en
Feedback
Deacon Chernet

Deacon Chernet

Open in Telegram

ነገር ግን በጌታችንና በመድኃኒታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ጸጋና እውቀት እደጉ። ለእርሱ አሁንም እስከ ዘላለምም ቀን ድረስ ክብር ይሁን፤አሜን 2ኛ ጴጥ 3፡18 ጥቆማ ወይም ጥያቄ ካላቹ በዚህ የተለግራም ቦት👉🏽https://t.me/Cher2112bot ይጠቀሙ

Show more
1 616
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
-1130 days
Posts Archive
በጥንት ዘመን በኢየሩሳሌም ውስጥ በሽታ የጸናበት ሰው ሁሉ የሚናፍቃት አንዲት መጠመቂያ ነበረች። ይህቺ መጠመቂያ ጤናማ ሰው ቢመለከታት የተለየ ነገር ላያይባት ይችላል። ታሞ ያያት ሁሉ ግን በውስጧ የመዳን ተስፋን ያይባታል። ስሟ ቤተ-ሳይዳ ይባል ነበር። በዚህች መጠመቂያ ቦታ ደዌ የበረታባቸው ሁሉ በዙሪያዋ ቁጭ ብለው አንዳች ነገር ይጠባበቃሉ። ይህ የሚጠባበቁት አንዳች ነገር የውሃውን መናወጥ ነበር። ሰላምና የተረጋጋ የነበረው ውሃ ድንገት ከተናወጥ፥ አካባቢው በአንዴ ይረበሻል። ሁሉም ይሯሯጣል። እድል ቀንቶት መጀመሪያ የገባ ካለበት በሽታ ሁሉ በአንዴ ይፈወሳል። የመዳን ሎተሪ እንደማለት ነው። ለአንድ ሰው ብቻ ይወጣል። ሐኪም ቤት ለመታከም ሄደን ቀድሞ የደረሰው ሰው ብቻ ታክሞ ቢድን፥ ሌላው ሁሉ ወደ ቤቱ ቢሸኝ ማለት ነው። ለአንዱ ፈንጠዚያ፥ ለሌላው ግን እንደገና ሌላ የመዳን ጥበቃ። ውሃው ግን የሚናወጠው በተፈጥሮ ምክንያት አልነበረም። የዮሐንስ ወንጌል "አንዳንድ ጊዜ የጌታ መልአክ ወደ መጠመቂያይቱ ወርዶ ውኃውን ያናውጥ ነበርና" (ዮሐ 5፡4) ይለናል። ለመሆኑ ይህ ውሃውን የሚያናውጥ መልአክ ማነው? በዚህ ዙሪያ ሁለት ምልከታዎች አሉ። አንዱ ወገን መልአኩ ቅዱስ ሚካኤል ነው ሲል ሌላው ወገን ደግሞ ቅዱስ ሩፋኤል መሆኑን ይገልጻል። ከሁለቱ ትውፊቶች ምናልባትም "ቅዱስ ሩፋኤል ነው" የሚለው ቢያመዝን ስንኳ የሚገርም አይሆንም። ቅዱስ ሩፋኤል ብዙ ነገሩ ከፈውስ ጋር የተጣመረ ነው። ሊቃውንት ስሙን ሲተረጉሙት "ደስ የሚያሰኝ፣ ቸር፣ መሐሪ፣ ቅን የዋህ" ብለው ቢሆንም፥ የዕብራይስጡ የስሙ ፍቺ ግን የመልአኩን እውነተኛ ማንነት ይበልጥ አጉልቶ ያሳያል። በዕብራይስጥ ስሙ ራፋኤል ሲሆን፥ የስሙ ዋና ሥር የሆነው ረፈአ እንደ ግሥ ስንጠቀመው "ፈውስ" ማለት ነው። በመሆኑም ራፋኤል የሚለው ስም ፍቺ "እግዚአብሔር ፈወሰ" ወይም "እግዚአብሔር ፈውሷል" ማለት ይሆናል። በአንድ የጥንት የአይሁድ ትውፊት ላይ አብርሃም ከተገረዘ በኋላ እግዚአብሔር ቁስሉን ይፈውስለት ዘንድ ቅዱስ ሩፋኤልን እንደላከለት ያትታል። መጽሐፈ ሄኖክም ስለዚህ መልአክ "በበሽታ ሁሉ ላይ በሰው ልጆችም ቁስል ላይ የተሾመው ቅዱስ ሩፋኤል ነው"(ሄኖ 10፡13) በማለት ይገልጻል። ሊቃውንትም ሕሙማንን የሚፈውስ (ፈዋሴ ዱያን) ይሉታል። እንግዲህ "ውሃውን እያናወጸ ሰዎች እንዲፈወሱ ያደርግ የነበረው ቅዱስ ሩፋኤል ነው" ቢባል የማይገርመው ለዚያ ነው፤ እንዲያውም ከስሙም ሆነ ከግብሩ የሚስማማ ይሆናል። ቅዱስ ሩፋኤል ሆይ፥ የእኛ ደዌ ለሠላሳ ስምንት ዓመት ከተኛው ከመጻጉዕ ይጸናል። በቤተሳይዳ ከተሰበሰቡት ድውዮች ሕመምም ሁሉ ይከፋል። የእነርሱ ደዌስ ለራስና ለአስታማሚ ብቻ ተረፈ። የእኛ ውስጣዊ ደዌ ግን መዘዙ ለሀገር ሁሉ ሆነ። ታላቁ መልአክ ሆይ፥ በተሾምህባት በዚህች ዕለት፥ የተጨነቁትን ነፍሳት ሁሉ አስብ። ደመናቱን አናውጸህ፥ ዝናቡንም ባርከህ በጠበልነቱ ክፉ በሽታችንን ፈውስልን። እንኳን ለቅዱስ ሩፋኤል ዓመታዊ ክብረ በዓል አደረሳችሁ።

