን።ድንኳን ሰፍቶ ያንንም ሽጦ በሚያገኘው ገንዘብ የእለት ወጭውን እየሸፈነ ያገለገላቸውን ሐዋርያ በገንዘብ ፍቅር ካሙት የእውነት የወር ቀለብ ቢሰፍሩለት ምን ያደርጉት ይሆን?
👉ዛሬም በዚህ ጊዜ እንዲህ ነው።ሙሉ ጊዜውን ሰጥቶ ሲያገለግላቸው "ሥራ ፈት" የሚመስላቸውና ሥራ እየሰሩ ያገልግሉ የማይል ማን ነው? አገልግሎትን ከቀን ሥራ የሚያሳንሱ ምስኪኖች ስንት ናቸው? ልጆቹን እያስራበ፤ለሚስቱ የሚገባትን ነገር ማድረግ አቅቶት በሀዘን ልቡ የተሰበረ ስንት አገልጋይ ነው? አገልግሎት አቁሞ ወደ ሥራ ዓለም የገባ ስንቱ ነው? በዚህ ላይ ለመሠረታዊ ፍላጎቱ ገንዘብ የጠየቀ ለመኪናውና አዲስ ለሚጀምረው ቢዝነስ ገንዘብ የሚጠይቅ አገልጋይ እኩል በገንዘብ ፍቅር የሚታማበት ጊዜ ላይ ነን።ለእኔ ከዚህ በላይ መተላለፍ የለም።ብዙ ክርስቲያኖች አገልጋይ እነርሱ ለራሳቸው የሚፈልጉትን ሕይወት ሚፈልግ አይመስላቸውም።እንደውም አንዳንዶቹ አገልጋይ ሚበላ ሁሉ አይመስላቸውም።ጳውሎስ ለዛ ነው፦
📖1ኛ ቆሮንቶስ 9 (አዲሱ መ.ት)
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
³ ለሚመረምሩኝ የምሰጠው መልስ ይህ ነው።
⁴ ለመሆኑ፣ የመብላትና የመጠጣት መብት የለንምን?
⁵ እንደ ሌሎቹ ሐዋርያት፣ እንደ ጌታ ወንድሞችና እንደ ኬፋ ሁሉ፣ እኛስ አማኝ ሚስት ይዘን የመዞር መብት የለንምን?
⁶ ወይስ ጥረን ግረን መኖር ያለብን እኔና በርናባስ ብቻ ነን?
⁷ ለመሆኑ #በገዛ_ገንዘቡ_በወታደርነት_የሚያገለግል_ማን_ነው? #ወይን_ተክሎ_ፍሬውን_የማይበላ_ማን_ነው? #መንጋ_እየጠበቀ_የከብቱን_ወተት_የማይጠጣ_ማን_ነው?
⁸ ይህን የምናገረው እንደ ሰው አስተሳሰብ ነውን? የኦሪትስ ሕግ ይህንኑ ይል የለምን?
⁹ በሙሴ ሕግ፣ “የሚያበራየውን በሬ አፉን አትሰር” ተብሎ ተጽፎአልና። ለመሆኑ፣ #እግዚአብሔርን_ያሳሰበው_የበሬ_ጒዳይ_ነውን?
¹⁰ ይህን የተናገረው በርግጥ ስለ እኛ አይደለምን? የተጻፈው በትክክል ስለ እኛ ነው፤ ዐራሹ የሚያርሰው፣ አበራዩ የሚያበራየው ከምርቱ ድርሻ እንዳለው ተስፋ በማድረግ ነውና።
¹¹ እኛ በእናንተ መካከል መንፈሳዊ ዘር ዘርተን ከሆነ ለሥጋ የሚሆን ነገር ብናጭድ ትልቅ ነገር መሆኑ ነውን?
¹² ሌሎች ይህን መብት ከእናንተ ማግኘት ከቻሉ፣ እኛ ይበልጥ ማግኘት አይገባንምን? እኛ ግን በዚህ መብት አልተጠቀምንም፤ ይልቁንም #ለክርስቶስ_ወንጌል_ዕንቅፋት_እንዳንሆን_ሁሉንም_ነገር_እንታገሣለን።
¹³ በቤተ መቅደስ የሚያገለግሉ ምግባቸውን ከቤተ መቅደስ እንደሚያገኙ፣ በመሠዊያውም የሚያገለግሉ ከመሥዋዕቱ እንደሚካፈሉ አታውቁምን?
¹⁴ እንደዚሁም #ወንጌልን_የሚሰብኩ_ለኑሮ_የሚያስፈልጋቸውን_ከወንጌል_እንዲቀበሉ_ጌታ_አዞአል።
❤️የእለቱ መልእክት❤️
(14/02/2014 የምሕረት ዓመት)
#የሰውና_የመላእክት_መጫወቻ_የሆኑ_አገልጋዮች (1)
🗣በአገልጋይ ብርሃኑ ታምራት
👉የቆሮንቶስ ቤተክርስቲያን የተተከለችው በጳውሎስ አማካኝነት ነው።እርሱ ቤተክርስቲያኒቱን ከተከለ በኋላ ወደ ኤፌሶን አቅንቶአል።ከጳውሎስ መውጣት በኋላ ብዙ አገልጋዮች በዚህች ቤተክርስቲያን አገልግለዋል።በዚህች ቤተክርስቲያን አጵሎስና ጴጥሮስ በርናባስ አገልግለዋል።ከጥቂት ጊዜያት በኋላ በተፈጠረው ነገር ጳውሎስን ልቡን የሚሰብረው ነገር ተከስቶአል።የጳውሎስ ልብ የተሰበረው ከዚህ በታች በምዘረዝራቸው ምክንያቶች ነው።ጳውሎስ ልቡ በተሰበረበት ጉዳይ በዚህም ጊዜ የብዙዎች አገልጋዮች ልብ ተሰብሯል እየተሰበረም ነው።እነዚህ ልብ ሰባሪ ጉዳዮች ምንድናቸው?
