የአገልጋይ ብርሃኑ ገፅ
Open in Telegram
ይህ የአገልጋይ ብርሃኑ ገፅ ነው።ዓላማዬ የተለያዩ መፅሐፍ ቅዱሳዊ ትምህርቶችን ማካፈልና ማድረስ ሲሆን ምክሮችን፥አባባሎችን፥ፀሎቶችንና ትዝብቶቼን የማካፍልም ይሆናል።የሰራዊት ጌታ እግዚአብሔር ወደ ልቤ ያመጣውንና የተናገረኝንም እፅፋለሁ።ትውልዱን ወደ ኢየሱስ የሚያስጠጋውን የትኛውንም ነገር የምፅፍበት ገፄ ነው።በማንበብና ሼር በማድረግ ከአገልግሎቴ ጎን ይቁሙ።0984005562.
Show more447
Subscribers
+224 hours
+87 days
+3030 days
Posts Archive
በመፅሐፍ ቅዱስ አንድም ነቢይ፤አንድም ሐዋርያ፤አንድም አባት ወደ መልአክ የፀለየ፤በመልአክ ስም የተማፀነ የለም።አንድስ እንኳ።ምክንያቱም እግዚአብሔርን የሚያስቆጣ ስህተት ነውና።
ቅዱስ ገብርኤል የሚናገራችሁን ስሙ፦
“ልጅም ትወልዳለች፤ #እርሱ_ሕዝቡን_ከኃጢአታቸው_ያድናቸዋልና_ስሙን_ኢየሱስ_ትለዋለህ።”
— ማቴዎስ 1፥21
የኃጢአት ሥርየት የምታገኙትና የምትድኑት በኢየሱስ ብቻ ነው ብሎአችኋል።
#የሰሎሞን_አቡቦከር_ትንቢት_ስለተሐድሶ
🗣በአገልጋይ ብርሃኑ
👉በቅርቡ ወደ ኦርቶዶክስ ተመልሻለሁ ባዩ ሰሎሞን አቡቦከር ትንቢት መናገር ጀምሯል።እርሱ እንደሚናገረው ከሆነ አሁን ምልክቱ እየታየበት ያለው ተሐድሶ ከሁለት ሲከፈል ታይቶታል።
👉ሰሎሞን አቡቦከር የዲዮስቆሮስን ታሪክ አስታወሰኝ።ዲዮስቆሮስ የሚባል አንድ የግብፅ ጳጳስ ድንግል ማርያምን በጣም ይወዳት ነበር።እናም "ምን ባደርግና ምን ብፅፍላት ማርያምን ማስከበር እችላለሁ" ብሎ አሰበ።አስቦም አልቀረ "ተአምረ ማርያምን" ፃፈ።እንዲሁ ሰሎሞንም ቁጭ ብሎ፦ "ኦርቶዶክሳውያንን ለማስደሰትና እንዲቀበሉኝ ለማድረግ ምን ብፅፍ ምን ብዘምር ይሻላል?" ብሎ የሚያስብ ሰው የሆነ ይመስለኛል።አስቦም አልቀረ ሟርት አይሉት ትንቢት "ተሐድሶ ከሁለት ይከፈላል በቅርቡ" አለን።ምንና ምን ሲሉት? ኦርቶዶክስ ጠልና ኦርቶዶክስን አፍቃሪ፤ ኦርቶዶክስን እንደቤተክርስቲያን ሚቀበሉና ማይቀበሉ።
ወደው አይስቁ ነው ነገሩ…😂
👉በመሠረቱ ተሐድሶአውያን ኦርቶዶክስን ቢወዱም ቢጠሉም፤ቤተክርስቲያን ናትም አይደለችምም ቢሉም ፦ በአንድ ድምፅ፦ "ለኦርቶዶክስ ወንጌልን መስበክ አለብን" ብለው ግን ያምናሉ።ስሜታቸው እንጂ ግባቸው አንድ ነው።
👉ተሐድሶአውያን ስለ ኦርቶዶክስ ምንም ዓይነት ስሜት ቢኖራቸውም መልእክታቸው ግን አንድ ነው።ሰሎሞን ኦርቶዶክስን ወዶም ለወንጌል ግድ ብሎትም ወደ ኦርቶዶክስ አልተመለሰም።ጴንጤ ላለመሆን ወደ ኦርቶዶክስ በመመለስና ኦርቶዶክስ ልክ ናት ተሳስቻለሁ ብሎ በመመለስ መካከል ልዩነት አለ።
🤷እናም የሰሎሞን ትንቢትም ሆነ ሟርት ከአቴንሽን ፍለጋ በቀር……
ሌላ ትርፍ
ወፍ!!!