ሆድ አምላክ ይሆናልን? የሰው ልጅ ወደድኳቸው በሚላቸው ነገሮች ሕይወቱ ይወሰናል። ሰይጣንም በምንወዳቸው ነገሮች ቀዳዳ በኩል ገብቶ ነው በውንብድና የጸጋችንን መዝገብ የሚበረብር። ለእግዚአብሔርም ያለንን ፍቅር የምንገልጠው በምንወዳቸው ነገሮች ነው።  እርሱ አንድ ልጁን በመስጠት ፍቅሩን እንደገለጠልን እኛም የምንወዳቸውን ለእግዚአብሔር ብለን ይቅርብን ብለን በመተው በዚህ ፍቅራችንን እንገልጣለን። የምንወዳቸው ሁሉ በእግዚአብሔር ፍቅር ፋንታ ከገቡብን፥ እነዚያ በእርግጥ የምንወዳቸው ነገር ግን በፍቅረ እግዚአብሔር የተካናቸው የወዳጅ ጠላት የሆኑበትን ጠዖታት ናቸው። ከእነዚህም ሳይገባን ጣዖታት አደርገን ከምናመልካቸው መካከል አንዱ ሆድ ነው። እግዚአብሔር አትብሉ ብሎ የከለከለንን ነገርና አትብሉ ባለን ሰአት የምንበላ ከሆነ በእርግጥ ከእግዚአብሔር ይልቅ ሆዳችንን እየወደድን ስለሆነ ሆዳችንን አመለክን ማለት ነው። ይህ ብቻ አይደለም፤ እግዚአብሔር እውነት ነው እቸገራለሁ ብሎ አስቦ መዋሸትም ጣዖት ማምለክ ነው። ለሆዱ ብሎ የሚዋሽ ሰው ከእግዚአብሔር ባሕርይ ጋር ይቃረናልና። የእግዚአብሔር ባሕርይው እውነት ነው።  ድኻ እየተቸገረ እያዩ ለነገ በማሰብ የማይመጸውቱ ሰዎችም በሁለት መንገድ ጣዖት አምልከዋል፦ አንደኛ አስቀድመን እንደ ገለጥነው ከፍቅር ይልቅ ገንዘብን በማስቀደም፤ ሁለተኛ ደግሞ እግዚአብሔር ያኖረኛል ከማለት ይልቅ ራሳቸውን ለራሳቸው ጠባቂ መጋቢ አድርጎ በመሾም መግቦተ እግዚአብሔርን በመካድ ነው። እንግዲህ እናስተውል ሆድ በሦስት መሠረታዊ ምክንያቶች ጣዖት ሊሆንብን እንደሚችል፦ መጀመሪያ እግዚአብሔር የከለከለንን በመመገብ ጊዜ ከእግዚአብሔር ይልቅ መብልን በመውደድ፤ ሁለተኛ ለቅዳሴ መላእክት የተፈጠርን ክቡራን አገልጋዮቹ ስንሆን መላ ዘመናችን ሆዳችንን በማገልገል ራሳችንን የራሳችን ባርያዎች በማድረግ፤ ሦስተኛ እግዚአብሔር እንደፈጠረኝ ያኖረኛል ከማለት ይልቅ ለነገ በመስገብገብ ለድኾች አለመራራት ናቸው።  ጾም ፍቅር እንጅ ቀመር አይደለም። የምንጾመው ከምንወደው መብል መጠጥ በመከልከል ለእግዚአብሔር ያለንን ፍቅር ለመግለጥ እንጅ ሰባት ጾም የጾምን ሰዎች ነን የሚል መስፈርት ለማሟላት አይደለም። የሰው ልጆች ሁሉ እናትና አባት የመጀመሪያዎቹ ሰዎች አንዲት የእንጨት ፍሬ የተከለከሉት ያችን በመተው ፍቅረ እግዚአብሔርን እንዲገልጡ እንጅ ለአንዲት እንጨት ፍሬ ነፍጓቸው አይደለም። እርሱማ እንኳን የበለስ ፍሬ ሊነፍገን  ሥጋውን ደሙን በለጋሥነት የሰጠ የባሕርይ ቸር አይደለምን? ክርስትና የፍቅር ሃይማኖት ነው። እግዚአብሔር ፍቅር ነውና ስለ ፍቅር ትጾማለህ፤ ስለ ፍቅር ትጸልያለህ፤ ሰለ ፍቅር ትሰደዳለህ፤ ስለ ፍቅር ትታሰራለህ፤ ስለ ፍቅር ትናቃለህ፤ ስለ ፍቅር ግፍን ሁሉ ተቀብለህ ትሞታለህ፤ በፍቅር ብርሃን ደምቀህ ትነሣለህ። ፍቅር ደግሞ ስለ ፍቅር በመማር የምታውቃት አይደለችም ስለ ፍቅር በመኖር እንጂ። ፍቅር በልቡናህ ዛፍ ሆኖ የተተከለ እንደሆነ ሥሩ እስከ ተረከዝህ ይወርዳል፤ ቅርንጫፎቹ ወደ ራስህ ያድጋሉ፤ አበባቸው በአንደበትህ ይፈነድቃሉ፤ የፍቅር ፍሬዎችም እነ ጾምና ጸሎት ምጽዋት ከአንተ በመላእክት እጅ እየተለቀሙ በሰማይ ጎተራ ይከማቻሉ፤ የፍቅርን ፍሬ እየበላህም ለዘለዓለም ትኖራለህ። እግዚአብሔርን የምትወደው ከሆነ እንኳን ሰባቱን አጽዋማትን ሁሉንም ቀን ትጾማለህ።  ፍቅረ እግዚአብሔር ያነሰህ ፍቅረ መብልዕ የበዛልህ ስትሆን ደግሞ ጾም ይቀነስልኝ ብለህ ክተት ሠራዊት ትወጣለህ፤ ነጋሪት ትጎስማለህ። እንዳትጾም የሚረዱህ የሚመስልህን ጥቅሶችም በመብራት እየፈለግህ ትለኩሳለህ። በጅብ ቆዳ የተለጎመ ከበሮ ሲመቱት 'እንብላው' ብሎ ይጮኻል እንዲሉ አበው፤ የሆድ ጠበቃ የሆኑ የጅብ ስብከት የሚያመሰጥሩ የእንብላው መጽሐፍ ሊቃውንትንም አታጣም። እናም ወዳጄ ሆይ "እለ ከርሦሙ ያመልኩ" "ሆዳቸው አምላካቸው ነው" እንደለ ቅዱስ ጳውሎስ (ፊልጵ. ፫፥፲፰ )የምትወደው ሆድህ ጠላት ሆኖ በግራ እንዳያቆምህ በእግዚአብሔር  ፍቅር ሰይፍነት የስስትን ገመድ ቆርጠህ ጥለህ ከምጽዋትና ከተገራ ሰውነት ጋር ጹም!