#1_የአገልጋዮች_ቲፎዞ_መሆን፦
👉 የእግዚአብሔር አገልጋዮች እንደተሰጣቸው ፀጋ ከእግዚአብሔር ጋር የሚሠሩ ናቸው።ለአማኞች መለወጥና ማደግ የሚተክሉና የሚያጠጡ ናቸው።አገልጋዮች ለቤተክርስቲያን የተሰጡ በመሆናቸው ሁሉም አገልጋዮች ያለ ልዩነት የእኛ ናቸው።ቆሮንቶሳውያን ግን ቲፎዞ መሆንን መረጡ።እናም እኔ የጳውሎስ፥እኔ የኬፋ፤እኔ የአጵሎስ ነኝ ይሉ ጀመር።የሞተልን ግን አንዱ ጌታ ኢየሱስ ነው።በአገልጋዮቻችን ስም አልተጠመቅንም።ያልተከፈለውን ክርስቶስን በአገልጋዮች ቲፎዞነት ሊከፋፍሉት መረጡ።
👉በዚህ ሁሉ ግን ኬፋ፥ጳውሎስና አጵሎስ በጭራሽ ቲፎዞ ለማፍራት አገልግለው አያውቁም።እንደምታውቁት ቲፎዞ አፈራ ተብሎ የሚከሰሰው ግን አገልጋዩ ነው።ቲፎዞ የሚያፈሩ አገልጋዮች ቢኖሩም ቲፎዞ ያላቸው ሁሉ ቲፎዞ እንዲኖራቸው የሰሩ አይደሉም።ለዛ ነው ጳውሎስ፦
📖 “ስለዚህ ጊዜው ሳይደርስ በምንም ነገር አትፍረዱ፤ ጌታ እስኪመጣ ጠብቁ። እርሱ በጨለማ ውስጥ የተሰወረውን ወደ ብርሃን ያመጣዋል፤ በሰዎች ልብ ውስጥ ያለውንም ሐሳብ ይገልጠዋል። በዚያን ጊዜ እያንዳንዱ ሰው የሚገባውን ምስጋና ከእግዚአብሔር ዘንድ ይቀበላል።”
— 1ኛ ቆሮንቶስ 4፥5 (አዲሱ መ.ት)
👉በግልፅ ቲፎዞ ለማፍራት እስካልተንቀሳቀሰ ድረስ አገልጋይ ቲፎዞ ቢኖረውም እንኳን ኃላፊነት ሊወስድ አይችልም።ይሄንን የምለው አገልጋዮች ሰውን ሁሉ ወደ ክርስቶስ የማምጣትና የማጣበቅ ሥራቸውን በታማኝነት እየሰሩት ስላሉት ነው።
#2_የአገልጋዮችን_ዋጋ_ማሳነስ፦
👉 የቆሮንቶስ ቤተክርስቲያን አገልግሎት የተወደደ አገልጋይ ግን ዋጋው ያነሰባት ቤተክርስቲያን ናት።ለአገልጋይ ያላቸው ዋጋ "ቢፈልግ ያገልግል፥ካልፈለገ ይተወው ጌታ ሰው አያጣም" የሚሉና ውስጡ ጥመት ያለበት ሀሳብ የሚናገሩ ናቸው።አገልጋዩ ያገልግል እንጂ እርሱን በተመለከተ ጉዳያቸው አይደለም።ብቻ ያገልግል እንጂ ቢበላ ባይበላ፤ቢቸገር ቢመቸው፤ቅር ቢሰኝ ወይም ባይሰኝ ጉዳያቸው አይደለም።ጳውሎስ እንዲህ አለ፦ “እንግዲህ ሰው ሁሉ እኛን እንደ ክርስቶስ አገልጋዮችና እንደ እግዚአብሔር ምስጢር ባለ ዐደራዎች ሊቈጥረን ይገባል።”
— 1ኛ ቆሮንቶስ 4፥1 (አዲሱ መ.ት)
👉አጠገባችሁ ላለው አገልጋዩ የምትሰጡት ዋጋ ምን ያህል ነው? እንደ ሥጦታችሁ ትቆጥሩታላችሁ? ወይስ እናንተን የግድ ማገልገል ስላለበት መብት የሌለው "ሠራተኛ" ብቻ ነው? መልሱን ለራሳችሁ።
ይቀጥላል……
❤️የእለቱ መልእክት❤️
#ምሬትን_ለተሞላች_ነፍስ
(11/02/2014 የምሕረት ዓመት)
🗣በአገልጋይ ብርሃኑ
👉ነፍሳችን በምሬት የምትሞላበት ጊዜ ብዙ ነው።ይሄ የነፍስ ምሬት በአግባቡ ካልተያዘ ራስን የሚጎዳ ከእግዚአብሔርም የሚለይ ነው።
👉ለመሆኑ ነፍስ በምሬት የምትሞላው መች ነው?
💔የሚያውቅህ እንጂ የሚረዳህ በጠፋ ጊዜ
💔ከዳቦ ይልቅ የሰው ፍቅር በማጣት የተጎዳህ ጊዜ
💔በተደጋጋሚ ባመንከው ሰው በተከዳህ ጊዜ
💔በችግርህ ጊዜ በሰላሙ ዘመን አብሮህ የነበረው ወዳጅህን ፈልገህ ባጣኸው ጊዜ
💔ልመናህና ፀሎትህ ባሰብከው ጊዜ ያልተመለሰ እንደሆን
💔በማያቋርጥ ሰልፍ ውስጥ በሆንክ ጊዜ
💔ነፍስህ መፅናኛ ባጣች ጊዜ
💔የጭንቀት ሸክም፤የሕይወት ትርጉም ጥያቄ ባንገላታህ ጊዜ ነፍስህ በምሬት ትሞላለች።
👉ለማመስገን አቅም ታጣለህ።ዝም ብለህ አልቅስ አልቅስ ይልሃል።ከጭንቅህ የተነሣ እግዚአብሔር እንደ ሰው የተለወጠ ይመስልሃል።የራስህ ፅድቅ ገዝፎብህ የአምላክ ፍትሐዊነት ያንስብሃል።ዝም ብሎ ተመስገን ማለት ራስን ማታለል መስሎ ይሰማሃል።ወደ ላይ ቀና ስትል የተረጋጋ ሰማይን ታያለህ እንጂ ድምፅ አይመጣም።ዙሪያህን ስታይ ብትሞት ብትኖር ቸክ እንኳን የማያደርጉህ በራሳቸው ጉዳይ የተጠመዱ እልፍ ሰዎችን ታያለህ።በዚህ ጊዜ ነፍስህ በምሬት ትሞላለች።መፅናናት ቀላል አይሆንም።
👉በዚህ ሁሉ የነፍስ ምሬትና ሁኔታ ስናልፍ እግዚአብሔር ሲያግዘን እነዚህን ነገሮች ለማስተዋል ዐይኖቻችን ይከፈታሉ፦