🗓16/04/2014 የምሕረት ዓመት
#የምርትነሽ_መዝሙር_ሰበብ_ነው!!
🗣በአገልጋይ ብርሃኑ
👉ሰይጣን ሀሰተኛና የሀሰት አባት ነው።መዋሸት ባህርዩ ነው።እናም ስለተሐድሶ አገልግሎት ኦርቶዶክሳውያንን ብቻ ሳይሆን ጥቂት የማይባሉ ተሐድሶአውያንን ሁሉ ሳይቀር እየዋሻቸው ነው።
👉የተሐድሶ አገልግሎት ዐይን ከፋች አገልግሎት ነው።አፍሳሽና አፍላሽ አይደለም።የተሐድሶ ጥሪ "ወደ ቀደመው የእግዚአብሔር ሀሳብ" ሰዎች ሁሉ እንዲመለሱ ነው።እኔም የዚህ ጥሪ ተቀባይና አገልጋይ በመሆኔ ደስተኛ ነኝ።
👉የሰሞኑን የዘማሪት ምርትነሽ ጥላሁንን መዝሙር መነሻ በማድረግ ብዙ እየተባለ ቢሆንም ከእውነቱ ውሸቱ ይበልጣል።ምርትነሽ ሰበብ ሆነች እንጂ ዋና ጉዳዩ በሦስት ጎራዎች መካከል ያለ ክርክር ነው።
👉አንደኛው ወገን፦ ተመለስን ባዮች(እነ ክብራቸው በነውራቸው)
👉ሁለተኛው ወገን፦ ለመመለስ የከጀሉና ቋፍ ላይ ያሉ(አፍቃሬ ኦርቶዶክስ መሳይ አቋም የለሾች)
👉ሦስተኛው ወገን፦ አንመለስም ባዮች(ለእውነት ያደሉ ተሐድሶአውያን) ናቸው።
አራተኞቹን ትቻቸዋለሁ።
👉ለሰሚ ለተመልካች የምለው ነገር ቢኖር በተሐድሶና በአገልግሎቱ ላይ ምንም አዲስ የሚያወዛግብ ነገር እንዳልተነሳ ነው።
👉በምርትነሽ ዝማሬ ላይ መወያየቱ ግን አስፈላጊ ነው ብዬ አላምንም።ምክንያቱም ኦርቶዶክስ ናት።ኦርቶዶክሳውያን ደግሞ ለፍጡር ይዘምራሉ፥ለፍጡር ይገዛሉ፥ለስእልም(ለእጅ ሥራቸው) ይሰግዳሉ።እርስዋም ያንኑ ታደርጋለች።ግን ተስፋ አደርጋለሁ፤አንድ ቀን እውነትን ትረዳለች።
👉"በሰበቡ መምሬ ተሳቡ" እንደሚባለው አቧራ አስነስተንና ትኩረት ስበን ካልተመለስን ባይና አስመሳዮች ግን ከሁለቱም ሳትሆኑ ከምትቀሩ ሂዱና የተፋችሁትን ላሱ።
መርጠን እንሰማለን፥ለእርስዋም እንፀልያለን የምትሉም በርቱ።🙏
🗓15/04/2014 የምሕረት ዓመት
❤️የእለቱ መልእክት❤️
#ኢየሱስ_በቂ_አይደለምን?