የጠዋት ቁርስ ተጋበዙ #የምክር_ቃል-ከቅዱስ_ኤፍሬም ቅዱስ፣ ጥንቁቅ፣ ግልጽና ብልህ ሁን፡፡ እርጋታን የተላበሰ ሰብእና ይኑርህ፡፡ ደስተኛ ሁን፤ ሰላምታህ በፈገግታ የታጀበ ንጹሕ ይሁን፡፡ ንግግርህ የታረመ አጭርና በጨው እንደ ተቀመመ ጣፋጭ ይሁን፡፡ቃላቶችህ የተመጠኑና ጤናማዎች ሁሉም የሚረዳቸው ይሁኑ፡፡ የጓደኛህን ምስጢር አትግለጥ፤ ለሚወዱህ ሁሉ የታመንክ ሁን፡፡ ወደ ጭቅጭቅና ንትርክ ከመግባት ራስህን ጠብቅ፡፡ የሚሰሙህ ሁሉ እንዳይጠሉህ ወደ ጠብ አትግባ፡፡ የበደሉንን ይቅር ማለት መሸነፍ ሳይሆን ፍቅርን ማስተማርነው። ከሰይጣን በቀር ምንም ጠላት አይኑርህ፡፡ የሰዎችን ስህተት አትመራመር፤ የባልንጀራህን ኃጢአት አትግለጥ፡፡ የባልጀራህን ውድቀት ደጋግመህ አታውራ፡፡ በራስህ ኃጢአት ላይ ፍረድ እንጂ በሌሎች ላይ አትፍረድ ገዢያቸው አይደለህምና፡፡ ኃጢአትን በፈጸመ ሰው ላይ ወቀሳ አታብዛ አንተም ትበድላለህና፡፡ ነገር ግን ከኃጢአቱ ይመለስ ዘንድ ረዳትና መካሪ ሁነው፡፡ ከወደቀበትም የስህተት ሥራ እንዲወጣ አበርታው፡፡ ተስፋውን በእግዚአብሔር ላይ ቢያደርግ ኃጢአቱ ልክ በእሳት ፊት እንደ ወደቀ ገለባ ፈጥኖ እንደሚወገድለት ንገረው፡፡ ተፈጥሮ እንደ መጽሐፍ ፍጥረታት እንደ ጽላት ይሁኑህ፡፡ ከእነሱ ሕግጋትን ተማር፤ በተመስጦ ሆነህ በመጽሐፍ ያልሰፈሩትን ምስጢራት ተረዳ፡፡ እግዚአብሔርን ከሚፈራ በቀር ባለጸጋ የሆነ ሰው ማነው? የእውነት እውቀት ከጎደለው ሰው በላይ ፍጹም ደሃ የሆነ ማን ነው? ሁል ጊዜም እውነተኛ ፍቅራችን ጸንቶ ይቀጥል ዘንድ ወደ እግዚአብሔር ጸልይ፡፡ እርሱን ለምነው፡፡ ስለ ቸርነቱ ምስጋና አቅርብ፤ ምክሬን ፈጽሞ ቸል አትበል፡፡ ሠናይ ቀን!

