en
Feedback
VGM Ethio

VGM Ethio

Open in Telegram

ስኬታማ ሰዎች አጋጣሚዎችን አይጠብቁም፣ አጋጣሚዎችን እራሳቸው ይፈጥራሉ እንጂ!

Show more
1 686
Subscribers
No data24 hours
-87 days
-5030 days
Posts Archive
sticker.webp0.03 KB

ይድረስ፡ ለኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤ/ክርስቲያን ሲኖዶስ ጽ/ቤት የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤ/ክርስቲያን የምትከበር አንጋፋ የሃይማኖት ተቋም ናት። ቤተ ክርስቲያኗ በሀገሪቱ በሚከሰቱ አበይት ጉዳዮች ላይ ተደጋጋሚ መግለጫ እንደምታወጣ ይታወቃል። ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በቤተ ክርስቲያኒቷ ውስጥ በሃይማኖት ማኅበር፣ በዲያቆንነትና ሰባኪነት እውቅና የተሰጣቸው ድርጅቶችና ግለሰቦች የሙስሊሙን ማኅበረሰብ ተቋማት ለማፈራረስና የሙስሊሙን አንድነት ለመክፈል በይፋ በተቀናጀ መልኩ እየተንቀሳቀሱ መኾኑ እየታየ ነው። በእርግጥ ድርጊቱ በኢሕአዴግም ዘመን በቤተ ክርስቲያኒቷ አካላት ለረዥም ጊዜያት በድብቅ ሲፈጸም መቆየቱ ይታወቃል። ነገር ግን ቤተ ክርስቲያኒቷ በስሯ ያቀፈቻቸውን እነዚህን ማኅበራትና ግለሰቦች የማውገዝም ሆነ ከድርጊታቸው እንዲቆጠቡ የማድረግ ሥራ እየሠራች አይደለም። የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤ/ክርስቲያን እነዚህን በሰው ሃይማኖት ውስጥ ገብተው ድንበር ዘለል እንቅስቃሴ የሚያደርጉ ማኅበራት፣ ዲያቆናትና ሰባኪዎችን በይፋ የማታወግዝ ከኾነ፣ ሙስሊሙ ማኅበረሰብ በተጠቀሱት አካላት እየተሞከረ ያለውን የሙስሊሙን ሃይማኖታዊ ተቋማት የማፈራረስና የሙስሊሙን አንድነት የመክፈል በታሪክ ያልታየ አሳፋሪ ሙከራ የቤተ ክርስቲያኗም ይፋዊ አቋምና አላማ አድርጎ እንደሚገነዘበው ሊታወቅ ይገባል። በመኾኑም የቤ/ክርስቲያኒቷ ሲኖዶስ ጽ/ቤት የተጠቀሱተን አካላት በማውገዝ ከድርጊታቸው በማስቆም ኃላፊነቱን ዛሬውኑ ሊወጣ ይገባል። ከሰላምታ ጋር Akmel Negash