❤️እግዚአብሔር ሁሉን የሚቆጣጠርና የሚጠብቀን ነው።መዝ.23
❤️በድካማችን ሊራራልን የማይችል ሊቀካህናት የለንም።ዕብ.4:15
❤️ከሰይጣን ውሸት የእግዚአብሔር እውነት እንደሚበልጥ ታስተውላለህ።የሰይጣን ውሸት እግዚአብሔር ትቶሃል የሚልነው።የእግዚአብሔር እውነት ግን አልተውህም ከቶም አልጥልህም የሚለው ኪዳን ነው።ዕብ.13:5-6
👉እግዚአብሔር እንድትወድቅ ቢፈቅድም በፍፁም ወድቀህ እንድትቀር አያደርግም።ያነሣሃል።ይረዳሃል።መዝ.91
❤️ሁሌም አብሮህ ነው።ፀሎትህ እንዳልተመለሰ ብታስብም እስከዛሬዋ ቀን ድረስ ሳትለምን ብዙ ነገር ሰጥቶሃል፤ኤፌ.3:18-21
❤️በድፍረት ኃጢአት በሠራህ ጊዜ እንኳን ታግሦሃል።መዝ.103:8-15
❤️እርሱ መልካም ነው።ለሚታገሱት ደግሞ እጅግ መሃሪና ቸር ነው።ናሆም.1:7
🤲ይሄ ቃል ለመፅናናትህ ይሁንህ፦
🙏“ #እኔ_ከአንተ_ጋር_ነኝና_አትፍራ፤ #እኔ_አምላክህ_ነኝና_አትደንግጥ፤ #አበረታሃለሁ፥ #እረዳህማለሁ፥ #በጽድቄም_ቀኝ_ደግፌ_እይዝሃለሁ።”🙏
— ኢሳይያስ 41፥10
❤️ክርስቶስ ኢየሱስ❤️
❤️ሰውን ለማዳን ሰው ቢሆንም ፍፁምና የተፈራ አምላክ ነው።
❤️ሐዋርያት የዳሰሱት እርሱ መላእክት ፊቱን ሊያዩት እንኳን የማይደፍሩት ግሩም ነው።
❤️5000 ሰዎችን ሁለት ዓሣና አምስት እንጀራ አበርክቶ ቢመግብም እርሱ ሁሌም የፍጥረት ሁሉ መጋቢ ነው።
❤️በተራራ ላይ ሆኖ ሲሰብክ ብዙዎች ቢሰሙትም እሥራኤላውያን እርሱ እንዳይናገራቸው የፈሩትና ሙሴን የላከው እርሱ ነው።
❤️ስለእኛ ኃጢአት በንጉሡ ሄሮድስና በጲላጦስ ፊት ቢቆምም ከአባቱ ጋር ማንም ሊቀርበው በማይችል ብርሃን የሚኖር ነው።
ይሄ የኔ አዲሱ የfb አካውንቴ ነው
አድ ያድርጉትና መንፈሳዊ መልእክቴን ያግኙ
https://www.facebook.com/100073659774240/posts/111189404679718/?substory_index=0&app=fbl
18-19፤ ይህም የልባችሁ ዓይኖች ሲበሩ የመጥራቱ ተስፋ ምን እንዲሆን በቅዱሳንም ዘንድ ያለው የርስት ክብር ባለ ጠግነት ምን እንዲሆን ለምናምን ከሁሉ የሚበልጥ የኃይሉ ታላቅነት ምን እንዲሆን ታውቁ ዘንድ ነው፤
#ድንግል_ማርያም
#ክፍል_ሁለት
#መልስ_የሚሻ_ጥያቄ
❓#የበዓላቶቿ_ብዛት
👉 እንደሚታወቀው በዓላት መታሰቢያዎች ናቸው።ትውልዱ መረሳት የሌለበት እንዳይረሳ በበዓላት በኩል ማስታወሻ ነገር ማኖር መፅሐፍ ቅዱሳዊ ነው።በተለይም በብሉይ ኪዳን የፋሲካ በዓል ዋናው ነበር።በአዲስ ኪዳን ግን ፋሲካችን ክርስቶስ ነውና ዓይናችንን ቀናት ላይ ማንሳት እንዳለብን ተፅፎልናል።
👉(ወደ ቆላስይስ ሰዎች ምዕ. 2)
----------
16፤ እንግዲህ በመብል ወይም በመጠጥ ወይም ስለ በዓል ወይም ስለ ወር መባቻ ወይም ስለ ሰንበት ማንም አይፍረድባችሁ።
17፤ እነዚህ ሊመጡ ያሉት ነገሮች ጥላ ናቸውና፥ አካሉ ግን የክርስቶስ ነው።
👉አሁን አካል የሆነው ክርስቶስ ስለመጣ በበዓላት መታሰር የለብንም።
👉በዓላት ሊኖሩን ይገባል እንኳን ካልን፦" ቀንን የሚያከብር ለጌታ ብሎ ያከብራል፤ የሚበላም እግዚአብሔርን ያመሰግናልና ለጌታ ብሎ ይበላል፤ የማይበላም ለጌታ ብሎ አይበላም እግዚአብሔርንም ያመሰግናል።"
(ወደ ሮሜ ሰዎች 14:6) ለኢየሱስ ክብር ብቻ ማድረግ አለብን።
👉 በኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን ግን እንዲህ አይደለም።ጌታ ኢየሱስ ሁለት ዓይነት በዓላት አሉት።እነርሱም፦ዐበይት(ትላልቅ) እና ንዑሳን(ትናንሽ) በዓላት ይባላሉ። ድንግል ማርያም ግን 33 ዐበይት በዓላት አሏት።የጌታ ትንሹም ትልቁም በዓሉ ቢደመር 18 ሲሆን የማርያም ግን 33 ነው።ትውልዱም ድንግል ማርያምን ከጌታ ጋር አስተካክሎ ወይም አስበልጦ ያስባታል።