በሩጫ ውድድር የሚሮጡ ብዙዎች እንደ ሆኑ፣ሽልማቱን የሚቀበለው ግን አንዱ ብቻ እንደ ሆነ አታውቁምን? ስለዚህ ሽልማቱን እንደሚቀበል ሰው ሩጡ። 1 ቆሮንቶስ 9፥24

እንኳን ሐዲስ ሐዋርያ፣ ጻድቅ፣ሰማዕት ለሆኑት ብርሃን ዘኢትዮጵያ አቡነ ተክለ ሃይማኖት በዓለ ዕረፍት አደረሳችሁ አደረሰን !!! ሠናይ በዓል ይሁንልን !

እርሱ ከጨለማ አገዛዝ ታደገን፤ ወደሚወድደው ልጁ መንግሥትም አሻገረን፤ በርሱም ቤዛነትን በደሙ አግኝተናል፤ ይህም የኀጢአት ይቅርታ ነው። #ቈላስይስ_1፥13-14

ስለዚህ ወደ አምላክህ ተመለስ፤ ፍቅርንና ፍትሕን ጠብቅ፤ ዘወትርም በአምላክህ ታመን።
But you must return to your God; maintain love and justice, and wait for your God always.
Hosea 12:6

እንግዲህ የምትበሉ ወይም የምትጠጡ ብትሆኑ ወይም ማናቸውን ነገር ብታደርጉ ሁሉን ለእግዚአብሔር ክብር አድርጉት። 1ኛ ቆሮ10:31