sticker.webp0.03 KB

‹‹…አንተ ሙስሊሙ ይሉኝታ ቀፍድዶህ በተቋምህ መጅሊስ ጉዳይ ባይተዋር ሆነህ ስትሽኮረመም ፡ እነሱ በአንተ ተቋም ይራኮታሉ። “የማህበረ ቅዱሳንና የሞዐ ተዋሕዶ ዲያቆናት ፣አባላትና ደጋፊዎች የመጅሊስ የበላይ ጠባቂ ሆኑ እንዴ? ወይስ ሳናውቀው መጅሊስ ለነርሱ ተላልፎ ተሸጠ ወይ?” ብለህ ልትገረም ሁሉ ትችላለህ!...›› አውነትም ያስገርማል! በሃይማኖታቸው ሳይሆን በሰው ሃይማኖት መልካምና የተሻለ ነገርን ከመመኘት በዘለለ ጣልቃ በመግባት ለሕዝበ ሙስሊሙ ሳይሆን ለራሳቸው ማን እንደሚጠቅማቸው ስሌት በመስራት «ሙፍቲን እንደግፍ» ብለው በኮሚቴ ደረጃ ተዋቅረውና ተናበው እየሠሩ ያሉ አካላት ፍላጎታቸው ከምን አስተሳሰብ እንደመነጨ ይገባኛል። ፍላጎታቸው ከሃይማኖት ስለሚዘል «ጥቅማችንና ፍላጎታችን ያለበት ጉዳይ ሁሉ ጉዳያችን ነው» በሚል መርህ የሚመሩ፣ «ድንበራችን ጥቅማችን ያለበት ድረስ ነው» በሚል አተያይ የተቀረጹ ቡድኖች ናቸው። በሙስሊሙ መጠቀሚያነት ማራመድ የሚሹት ፖለቲካዊ ዓላማ እውን የሚሆነው ደካማ፣ ልፍስፍስና ሽባ መጅሊስ ሲኖር ነው። ይህን ፍላጎታቸው እውን እንዲሆን አውቆም ይሁን ሳይገባው በመጅሊስ መጠናከር ላይ እንቅፋት የሆነን አካል ባላቸው ስልጣን፣ በሚዲያና በተለያዩ መልኮች ይደግፋሉ። ሙፍቲም በመጅሊስ ጉዳይ «ከጎናችን ቁሙ» ብለው ለክርስቲያኖች ጭምር ጥሪ ማድረጋቸው «ጥሪ ቀርቦልናል።» በሚል በግልጽ የችግሩ አካል ሆነው ለመቆም የተመቻቸው ይመስላል። ከፊሎቹ ሚዲያዎች ደግሞ በጉጉት ሲጠብቁትና ሲመኙት የነበረውን ፍላጎታቸውን በአንድን ሰው ንግግር ብቻ ተመሥርተው «መጅሊስ ለሁለት ተከፈለ» ብለው ዜና ያውጁልሃል። ሌሎቹ ደግሞ እነርሱ በብሄር ፖለቲካ ፍልሚያ በገቡበት አጣብቂኝ ውስጥ ሆነው እየተሳደዱም እንኳ የመጅሊስን ጉዳይ ሳይዘነጉ ለሚፈልጉት አካል ድምጽ ሲሆኑ ታያቸዋለህ። ለዚህ አጥፊ ትግላቸው አጋዥ የሆኑ ደጋፊ ሙስሊሞችን ለማሰባሰብ ሲፍጨረጨሩም ታያቸዋለህ። አንተ በእነርሱ መርሆች ተመርተህ በቤተ ክርሲያኒቱና በሲኖዶሱ ጉዳይ ጣልቃ በመግባት አንዱን ወገን በመደገፍ እንቅልፍ አጥተህ ጠዋት ማታ አጀንዳውን ብታራግብ ሌላውን ተውና ዛሬ ገለልተኛ መስለው በዝምታ ያለፉት ታዋቂ ሰዎችና ሚዲያዎች እንኳ በምን መልኩ ምላሽ ሊሰጡህ እንደሚችሉ አስበው እስቲ? @አህመዲን ጀበል

sticker.webp0.03 KB

ሙፍቲን ስሟቸው ኢኃዴግ 2005 ላይ ሙስሊሙን ከፊሉን አስሮ፣ ከፊሉን ከሀገር አባሮ እሱ ሚፈልጋቸውን የማይገዳደሩትን ጠምጣሚ ካድሬዎች የሰየመበትን የመጅሊስ ምርጫ ሙፍቲ ፍትሐዊና ሁሉንም ያካተተ ነው ሲሉ ነበር የገለፁት https://t.me/Zelebet

