Deacon Chernet
Открыть в Telegram
ነገር ግን በጌታችንና በመድኃኒታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ጸጋና እውቀት እደጉ። ለእርሱ አሁንም እስከ ዘላለምም ቀን ድረስ ክብር ይሁን፤አሜን 2ኛ ጴጥ 3፡18 ጥቆማ ወይም ጥያቄ ካላቹ በዚህ የተለግራም ቦት👉🏽https://t.me/Cher2112bot ይጠቀሙ
Больше1 622
Подписчики
+124 часа
Нет данных7 дней
-1030 день
Архив постов
1 622
አጋንንት እጅግ በጣም ቀናተኛ ነው ነገር ግን እርሱን በሚመሰሉ አጋንንት አይደለም ፡፡ የሰው ልጅ ግን እርሱን በሚመስል የሰው ልጅ ይቀናል ። በአጋንንት የማይደረግ ክፋት በእኛ ዘንድ ይደረጋል !
#ቅዱስ_ዮሐንስ_አፈወርቅ
1 622
እንግዲህ ክፋትን ሁሉ፣ ማታለልን ሁሉ፣ ግብዝነትን፣ ቅናትንና ሐሜትን ሁሉ አስወግዱ። በድነታችሁ እንድታድጉ፣ አዲስ እንደ ተወለዱ ሕፃናት ንጹሑን መንፈሳዊ ወተት ተመኙ፤ ጌታ መልካም መሆኑን ቀምሳችኋልና።
1ጴጥሮስ 2:2
1 622
ንብ የምትሞተው መቼ ነው ?
የብልህ ሰው መገለጫው ይኼ ነውና ኹል ጊዜ የምታመሰግኑ ኹኑ፡፡ ክፉ ደረሰባችሁን? ይህስ እናንተ ከፈቀዳችሁ ክፉ አይደለም፡፡ ኹል ጊዜ አመስግኑ፤ ክፉ የኾነባችሁም መልካም ይኾንላችኋል፡፡ ከተወደደው ኢዮብ ጋር ኾናችሁ “የእግዚአብሔር ስም የተባረከ ይኹን" እያላችሁ አመስግኑ #ኢዮ.1:21::
እስኪ ንገሩኝ! ደረሰብኝ የምትሉት ክፉ ነገር ምንድን ነው? በሽታ ነውን? ታዲያ ይኼ'ኮ አዲስ ነገር አይደለም፡፡ ምክንያቱም ሥጋችን መዋቲና ለስቃይ የተጋለጠ ነውና፡፡
“ሀብት ንብረት ማግኘት አለብኝ" የሚል መሻት ነውን? ታዲያ ይኼ'ኮ ማግኘት የሚቻል ነው፤ ካገኙት በኋላ ግን መልሶ የሚጠፋና በዚህ ዓለም ብቻ የሚቀር ነው፡፡
ከወንድሞች የሚደርስ ሐሜትና የሐሰት ክስ ነውን? ታዲያ ተጐጂዎቹ'ኮ የሚያሙንና በሐሰት የሚከሱን ሰዎች እንጂ እኛው አይደለንም፡፡ “ኃጢአት የምትሠራ ነፍስ ትሞታለች” እንዲል ተጐጂዎቹ ይህን ኃጢአት የሚሠሩት እንጂ እኛው አይደለንም #ሕዝ.18፡4)፡፡
ተጐጂው ምንም በደል ሳይኖርበት ክፉ የሚደርስበት ሰው ሳይኾን ክፉ የሚያደርሰው ሰው ነው፡፡ ስለዚህ በዚህ ሙት ሰው ልትቈጡ አይገባም፤ ከዚያ ይልቅ ከሞት ይድን ዘንድ ልትጸልዩለት ይገባል እንጂ፡፡
ንብ የምትሞተው መቼ ነው ? ሌላውን ስትናደፍ ነው፡፡ እግዚአብሔር በዚህች ፍጥረት በወንድሞቻችን ላይ ልንቈጣ እንደማይገባ ያስተምረናል፡፡ የምንቈጣ (የምንናደፍ) ከኾነ ግን ቀድመን የምንሞተው እኛው ነን፡፡ ስንቈጣቸው የጎዳናቸው ይመስለን ይኾናል፤ ነገር ግን እንደዚያች ንብ ተጐጂዎቹ እኛው ነን፡፡
