en
Feedback
Debtera Media

Debtera Media

Open in Telegram

ደብተራ ሚዲያ የእውነት ድምጽ! ሰብስክራይብ በማድረግ ቤተሰብ ይሁኑ!👇 በዩቲዩብ 👉 https://bit.ly/3bMfT8D በፌስቡክ 👉 fb.me/DebteraMedia በቴሌግራም 👉 t.me/DebteraMedia ማንኛውንም ሃሳብ አስተያየት ሆነ መረጃ በ t.me/DebteraMedia_Bot ማድረስ ትችላላችሁ።

Show more
3 634
Subscribers
-324 hours
-117 days
-5830 days

Data loading in progress...

Tags Cloud
No data
Any problems? Please refresh the page or contact our support manager.
Incoming and Outgoing Mentions
---
---
---
---
---
---
Attracting Subscribers
September '26
September '26
+7
in 0 channels
August '26
+24
in 0 channels
Get PRO
July '26
+32
in 1 channels
Get PRO
June '26
+21
in 0 channels
Get PRO
May '26
+19
in 0 channels
Get PRO
April '26
+14
in 0 channels
Get PRO
March '26
+9
in 1 channels
Get PRO
February '26
+16
in 0 channels
Get PRO
January '26
+22
in 0 channels
Get PRO
December '25
+15
in 0 channels
Get PRO
November '25
+19
in 0 channels
Get PRO
October '25
+24
in 0 channels
Get PRO
September '25
+10
in 0 channels
Get PRO
August '25
+16
in 0 channels
Get PRO
July '25
+21
in 0 channels
Get PRO
June '25
+17
in 0 channels
Get PRO
May '25
+24
in 0 channels
Get PRO
April '25
+30
in 0 channels
Get PRO
March '25
+42
in 0 channels
Get PRO
February '25
+20
in 0 channels
Get PRO
January '25
+35
in 0 channels
Get PRO
December '24
+32
in 0 channels
Get PRO
November '24
+18
in 0 channels
Get PRO
October '24
+21
in 0 channels
Get PRO
September '24
+14
in 0 channels
Get PRO
August '24
+11
in 0 channels
Get PRO
July '24
+26
in 0 channels
Get PRO
June '24
+16
in 0 channels
Get PRO
May '24
+15
in 0 channels
Get PRO
April '24
+25
in 0 channels
Get PRO
March '24
+26
in 0 channels
Get PRO
February '24
+15
in 0 channels
Get PRO
January '24
+32
in 1 channels
Get PRO
December '23
+68
in 4 channels
Get PRO
November '23
+13
in 0 channels
Get PRO
October '23
+9
in 0 channels
Get PRO
September '23
+17
in 0 channels
Get PRO
August '23
+28
in 0 channels
Get PRO
July '23
+27
in 0 channels
Get PRO
June '23
+81
in 0 channels
Get PRO
May '23
+32
in 0 channels
Get PRO
April '23
+49
in 0 channels
Get PRO
March '23
+28
in 0 channels
Get PRO