እንኳን ለፍልሰታ ለማርያም በሰላም አደረሳችው "የህይወት እናት ድንግል ማርያም ሆይ ትንሳኤሽ ሳይሆን ሞትሽ ይደንቀኛል፤ እርገትሽ ሳይሆን ወደ መቃብር መውረድሽ ይገርመኛል፤ የብርሃን እናት ድንግል ማ
እንኳን ለፍልሰታ ለማርያም በሰላም አደረሳችው "የህይወት እናት ድንግል ማርያም ሆይ ትንሳኤሽ ሳይሆን ሞትሽ ይደንቀኛል፤ እርገትሽ ሳይሆን ወደ መቃብር መውረድሽ ይገርመኛል፤ የብርሃን እናት ድንግል ማርያም ሆይ ትወጂኛለሽን? ብየ አልጠይቅሽም ፍቅርን የወለድሽ አንቺ ለአለሙ ሁሉ ፍቅርሽ የበዛ ነውና፤ አትናፍቂኝምን? ብየም አልጠይቅሽም ዘወትር እኔን ለመጠበቅ ከጎኔ እንደማትለይ አውቃለሁኝና፤ ሆኖም እመቤቴ ሆይ፦ እንደ ቶማስ አይሽ ዘንድ በእጅጉ እጓጓለሁ የቶማስ ንፅህናና ቅድስና ግን የለኝም እንደ ዮሃንስ ከጎንሽ ልሆን እጓጓለሁ የዮሃንስ ፀጋ ግን የለኝም። እናቴ ሆይ፦ እንደ ኤልሳዕ የልቦናዬ አይን በርቶ ሰማያዊ ክብርሽን ላይ አልተቻለኝምና አዝናለሁ ኤልሳዕ በፀሎት ሃይል የግያዝን አይን እንዳበራ አንቺም አይኔን ታበሪልኝ ዘንድ ሃይልሽን በእኔ ላይ አበርቺ፡፡ ድንግል ሆይ፦ ይህን የምል የእምነት ማረጋገጫ ፈልጌ አይደለም በልጅሽ መሰረትነት የታነፅኩኝ በልጅሽ ስምም የተጠመቅኩኝ ነኝና፤ ነገር ግን ስለምትናፍቂኝ ይህን አልኩኝ ስለዚህም ነይ ነይ እምየ ማርያም እያልኩኝ እንደ እናቶቼም እለምንሻለሁ፡፡ የብርሃን ልብስሽን ለብሰሽ ነይ የክብር አክሊልሽን ደፍተሽ ነይ አንቺ ሱላማጢስ ሆይ ነይ እናይሽ ዘንድ ነይ፡፡ መልካም በዓል !

እግዚአብሔር ሆይ፤ ወደ አንተ እጣራለሁ፤ ዐለቴ ሆይ፤ ሰምተህ እንዳልሰማ አትሁንብኝ፤ አንተ ዝም ካልኸኝ፤ ወደ ጕድጓድ እንደሚወርዱ እሆናለሁ። ለርዳታ በጮኽሁ ጊዜ፣ ወደ ቅዱስ ማደሪያህ፣ እጆቼን በዘረጋሁ ጊዜ፣ የልመናዬን ቃል ስማ። #መዝሙር_28፥1-2

እንኳን ለደብረ ታቦር በዓል በሰላም አደረሰን፤ አደረሳችሁ!!! የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን በከፍተኛ መንፈሳዊ ሥርዓት ከምታከብራቸው ከጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ዘጠኝ ዓበይት በዓላት አንዱ በየዓመቱ ነሐሴ ፲፫ ቀን የምናከብረው የደብረ ታቦር በዓል ነው፡፡ ይህ በዓል ቡሄ በመባልም ይታወቃል፡፡ የደብረ ታቦር በዓል ጌታችን አምላካችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በታቦር ተራራ ብርሃነ መለኮቱን፣ ክብረ መንግሥቱን መግለጡን በማሰብ በየዓመቱ በድምቀት ይከበራል /ማቴ. ፲፯፥፩ ማር.፱፥፩፤ሉቃ.፱፥፳፰/፡፡ በዚህ በዓል መለኮታዊ ክብሩ፣የነቢያትና የሐዋርያት ምስክርነት ይተረጎምበታል፡፡ መልካም በዓል