🗣በአገልጋይ ብርሃኑ ታምራት
👉ከበላኸው ደግመህ አትራብም፤ከጠጣኸው ደግመህ አትጠማም።ዮሐ.6:35
👉ብትሞት ትንሣኤህ ነው፤ብትኖር ሕይወትህ እርሱ ነው።ዮሐ.11:25-26
👉በጨለማ እንዳትመላለስ ብርሃንህ ነው።ዮሐ.8:12
👉ፀልዮ ለመሰማት በስሙ መለመን አስተማማኝ ነው።ዮሐ.14:14፤16:23
👉ኃጢአትን ብታደርግ የሚያጥብ ደም አለው።1ዮሐ.1:7፤2:1-2
👉ወደ መንግስቱ በምን ልግባ እንዳትል በሩ እርሱ ነው።ዮሐ.10:9
👉ተኩላ እንዳይበላህ እረኛህ ነው።ዮሐ.10:14-15
👉ወደ አብ ለመድረስ ብትፈልግ መንገድ ይሆንልሃል።ዮሐ.14:6
👉አጋንንትን እንዳትፈራ በስሙ እንድትገዛቸው ሥልጣን ሰጥቶሃል።ሉቃ.10:17-19
👉መፃሕፍትን ብታገላብጥ የሚያወራው ስለ እርሱ ነው።ዮሐ.5:39
👉ሥራህን የሰራልህ፤በአብ ፊት በብቃት የወከለህ ኢየሱስ ነው።ኤፌ.2:18
📖“እናንተም የገዥነትና የሥልጣን ሁሉ ራስ በሆነው #በክርስቶስ_ሙሉ_ሆናችኋል።”📖
— ቆላስይስ 2፥10
👉ታዲያ ኢየሱስ አይበቃህምን?
#ኢየሱስ_በቂ_ከበቂም_በላይ_ነው።።።🙏
🗓10/04/2014 የምሕረት ዓመት
ሰላም ለአቃቤ አሚን ግሩፕ አባላት
እንዴት ናችሁ?
ከምሽቱ 3:30 ከኔ ጋር በጌታ ቃል ዙሪያ ብንወያይ ምን ይመስላችኋል?
ምትገኙ ሰዎች…እጅ አሳዩኝ
❤️የእለቱ መልእክት❤️
#ተስፋ_አለ
🗣በአገልጋይ ብርሃኑ ታምራት
👉የሰው ሕይወት ብርቱ ሰልፍ ነው።አንድ አይነት እንዳልሆንን ሁሉ ሁላችንም አንድ አይነት ሰልፍ አይኖርብንም።ፈተናችን በአቅማችን ልክ ነው።በአቅማችን ልክ የሚባለው ግን በእግዚአብሔር ሚዛን ነው።አቅማችንን እርሱ እንጂ እኛ አናውቀውምና።
👉ስንደክም ምንጠፋ፤ስንወድቅ የሚያልቅልን ቢመስለንም እግዚአብሔር ጋ ግን ሁሌም ተስፋ አለ።
👉መውደቅና መሳት የመጨረሻው አይደለም።መነሳትና መመለስ የሚባል ተስፋ አለው።ማጣት፥መጎሳቆል፥ስደትና ሕመም ውስጥ ነው ተአምራትና ምሥክርነት ያለው።
👉ምንም አይነት ችግር መጨረሻችን አይደለም። በድካማችን ኃይሉ፤በውድቀታችን ምሕረቱ፤በስህተታችን ትእግስቱ ይዘመራል።
👉ያለ ውድቀት፥ያለ ሕመም፥ያለ ፈተና ተአምራትና ምሥክርነት ከየት ይመጣሉ?
❤️ምንም ነገር ውስጥ እለፉ መጨረሻችሁ እርሱ አይደለም።በርቱ እግዚአብሔርንም ተስፋ አድርጉ።❤️
📖“ጠላቴ ሆይ፥ ብወድቅ እነሣለሁና፥ በጨለማም ብቀመጥ እግዚአብሔር ብርሃን ይሆንልኛልና በእኔ ላይ ደስ አይበልሽ።”
— ሚክያስ 7፥8
📖“እንዲህም ትላቸዋለህ፦ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፦ የወደቁ አይነሡምን? የሳተስ አይመለስምን?”
— ኤርምያስ 8፥4
05/04/2014 የምሕረት ዓመት
#አለ_አንዳንድ_ቀን
🗣እኔው ነኝ
አለ አንዳንድ ቀን፦ ልብ ሚሰበርበት
ተስፋ ፀሀይ ጠልቃ ጨለማ ያጠላበት
👉አለ አንዳንድ ቀን
አለ አንዳንድ ቀን፦እግዚአብሔር እያለ፤ በዙፋኑ ፀንቶ
አምላክ እንደሌለው የምንሆንበት፤ ሀዘናችን በዝቶ
👉አለ አንዳንድ ቀን
ርጉም ቀን ይኖራል፦ መፈጠርን 'ሚያስረግም
ለማመስገን ቀርቶ፤ ፀሎት ላይ ሚያደክም
👉አለ አንዳንድ ቀን
ቆይ ማን ነኝ እኔ፤ለምን እዚህ መጣሁ
ሕይወቴ እንዲ ለመሆኑ፤ እኔ ምን አጠፋሁ
የሚያስብል ፤ርጉም ቀን
ደስታችንን ሰርቆ፤ ሚያበዛ ሰቀቀን
ደግሞ ሌላኛው ቀን አለ
አለ ሌላ ክፉ ቀን፤ አምላክን ሚያስረሳ
እግዜርን አይፈራም፤ ታሞ የተነሳ
ይሄኛውም ክፉ ቀን፤በመዘመር ፋንታ ጮቤ ያስረግጣል
የስኬት ምክንያቱ ፤እግዜሩ መሆኑን፤ ፈፅሞ ያስረሳል
ከውለታው በላይ፤ደክሜበት ነበር ብሎ ያስኮፍሳል
#ሰው_ለካ_ምስኪን_ነው
ሰው ለካ ምስኪን ነው ሁሉንም አይችልም
እንኳን በስቃዩ በደስታው አያምርም።
🤐ግጥም እኮ ነው
እሽሽሽ🤫…ለማንም እንዳትናገሩ
ሀሳቡን ያዙልኝ ያ ነው ቁምነገሩ!!
🙏ፀሎት፦
ምሳሌ 30 (አዲሱ መ.ት)
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
⁸ ሐሰትንና ሐሰት መናገርን ከእኔ አርቅልኝ፤ ድኽነትንም ሆነ ብልጽግናን አትስጠኝ፤ ብቻ የዕለት እንጀራዬን ስጠኝ።
⁹ ያለዚያ ግን ያለ ልክ እጠግብና እክድሃለሁ፤ ‘እግዚአብሔር ማን ነው?’ እላለሁ፤ ወይም ድኻ እሆንና እሰርቃለሁ፤ የአምላኬንም ስም አሰድባለሁ።
27/03/2014 የምሕረት ዓመት
#ፀጋና_ምሕረት
🗣በአገልጋይ ብርሃኑ ታምራት
👉የድነታችን መሠረት የእግዚአብሔር ፀጋና የእግዚአብሔር ምሕረት ነው።ሐዋርያው ጳውሎስ በኤፌሶን መልእክቱ ፀጋና ምሕረትን እንዲህ ብሎታል፦
📖 “ነገር ግን እግዚአብሔር #በምሕረቱ_ባለ_ጠጋ ስለ ሆነ፥”
— ኤፌሶን 2፥4
📖“ከሁሉ የሚበልጠውን #የጸጋውን_ባለ_ጠግነት ያሳይ ዘንድ፥”
— ኤፌሶን 2፥6-7
👉እግዚአብሔር በምሕረት ባለጠጋ ነው።የፀጋውም ባለጠግነት ከመታወቅ የሚያልፍ ነው።በበደልና በኃጢአት ለወደቀው፤ከእግዚአብሔር ኅብረት ለተለየው ሰው እጅግ አስፈላጊው ነገር የራሱ የእግዚአብሔር ምሕረትና ፀጋ ነው።
👉ሁሉም ሰው ኃጢአተኛ ነው።ማንኛውም ኃጢአተኛ ሰው ደግሞ በእግዚአብሔር ፊት ለመቅረብ ድፍረት የሚሆነው ፅድቅ፤ከቁጣውም የሚያመልጥበት መጠለያ የለውም[ሮሜ.3:11.3:23]።ስለዚህ እግዚአብሔር በራሱ ምሕረትና ፀጋ አዳነን።እንዲህም ሆነ፦
👉 #በእግዚአብሔር_ምሕረት ምክንያት ከፍርዱና ከቁጣው ፊት #ዳንን።
👉 #በእግዚአብሔር_ፀጋ ምክንያት በፊቱ ለመቆም የምንችልበትን #ፅድቅ_አገኘን።