👉 በወር እንኳን በ1 ልደቷ-በ3 ቤተ መቅደስ መግባቷ(ባታ)-በ6 ቁስቋም መግባቷ-በ7 ፅንሰቷ-በ10 የሥዕሏ በዓል-በ16 ኪዳነ ምሕረት ተብላ-በ21 እረፍቷ ትከበራለች።ጌታ ደግሞ በ27 መድኃኔዓለም-በ28 አማኑኤልና በ29 ኢየሱስ(ልደቱ) ይከበራል።
👉 ወገኖቼ ትውልዱ ላይ በዓል ብቻውን እንዴት ተፅዕኖ እንደፈጠረበት ተመልከቱ።
❓#የተጋነነ_ርኅራኄና_የተጋነነ_ጭካኔ
👉 በኦርቶዶክስ ሁሌም የሚሰበከው የድንግል ማርያም አዛኝነትና ርኅራኄና የእግዚአብሔር ፍርድና ጭካኔ ነው።መዝሙሩ ሁሉ <<አዛኜን አላት ተማሪው>> የሚል ነው።ኢየሱስ ከውርስ ኃጢአት ሊያድነን መጣ አድኖንም ሄደ አሁንም ከምንሰራው ተግባራዊ ኃጢአት ግን <<ያለ ማርያም አማላጅነት ዓለም አይድንም>> ይላሉ።ስለጌታ ኢየሱስ አመጣጥና መድኃኒትነት ግን መፅሐፍ የሚለው በጣም የተለየ ነው።
📖" መዳንም በሌላ በማንም የለም፤ እንድንበት ዘንድ የሚገባን ለሰዎች የተሰጠ ስም ከሰማይ በታች ሌላ የለምና።"
(የሐዋርያት ሥራ 4:12)
❤️ሰው ከኢየሱስ ቀር መዳኛ ምንም መንገድ የለውም።❤️
👉❤️ኢየሱስ ደሙን ያፈሰሰው ለጥንተ አብሶ ብቻ አይደለም።አሁን ለምንሰራውም ኃጢአት ጭምር ነው እንጂ።
👉(1ኛ የዮሐንስ መልእክት ምዕ. 2)
----------
1፤ ልጆቼ ሆይ፥ ኃጢአትን እንዳታደርጉ ይህን እጽፍላችኋለሁ። ማንም ኃጢአትን ቢያደርግ ከአብ ዘንድ ጠበቃ አለን እርሱም ጻድቅ የሆነ ኢየሱስ ክርስቶስ ነው።2፤ እርሱም የኃጢአታችን ማስተስሪያ ነው፥ ለኃጢአታችንም ብቻ አይደለም፥ ነገር ግን ለዓለሙ ሁሉ ኃጢአት እንጂ።
👉 ጌታን ጨካኝ ማርያምን ሩኅሩኅ ለማስመሰል ያልተፈጠረና ያልተፈበረከ ታሪክና ተረት የለም።ለምሳሌ፦ 78 ነፍስ የበላውን ሰው በእፍኝ ውኃ ምሕረት አሰጠጪው የሚለው ታሪክ ፌመስ ነው። ሌላም ታሪክ አለ፦ሥላሴን ክዶ በማርያም አማላጅነት ዳነ የሚባል።እንደውም ጌታ አልምርም ሲላት አንተን ጡቴን ያጠቡ ጡቶቼን እቆርጣቸዋለሁ ብላ የጌታን ልብ እንዳራራችው ተፅፏል።ይህ ሁሉ ተረትና ፈጠራ ትውልዱ የእግዚአብሔርን ፍቅር፥በልጁም የተደረገውን ቤዛነትና የመስቀሉን ሥራ እንዳያስተውል የተሰራ አዚም ነው።
📖" የማታስተውሉ የገላትያ ሰዎች ሆይ፥ በዓይናችሁ ፊት ኢየሱስ ክርስቶስ እንደ ተሰቀለ ሆኖ ተሥሎ ነበር፤ ለእውነት እንዳትታዘዙ አዚም ያደረገባችሁ ማን ነው?"
(ወደ ገላትያ ሰዎች 3:1) ተብሎ እንደተፃፈው ነው።
👉 #እግዚአብሔር_ከድንግል_ማርያም_በላይ_ይወደናል።የእግዚአብሔር አባትነትና ፍቅር ልዩ ነው ወገኖቼ።
👉ኢየሱስ የሞተው ለማን ነው?? እስከሞት ድረስስ የወደደን ማን ነው?? እመኑኝ እንደ እግዚአብሔር ያለ አዛኝ እንደ ኢየሱስ ያለ አፍቃሪ የትም አታገኙም።ተረትን አትከተሉ።ኢየሱስ ይወዳችኋል።
📖" ከቅዱሳን ሁሉ ጋር ስፋቱና ርዝመቱ ከፍታውም ጥልቅነቱም ምን ያህል መሆኑን ለማስተዋል፥ ከመታወቅም የሚያልፈውን የክርስቶስን ፍቅር ለማወቅ ትበረቱ ዘንድ፥ እስከ እግዚአብሔርም ፍጹም ሙላት ደርሳችሁ ትሞሉ ዘንድ።"
(ወደ ኤፌሶን ሰዎች 3:18-19)
📖 ነፍሱን ስለ ወዳጆቹ ከመስጠት ይልቅ ከዚህ የሚበልጥ ፍቅር ለማንም የለውም።[ዮሐንስ 15:13]
📖(መዝሙረ ዳዊት ምዕ. 103)
----------
8፤ እግዚአብሔር መሓሪና ይቅር ባይ ነው፥ ከቍጣ የራቀ ምሕረቱም የበዛ። . . .
10፤ እንደ ኃጢአታችን አላደረገብንም፥ እንደ በደላችንም አልከፈለንም።. . .
13፤ አባት ለልጆቹ እንደሚራራ እንዲሁ እግዚአብሔር ለሚፈሩት ይራራል፤
👉ወገኖቼ የእግዚአብሔር ፍቅር አስተማማኝ ነው።ኃጢአተኛ መሆናችንን ማመናችን ጥሩ ነገር ነው፤በሥራችንም ወደ እግዚአብሔር መድረስ እንደማንችል መረዳትም ጥበብ ነው።መዳኛና ወደ አብ መቅረቢያዋ ግን ድንግል ማርያም አይደለችም።ኢየሱስ አምላካችን ነው እርሱ እውነተኛ ነው አይዋሽም ያለውን ስሙት፦
📖(የዮሐንስ ወንጌል ምዕ. 10)
----------
7፤ ኢየሱስም ደግሞ አላቸው። እውነት እውነት እላችኋለሁ፥ እኔ የበጎች በር ነኝ።. .