February '23
+802
in 0 channels
Get PRO
January '23
+1 371
in 0 channels
Get PRO
December '22
+111
in 0 channels
Get PRO
November '22
+280
in 0 channels
Get PRO
October '22
+17
in 0 channels
Get PRO
September '22
+212
in 0 channels
Get PRO
August '22
+159
in 0 channels
Get PRO
July '22
+49
in 0 channels
Get PRO
June '22
+523
in 0 channels
Get PRO
May '22
+1 661
in 0 channels
Get PRO
April '22
+2 256
in 0 channels
Get PRO
March '22
+177
in 0 channels
Get PRO
February '22
+399
in 0 channels
Get PRO
January '22
+537
in 0 channels
Get PRO
December '21
+17
in 0 channels
Get PRO
November '21
+20
in 0 channels
Get PRO
October '21
+120
in 0 channels
Get PRO
September '21
+48
in 0 channels
Get PRO
August '21
+64
in 0 channels
Get PRO
July '21
+75
in 0 channels
Get PRO
June '21
+86
in 0 channels
Get PRO
May '21
+50
in 0 channels
Get PRO
April '21
+78
in 0 channels
Get PRO
March '21
+139
in 0 channels
Get PRO
February '21
+128
in 0 channels
Get PRO
January '21
+186
in 0 channels
Get PRO
December '20
+6 831
in 0 channels
Date
Subscriber Growth
Mentions
Channels
07 September+1
06 September0
05 September0
04 September+1
03 September+2
02 September+1
01 September+2
Channel Posts
photo content
+1

2
[ ስንክሳር ጳጉሜ - ፪ - ] .mp3
76
3
🕊 [  † እንኳን ለቅዱስ ቲቶ ሐዋርያ ዓመታዊ የዕረፍት በዓል በሰላም አደረሳችሁ ፤ አደረሰን። †  ] † በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን! † [  🕊  †   ቅዱስ ቲቶ ሐዋርያ   †   🕊  ] † የጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ደቀ መዝሙር ቅዱስ ቲቶ ከሰባ ሁለቱ አርድእት አንዱ ሲሆን በተወሰነ መንገድም ቢሆን የተዘነጋ ሐዋርያ አይደለም:: በተለይ ደግሞ ቅዱስ ጳውሎስ ከጻፋቸው አሥራ አራት መልእክታት መካከል አንዷ የተላከችው ለዚህ ቅዱስ በመሆኗ ታሪኩ እንኳ ባይነገር ስሙ አይረሳም:: ቅዱስ ጳውሎስም በመልዕክታቱ በጐ ስሙን እየደጋገመ ያነሳዋል:: ለመሆኑ ሐዋርያው ቅዱስ ቲቶ ማን ነው? ቅዱስ ቲቶ የተወለደው በ፩ ኛው መቶ ክ/ዘመን እስያ ውስጥ: ቀርጤስ በምትባል ከተማ ነው:: የዘር ሐረጉ ከእሥራኤልም: ከጽርእም [ግሪክ ለማለት ነው::] ይወለዳል:: አካባቢው አምልኮተ እግዚአብሔር የጠፋበት ስለሆነ እሱም: ቤተሰቦቹም የሚያመልኩት ከዋክብትን ነበር:: መዳን በእውቀት ይመስላቸው ስለ ነበር የአካባቢው ሰዎች የግሪክን ፍልስፍና ጠንክረው ይማሩ ነበር:: ቅዱስ ቲቶም በወጣትነቱ ወደ ት/ቤት ገብቶ የግሪክን ፍልሥፍናና የዮናናውያንን ጥበበ ሥጋ ተማረ:: በጥቂት ጊዜም የሁሉ የበላይ ሆነ:: ቅዱሱ በወቅቱ ምንም እውነተኛውን ፈጣሪ አያምልክ እንጂ በጠባዩ እጅግ ቅንና ደግ ነበር:: ምክንያቱን ሳያውቀው ለእኔ ቢጤዎች ያበላ: ያጠጣ: ይንከባከባቸውም