👉 #በምሕረቱ፦ የሚገባንን አልተቀበልንም
👉 #በፀጋው፦ የማይገባንን ተቀበልን።
👉 #ምሕረቱ ሥርየታችን፤ #ፀጋው ፅድቃችን ነው።
👉 #ምሕረቱ ነፃነታችን፤ #ፀጋው ድፍረታችን ነው።
👉 #ምሕረቱ ፈውሳችን፤ #ፀጋው ጉልበታችን ነው።
👉 #ምሕረቱ የእዳችን መሠረዝ፤ #ፀጋው ባለጠግነታችን ነው።
👉ፀጋው አንድ ሆኖ ግን የሚበዛና የሚጨመር ነው[ዮሐ.1:16-18.ሮሜ.5:20-21]።ምሕረቱ የተቀበልነው ሆኖ እያለ ከላይ የምንጠብቀውም ነው።[2ቆሮ.4:1.ይሁዳ.21]
👉ፀጋው የሚያድን ታዳጊ፤የሚያስተምር ሊቅ፥የሚረዳ አቅምም ነው[ቲቶ.2:11-13.ዕብ.4:16]።ምሕረቱ አስታርቆን የሚያወዳጅ፤የመኖራችንም ምክንያት፤የመንገሳችንም መሠረት ነው።[ኤፌ.2:4-5.1ጴጥ.1:3-5]
🙏የጌታ ፀጋና ምሕረት ከእናንተ ጋር ይሁን።🙏
❤️“እንደ ኃይሉ ሥራ እንደ ተሰጠኝም እንደ እግዚአብሔር ጸጋ ስጦታ መጠን የወንጌል አገልጋይ ሆንሁለት።”❤️
— ኤፌሶን 3፥7
26/03/2014 የፀጋና የምሕረት ዓመት
❤️የእለቱ መልእክት❤️
#የመተውን_ጥበብ_ተማሩ
🗣በአገልጋይ ብርሃኑ ታምራት
👉አንድ ወንድም አንዲትን ሴት ይወዳል።ይጠይቃትና ፈቃደኝነቷን ሲያገኝ ፍቅርን ይጀምራሉ።የፍቅረኝነት ጊዜያቸውን በጥሩ ሁኔታ ያሳልፋሉ።ለነገ ቤቱ በማሰብ ብዙ ዋጋዎችን እየከፈለ ግንኙነታቸውን ለማሳደግ ብዙ ጣረ።ከጊዜያት በኋላ አንድ ችግር እንዳለ ደረሰበት።ፍቅረኛው ለእርሱ ታማኝ እንዳልሆነችና እንደምትማግጥበት አወቀ።ሊተዋት ፈለገ።ግን አንድ ነገር ውሳኔውን ቀላል አላደረገለትም።እርሱም ለነገ ቤታቸውና ለእርስዋ የከፈለው ያ ሁሉ ዋጋ።እንዳይተዋት ያ ሁሉ ጊዜ ያሳለፉትን ነገር፤የከፈለውን ዋጋ ከንቱነት በቀላሉ ማባከን ሆነበት።እንዳይቀጥል ክፉ ዓመል አለባት።ምን ትመክሩታላችሁ?
👉አዎ በእርግጠኝነት ከከፈለው ዋጋ በላይ የሚከፍለው ዋጋ ስለሚበልጥ እንዲተዋት ትመክሩታላችሁ።ምክራችሁ ልክ ነው።አንዳንድ ነገሮች ለመተው ጭካኔን ይጠይቃሉ።አንድን ነገር ወይም ሰው ወይም ሥራ ለማግኘት ብለን የከፈልነው ብዙ ዋጋ ፍፃሜውን መልካም የማያደርግና የበለጠ ዋጋ የሚያስከፍለን ከሆነ እያመመንም ቢሆን እንተወው።
👉መተውን ልመዱ።ለመተው ጨክኑ።ከከፈላችሁት ዋጋ ጋር ተፋቱና ነጋችሁን እዩ።ሰው ዋጋ ከፍሎ ባገኘው ነገር ማረፍ ነው ያለበት።የበለጠ ዋጋ የምትከፍሉበትን ጉዳይ ከዚህ በፊት ዋጋ ስለከፈላችሁበትና ስለደከማችሁበት ብቻ አታስቀጥሉት።በቃ ተውት።
❤️“ #ጠቢብ_ብትሆን ጥበበኛነትህ #ለራስህ_ነው፤ #ፌዘኛ_ብትሆን #የምትጐዳው #ያው_አንተው_ነህ።””
— ምሳሌ 9፥12.❤️
25/03/2014 የምሕረት ዓመት
❤️የእለቱ መልእክት❤️
#እግዚአብሔር_ያዘጋጃል
🗣በአገልጋይ ብርሃኑ ታምራት