sticker.webp0.03 KB

ለእስልምና የተከፈሐ ውድ ዋጋ እስልምና በተደላደለ መንገድ እንዲሁ በቀላሉ እዚህ አልደረሰም። ይልቁኑም እጅግ ውድ ዋጋ ተከፍሎበታል፣ ሙስሊሞች ዘግናኝ ግፍ አስተናግደዋል። ይህንን በጥቂቱም ቢሆን የሚያሳይ የአንድ ሶሐባ ታሪክ ላንሳ። ኸባብ ኢብን አል-ዐረት ረዐ ኸባብ (ረዐ) አንጥረኛ ሲሆን ኡሙ አንማር የምትባል፣ መካ ውስጥ የምትኖር፣ የኹዛዕ ጎሳ አባል የሆነች ሴት ባሪያዋ ነበር። እስልምናን እንደተቀበለ እና ነብዩም ”ﷺ” ጓደኛ እንዳደረጉት ስታውቅ ታሰቃየው ጀመር። ድንጋይ አሊያም ብረት በእሳት እያጋለች እራቁት እንዲሆን አስደርጋው፤ ገላውን ትተኩሰው ነበር። አንድ ዕለትም በጋለ ብረት ግምባሩን ክፉኛ ተኮሰችው። ኸባብም የደረሰበትን በደል ለረሱል ”ﷺ” ነገራቸው። ነብዩም ”ﷺ” አላህ ሆይ! "ኸባብን እርዳው" ብለው ዱዓ አደረጉለት። ብዙም ሳይርቅ ኡሙ አንማር እራሷን ያማት ጀመር። ህመሙ እጅግ ሲበረታባት እንደ ውሻ ትጮኽ ነበር። ሐኪሞች ጋር ስትሄድ፤ ህመሟን ለማስታገስ ጭንቅላቷን በእሳት እንድትተኩስ መከሯት። በዚህ ጊዜ በጋለ ብረት እና ድንጋይ ገላውን እየተኮሰች የምታሰቃየውን ኸባብን (ረዐ) ጭንቅላቷን እንዲተኩሳት ጠየቀችው። እሷ እንደተኮሰችው ሁሉ እሱም ይተኩሳት ጀመር። ዑመር ኢብን አል-ኸጣብ (ረዐ) ኸሊፊ በነበሩበት ወቅት ኸባብን (ረዐ) በመስለሙ ምክንያት የደረሰበትን ግፍ ሲጠይቁት። ቀሚሱን ገልቦ ጀርባውን አሳያቸው። ዑመር ባዩት ነገር እጅግ ደነገጡ። "ከዚህ በፊት እንዲህ ዓይነት ግፍ የተፈፀመበት ጀርባ አይቼ አላውቅም" አሉ። "አሚሩል ሙዕሚኑን ሆይ! የመካ ከሀዲያን ፍም እሳት ላይ በጀርባዬ ያስተኙኛል። ከዛም በእግራቸው ደረቴን ይረግጡኛል። እሳቱ የሚጠፋው ከአካሌ በሚፈሰው ፈሳሽ ምክንያት ነበር" አላቸው። ልክ እንደትላንቱ ሁሉ በታሪክ ሂደት ውስጥ እስልምናን የሚቀበሉ ሰዎችም ሆኑ ቀድሞውኑ ሙስሊም የነበሩ ሰዎች ላይ የኢስላም ጠላቶች ሰቅጣጭ ግፍ ፈፅመውባቸዋል። ዛሬ ስንቶቻችን ይህንን ውድ ዋጋ ለእስልምና ለመክፈል ዝግጁዎች ነን? https://t.me/Zelebet