ነበር:: እግዚአብሔር ግን የዚህ ቅን ሰው በጐነቱ እንዲሁ እንዲቀር አልወደደምና አንድ ቀን በራዕይ ተገለጠለት:: በራዕይም አንድ ምንነቱን ያልተረዳው ነገር "ቲቶ ሆይ! ስለ ነፍስህ ድኅነት ተጋደል:: ይህ ዓለም ኃላፊ ነው::" ሲለው ሰማ:: ከእንቅልፉ ነቅቶ በእጅጉ ደነገጠ:: የሚያደርገውንም አጣ:: ያናገራቸው ሁሉ ምንም ሊገባቸው አልቻለም:: ለተወሰነ ጊዜም ለጉዳዩ ምላሽ ሳያገኝለት በልቡ እየተመላለሰ ኖረ:: ድንገት ግን በዚያ ሰሞን ከወደ ኢየሩሳሌም አዲስ ዜና ተሰማ:: "ክርስቶስ የሚሉት ኢየሱስ: እርሱም የባሕርይ አምላክ የሆነ ወደ ምድር ወርዶ: ስለ እግዚአብሔር መንግስትም እየሰበከ ነው::" ሲሉ ለቲቶ ነገሩት:: "ሌላስ ምን አያችሁ?" አላቸው:: "በእጆቹ ድውያን ይፈወሳሉ:: ሙታን ይነሳሉ:: እውራን ያያሉ:: ለምጻሞች ይነጻሉ:: ሌሎች ብዙ ተአምራትም እየተደረጉ ነው::" አሉት:: የወቅቱ የሃገረ አክራጥስ መኮንን ፈላስፋ ነበርና ስለ ክርስቶስ ሲሰማ ሊመራመር ወደደ:: እርሱ መሔድ ስላልተቻለው "ብልህ ጥበበኛ ሰው ፈልጉልኝ::" ብሎ ተከታዮችን ቢልካቸው ከቲቶ የተሻለ በአካባቢው አልነበረምና እርሱኑ አመጡት:: መኮንኑ ቲቶን "ነገሩ ትክክል ወይም ስሕተት መሆኑን በጥልቅ መርምረህ ምላሽ አምጣልኝ::" ብሎ ላከው:: ቅዱስ ቲቶም ፈጥኖ ተነስቶ ወደ ኢየሩሳሌም ገሰገሰ:: ወደ ከተማዋ እንደገባም ጌታችንን አፈላልጐ አገኘው:: ፩.ጌታችን ክርስቶስ በሥልጣነ ቃሉ ደዌያትን ሲያርቅ: አጋንንትን ሲያሳድዳቸው ተመልክቶ ይህ ሥራ የፍጡር እንዳልሆነ ተረዳ:: ፪.ጌታችን የሚያስተምረው ትምሕርት ከግሪክ ፍልሥፍና እጅግ ርቆና መጥቆ አገኘው:: የግሪክ ፍልሥፍና መነሻውም ሆነ መድረሻው ሥጋዊ ነው:: ጌታ ግን በጣዕመ ቃሉ የሚያስተምረው ሰማያዊ: በዚያ ላይ ዘላለማዊ የሆነ ትምሕርት ነው:: በራዕይ "ስለ ነፍስህ ተጋደል::" ያለው ምሥጢር አሁን ተተረጐመለት:: በዚህ ምክንያትም ጊዜ አላጠፋም:: ወዲያውኑ አምኖ ተከታዩ ሆነ:: ጌታም ከሰባ ሁለቱ አርድእት ደመረው:: የአክራጥስ መኮንን "ምነው ዘገየህ?" ቢለው ያየውን ሁሉ ጽፎ: እንደማይመለስም አክሎ ደብዳቤ ላከለት:: ከዚህ በኋላ ቅዱስ ቲቶ ከጌታችን እግር ለሦስት ዓመታት ተምሮ: በበዓለ ሃምሳ መንፈስ ቅዱስን ተቀብሎ: በመላው እስያ ለስምንት ዓመታት ወንጌልን ሰብኳል:: ቅዱስ ጳውሎስ ባመነ ጊዜ ደግሞ የእርሱ ደቀ መዝሙር ሆኖ ለሃያ አምስት ዓመታት አስተምሯል:: ቅዱስ ጳውሎስ ሰማዕት ከሆነ በኋላ ደግሞ ወደ አክራጥስ ተመልሶ: ሕዝቡን አሳምኖና አጥምቆ: ቤተ ክርስቲያንን አንጿል:: ዕድሜው በደረሰ ጊዜም መምሕራንን: ካህናትን ሹሞላቸው: ባርኳቸውም በዚህች ቀን ዐርፏል:: † አምላከ ቅዱስ ቲቶ መልካሙን የሕይወት ምሥጢር ይግለጽልን:: ከሐዋርያውም በረከቱን ያድለን:: 🕊 [  † ጳጉሜን ፪ [ 2 ] ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት  ] 1.ቅዱስ ቲቶ ሐዋርያ [ከሰባ ሁለቱ አርድእት] [   † ወርኀዊ በዓላት   ] -   የለም † " የእግዚአብሔር ባሪያና የኢየሱስ ክርስቶስ ሐዋርያ የሆነ ጳውሎስ. . . መድኃኒታችን እግዚአብሔር እንዳዘዘ: ለእኔ አደራ በተሰጠኝ ስብከት ቃሉን ገለጠ: በሃይማኖት ኅብረት እውነተኛ ለሚሆን ልጄ ቲቶ:: ከእግዚአብሔርም አብ: ከመድኃኒታችንም ከጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ ጸጋና ምሕረት: ሰላምም ይሁን::" † [ቲቶ. ፩፥፩] † ወስብሐት ለእግዚአብሔር † † ወለወላዲቱ ድንግል † † ወለመስቀሉ ክቡር † [ ዲ/ን ዮርዳኖስ አበበ  ]          †              †               † ▬▬▬▬▬ ▬▬▬ ▬▬▬▬▬ 💖                   🕊                    💖
74
4
No text...