👉ለእግዚአብሔር ክብር መኖር ክብር ነው።ለጌታ መለየት ቅድስና ነው።አምላክ እንዳለው ሰው ደስ የሚያሰኘውን እየመረመሩ ማድረግ ማስተዋል ነው።ሲናገረን መስማት፤ሲያዘን መታዘዝ የልጅነት መታወቂያው ነው።እንደ ፈቃዱ እየኖርን፤እንደ ሀሳቡ ስንሄድ እርሱም ለእኛ የሚሆነውን ያዘጋጃል።
👉ከለመነው ይልቅ አብልጦ ሊሰጥ የሚቻለው እግዚአብሔር የታመነ ነው።
👉ጊዜ ለሰጡት ጊዜ ይሰጣል።
👉የፈሩትን ይጠብቃል።
👉የሰሙትን ፀሎታቸውን ይመልሳል።እርሱ እግዚአብሔር ታማኝ ነው።
👉በማታውቁት ሀገር ወገንን ያዘጋጃል።
👉በርሃባችሁ ጊዜ መጋቢ ሰራፕታን ይሰጣል።
👉በችግራችሁ ጊዜ ማለፊያ ሰውና መንገድ ይሰጣችኋል።
👉በክሳችሁ ጊዜ ድንገት ከከሳሾቻችሁ አንዱን ጠበቃችሁ ያደርገዋል።
👉የሞትን አዋጅ ይሽርላችኋል።
❤️እናንተን ካላጠፋሁ አላርፍም ያለውን ሌሊት መጥቶ ያስጠነቅቀዋል።
👉የእናንተን ነገር የወሰደውን እጥፍ ያስከፍለዋል።
❤️በአጭሩ ጠላትና ችግር እናንተን ባይነካ ይሻለው ነበር።
🙏ክብር ለእረኛችን እግዚአብሔር።🙏
🎼እኔ አንድ ተረዳሁ ትልቅ ምሥጢር ገባኝ
በምንም ሁኔታ ውስጥ እንደማትጥለኝ!!!🎼
24/03/2014 የምሕረት ዓመት
#5ቱ_አይቀሬ_ጉዳዮች
1⃣ #ሞት
2⃣ #የዘሩትን_ማጨድ
3⃣ #የምድርና_የክፉዎች_ማለፍ
4⃣ #እግዚአብሔር_በቃሉ_የተናገራቸው_ሁሉ
5⃣ #የኢየሱስ_መምጣት
👉 #እንደሚሞት_ሰው ተዘጋጁ፤ #የዘራውን_እንደሚያጭድ_ሰው በጊዜውም አለጊዜውም መልካምን ነገር ዝሩ፤ #ምድር_ከነክፋቷ ታልፋለችና ተፅናኑ በክፉዎችም አትቅኑ፤ #ጌታ_በቃሉ_የተናገረው ሁሉ ይፈፀማልና በእምነት ፅኑ፤ #ኢየሱስ_ይመጣልና ጠብቁት በፊቱም እንዳታፍሩ ታማኝ ባሪያዎች ሁኑ።
🗣በአገልጋይ ብርሃኑ 23/03/2014
#የምሥጋና_ርእስ_ሁኑ!!!
🗣በአገልጋይ ብርሃኑ ታምራት
👉አማኞች የምሥጋና ርእስ ናቸው።ስለአማኞች መዳን የሰማይ መላእክት ይዘምራሉና።ራእይ 5፥9-10
👉መላእክት እግዚአብሔርንና የእግዚአብሔርን በግ ኢየሱስን ያመሰገኑት ስለሰዎች መዳን እንጂ ስለራሳቸው አይደለም።ዋጅተሃቸዋልና ተመስገን።አድነሃቸዋልና ተመስገን።ካህናት አድርገሃቸዋልና ተመስገን።ድል ነስተሃልና ተመስገን።ይላሉ።እኛን ለመላእክት የምሥጋና ርእስ አድርጎናል።
👉ጥንቱንም ሲያድነን ለክብሩ ምሥጋና እንሆን ዘንድ ነው።አስተውሉ እንድናመሰግነው አይልም መፅሐፉ።እኛ ራሳችን ምሥጋና እንድንሆን እንጂ።
“ይኸውም፥ በክርስቶስ አስቀድመን ተስፋ ያደረግን #እኛ_ለክብሩ_ምስጋና_እንሆን_ዘንድ_ነው።”
— ኤፌሶን 1፥12
👉ክርስቶስ በሞቱ ባደረገልን ነገር ሁሉ እኛ የምሥጋና ርእስ ነን።ለማመስገን ዝንጉዎች ብንሆን እንኳን የማይደክሙና የማይዘነጉ መላእክት ጌታን ስለእኛ ሁሌ ያመሰግኑታል።
#ምሥጋና_ናችሁና_ምሥጋና_ሁኑ!