እግዚአብሔር ሆይ፤ እንደ አንተ ያለ ማንም የለም፤ አንተ ታላቅ ነህ፤ የስምህም ሥልጣን ታላቅ ነው። የሕዝቦች ሁሉ ንጉሥ ሆይ፤ አንተን የማይፈራ ማነው? ክብር ይገባሃልና። ከምድር ጠቢባን ሁሉ፣ ከመንግሥቶቻቸውም ሁሉ መካከል፣ እንደ አንተ ያለ የለም። #ኤርምያስ_10-6

በእውነት ያለ ሐሰት ይቅርታን የመሰለ ምግባር ምንም የለም። ተወዳጅ ሆይ! የይቅርታን ኃይል ልታውቅ ትወዳለህን? መልካም! እነግርሃለሁና አድምጠኝ እግዚአብሔር እንዲህ ብሏል፦ ሙሴና ሳሙኤል በፊቴ ቢቆሙም ልቤ ወደዚህ ሕዝብ አያዘነብልም" (ኤር 15፥1) ኾኖም እነዚህ ሙሴና ሳሙኤል ከእግዚአብሔር ቍጣ ሊታደጉአቸው ያልቻሉ ሰዎች ይህን ትእዛዝ መፈጸም በቻሉ ጊዜ ከዚያ ቍጣ ሊድኑ ችለዋል። እንዲህም ስለኾነ እግዚአብሔር ደጋግሞ ይህን ትምህርት አስተምሯል፤ እንዲህ ሲል፦ ኹላችሁም በባልንጀራችሁ ላይ ክፉ ነገርን በልባችሁ አታስቡ" (ዘካ 8፥17)፤ “ከእናንተ ማንም በወንድሙ ላይ ክፉ ነገር አያስብ" (ዘካ.7፥10)። እየተባለ ያለው በአእምሮህም አታስቀምጠው፣ አታስበው፥ ከቂምህ ጋር ቁስልህን ፈውስው ነው እንጂ እንዲሁ "ቍጣህን ተው" ብቻ አይደለም፡፡ ምናልባት ቂም በቀልህን ስትወጣ ባልንጀራህን የጎዳኸው ሊመስልህ ይችላል፤ ቀድመህ የምትጎዳው፣ በኹሉም ረገድ በንዴትህ የምትቃጠለው፣ አንጀትህም የምትቈረጠው ግን አንተ ነህ፡፡ በየጊዜው ከሚቆጣ ሰው በላይስ ማን ጐስቋላ ሰው አለ?

"ኦ ድንግል አኮ በፍትወተ ደነስዘተፀነስኪ አላ በሩካቤ ዘበሕግ እምሐና ወኢያቄም ተወለድኪ።" ድንግል ሆይ በኃጢአት ፍትወት የተፀነስሽ አይደለም በሕግ በሆነ ሩካቤ ከሐና ከኢያቄም ተወለድሽ እንጂ።
ቅዳሴ ማርያም

ፅንሰታ ለማርያም ነሐሴ 7 በዚህች ዕለት እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ተጸነሰች የእመቤታችን ወላጆችዋ ኢያቄም እና ሃና ይባላሉ እነዚህ ቅዱሳን ኢያቄም እና ሃና በአንድነት ተጋብተው ሲኖሩ ልጅ አጡ ከእለታት አንድ ቀን ወደ ቤተ እግዚአብሄር ሂደው ሲፀልዩ ሲያዝኑ ዋሉ ኃዘናቸው እንዴትስ ነው ቢሉ ፦ ኢያቄም:-"አቤቱ ጌታዬ ያባቶቼ የእስራኤል አምላክ እኔ ባርያህ እለምንሃለሁ አትጣለኝ አትናቀኝ ፀሎቴን ስማኝ ፈቃዴን ፈጽምልኝ፤ለአይኔ ማረፊያ ለልቤ ተስፋ የሚሆን የተባረከ ወንድ ልጅ ስጠኝ" ብሎ ሲለምን ዋለ:፡ ሐናም በበኩሏ "አቤቱ ጌታዬ የአባቶቼ የእስራኤል አምላክ እኔ ባርያህ እለምንሃለሁ ስማኝ ለአይኔ ማረፊያ ለልቤ ተስፋየምትሆነኝ የተባረከች ሴት ልጅ የማህፀኔን ፍሬ ስጠኝ" ብላ ስትለምን ዋለች እንዲህ ብለው ሲያዝኑ ሲጸልዩ ውለው ርግብ ከልጆቿ ጋር ስትጫወት አይታ አቤቱ ጌታዬ ለዚች ግዕዛን ለሌላት እንስሳ ልጅ የሰጠህ አምላክ ምነው ለኔ ልጅ ነሳኸኝ ! ብላ ምርር ብላ አለቀሰች። እንዲህ ብለው ሲያዝኑ ሲፀልዩ ውለው ከዘካርያስ ከሊቀ ካህናቱ ሄደው አቤቱ ጌታችን ሆይ ወንድ ልጅ ብንወልድ ተምሮ ቤተ እግዚአብሔርን አገልግሎ እንዲኖር እንሰጣለን ፤ ሴት ልጅም ብንወልድ ማይ(ውሃ) ቀድታ መሶብ ወርቅ ሰፍታ መጋረጃ ፈትላ ካህናትን አገልግላ እንድትኖር እንሰጣለን ብለው ስዕለት ገቡ።  ዘካርያስም እግዚአብሄር ጸሎታችሁን ይስማችሁ ስእለታችሁን ይቀበልላችሁ ብሎ አሳረገላቸው። ከዚያም  ቅድስት ቡርክት ሐና እና ቅዱስ ኢያቄም ዕለቱን ራእይ አይተው ነገር አግኝተው አደሩ ራእዩም እንዴት ነው ቢሉ ፦ ኢያቄም 7ቱሰማያት እንደ መጋረጃ ተገልጠው ከላይኛው ሰማይ ነጭ ወፍ ወርዶ በራሴ ላይ ሲቀመጥ አየሁ አላት ሃናም እኔም አየሁ አለችው:ምን አየሽ ቢላት:ነጭ ርግብ መጥታ በራሴ ላይ ወርዳ በጆሮዬ ገብታ በማህጸኔ ስትተኛ አየሁ። ይህንን ራእይ ያዩት ሐምሌ 30 ዕለት ነው:: እነሱም እንዲ ያለ ራዕይ ካየን ነገር ካገኘን ብለው ዕለቱን በሩካቤ ሥጋ አልተገናኙም ፤ ፈቃደ እግዚአብሄር ቢሆን ብለው አዳምንና ሔዋንን ብዙ ተባዙ ምድርንም ሙሏት ብሎ ያበሰረ አምላክ ለኛስ ይልክልን የለምን ? ብለው ዕለቱን አልጋ ምንጣፍ ለይተው እስከ 7ቀን ድረስ ለየብቻቸው ሰነበቱ፡፡ ነሐሴ በባተ በሰባተኛው ቀን ከሰው የበለጠች ከመላእክት የከበረች ደግ ፍጥረት ትወልዳላቹህና ዛሬ በሩካቤ ስጋ ተገናኙ ብሎአቹሃል ጌታ ብሎ መልአኩ ለሐና ነገራት በፈቃደ እግዚአብሄር በብስራተ መልአክ እመቤታችን እግዝእትነ ማርያም እሁድ እለት ነሐሴ 7 ቀን ተፀነሰች ። ምልጃዋ በረከቷ በሁላችን ጋር ይሁን

4.ውዳሴ ማርያም ትርጓሜ ዘሐሙስ.mp313.57 MB

እኔ ግን ጠላቶቻችሁን ውደዱ፤ ለሚያሳድዷችሁም ጸልዩ እላችኋለሁ፤ እንደዚህም በማድረጋችሁ በሰማይ ላለው አባታችሁ ልጆች ትሆናላችሁ። እርሱ ፀሓዩን ለክፉዎችና ለመልካሞች ያወጣል፤ ዝናቡንም ለኀጢአተኞችና ለጻድቃን ያዘንባል። ማቴዎስ 5፥44-45

3.ውዳሴ ማርያም ትርጓሜ ዘረቡዕ.mp318.30 MB

2.ውዳሴ ማርያም ትርጓሜ ዘሠሉስ.mp319.81 MB

እርስ በርሳችሁም ተቻቻሉ፤ ከእናንተ አንዱ በሌላው ላይ ቅር የተሠኘበት ነገር ቢኖር ይቅር ተባባሉ፤ ጌታ ይቅር እንዳላችሁ እናንተም ሌላውን ይቅር በሉ።በእነዚህ ሁሉ ላይ ሁሉን በፍጹም አንድነት የሚያስተሳስረውን ፍቅርን ልበሱት። ቈላስይስ 3፥13-14