9፤ በሩ እኔ ነኝ፤ በእኔ የሚገባ ቢኖር ይድናል፥ ይገባልም ይወጣልም መሰማሪያም ያገኛል።
📖" ኢየሱስም። እኔ መንገድና እውነት ሕይወትም ነኝ፤ በእኔ በቀር ወደ አብ የሚመጣ የለም።"
(የዮሐንስ ወንጌል 14:6)
✝ ቅዱስ ጳውሎስ ያለውን ደግሞ ስሙ፦
📖(ወደ ሮሜ ሰዎች ምዕ. 10)
----------
9፤ ኢየሱስ ጌታ እንደ ሆነ በአፍህ ብትመሰክር እግዚአብሔርም ከሙታን እንዳስነሣው በልብህ ብታምን ትድናለህና፤
10፤ ሰው በልቡ አምኖ ይጸድቃልና በአፉም መስክሮ ይድናልና።
11፤ መጽሐፍ። በእርሱ የሚያምን ሁሉ አያፍርም ይላልና።
12፤ በአይሁዳዊና በግሪክ ሰው መካከል ልዩነት የለምና፤ አንዱ ጌታ የሁሉ ጌታ ነውና፥ ለሚጠሩትም ሁሉ ባለ ጠጋ ነው፤
13፤ የጌታን ስም የሚጠራ ሁሉ ይድናልና።
❤️ስለዚህ ወገኖቼ በኢየሱስ አምናችሁ በስሙ የዘላለምን ሕይወት እንድታገኙ በኢየሱስ ብቻ እመኑ።ያመናችሁ ደግሞ ፅኑ። #መንግስተ_ሰማያት_የምትወረሰው #በኢየሱስ_በማመን_ብቻ_ነው።በእናቱ በኩል ለመግባት የሚፈልግ ሌባና ሙሰኛ ነው።ድንግል ማርያም ያመነችውን እመኑ።ያከበረችውን አክብሩ።#ሌላው_ቢቀር_ድንግል_ማርያም_ያለችውን_ስሙ።
📖" እናቱም ለአገልጋዮቹ። የሚላችሁን ሁሉ አድርጉ አለቻቸው።"
(የዮሐንስ ወንጌል 2:5)
📖(የሉቃስ ወንጌል ምዕ. 1)
----------
46፤ ማርያምም እንዲህ አለች።
47፤ ነፍሴ ጌታን ታከብረዋለች፥ መንፈሴም በአምላኬ በመድኃኒቴ ሐሴት ታደርጋለች፤
ተባረኩልኝ።በመጨረሻም፦
📖(ወደ ኤፌሶን ሰዎች ምዕ. 1)
-----
17፤ የክብር አባት የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ አምላክ እርሱን በማወቅ የጥበብንና የመገለጥን መንፈስ እንዲሰጣችሁ እለምናለሁ።
#ድንግል_ማርያም
#መልስ_የሚሻ_ጥያቄ
👉በመፅሐፍ ቅዱስ ከተጠቀሱት ቅዱሳት ሴቶች አንዷ ብትሆን ከሌሎች ቅዱሳት አንስት እርሷን የሚለያት ዋነኛው ነገር የጌታችን የኢየሱስ እናት መሆኗ ነው።ይህም ክብር ልዩና ብቸኛ ነው።
👉 ድንግል ማርያም በክርስቲያኖች ዘንድ ልዩ ቦታ አላት።እርሷን ከመውደዳቸው የተነሳ በምን ላስከብራት ብለው በመጨነቅ ውለው የሚያድሩ ብዙ ሰዎችን ዓለማችን አስተናግዳለች።ታዲያ እነዚህ የድንግል ማርያምን ክብር ከፍ ለማድረግ የሚፈልጉ ሰዎች ብዙ ድርሰት ደርሰዋል።ብዙ ትምህርት አስተምረዋል።በጣም አሳዛኙ ጉዳይ ግን ፈጠራቸው የትውልዱን ልብ ያደነዘዘ፥ምክንያታዊነትን የተሞላ፥ላለማመን የሚያስቸግር፥የሰዎችን ዓይን ከተባረከው ተስፋችን ከክርስቶስ ኢየሱስ እንዲያነሱ የማድረግ አቅም ነበረው።
👉 አንድ አባባል ትዝ ይለኛል፦<<አንድ ሞኝ የተከለውን፤ ብዙ ብልሆች አይነቅሉትም።>> በቅድስቲቱ ድንግል ማርያም ስም የተሰራውን ስህተት ብዙ አስተዋዮች መንቀል አልቻሉም።ዘርዐያዕቆብ የዘራውን እስጢፋኖስ መንቀል አልቻለም ታገለ እንጂ።ግን ጊዜው ይርዘም እንጂ ሙሉ ለሙሉ ከነሥሩ መነቀሉ አይቀሬ ነው።ዘመኑ የወንጌል ነውና።ትውልዱን የሚያነቃ የመንፈሱ ኃይል እየሰራ ነው።
👉 ድንግል ማርያምን ከመውደዳቸውና ከፍቅራቸው የተነሳ <<ሰው መሆኗን እንኳን>> መቀበል ይከብዳቸዋል።አንድ መነኩሴ <<ምድራዊ ምግብ ተመግባ አታውቅም>> እንዳሉኝ አስታውሳለሁ።እኛ የበላነው ከበላችማ ምኑን የአምላክ እናት ሆነችው ብለው ቁርጤን ነግረውኛል።በጊዜው አምኛቸው ነበር።በልቤም፦ <<ድንግል እኮ ከመፍጠር ውጭ በቃ ከአምላክ በምንም አታንስም>> አልኩ።እንዴት የዋህ ሰው ነበርኩ።ግን እውነታው ድንግል ማርያም እንደ እኛ ሰው መሆኗን አለማስተዋል ነበር።
👉 ድንግል ማርያም ከፈጣሪ እኩል ወይም በላይ መደረጓን ከሚያሳዩ ነገሮች የተወሰኑትን ላስታውሳችሁ፦
❓#የምስጋናዋና_የውዳሴዋ_ከኢየሱስ_መብለጥ፦
👉 ታስታውሱ እንደሆን <<ውዳሴ ማርያም>> የሚባል ፀሎት ጠዋት ማታ እንፀልይ ነበር።ዲያቆን ለመሆንም የግድ በቃል መያዝ ካለባቸው ፀሎቶች ውስጥ 4 የተለያዩ ድርሰቶች(የድንግል ማርያም) እና 1 ስለ ኢየሱስ የተደረሰን ድርሰት ይጠቀሳሉ።4ቱ ድርሰቶች፦ውዳሴ ማርያም፥ይዌድስዋ መላእክት(መላእክት ያወድሷታል)፥አንቀፀ ብርሃን(ለማርያም የቀረበ ውዳሴ) እና መልክአ ማርያም ናቸው።አንዱ የጌታ ደግሞ መልክአ ኢየሱስ የሚባለው ነው።በምስጋናዋ ጌታን በልጣ ነው ምናገኛት።በበዐላቶቿ ልክ ማህሌቱና መልካ መልኩ ብዙ ነው።ምዕመኑም መልካም ቢሆንለት የሚያመሰግነው ማርያምን፤ ክፉ ቢገጥመው የሚማፀነው ማርያምን ነው።ግን የሥጋ ለባሹን ሁሉ ፀሎት የሚሰማውና የሚመልሰው እግዚአብሔር ብቻ ነው።አምልኮና ስግደት የሚገባውም እርሱ ብቻ ነው።ፈጥሮ የሚገዛ፥ስለሰው ሁሉ ዋጋ የከፈለ ኢየሱስ ብቻ ነውና።