92
5
🕊 🕊 🌼    ጳጉሜ / ጾመ ዮዲት    🌼 🌸                                                  🌸 🌼 በስመ አብ : ወወልድ : ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን። ጳጉሜ ማለት ጭማሪ ማለት ነው፡፡ ይህም በዓመቱ መጨረሻ ላይ አምስት ወይም ስድስት ቀን በመሆን የምትመጣ ናት፡፡ በአራት ዓመት አንዴ ማለትም በዘመነ ዮሐንስ ጳጉሜ ስድስት ቀን ይሆናል፡፡ በዚህም ሐገራችን ኢትዮጵያ የአሥራ ሦስት ወራት ጸጋ / Thirty months of sunshine / በመባል ትታወቃች ፡፡ ጳጉሜ በዘመነ ዮሐንስ ስድስት በምትሆንበት ጊዜ ጾመ ነቢያት /የገና ጾም/ ህዳር ፲፬ [14] ቀን ይገባና ታህሳስ ፳፰ [28] ቀን ጾሙ ተፈቶ የልደት በዓል ይከበራል፡፡ በቅድስት ቤተክርስቲያን ካሉት ሁለት የፈቃድ አጽዋማት መካከል አንዱ በዚህ በጳጉሜ ወር የምንጾመው የፈቃድ ጾም ነው፡፡ ይህም ጾመ ዮዲት በመባል ይታወቃል፡፡ ይህ ግን እንደ አንደኛው የፈቃድ ጾም /ጽጌ ጾም/ በብዙዋኑ ዘንድ የታወቀ አይደለም፡፡ የዮዲት ጾም የሚባለውም እርሷ ስለ ጾመችው ነው፡፡ እዚህ ላይ ዮዲት ተብላ የተጠቀሰችው በቤተክርስቲያን ታሪክ ትምህርት ላይ በጥፋት ሥራዋ በተደጋጋሚ የምትጠቀሰው ዮዲት ጉዲት እንዳልሆነች ለማሳወቅ እንወዳለን፡፡ ወደ ታሪኩ ስንመለስ የፋርስ ንጉስ ናቡከደነጾር በሠራዊቱ ተመክቶ ሹም ጠላት አጥፋ ድንበር አስፋ ካመነው እጅ መንሻ እየተቀበልህ ያላመነውን እያሳመንህ ና ብሎ ለጦር አበጋዙ ለሆሎፎርኒስ ትዕዛዝ ሰጠ፡፡ [ዮዲ.፪፥፯]፡፡ እርሱም እንደታዘዘው በኃይላቸው የታመኑ ፲፪ [12] ሺህ እግረኞችንና በፈረስ የተቀመጡ ፲፪ [12] ሺህ ጦረኞችን እየመራ ዘምቶ ካመነው እጅ መንሻ እየተቀበለ ያላመነውን እያሳመነ ብዙ ሀገሮችን እያጠፋ ሲሔድ ከአይሁድ ከተማ ደረሰ በዚህም ብዙ ጥፋ በመድረሱ የእስራኤል ልጆች አለቀሱ፡፡ ዮዲት ባሏ ሞቶባት ከወንድ ርቃ ንጽሕናዋን ጠብቃ በጾም በቀኖና በሀዘን ተወስና ትኖራለች በተፈጠረው ጥፋት ህዝቡ ላይ ለመጣው መከራ ማቅ ለብሳ በራስዋ ላይ ትብያ ነስንሳ ወደ እግዚአብሔር አለቀሰች፡፡ የፍጥረቱን ጥፋት የማይሻ እግዚአብሔር አምላክም ሕዝቡን የሚያድኑበትን መንገድ ለመጠየቅ ሱባኤ በገባች በሦስተኛው ቀን ገለፀላት፡፡ [ዮዲ.፰፥፪]፡፡ ከዚህ በኋላ ጠላታቸውን በዮዲት ምክንያት እስራኤላውያን እስከ ዮርዳኖስ እየተከተሉ አጥፍተዋቸዋል፡፡ ዮዲት ጠላቷን ለማጥፋት የቻለችው በጾምና በጸሎት ከእግዚአብሔር አምላክ ኃይል አግኝታ ነው፡፡ ስለዚህ ምዕመናን ጥንተ ጠላታችን ሰይጣንን ፈቃደ ሥጋን ለማሸነፍ በጾም ከፈጣሪያችን ኃይልን መጎናጸፍ አለብን ብለው ጳጉሜን በፈቃድ ይጾማሉ፡፡ የጳጉሜ ወር ዕለተ ምጽአት የሚታሰብበትም ወር ነው፡፡ ይህም ጳጉሜ የዓመታት መሸጋገሪያ ጨለማው የክረምት ወቅት ወደ ማብቂያው የምናልፍባት እንደሆነች ሁሉ ምጽአትም ከጊዜያዊው ወደ ዘላለማዊ ከምድራዊ ወደ ሰማያዊ ከዚህ ዓለም ወደ ወዲያኛው መሸጋገሪያ ነውና ነው፡፡ ክርስቲያኖች ሁሉ በየዓመቱ በጳጉሜ ወር ሁሉም ተሰብስበው ከሌሊት ጀምረው በቤተክርስቲያን ተገኝተው ጸበል ይጠመቃሉ፡፡ ይህንን የምናደገውም እግዚአብሔር የተባረከ ዓመት እንዲሰጠን ፣ ባሳለፍነው ዓመት የሰራነውን ኃጢአት ይቅር እንዲለን ነው የምንጠመቀውም ንስሐ ገብተን ነው፡፡ በእግዚአብሔር ስም የተቀደሰው ጸበል ደግሞ ከበሽታችን ያድነናል፣ የተቀደስንም ያደርገናል ፣ መጪውንም ህይወታችን የተባረከ ያደርግልናል፡፡ ስለ ቅድስት ቤተክርስቲያናችንና ስለ ሀገራችን ኢትዮጵያ ወደ እግዚአብሔር በመጮህና በማሳሰብ አጽራረ ቤተክርስቲያንን ያስታግስልን ዘንድ ፡ ሀገራችን ኢትዮጵያም ከመለያየት ፡ ከጥላቻ ፡ ከዘረኝነት ከመከራና ከስቃይ በቃሽ ይላት ዘንድ የምናለቅስበትም ጾም ነው፡፡ ወስብሐት ለእግዚአብሔር ፡ ወለወላዲቱ ድንግል ፡ ወለመስቀሉ ክቡር፡፡ 🌼 መልካም የአዲስ ዓመት ዋዜማ [ ጷጉሜ ] ይሁንላችሁ፡፡ 🌸                                                  🌸                            †††                ✟𝐎𝐑𝐓𝐇𝐎𝐃𝐎𝐗Y✟ 🕊                        💖                        🕊
101
6
No text...
173
7
[ ስንክሳር ጳጉሜ - ፩ - ] .mp3
156
8
🕊 [  † እንኳን ለተባረከ ወር ጳጉሜን እና ለቅዱሳኑ ዮሐንስ መጥምቅ : ዑቲኮስ ሐዋርያና ቀሲስ አባ ብሶይ ዓመታዊ በዓል በሰላም አደረሳችሁ ፤ አደረሰን። †  ] † በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን ! † [  🕊 †   ወርኀ ጳጉሜን  † 🕊  ] † እግዚአብሔር አዝማናትን የፈጠራቸው ለሰው ልጆች ጥቅም መሆኑ ይታወቃል:: እርሱ ባወቀ: በረቂቅ ሥልጣኑ ዓለምን ፈጥሮ: ጊዜያትን እንዲከፍሉ ብርሃናትን [ፀሐይ: ጨረቃ: ከዋክብትን] ፈጥሮልናል:: ጊዜያትንም በደቂቃ: በሰዓት: በቀን: በሳምንት: በወር: በዓመታት: በኢዮቤልዩ: በክፍላተ ዘመናት እንድንቆጥር ያስማረንም እርሱ ነው:: የሰከንድ ፭ መቶ ፵ ሺህ [540,000] ክፋይ ከሆነችው 'ሳድሲት' እስከ ትልቁ ቀመር ፭፻፴፪ [532 ዓመት] ድረስ እርሱ ለወደዳቸው እንዲያስተውሉት ገልጧል:: በየዘመኑም በቅዱስ ድሜጥሮስ: በቅዱስ ዮሐንስ ዘደማስቆ : በቅዱስ አቡሻኽር እና በሌሎቹም አድሮ መልካሙን አቆጣጠር አስተምሯል:: ሃገራችን ኢትዮጵያ ደግሞ የአሥራ ሦስት ወራት የፀሐይ ጸጋ [thirteen months sun shine] ያላት: አራቱ ወቅቶች የተስማሙላት ናት:: † ሌላው ዓለም ወሮችን 31,30,29 [28] እያደረገ ሲጠቀም እኛ ግን እንደ ኖኅ [ዘፍ.