#ቅዱስ_ዮሐንስ_አፈወርቅ
1 622
ስትበሳጭ፣ ነርቮችህን ተቆጣጠር፣ ምላስህንም ተቆጣጠር፤ የፊት ገጽታህንና እንቅስቃሴዎችህንም ተቆጣጠር። በምንም ያህል መጠን ቢበድሉህ እንኳ፣ ሌላውን ሰው እንድትበድል ለራስህ ፈቃድ አትስጥ።#ብፁዕ_አቡነ_ሺኖዳ
1 622
ከንስሐ አባትህ ጋር ስትሆን ጥያቄህን እንጂ ውሳኔህን አታቅርብላቸው፤ በልብህ ካሰብከው ጋር እንዲስማሙ ሳይሆን በሀሳብህ ላይ ሀሳባቸውንና ምክራቸውን እንዲሰጡህ አድርግ።
#ብፁዕ_አቡነ_ሺኖዳ
1 622
በመስቀል ምልክት ሳታማትብ ከቤትህ አትውጣ፡፡
በትር፣ መሳሪያ፣ የማይበገር ምሽግም ይሆንሀል፡፡ ሰውም ሆነ ጋኔን አንተን ለማጥቃት አይደፍሩም፤ እንደዚህ ያለ ኃይለኛ የጦር ትጥቅ ታጥቀሃልና፡፡ ይህም አንተ ልክ እንደ ወታደር እንደሆንክ፣ ከአጋንንት ጋር ለመዋጋት ዝግጁ እንደሆንክ፣ በድልም አክሊልን እንደምታገኝ ምልክት ነው፡።
መስቀሉ ሞትን አሸንፏል፣ ኃጢአትን አጥፍቷል፣ ሲኦልን ባዶ አድርጓል፣ ሰይጣንን ከዙፋን አውርዷል፣ አጽናፈ ዓለሙንም ወደ እግዚአብሔርመልሷል፡፡
ታዲያ ኃይሉን ትጠራጠራለህ? መስቀሉ ይህን ኹሉ ድንቅ ነገር አድርጎልናል፤ መስቀል በአጋንንት ፊት የቆመ የሽንፈታቸው መታሰቢያ ነው፤ ክርስቶስ እባቡን የገደለበት ሰይፍም ነው::
መስቀል የአብ ፈቃድ፣ የአንድያ ልጁ ክብር፣ የመንፈስ ቅዱስ ደስታ፣ የመላእክት ውበት፣ የቤተክርስቲያን ጠባቂ ነው፡፡ ጳውሎስም እንዳለው መስቀል የቅዱሳን መከታ ነው፤ የዓለም ኹሉ ብርሃንም ነው፡፡
#ቅዱስ_ዮሐንስ_አፈወርቅ
1 622
እንኳን ለመጥምቁ ቅዱስ ዮሐንስ የልደት በዓል በሰላም አደረሳችሁ!
ሰኔ ሠላሳ በዚች ዕለት ነቢይሰማዕትና ሐዋርያ የሆነ መጥምቁ ዮሐንስ ተወለደ።
በስምንተኛውም ቀን ሊገዝሩት መጡ በአባቱ ስም ዘካርያስ ብለው ጠሩት። እናቱ ግን አይሆንም ዮሐንስ ይባል አለች። ከዘመዶችሽ ስሙ እንዲህ የሚባል የለም አሏት። አባቱንም ጠቅሰው ማን ሊባል ትወዳለህ አሉት። እርሱም ብራና ለምኖ ስሙ ዮሐንስ ይባል ብሎ ጻፈ። ሁሉም አደነቁ። ያን ጊዜም አንደበቱ ከድዳነት ተፈትቶለት ተናገረ።የበለጠ ለማንበብ 👇 ስንክሳር ዘሰኔ ፴ (30)
ሉቃስ ፩ :፶፯ – ፍ፡ም(1:57-ፍ:ም)
1 622
እኔ ከአንተ ጋር ነኝና አትፍራ; እኔ አምላክህ ነኝና አትደንግጥ። አበረታሃለሁ፥ አዎን እረዳሃለሁ፥ በጽድቄም ቀኝ እይዝሃለሁ።
ኢሳ 41:10
Fear not, for I am with you; Be not dismayed, for I am your God. I will strengthen you, Yes, I will help you, I will uphold you with My righteous right hand.