📖" ሀያ አራቱ ሽማግሌዎች በዙፋን ላይ በተቀመጠው ፊት ወድቀው፥ ከዘላለም እስከ ዘላለም በሕይወት ለሚኖረው እየሰገዱ። ጌታችንና አምላካችን ሆይ፥ አንተ ሁሉን ፈጥረሃልና ስለ ፈቃድህም ሆነዋልና ተፈጥረውማልና ክብር ውዳሴ ኃይልም ልትቀበል ይገባሃል እያሉ በዙፋኑ ፊት አክሊላቸውን ያኖራሉ።
"
(የዮሐንስ ራእይ 4:10-11)
📖(መዝሙረ ዳዊት ምዕ. 65)
----------
1፤ አቤቱ፥ በጽዮን ለአንተ ምስጋና ይገባል፥ ለአንተም ጸሎት ይቀርባል።
2፤ ሥጋ ሁሉ ጸሎትን ወደምትሰማ ወደ አንተ ይመጣል።
👉 ዘማሪዎችን ብትመለከቱ <<መናፍቅ>> ላለመባልና የሕዝቡን ልብ ለማግኘት <<ማርያም ማርያም>>ማለት ግድ ካላቸው ቆይቷል።የተወሰኑትን እንኳን ብናይ እንግዳ ወርቅ በቀለ ከሚዘምራቸው 12 መዝሙሮች ቢያንስ 8ቱ የማርያም እንደሆነ ይታወቃል።ለብቻዋ መመሰገን አለባት ብሎም ስላመነ የሷን ብቻ መዝሙር <<ውዳሴ ማርያም>>ብሎ አውጥቶታል።ለኢየሱስ ግን መዘመር ነውር ሆኖበታል።እንደውም፦<<" ስለዚህም ምክንያት ይህን መከራ ደግሞ ተቀብዬአለሁ፥ ነገር ግን አላፍርበትም፤ ያመንሁትን አውቃለሁና፥ የሰጠሁትንም አደራ እስከዚያ ቀን ድረስ ሊጠብቅ እንዲችል ተረድቼአለሁ።"
(2ኛ ወደ ጢሞቴዎስ 1:12) የሚለውን ቃል <<በእስራቴ አላፍርም፥እኔ የማርያም ነኝ፤ሮማዊ አይደለሁ ፍፁም ክርስቲያን ነኝ።>> ብሎ የቀየረ ደፋር ነጋዴ ሲሆን፤ " ከክርስቶስ ፍቅር ማን ይለየናል? መከራ፥ ወይስ ጭንቀት፥ ወይስ ስደት፥ ወይስ ራብ፥ ወይስ ራቁትነት፥ ወይስ ፍርሃት፥ ወይስ ሰይፍ ነውን?"
(ወደ ሮሜ ሰዎች 8:35) የሚለውን ደግሞ <<ከእመቤቴ ፍቅር የሚለየኝ ማነው፤መከራ ነው ችግር ወይስ እስራት ነው>> ብሎታል።ታዲያ ይሄ ሰው ዘማሪ ነው አዝማሪ??
🎤ምስጋናና አምልኮ ለታረደው በግ ብቻ ይገባል።
" የታረደው በግ ኃይልና ባለ ጠግነት ጥበብም ብርታትም ክብርም ምስጋናም በረከትም ሊቀበል ይገባዋል።"
(የዮሐንስ ራእይ 5:12)
ይቀጥላል.....
#እውን_በኦርቶዶክስ_ቤተክርስቲያን_ቅዱሳን_አይመለኩምን?
#መልስ_የሚሻ_ጥያቄ
👉በኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን አማኝና አገልጋይ እንደነበረ ሰው "እግዚአብሔርን እንጂ ቅዱሳንን አናመልክም" የሚል መልስን እጠብቃለሁ።እውነታው ግን እርሱ አይደለም።በኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን ቅዱሳን መላእክት፥ድንግል ማርያም፥ፃድቃን፥ሰማእታት፥መነኮሳትና ሊቃውንት ሁሉም ይመለካሉ።ይሄንን ስላችሁ ከመሬት ተነስቼ ሳይሆን ማስረጃ ይዤ ነው።
👉⚠️እግዚአብሔር ማምለካችሁን ምትገልፁት በምንድን ነው? እንደቃሉ በእነዚህ ነገሮች በመግለፅ አይደለምን?
#1 ሙሉ በሙሉ በእርሱ በመታመን…ኤር.17:7
#2 በስሙ በመታመን፥ስሙን በማመስገንና በስሙ በመማል…ዘዳ.6:13፤ማቴ.12:21፤ማቴ.6:10
#3 ለጌትነቱ መገዛታችሁን ለመግለፅ ለእርሱ በመስገድ……መዝ.95:6፤ፊልጵ.2:10
#4 ወደ እርሱ በመፀለይ……መዝ.65:1-2
#5 ትእዛዙን በመጠበቅ……ዘዳግ.8:6፤መዝ.119:4
#6 ለእርሱ በመዘመር……መዝ.47:7
#7 ሥጦታ፥ስእለት፥አሥራትና መባ ለስሙ በማምጣት………መዝ.42:8፤ዘሌዋ.27:30፤ዘፀአ.35:5
#8 በሕይወታችን፥በሥራችን፥በቤተሰቦቻችን፥በሀገራችን በማንኛውም ነገርና የእኛ በሆነው ነገር ሁሉ ብቸኛ ባለ ሥልጣን እግዚአብሔር እንደሆነ መታመን አምልኮ ነው።ማቴ.28:18፤ዳን.4:26፤መዝ.127:1
#9 እርሱን መፍራትና መገዛት፥መውደድና ማክበር……ሉቃ.10:27፤ራእይ.14:7
👉ከላይ የተዘረዘሩት ነገሮች "የምናመልከውን አምላክ የምናመልክበት የአምልኮ መገለጫዎች" ናቸው።
⚠️በመገለጫዎቹ መሠረት ቅዱሳን መላእክት፥ድንግል ማርያም፥ፃድቃን፥ሰማእታት፥መነኮሳት፥ሊቃውንት፥እለታት፥ስእላት፥ታቦታት አይመለኩምን?