፰፥፩-፭] (8:1-15) አቆጣጠር ወሮችን በሠላሳ ቀናት ወስነን: ጳጉሜንን ለብቻዋ እናስቀምጣለን:: ጳጉሜን 'ኤጳጉሚኖስ' ከሚል የግሪክ [ጽርዕ] ቃል የተወሰደ ሲሆን ትርጉሙም 'ትርፍ: ጭማሪ' እንደ ማለት ነው:: የወርኀ ዻጉሜን አምስቱ [ስድስቱ] ቀናትም ወደ አዲስ ዓመት መሸጋገሪያ እንደ መሆናቸው ብዙ ምሳሌያት [ምሥጢራት] አሏቸው:: ዋናው ግን በዚህ ጊዜ ዳግም ምጽዓት ይታሠባል:: ጊዜውንም በጾምና በጸሎት ሊያሳልፉት ይገባል:: ግን በፈቃድ ነው እንጂ የግዴታ አይደለም:: [ 🕊 †  ቅዱስ ዮሐንስ መጥምቅ  † 🕊 ] ¤ የቅዱሳኑ ዘካርያስና ኤልሳቤጥ ልጅ ¤ በማኅጸን ሳለ መንፈስ ቅዱስ የሞላበት ¤ በበርኀ ያደገና በገዳማዊ ቅድስና ያጌጠ ¤ እሥራኤልን ለንስሐ ያጠመቀ ¤ የጌታችንን መንገድ የጠረገ ¤ ጌታውን ያጠመቀና ¤ ስለ እውነት አንገቱን የተቆረጠ ታላቅ ሰው ነው:: † ስለዚህም ቤተ ክርስቲያን :- ነቢይ: ሐዋርያ: ሰማዕት: ጻድቅ: ገዳማዊ: መጥምቀ መለኮት: ጸያሔ ፍኖት: ቃለ ዐዋዲ ብላ ታከብረዋለች:: † ቅዱሱ በዚህች ዕለት ወደ እሥር ቤት ገብቷል:: ይሕስ እንደ ምን ነው ቢሉ :- ንጉሡ ሔሮድስ የወንድሙን የፊልጶስን ሚስት ሔሮድያዳን በማግባቱና በመሰል ክፋቶቹ ቅዱስ ዮሐንስ ይገስጸው ነበር:: ቅዱስ ዮሐንስ "መምሕር ወመገስጽ: ዘኢያደሉ ለገጽ - ፊት አይቶ የማያዳላ" ነውና ገሰጸው:: ሔሮድስ ቅዱሱን ይፈራው: ያከብረውም ነበር:: በኋላ ግን ፈቃደ ሥጋው ስላየለበት: በተለይ ደግሞ ከሰባት ቀናት በኋላ ልደቱን ሲያከብር እንዳይረብሸው በመስጋት በዚህች ቀን በወታደሮቹ አስይዞ እሥር ቤት ውስጥ ጥሎታል:: ለሰባት ቀናት በጨለማ ውስጥ አሥሮ መስከረም 2 ቀን አንገቱን እንዴት እንዳስቆረጠው ዕለቱን ጠብቀን እንመለከታለንና የዚያ ሰው ይበለን:: [ 🕊 †  ቅዱስ ዑቲኮስ ሐዋርያ † 🕊 ] † ቅዱሱ ሐዋርያ ጭራሽ ከነስማቸው እንኳ እየተዘነጉ ከሔዱ ሐዋርያት አንዱ ሲሆን ቁጥሩም ከሰባ ሁለቱ አርድእት ነው:: በወጣትነት ዘመኑ የጌታችን ደቀ መዝሙር መሆንን መርጦ ለሦስት ዓመት ከሦስት ወር ምሥጢረ ወንጌልን ጠንቅቆ ተምሯል:: መንፈስ ቅዱስ በወረደ ጊዜም እንደ መጠኑ ተቀብሎ ለአገልግሎት ወጥቷል:: በመጀመሪያ የወንጌላዊው ዮሐንስ ተከታይ ሁኖ ብዙ ምሥጢራትን ተካፍሏል:: ቀጥሎም ቅዱስ ጳውሎስን ተከትሎ ብዙ አሕጉራትን በስብከተ ወንጌል አዳርሷል:: በመጨረሻም በእስያ አካባቢ ለብቻው ተጉዞ: ብዙ ነፍሳትን ማርኮ: ጣዖታትን አጥፍቷል:: ስለዚህ ፈንታም በእሳት: በስለትና በግርፋት ብዙ መከራዎችን አሳልፏል:: በዚህች ቀንም በበጐው እርግና [ሽምግልና] ዐርፏል:: [ 🕊 †  ቅዱስ ብሶይ ቀሲስ  † 🕊 ] † ከ፫ [3] ኛው መቶ ክ/ዘመን ካህናት አንዱ የነበረው አባ ብሶይ ለአገልግሎት ወጥቶ ሲመለስ የቤተሰቦቹ ቤት ሰው አልነበረበትም:: "የት ሔዱ?" ብሎ ቢጠይቅ "ወንድምህ አባ ሖር እና እናትህ ቅድስት ይድራ ወደ እስክንድርያ ሔደዋል:: በዚያም ስለ ክርስቶስ ፍቅር ተሰውተዋል::" አሉት:: በማግስቱ የኔ ብጤዎችን ጠርቶ ሃብቱን: ንብረቱን: ቤቱን አካፈላቸው:: ለራሱ ግን አንዲት በትር እና