በተደረገልን ምሥጋና ነን።በምናደርገው ደግሞ ምሥጋና እንሁን።በድርጊታችን ደግሞ እግዚአብሔር ስለእኛ ይክበር።
“ #መልካሙን_ሥራችሁን_አይተው በሰማያት ያለውን #አባታችሁን_እንዲያከብሩ #ብርሃናችሁ እንዲሁ #በሰው_ፊት_ይብራ።”
— ማቴዎስ 5፥16
👉ሕይወታችን ለክብሩና ለምሥጋናው ይሁን።በእኛ ምክንያት ሰዎች እግዚአብሔርን ያክብሩ። #ጌታን_ስለእኛ_የሚያመሰግኑ_ሰዎች_አሉን?
👉ወላጆቻችን ስለእኛ ስለልጆቻቸው ጌታን ያመሰግናሉን? ወይስ ያማርሩታል? ሚስቶች ስለባሎቻቸው ጌታን ያመሰግናሉን? ባሎችስ ስለሚስቶቻቸው ጌታን ያመሰግናሉን? ድሆች ስለእኛ ጌታን ያመሰግናሉን? አገልጋዮቻችን ስለእኛ ጌታን ያመሰግናሉን? ያላመኑ ሰዎች ስለእኛ ለውጥና ፀባይ አምላካችንን አድንቀው ይሆንን?
👉ለሰው የምሬትና የሀዘን ምክንያት አትሁኑ።በእናንተም ምክንያት ሰዎች እግዚአብሔር አያማርሩ።
👉 #የምሥጋና_ርእስ_ሁኑ።ለምሥጋናው ሰበብ ሁኑ።።።
❤️ተከናወኑ❤️
#ቀሪው_እግዚአብሔር_ነው።
🗣በአገልጋይ ብርሃኑ ታምራት
👉ጊዜው የወረተኝነት ነው።ሰው እንዲሁ አይቼ ወደድኩህ ባለህ በማግስቱ እንዲሁ ይጠላሃል።ዛሬ እየተቃወመህ ያለው ትናንት ቲፎዞህ ነበር።በነገራችን ላይ ስለሌላው ሳወራህ ስላንተም እያወራሁ ነው።አንተም እንዲሁ ቀርበህ እንዲሁ ርቀሃል።ወደህ ጠልተሃል።ጠልተህ ወደሃል።ከምክንያታዊነት ይልቅ ስሜታዊነት ነግሶአል።ያልተመረመረ ሕይወት እየኖርን፤ባላወቅነው ጉዳይ ፍርድ እንሰጣለን።የወደደ ሲጠላ፤የቀረበ ሲርቅ ቀሪው ግን እግዚአብሔር ነው።
👉ዛሬ ሰው የተመካበት ውበት ነገ የሚረግፍ ነው።በዚህም ጊዜ ቀሪው እግዚአብሔር ነው።ዛሬ የተኩራራንበት ሀብት ነገ እስትንፋስና ጤና የማይገዛበት ጊዜ ይመጣል።በዚህም ጊዜ ቀሪው እግዚአብሔር ነው።
👉አለን ያልነው ሁሉ አያስመካም።ሲመቸን የምንረሳው፤ሲቸግረን የምናማርረው እግዚአብሔር ግን ቀሪ ወዳጃችን ነው።እኛ ጋር ሁሌ ያለ፤ ሁሌም የሚኖር ቀሪ ሀብታችን እግዚአብሔር ነው።
👉ከተጨነቃችሁ አይቀር……ወዶ ለሚጠላችሁ፤……ቀርቦ ለሚርቃችሁ፤……አክብሮ ለሚያዋርዳችሁ፤……በሰላም እንድትኖሩ ሳይፈቅድላችሁ ንፍሮ ቀቅሎ ዳስ ጥሎ ለሚቀብራችሁ… #ሰው ሳይሆን #የሁልጊዜ_ወዳጅ #ለቀሪያችሁ_እግዚአብሔር እርሱን #ላለማሳዘን_ተጨነቁ።።።።
📖““ነገር ግን በእግዚአብሔር የሚታመን፣ መታመኛውም እግዚአብሔር የሆነ ሰው ቡሩክ ነው።”
— ኤርምያስ 17፥7
📖““እኔ እግዚአብሔር አልለወጥም፤።”
— ሚልክያስ 3፥6
❤️የእለቱ መልእክት❤️
09/03/2014 የምሕረት ዓመት