Isaiah 41:10
1 622
የየበዓላቱና የየሳምንቱ ምስባክ እንድሁም የቅዳሴ ምንባባት ከአማርኛ ትርጒም ጋር የሚቀርቡበት ቻናል ነው👇ተቀላቀሉ
@Fenoteyared
@Fenoteyared
@Fenoteyared
1 622
እግዚአብሔር ሆይ፤ የተገፉትን ምኞት ትሰማለህ፤ ልባቸውን ታበረታለህ፤ ጆሮህንም ወደ እነርሱ ጣል ታደርጋለህ፤ ከዐፈር የተፈጠረ ሰው ከእንግዲህ እንዳያስጨንቃቸው፣ አንተ ለድኻ አደጉና ለተገፋው ትሟገታለህ።
መዝሙር 10፥17-18
1 622
በፍቅር እና ምኞት መካከል ያለው ትልቅ ልዩነት ይህ ነው: ፍቅር ሁል ጊዜ መስጠት ይፈልጋል, ምኞት ግን ሁልጊዜ መውሰድ ይፈልጋል.
"This is the big difference between love and lust: love always wants to give, whereas lust wants always to take''#Pope_Shenouda_III
1 622
እግዚአብሔር ወደ ቤተ ክርስቲያን የተመላለስክበትን ግዜያት ፣ችግር ለመፍታት የወስድካቸውን እርምጃዎች አይረሳም፤ ለሐዘንተኛ የሰጠኸውን ፈገግታ ወይም ሐዘንተኛውን ያጽናናህበትን መጽናኛ ቃል አይረሳም።
#Pope_Shenouda_III
1 622
እግዚአብሔርን እንደ ጓደኛህ አድርገው፤ ስለ ሁሉም ነገር ንገረው፣ በአጠገብህ እንዳለም ይሰማህ። በሁሉም ጉዳይ ውስጥ እርሱን አስገባው። ለምሳሌ ያህል፦ ስትነቃ እንዲህ በለው፦ 'ጌታ ሆይ፤ ሌሊቱን በሰላም ስላሳደርከኝ አመሰግንሃለሁ፤ ቀኑንም በሰላም እንድታውለኝ እለምንሃለሁ። ፍቅርህን ስጠኝ፣ በአንተም ላይ ኃጢአት እንዳላደርግ እርዳኝ።' ከዚያም ፊትህን ስትታጠብና ውኃው በፊትህ ላይ ሲፈስ እንዲህ በለው፦ 'በሂሶጵ እርጨኝ እነጻማለሁ፤ እጠበኝ ከበረዶም ይልቅ ነጭ እሆናለሁ።' ደግሞም እንዲህ በለው፦ 'ዋናው ነገር የሥጋ ንጽሕና ሳይሆን የመንፈስ ንጽሕና ነው። ለሥጋዬ ንጽሕና እንድጠነቀቅ እንደረዳኸኝ ሁሉ፣ ለነፍሴም ንጽሕና እንድጠነቀቅ እርዳኝ።#Pope_Shenouda_III
1 622
◽️ “እጅግ የተከበርህ ወዳጄ ሆይ አካላዊ የእግዚአብሔር ቃልን በጸሎትህ ስትጠራውና ያለ ስለት የጌታችንን ቅዱስ ሥጋዉንና ክቡር ደሙን በምትፈትትበት ጊዜ ስለኔ መጸለይንና መማለድን አታቋርጥ፡፡”
-ቅዱስ ጎርጎርዮስ ዘእንዚናንዙ፣ ሃይማኖተ አበው
1 622