ለምሳሌ ከላይ በዘረዘርናቸው የአምልኮ መገለጫዎች መሠረት ድንግል ማርያምን እያመለካችሁ ነው ወይስ እያከበራችሁ?
1⃣ በድንግል ማርያም አትታመኑም?
2⃣በስሟ አትታመኑም? በስሟ አትምሉም? በስሟስ አትምሉም?
3⃣ለድንግል ማርያም በመገዛት አትሰግዱምን?
4⃣ ወደ ድንግል ማርያም አትፀልዩም?
5⃣ "ያዘዘችውን" ለመጠበቅ አትጥሩምን? (ብዙ ባህታውያን በእርስዋ እንደታዘዙ ይናገራሉ…ብዙ ደራሲዎች ታዘው እንደፃፉላት ተናግረዋል)
6⃣ ለድንግል ማርያም አትዘምሩምን?
7⃣ ስእለትን ለድንግል ማርያም አትሳሉምን? መባ ሥጦታና አሥራታችሁን ለድንግል ማርያም አትሰጡምን?
8⃣ በሁሉም ነገራችሁ ላይ ባለሥልጣን እንደሆነች አታምኑምን?
9⃣ አትፈሯትም? ከጌታ እኩል ወይም በላይ አትወዷትምን? ባላመኑ ሰዎች ጌታ ሲነቀፍ ወይስ ድንግል ስትነቀፍ ነው የበለጠ ምትበሳጩት?
⚠️ድንግል ማርያምን ማክበር ነው ወይስ ማምለክ? አታመልኳትም እንበልና………#ብታመልኳት_ግን_ከዚህ_የተለየ_ምን_ነበር_ምታደርጉት?⚠️
🛑መልስ ያላችሁ ወንድሞችና እህቶች ምትሉትን ለመስማት ዝግጁ ነኝ።
👉ክፍል ሁለት ነገ ይቀጥላል……
“…#ለጌታህ_ለአምላክህ_ስገድ_እርሱንም_ብቻ_አምልክ…”
— ማቴዎስ 4፥10
👉ሼር በማድረግ አብረውኝ ያገልግሉ።
#ተሐድሶን_መረዳት
🗣በአገልጋይ ብርሃኑ
(30/01/2014 የምሕረት ዓመት)
👉ጥቂት ወንድሞች ከሰሞኑ "ተሐድሶን ለቅቄያለሁ…ተሐድሶ አይደለሁም……ተሐድሶ ነበርኩ" የሚል ቃል ሲጠቀሙ እየሰማን ነው።ምን እያሉ ነው? ሕዝቡ እንደ ሃይማኖት ስለሚረዳው በሚረዳው መንገድ መግለፃቸው ነው ወይንስ እንደ ሃይማኖትና እንደ አንድ ድርጅት ቆጥረውት ነው?
👉ይሄ ሁሉ ችግር ግን ተሐድሶን እንደተቋምና እንደ የሃይማኖት ድርጅት መቀበል ያመጣው ጦስ ነው።ተቋማዊ አስተሳሰብ እንጂ የእግዚአብሔር መንግስት እሳቤ በሌለህ ቁጥር የምትለው ይሄንኑ ነው።
👉ማንም ውጡ ሳይላቸው የወጡ ሰዎች ተታለው እንደወጡ ማውራታቸው፤የተሐድሶን አገልግሎት የለቀቁበት አሳማኝ ያልሆነው ምክንያታቸው፤ከተሐድሶ እንቅስቃሴ የለቀቁበትን የስህተት ትምህርት ወይ ሌላ መፅሐፍ ቅዱሳዊ ያልሆኑ ነገሮች አለመጥቀሳቸው #ለግላቸው_ምቾትና_ጥቅም_ካልሆነ #በቀር #ለኦርቶዶክስ_ያላቸውን_ፍቅርም #ሆነ #ጉዳዩ_ወንጌል_መሆኑን_በፍፁም_አያሳይም።የሆነ ሆኖ ወደ መጀመሪያው ሀሳቤ ልምጣና ተሐድሶን በጥቂቱ ለማስረዳት ልሞክር፦
#ተሐድሶ እንቅስቃሴ እንጂ #ተቋም ወይም #ሃይማኖት_አይደለም።ይሄ የታወቀና የማይሸሸግ ነገር ነው።
ምን አይነት እንቅስቃሴ ነው ያልን እንደሆነ፦
👉 #ክርስትናን_ወደ_ሐዋርያዊና_መፅሐፍ_ቅዱሳዊ #መሠረቱ #መመለስ ነው።የዚህም እንቅስቃሴ መነሳት ምክንያት #የቤተክርስቲያን_መሪዎችና_ነገስታት_ሥልጣናቸውን #በመጠቀም_የጨማመሯቸው #ለመፅሐፍ_ቅዱስ_ባእድ_የሆኑ_ድርሰቶች፥#ትምህርቶችና_ልምምዶች_ናቸው።
👉 #በዚህም #የተሐድሶ_እንቅስቃሴ #የማይካተት #የእምነት #ተቋም #አይኖርም።ተሐድሶ አድራሻ የሚያደርገው "ኦርቶዶክስን ብቻ" ለብዙዎች የመሰላቸው አብዛኞቹ የተሐድሶ እንቅስቃሴ አራማጅ ወንድሞች ከኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን የወጡ ስለሆነ ነው።ግን የተሐድሶው እንቅስቃሴ የማይነካካው የእምነት ድርጅት የለም። #የተሐድሶ_እንቅስቃሴ_ግብ #ቤተክርስቲያንና_ክርስትናን #ወደ #ሐዋርያዊ_መሠረቱ_መመለስ_ነውና። #ከሐዋርያዊ_መሠረቱ #ያፈገፈገና_መሠረት #የለቀቀ_ሁሉ #ተሐድሶ_ያስፈልገዋል።
#የተሐድሶ_እንቅስቃሴ_ዋና_መሠረቱ፦
👉ቤተክርስቲያንና መሠረታዊ የእምነት አቋሞቿ ቃሉ ላይ የተመሠረተ ይሁን።መፅሐፍ ቅዱስ ብቸኛ ባለሥልጣን ነው የሚል ነው።2ጢሞ.3:14-17፤1ጴጥ.4:11