#በግ_ሆኖ_በግ_አደረገን
🗣በአገልጋይ ብርሃኑ ታምራት
👉አንድ በድብድብ የታወቀ ወጣት ነበር።ወንጌልን ሰምቶ በክርስቶስ አመነ።እናም ጌታ ሕይወቱን ለወጠለት።አስቀድሞ ያደረጋቸው የነበሩትን ዓመፆች ሁሉ በጌታ ፀጋ እርግፍ አድርጎ ተወ።እናም አንድ ቀን መለወጡን የሰማ በብዙ ከእርሱ የሚያንስ አንድ የሰፈሩ ሰው አግኝቶት ሙልጭ አድርጎ ይሰድበዋል።ስድቡ በውስጡ ቁጣውን ቢቀሰቅስበትም እንደምንም ዋጥ አድረጎ ያዘው።አንድ ሰውም፦ "ለምን ዝም ትለዋለህ? እንዳይደግም አድርገህ ዋጋውን አትሰጠውም?" ሲለው ልጁ መልሶ፦ "የእግዚአብሔር ልጅ በግ ሆኖ በግ አድርጎኝ እንዴት ልምታው?" አለ ይባላል።
👉እውነትም ክርስትና ክርስቶስ የሆነውን መሆን ነው።ክርስቶስ ለሰዎች ስድብ በግ ነበር።ሲሰድቡት መልሶ አልተሳደበም።ሲመቱትም አልዛተም።በቁጣ ሲጎትቱት በፍቅር ተከተላቸው።እንዲህ ተብሎ እንደተፃፈ፦
📖“ሲሰድቡት መልሶ አልተሳደበም መከራንም ሲቀበል አልዛተም፥ ነገር ግን በጽድቅ ለሚፈርደው ራሱን አሳልፎ ሰጠ፤”
— 1ኛ ጴጥሮስ 2፥23
👉የተቆጡንን መቆጣት፤የሰደቡንን መስደብ፤ያሳደዱንን ማሳደድ፤የጠሉንን መጥላት ሰውነት ነው።የጠሉንን መውደድ፤የሰደቡንን መታገስ ግን ከሰውነት ከፍ ያለ መንፈሳዊነት ነው።
📖1ኛ ቆሮንቶስ 4 (አዲሱ መ.ት)
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
¹² ሲረግሙን እንመርቃለን፤ ሲያሳድዱን እንታገሣለን፤
¹³ ስማችንን ሲያጠፉ መልካም እንመልሳለን። እስከ አሁን ድረስ የዓለም ጒድፍ፣ የምድር ጥራጊ ሆነናል።
#በጉ_የእግዚአብሔር_ልጅ_በግ_አድርጎናል።
❤️“ወንድሞች ሆይ፥ … #ለክፋት_ነገር_ሕፃናት_ሁኑ…።”❤️
— 1ኛ ቆሮንቶስ 14፥20
🌬#ኢየሱስ_ሕይወቴ_ነው በሁለተኛው ሞት አልጎዳም። ቆላስ.3:4
🆓 #ኢየሱስ_ፅድቄ_ነው ማንም አይኮንነኝም።ሮሜ.8:1
🛣 #ኢየሱስ_መንገዴ_ነው ወደ አብ እደርሳለሁ።ዮሐ.14:6
👼 #ኢየሱስ_ትንሣኤዬ_ነው ሞት ታሪክ ሆኖልኛል።ዮሐ.11:25-26
😇 #ኢየሱስ_ቅድስናዬ_ነው ወደ አብ ለመቅረብ ድፍረት አለኝ።ኤፌ.2:18
🚪#ኢየሱስ_በሬ_ነው ወደ ክብሩ እገባለሁ።ዮሐ.10:9
🗣 #ኢየሱስ_ወንጌሌ_ነው እሰብከዋለሁ።ሮሜ.1:3-4
✅ #ኢየሱስ_እውነቴ_ነው እተማመንበታለሁ።ዮሐ.14:6
☀️🕯#ኢየሱስ_ብርሃኔ_ነው ጨለማ የለም በእኔ።ዮሐ.8:12
🥖 #ኢየሱስ_እንጀራዬ_ነው ፈፅሞ አልራብም።ዮሐ.6:35
🍇 #ኢየሱስ_የወይን_ግንዴ_ነው ዘመኔ ፍሬያማ ነው።ዮሐ.15:5