photo content

sticker.webp0.03 KB

«እኔ ስልጣን አልፈልግም» እያሉ በተለያዩ አጋጣሚዎች የሚናገሩት ሐጅ ዑመር እድሪስ ተስማምተው ለፈረሙበት ቃላቸው ጭምር የማይታመኑ፣ ሕግና መመሪያን ሲጥሱ ጭራሽ ማፈርም ሆነ መሳቀቅ የማያውቁ፣ የመጅሊስን ችግር በመነጋገርና በሽምግልና ለመፍታት ስድስት የተለያዩ የሽማግሌ ቡድኖች ተቋቁመው ሁሉንም ሙከራ አድረገው በርሳቸው አምብተኝነት የከሸፉ ናቸው። በእስቴ መስጊዶች ሲቃጠሉ ዝምታን መርጠው፣በቢቸና መሰጊድ ላይ ቦንብ ተወርዉሮ ሙስሊሞች ሲገደሉ ባለየ አልፈው፣በሞጣ ሙስሊሞች ላይ ሽብር ሲፈጸም ድምጻቸውን አጥፍተው፣ነጃሺ መስጊድ ሲጠቃ በተአቅቦ አልፈው፣በወሎ ያሁሉ የሱፊያ ሀሪማ ሲወድም ሱፍይነት ትዝ ብሏቸው እንድረስላቸው ሳይሉ፣ ሰበጎንደር ሙስሊሞች ሲገደሉና የሽብር ጥቃት ሲፈፀምባቸው እንደመሪ ተቆጥተው ፍትህ መጠየቅ ሲገባቸው «የጎዳና ላይ ኢፍጣር በእስልምና የለም» ብለው ለከሳሾቸ ዋቢ ምስክር የሆኑት ሰው፣ የመጅሊስ ጠቅላላ ጉባኤ ከመሪነት አንስቶ በፈትዋ ዘርፍ ሲመድባቸው ለኢስላምና ለሙስሊሞች መብት ተቆርቁረው ለመናገር ምላሳቸውን የያዛቸው በስልጣኔ መጡ ስሜት ተሞልተው «ተነሱ።ለትግል ተዘጋጁ።» ብለው ወደ ደም መፋሰስ ሀጂ ዑመር የቀሰቀሱት «አላህ ሽቶባቸው ነው እንጂ ለስልጣን ብለው እይደለም እኮ።» ብሎ የሚያስብ የዋህ አይጠፋም። ያም ሆኖ ተቋሙ የሕዝበ ሙስሊሙ እንጂ የእርሳቸው የግል ርስት ስላልሆነ የመጅሊስ ጠቅላላ ጉባኤ በድምጽ ብልጫ እሳቸውና ሌሎች 3 ዑለሞች ወደፈትዋ ክፍል እንዲዛወሩ ውሳኔ አሳለፈ። ይህንን የወሰኑት ዑለሞች ናቸው። ሙፍቲ ይህን ሁሉ ሲያደርጉ የቆዩት በሕግም በሸሪዓውም የሌሎችን ዑለሞች የአብላጫ ውሳኔ የመሻር ቬቶ ስላላቸው ሳይሆን በተግባር ለአንድነት እየተባለ እየታለፉ፣ በተጨማሪም እርሳቸውን "አይዞህ" በሚላቸው ስውር አካል እየተደገፉ ነው ያሻቸውን ሲፈጽሙ የቆዩት። በተደጋጋሚ መመሪያ ተጥሷል። ስምምነት ተሽሯል። እርሳቸው የሚፈልጉት ካልሆነ እንደማይስማሙ እየታወቀ በስምምነት እንጂ በድምጽ ብልጫ አትወስኑ እየተባለላቸው የህዝበ ሙስሊሙ መብትና ጥቅም ላይ እንዲረማመዱ ተፈቅዶላቸዋል። እርሳቸው አሁንም ከሕግም ከመመሪያም በላይ ሆነው ለመቀጠልና «ደም ይፈሳታል እንጂ» እንዳሉት ሁሉ ሙስሊሞችን ለማበጣበጥና ደም ለማፋሰስ ጥረታቸውን ቀጥለዋል። ይህ ግን በዝምታ ሊታይ አይገባም። ኢትዮጵያውያን ሙስሊሞች የእነርሱ የሆነና ለእነርሱ የቆመ፣ በሕግ የበላይነት የሚመራ ጠንኳራ ተቋም ባለቤት የመሆን መብታቸውን በተግባር መጎናጸፍ ከፈለጉ ጠንክረው መቆም አለባቸው። የየትኛውንም ግለሰብ ማስፈራሪያ በመስማት ከህግ የበላይነት ይልቅ ግለሰቦችን ኡሹሩሩ ማለት መቆም አለበት። ይህን እሹሩሩ ሳያቆሙ የታሰበው የሕዝበ ሙስሊሙ ተቋም ፈጽሞ እውን ሊሆን አይችልም።