👉አምልኮን ለእግዚአብሔር ብቻ እንስጥ።ቅዱሳን ያመለኩትን እናምልክ እንጂ እነርሱን አናምልክ።ለሰገዱለት እንስገድ፤ለዘመሩለት እንዘምር የሚል ነው።መፀለይም ያለብን የሥጋ ለባሹን ሁሉ ፀሎት ወደ ሚሰማና በሁሉ ቦታ ወደ ሚገኝ ወደ እግዚአብሔር ብቻ ይሁን የሚል ነው።ዘፀ.20:1፤ኢሳ.48:11፤መዝ.65:2፤ራእ.4:8-11
👉ደኅንነትንም በተመለከተ እግዚአብሔር ሰዎች ሁሉ እንዲድኑበት መድኃኒት አድርጎ የሰጠን ልጁን ኢየሱስ ክርስቶስ ብቻ ነው።መዳን በሌላ በማንም የለም።ይሄም ትምህርት ሐዋርያዊ በመሆኑ ወደዚህ መሠረት እንመለስ የሚል ነው።የሐዋ.4:12
👉ሰው የሚድነው በጥረቱና በሥራው ሳይሆን በእግዚአብሔር ፀጋ ብቻ በእምነት አማካኝነት ነው።ይሄም እውነት ከሐዋርያዊነት በፊት የነበረ እነ አብርሃም ከግርዛትም ከሕግም መሠጠት በፊት የነበረ ወንጌል ነው የሚልና ከክርስቶስ የመስቀል ሥራ በቀር ሌላ የምንድንበትን መንገድ መፈለግ እግዚአብሔር ስለ ልጁ የመሠከረውን ምሥክርነት መናቅ ነው የሚል ነው።ሮሜ.3:20-26፤ገላ.2:16:21፤ኤፌ.2:8
👉ተሐድሶ በሥላሴ አንድነትና ሦስትነት፤በክርስቶስ ሰውነትና አምላክነት፤በክርስቶስ ተመልሶ መምጣት፤በሙታን ትንሣኤ በዘላለምም ፍርድ ላይ ያለውን እምነት ይዞ ለቃሉ ባእድ የሆኑትን እምነትና አመለካከት ብቻ ይቃወማል።
👉 #የተሐድሶ_እንቅስቃሴ_ግብ #ይሄ #እንጂ #አፍላሽና_አፍሳሽነት #አይደለም።በዚህ እንቅስቃሴ ውስጥ ያሉ አንዳንድ ግለሰቦችና ጥቂት ኅብረቶች መላውን የተሐድሶን እንቅስቃሴ አይወክሉም።
#እውነተኛና ልበ ቀና #ክርስቲያኖች #የራሳቸውን #መዳን #ሊጠራጠሩ ይችሉ ይሆናል፤ ነገር ግን #ብቸኛ #መድኃኒታቸውና #ተስፋቸው #ኢየሱስ #መሆኑን #በፍፁም #አይጠራጠሩም!!!
የዕለት ስንቅ
ክርስቶስ በእኛ ውስጥ
" ስለዚህ ምክንያት በሰማይና በምድር ያለ አባትነት ሁሉ ከሚሰየምበት ከአብ ፊት እንበረከካለሁ፤ በመንፈሱ በውስጥ ሰውነታችሁ በኃይል እንድትጠነክሩ ክርስቶስም በልባችሁ በእምነት እንዲኖር እንደ ክብሩ ባለ ጠግነት መጠን ይስጣችሁ፤ ....( ኤፌ 3: ¹⁴ -¹⁹)
ይህ በኤፌሶን መልእክት ላይ 2ኛው የሐዋርያው የዻውሎስ ጸሎት ተብሎ የሚታወቅ ነው ።አሁን የጠቀስሁት የጸሎቱ ሙሉ ክፍልም ባይሆን።
በሰማይና በምድር አባትነት ሁሉ የሚሰየምበት አባትነት የእግዚአብሔር አባትነት ነው .።
በእግዚአብሔር አባትነት ፊት መንበርከክ :- በልጅነት ሥልጣን መጠየቅን ያሳያል።
እግዚአብሔር አባታችን የሆነውን ያህል እኛም ልጆቹ ነን ( 1ኛ ዮሐ 3:¹ ) "እንደተወደዱ ልጆች" እግዚአብሔርን ከተከተልን ( ኤፌ 4:¹ ) ፣በዚሁ መጠን ከልብ በሆነ መንበርከክ የጠየቅነውን እንደሚሰጠንም ማመን ይሆንልናል ።
" በመንፈሱ በውስጥ ሰውነታችሁ በኃይል እንድትጠነክሩ " (ቁ .¹⁶ ) ።
ሐዋርያው ዻውሎስ በጸሎቱ የጠየቀው በመንፈሱ በውስጥ ሰውነታቸው በኃይል እንዲጠነክሩ ነው።
"የውስጥ ሰውነት" :- የተባለው ከውኃና ከመንፈስ የተወለደው አዲሱ ሰው ነው ።ለውስጠኛው ሰው የጥንካሬው ምንጭ ደግሞ መንፈስ ቅዱስ ነው።
የውስጥ ሰውነት ኃይል ካልተቀበለ የእግዚአብሔርን ሕይወት መግለጥ አይችልም።
ይህ ኃይልስ ከምን ይመጣል? ከላይ ቃሉ እንደሚመልስልን : - " ከክብሩ ባለጠግነት " ነው ።:- " እንደ ክብሩ ባለጠግነት መጠን ይስጣችሁ!" ይላልና ፣ የኃይሉ ዓላማስ ምንድነው? :-
የኃይሉ ዓላማም ከላይ እንደተገለጠው: - "ክርስቶስ በልባችን በእምነት እንዲኖር! "ነው ።
የእንግሊዘኛው ትርጉም " ቤተኛነት ተሰምቶት" እንዲኖር የሚል አሳብ አለው።
ተወዳጆች ሆይ :- ክርስቶስ ቤተኛነት እስኪሰማው ራሳችን የያዝነውን ልባችንን ካልለቀቅንለት በእምነት በእኛ በፍጹም አይኖርም።
ስናምን ከክብሩ ባለጠግነት ውስጥ ያለውን በጎ ስጦታ ሁሉ እንቀበላለን ።ኃይሉም:- የክብሩ ባለጠግነት ስጦታ ነው ፣ ትልቅ ስጦታ !!! በዚህ ኃይል ክርስቶስ በልባችን በእምነት ይኖራል ። ክብር ለስሙ ይሁን!
አገልጋይ ቃለአብ ካሳዬ