◽️ “እጅግ የተከበርህ ወዳጄ ሆይ አካላዊ የእግዚአብሔር ቃልን በጸሎትህ ስትጠራውና ያለ ስለት የጌታችንን ቅዱስ ሥጋዉንና ክቡር ደሙን
በምትፈትትበት ጊዜ ስለኔ መጸለይንና መማለድን አታቋርጥ፡፡”
-ቅዱስ ጎርጎርዮስ ዘእንዚናንዙ፣ ሃይማኖተ አበው
1 622
እንደ አንድ አካል ሆናችሁ የተጠራችሁበት የክርስቶስ ሰላም በልባችሁ ይንገሥ፤ የምታመሰግኑም ሁኑ። የክርስቶስ ቃል በሙላት ይኑርባችሁ፤ እርስ በርሳችሁ በጥበብ ሁሉ ተማማሩ፤ ተመካከሩ፤ በመዝሙርና በማሕሌት፣ በመንፈሳዊም ቅኔ በማመስገን በልባችሁ ለእግዚአብሔር ዘምሩ
#ወደ_ቆላስይስ_፲፭:፲፯_15:17
1 622
በፍጹም ተስፋ አትቁረጥ፥ ሕይወት አልባ ብትሆን፥ ከእነዚህ ድንጋዮች ለአብርሃም ልጆች ሊያስነሣለት እግዚአብሔር ይችላልና፥ #ማቴ 3፡9 አንተም ያለ ጥርጥር ከብዙ ድንጋዮች ትበልጣለህ።
#Pope_Shenouda_III
1 622
#እንኳን_ለገናናው_መልአክ_ለቅዱስ_ሚካኤል_በዓል_በሰላም_በጤና_እና_በፍቅር_አደረሳችሁ።
“ ይትዐየን መልአከ እግዚአብሔር ዐውዶሙ ለእለ ይፈርህዎ ወያድኅኖም ጣዕሙ ወታእምሩ ከመኄር እግዚአብሔር።” መዝ.33 (34)7-8
ቅዱስ ሚካኤል ለፍጥረታት ሁሉ የሚራዳና የሚያዝን የምሕረትና የመዳኛ፤ የሰላም መልአክ ነው፡፡ ‹‹በዚያም ዘመን ስለ ሕዝብህ ልጆች የሚቆመው ታላቁ አለቃ ሚካኤል ይነሣል›› /ዳን.12፥1/ በማለት በነቢዩ ዳንኤል የተነገረ ሲሆን በሌላ ቦታ ‹‹ከዋነኞቹ አለቆች አንዱ ሚካኤል ሊረዳኝ መጣ›› /ዳን. 10፥13/ በማለት ያስረዳል፡፡ ቅዱስ ሚካኤል በስሙ የተራቡትን ለሚያበሉ የታረዙትን ለሚያለብሱ የተጠሙትን ለሚያጠጡ በዓሉን በክብር በደስታ ለሚያከብሩ ሁሉ ምልጃው ፈጣን የችግረኞች ረዳት ታማኝ ጽኑዕ ኃያል መልአክ ነው።
#ሰኔ_12_ለምን_ይከበራል_ቢሉ_?
1.የሊቀ መላእክት ቅዱስ ሚካኤል #ሲመቱ ወይም የ #ተሾመበት ዕለት ነው።
2.በስሙ የታነጸ ቤተ ክርስቲያን የከበረበት #ቅዳሴ_ቤቱ ነው።
3. ቅድስት #አፎምያ ዝክሩን የምትዘክር ወዳጁን ከሳጥናኤል ያዳነበት ዕለት ነው።
4.ምስኪኑ ታዛዡ ልጅ የኃለኛ ስሙ #ባህራን በጎረቤቱ ባለጸጋው ምክንያት የታወጀበት የሞት ደብዳቤ ለውጦ ያዳነው ዕለትም ነው።
ከዚህ በተጨማሪ ይህ ሰኔ 12 ጻድቁ የኢትዮጵያ ንጉስ ላሊበላ ዕረፍቱም ነው።
ካልታሰበ መከራ ይሰውረን አሜን።