«አላህ ሽቶብኝ ነው እንጂ እኔ ስልጣን አልፈልግም።» ❄❄❄❄❄❄❄❄❄❄❄❄❄❄❄ ሙፍቲ ሐጅ ዑመር እድሪስ አልፎ አልፎ ሚዲያ ባለበት ሕዝባዊ ስብሰባዎችም ሆነ መግለጫ ላይ ከሚያነሷቸው ነጥቦች አንዱ ስልጣንና ዱንያዊ ጥቅማ ጥቅምን እንደማይፈልጉ የሚገልጹባቸው ቃላቶች ይገኙባቸዋል። የዱንያዊው ጥቅም ጉዳይ ለጊዜው በይደር ይቆየኝና ስልጣን እንደማይፈልጉ ከሚገልጹባቸው መካከል «አላህ ሽቶብኝ ነው እንጂ እኔ ስልጣን አልፈልግም» ከሚለው ጋር በተያያዘ ጥቂት ልበል። በቅርበት የማያውቃቸው ሰው "ታዲያ ስልጣን የማይፈልጉ ከሆነ የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት (መጅሊስ) በይፋ ከተመሠረተበት እስከ ዛሬ (ከመጋቢት 4 ቀን 1968 እስከ 2014 ግንቦት) መንግስታት ሲቀያየሩ ጭምር ቦታ እየቀያየሩና እየተመሳሰሉ እንዴት መጅሊስ ዉስጥ ለ46 ዓመታት በስልጣን ላይ መቆየት ቻሉ?" የሚል ጥያቄ በአዕምሮው ሊያጭርበት ይችላል። ሙፍቲ የመጅሊስ ምርጫ ጉዳይ ሲነሳ ምርጫ ከተደረገ ከስልጣን እንደሚለቁ ስለሚያውቁ አጀንዳውን ለማዳፈን በተደጋጋሚ የሚያቀርቡት ማስፈራሪያ ከመጅሊስ ስልጣን ከተነሱ «መጅሊስ ለሁለት ይከፈላል» የሚለው ዛቻ ነው። ለሁለት ሲከፈል እሳቸው የአንዱ ክፋይ መሪ ሆነው እንዲቀጥሉ ሲባል ማለት ነው። መጀመሪያ ዑለሞችና የቦርድ አባላት ሲመረጡ የመጅሊስ ፕሬዝዳንት ሆነው ተመረጡ። ለስድስት ወራት በተባለው የሽግግር ጊዜ የተሰጣቸውን ኃላፊነት በአግባቡ ሳይወጡ 3 ዓመት አለፋቸው። ቆይተው ደግሞ በግልጽና በይፋ የተሰጠ ኃላፊነት ሆኖ ሳለ አንዴ «ስድስት ወር ብሎ ነገር የለም። ቋሚ ነን»፣ ሌላ ጊዜ ደግሞ «እንደ ፓትሪያርኩ አንዴ ተመርጫለሁ እስከ ሕይወት ፍጻሜ ድረስ አልወርድም» ማለት ጀመሩ። በኢትዮጵያ ሙስሊሞች ተቋማዊ ለውጥ የጋራ ኮሚቴ ሥር የመጅሊስ መተዳደሪያ ደንብን እንዲያዘጋጅ ተሰይሞ የነበረው የነበረው ኮሚቴ መተዳደሪያ ደንቡን ለዋናው ኮሚቴው ሲያቀርብ የሚመረጠው ዋና ሙፍቲ በንቃት ሕዝበ ሙስሊሙን ለማገልገል እንዲችል «እድሜው ከ40 ያላነሰና ከሰማንያ ያልበለጠ» የሚለው ነጥብ ሲጠቀስ ከሐጅ ዑመር ተቃውሞ ገጠመው። «ከሰማንያ ያልበለጠ የሚለው የእድሜ ገደቡ ይነሳ» አሉ። ይህም ስልጣናቸውን ለማስጠበቅ መሆኑ ግልጽ ነው። ቀጥሎም ሌላኛው መስፈርት «ዐረብኛ ቋንቋ መናገር፣ መጻፍና ማንበብ መቻል አለበት» የሚለው ነጥብ ጋር ሲደረስም «የሀገራችን ብዙ ዑለሞች ዐረብኛ መናገር ስለማይችሉ የዐረብኛ ቋንቋ መስፈርቱ ይቅር» ብለው ተቃወሙ። በኋላ ስረዳ እሳቸው «ይህ መስፈርት እኔ እንዳልመረጥ ሆነ ብላችሁ ያስገባችሁት ነው» ብለው መተዳደሪያ ደንቡን በአሉታዊ ጎኑ ማየት መጀመራቸውን ተረዳሁ። ለስድስት ወራት ከ26 ዑለማና ቦርድ ጋር የጊዜያዊ መጅሊስ ፕሬዝዳንት ሆነው ሲሾሙም አንዱ በጊዜው እንዲሰሩ በይፋ የተቀመጠው በባለሞያዎች የተዘጋጀው ረቂቅ መተዳደሪያ ደንብ ላይ ተጨማሪ ዉይይት በማድረግ ማፅደቅ ቢሆንም ባለፉት 3 ዓመታት አንዴ እንኳን ዞር ተብሎ ሳይታይ ያ መተዳደሪያ ደንብ ተትቶ ሌላ ተዘጋጅቶ በቅርብ ጊዜ ለውይይት ቀረበ።በእርሳቸው መሪነትም ዉይይት ተደረገበት።በመጨረሻም በአብላጫ ድምፅ ጸደቀ። መጅሊስ በ1968 ሲመሠረት በመተዳደሪያ ደንቡ ምርጫ እንደሚደረግ በግልጽ እንደሚደነግግ የሚያውቁና መተዳደሪያ ደንቡ ላይ የፈረሙ፣ በተደጋጋሚ ጊዜም በመጅሊስ ምርጫ ላይ የተሳተፉ ነበሩ። ሌላው ቀርቶ በ2005 ሕዝበ ሙስሊሙ በፌደራል ጉዳይ አማካኝነት በየቀበሌ ተደረገ በተባለው ምርጫ እንኳን በመራጭም ሆነ በተመራጭነት የተሳተፉ ነበሩ። ሆኖም እርሳቸው ለጊዜያዊነት ተብሎ ለስድስት ወር የመጅሊስ ፕሬዝዳንት ሲሆኑ ከቦታው ላለመነሳት አንዴ «በእስልምና ምርጫ የለም» ሲሉ፣ ሌላ ጊዜ ደግሞ «የክርስቲያኖች ፓትሪያርክ አንዴ ከተመረጠ በሕይወት እስካለ ሌላ ምርጫ አይደረግም። የኛም እንደዚህ ቢሆን ጥሩ ነው» የሚል ሐሳብ አመጡ። ይህም ተቀባይነት ሲያጣ በሕዝባዊ ምርጫ እሳቸው መሪ ሆነው እንደማይመረጡ ሲረዱ «ዑለማ ዑለማን ይመርጣል እንጂ ሕዝቡ ምርጫው አይመለከተውም፞። የሚመርጡትን ዑለሞች ደግሞ እኛ እንመርጣቸዋለን። የመረጥናቸው ዑለሞች ደግሞ መሪዎቻቸውን ይመርጣሉ» የሚል አቋም አራመዱ። ሐጅ ዑመር እድሪስ ከ1968 እስከ 1985 ለ18 ዓመታትም የመጅሊስ ጠቅላላ ጉባኤ አባል፣ ከ1985-1986 ድረስ የመጅሊስ ሊቀመንበር (ፕሬዝዳንት) አማካሪ ሆነው አገለገሉ። በየካቲት 14 ቀን 1987 በአንዋር መስጂድ ግርግርና በመንግስት ጥቃት 10 ሙስሊሞች በመንግስት የጸጥታ አካላት ከተገደሉ በኋላ ሕዝቡን እንዲያረጋጉና የኢድ ሰላት አስተባባሪ ኮሚቴ አባል እንዲሆኑ ተደረገ። በ1988 ከቢሾፍቱ ከተማ መንግስት ለርሱ ቅርብ የሆኑ ሰዎችን ሰብስቦ የመጅሊስ አመራር ሲመርጥ ሐጅ ዑመር እድሪስም በድጋሚ የመጅሊስ ጠቅላላ ጉባኤና የዑለማ ምክር ቤት አባል ሆነው ተመረጡ። እስከ 1992 ድረስም በዚያው ቆዩ። ከ1993 እስከ ሚያዚያ 2001 የአዲስ አበባ መጅሊስ ፕሬዝዳንት፣ ከሚያዚያ 2001 እስከ መስከረም 2005 የፌደራል መጅሊስ መስጊድና አውቃፍ ዘርፍ ኃላፊ፣ ከ2005 እስከ 2010 የፌደራል መጅሊስ የጠቅላላ ጉባኤው አባል፣ የመስጊድና አውቃፍ ዘርፍ ኃላፊ፣ እንዲሁም የዑለማ ምክር ቤት አባል ሆነው ቆዩ። ጠቅላይ ሚኒስተር ዶ/ር አብይ ወደ ስልጣን ሲመጡ ህዝበ ሙስሊሙና የመፍትሄ አፈላላጊ ኮሚቴው በመጅሊስ ጉዳይ ጥያቄ ሲያቀርብ መጀሊስን በመወከል ከጠቅላይ ሚ/ሩ ጋር ከቀረቡት መካከል ነበሩ። ከ2010 ሰኔ 26 እስከ ሚያዚያ 23 2011 ድረስ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር አብይ አህመድ ባቋቋሙት የኢትዮጵያ ሙስሊሞች ተቋማዊ ለውጥ የጋራ ኮሚቴ ላይ በጠቅላይ ሚኒስትሩ ሰብሳቢ ተደርገው ተሾሙ። በሚያዚያ 23/2011 የጊዜያዊ መጅሊስ ፕሬዝዳንት ተደርገው ለ6 ወራት ተሹመው በሕገ ወጥ መንገድ ከ3 ዓመታት በላይ ቆዩ። ከሰሞኑ ደግሞ የመጅሊስ ጠቅላላ ጉባኤ ሐጅ ዑመር እድሪስንና ምክትላቸውን ዶ/ር ጄይላንን ጨምሮ አራት ዑለሞችን ከአመራርነት አንስቶ ወደ ፈትዋ ዘርፍ መደባቸው። ተቋሙ ከተመሠረተ ጀምሮ ላለፉት 46 ዓመታት በተለያዩ ኃላፊነቶች በአመራር ወንበር ላይ የነበሩት ግለሰብ ተቋሙ በዚህ ሁሉ ዘመኑ ለሕዝበ ሙስሊሙ ተገቢውን አገልግሎት ባለመስጠቱ ይቅርታ ጠይቀው በራሳቸው ፈቃድ ሊሰናበቱ ይገባቸው ነበር። ዕድሜያቸው 90 ሞልቷል። በፈትዋ ክፍል በሙፍቲነት እንዲያገለግሉ ሲወሰን በእምቢተኝነት ሕዝበ ሙስሊሙን ወደ መክፈል ድረስ የሚያደርሰው የስልጣን ፍቅር እንዴት ስር ቢሰድ ነው አቅል እስከ ማሳት የሚያደርሰው? ከ3 ሳምንታት በፊት የተለያዩ የሕብረተሰብ ክፍሎች የመንግስታዊ ተቋማት ሪፎርምን እንዲገበኙ ተሰናድቶ በነበረው ጉብኝት ማጠናቀቂያ በጠቅላይ ሚኒስትር ጽ/ቤት ጠቅላይ ሚኒስትሩ በመሩት ስብሰባ ላይ 120 የምንሆን ሙስሊሞች ተገኝተን ነበር። ስለመጅሊስ ምርጫ አጀንዳ ሲነሳ ግን በተለያዩ መድረኮች «አላህ ሽቶብኝ ነው እንጂ እኔ ስልጣን አልፈልግም» ያሉትን ንግግር ተቃርነው ዛቻ ጀመሩ። ያው በተለመደው የሱፊያ ካባ ስር ሆነው «ደም ይፈሳታል እንጂ አልለቅም» ሲሉ በግልጽ ተናገሩ። ኢናሊላሂ ወኢናኢለይሂ ራጂኡን!

photo content
+2

sticker.webp0.03 KB

photo content

sticker.webp0.03 KB

ሙፍቲ እንዴት ከሀላፊነቴ እነሳለሁ? ወንዱም ሴቱም፣ ሙስሊሙም ክርስቲያኑም፣ መንግስትም ሁሉም ተባብሮ ወደ ስልጣኔ ሊመልሰኝ ይገባል። እያሉ ነው። ያሁሉ መስጂድ በፅንፈኞች ሲቃጠል በአግባቡ ያላወገዙት ሙፍቲ ዛሬ ከስልጣን መነሳታቸው የዲን መደፈር አድርገውት "ሙስሊሞች ተነሱ! ለዲናችሁ ታገሉ" የሚል ጥሪ አቅርበዋል። ይህ ጥሪ የሚያስፈልገው የነበረው እሳቸው ከስልጣን ሲወርዱ ወይስ መስጂድ ሲቃጠል፣ ቁርዓን ሲረገጥ? https://t.me/Zelebet

sticker.webp0.03 KB

photo content

sticker.webp0.03 KB