ሦስት የዳቦ ቁራሾች ይዞ ጉዞ ተነሳ:: ወደ እስክንድርያ እንደ ደረሰ አፈላልጐ የቤተሰቦቹን መቃብር አገኘ:: ከፊታቸው ወድቆም የናፍቆት ለቅሶን አለቀሰ:: ወዲያውም እንዲህ አላቸው:- "ፈጥኜ ወደ እናንተ ስለምመጣ ጠብቁኝ:: ደግሞም ጸልዩልኝ::" ከዚያ ተነስቶ በመኮንኑ ፊት ስለ ክርስቶስ የባሕርይ አምላክነት መሰከረ:: በዚህ ምክንያት ብዙ ተሰቃይቶ በዚህች ቀን ሰማዕት ሆኗል:: ከወገኖቹም ጋር ተቀብሯል:: † አምላከ ቅዱሳን ተረፈ ዘመኑን ባርኮ ለአዲሱ ዘመን በቸር ያድርሰን:: ከወዳጆቹም ጸጋ በረከትን ይክፈለን:: 🕊 [  † ጳጉሜን ፩ [ 1 ] ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት  ] ፩. ቅዱስ ዮሐንስ መጥምቅ [የታሠረበት] ፪. ቅዱስ ዑቲኮስ ሐዋርያ [ከሰባ ሁለቱ አርድእት] ፫. ቅዱስ ብሶይ ቀሲስ [ሰማዕት] ፬. አባ ጳኩሚስ /ባኹም [የሦስት ሺ ቅዱሳን አባት] ፭. አባ ሰራብዮን /ሰራፕዮን [የአሥር ሺ ቅዱሳን አባት] [  † ወርኀዊ በዓላት  ] - የለም [  † " ጌታ ኢየሱስ ለሕዝቡ ስለ ዮሐንስ ሊናገር ጀመረ . . . ምን ልታዩ ወጣችሁ? ነቢይን? አዎን እላችኋለሁ ከነቢይም የሚበልጠውን . . . እውነት እላችኋለሁ ከሴቶች ከተወለዱት መካከል ከመጥምቁ ዮሐንስ የሚበልጥ አልተነሳም . . . ነቢያት ሁሉና ሕጉ እስከ ዮሐንስ ድረስ ትንቢት ተናገሩ:: ልትቀበሉትስ ብትወዱ ይመጣ ዘንድ ያለው ኤልያስ ይሕ ነው:: የሚሰማ ጆሮ ያለው ይስማ::" † [ማቴ. ፲፩፥፯-፲፭] † ወስብሐት ለእግዚአብሔር † † ወለወላዲቱ ድንግል † † ወለመስቀሉ ክቡር † [ ዲ/ን ዮርዳኖስ አበበ  ]          †              †               † ▬▬▬▬▬ ▬▬▬ ▬▬▬▬▬ 💖                   🕊                    💖
161
9
No text...
193
10
[ ስንክሳር ነሐሴ - ፴ - ] .mp3
186
11
🕊 [  † እንኳን ለሐዋርያው ቅዱስ እንድርያስ እና ለቅዱስ ሚልክያስ ነቢይ ዓመታዊ በዓል በሰላም አደረሳችሁ ፤ አደረሰን። †   ] † በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን ! † † መሐሪ እግዚአብሔር ኃጢአታችሁ በዛ: ሰውነታችሁ ከፋ ሳይል በአባታዊ ርሕራሔው ጠብቆ ይሔው ወርኀ ነሐሴን በሰላም አስፈጸመን:: አይመስለንም እንጂ በእነዚህ ሰላሳ ቀናት ሚሊየኖች አንቀላፍተዋል: ሚሊየኖች በደዌ ዳኝነት ተይዘዋል: በርካቶቹም ከሃይማኖታቸው ወጥተዋል:: እኛ ይህ ሁሉ ያልደረሰብን በጐ ስለሆንን አይደለም:: ይልቁኑ ቸርነቱ በእኛ ላይ ስለበዛ ብቻ ነው እንጂ:: አሁንም በሰላም ከአዲሱ ዘመን እንዲያደርሰን ልንማጸነው ይገባል:: በዚህች ዕለት ደግሞ እነዚህን ቅዱሳን እናከብራለን:: [ 🕊 † ቅዱስ እንድርያስ ሐዋርያ † 🕊 ] † ቅዱሱ ሐዋርያ ተወልዶ ያደገው በቤተ ሳይዳ አካባቢ ሲሆን የሊቀ ሐዋርያት ቅዱስ ጴጥሮስ ትንሽ ወንድም ነው:: አባቱም ዮና ይባላል:: ገና ከልጅነቱ ጀምሮ ዓሣ ማጥመድን ከትልቅ ወንድሙ ተምሯል:: እድሜው ከፍ ባለ ጊዜ ኦሪትን ተምሮ የመጥምቁ ቅዱስ ዮሐንስ ደቀ መዝሙር ሆኗል:: ከእርሱም እያገለገለ ለስድስት ወራት ተምሯል:: በወቅቱ ከወንጌላዊው [ወልደ ዘብዴዎስ] ዮሐንስ ጋር ቅርብ ባልንጀራም ነበር:: ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በተጠመቀ ጊዜ ያን ድንቅ ምሥጢረ ሥላሴ ከተመለከቱትም አንዱ ነው:: ጌታ ከጾም [ከገዳመ ቆረንቶስ] በተመለሰ ጊዜ እንድርያስ መንፈስ ቅዱስ አነሳስቶት ተከትሎታል:: መጥምቁ ቅዱስ ዮሐንስ "ነዋ በግዑ ለእግዚአብሔር ዘያዐትት ኃጢአተ ዓለም - የዓለምን ኃጢአት የሚያስወግድ የእግዚአብሔር በግ እነሆ::" ማለቱን ሰምቶ ቅዱስ እንድርያስ ጌታን ተከተለ:: በዚህም የመጀመሪያው የክርስቶስ ደቀ መዝሙር ለመባል በቃ:: [ዮሐ.፩፥፵፯] (1:47) ሊቁ ማር ገላውዴዎስም እመቤታችንን ሲያመሰግናት "ለሐዋርያ እንድርያስ ቀዳማዊ ማርያም ሃይማኖቱ [ለመጀመሪያው ሐዋርያ ለእንድርያስ ሃይማኖቱ ማርያም አንቺ ነሽ::]" ብሏል:: [መልክዐ ስዕል] ቅዱሱ ሐዋርያ ስሉጥ [ፈጣን] አገልጋይ እንደ ነበርም ወንጌል ይነግረናል:: [ዮሐ.፮፥፱ (6:9), ፲፪፥፳፪ (12:22) ለሦስት ዓመታት ከሦስት ወር ከጌታ እግር ሥር ተምሮ: በበዓለ ሃምሳ መንፈስ ቅዱስን ተቀበሎ: ምን ሃገረ ስብከቱ ልዳ ብትሆን ብዙ አሕጉረ ዓለምን ሰብኳል:: ይህች ቀን ሐዋርያው ከጌታ ጋር በመርከብ ውስጥ የተነጋገረባትና ቅዱስ ማትያስን ሰውን ከሚበሉ ሰዎች እጅ ያዳነባት ናት:: ቅዱስ እንድርያስ ሰላሳ ቀናት የሚፈጅ የባሕር ላይ ጉዞ ለማድረግ ከአርድእቱ ጋር ወደ ወደብ ቢሔድም መርከበኞች ሁሉ አናሳፍርም በማለታቸው የክብር ባለቤት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ወጣት መርከበኛ መስሎ ሐዋርያውንና አርድእቱን የሰላሳውን ቀን መንገድ በሰዓታት ልዩነት እንዲጨርሱ አድርጓል:: ቅዱስ እንድርያስም ፍጡር [እንዲሁ ሰው] መስሎት ለጌታችን ስለ ጌታችን ሰብኮለታል: መርቆታልም:: መርከበኛው ጌታችን መሆኑን ሲያውቅም ደንግጦ አልቅሷል:: "ሶበ አእመረ ኪያሁ ወጠየቀ አምሳሎ: ዘተናገርኩ በድፍረት ምስሌከ ኩሎ: ሥረይ ሊተ ጌጋይየ ወኅድግ ይቤሎ::" እንዲል "ማረኝ?" ብሎታል:: ጌታችንም "አይዞህ እኔ ከአንተ ጋር ነኝ::" ብሎታል:: ቅዱሱ ሐዋርያ ለወንጌል አገልግሎት ተግቶ ያረፈው ታኅሣሥ 4 ቀን ነው:: [ 🕊 † ቅዱስ ሚልክያስ ነቢይ † 🕊 ] † ሚልክያስ ከአሥራ ሁለቱ ደቂቀ ነቢያት አንዱ ሲሆን "የመጨረሻው ነቢይ" እየተባለ ይጠራል:: ለዚህ ምክንያቶቹ ሁለት ናቸው:: ፩ኛ. ከእርሱ በኋላ የተጻፈ ጥሬ የትንቢት መጽሐፍ የለም:: ፪ኛ.እርሱ ካረፈ በኋላ ያለው ዘመን "ዘመነ ካህናት" በመሆኑ ምንም ነቢያት በየጊዜው ባይጠፉ ጐልተው የተነገረላቸው ጥቂቶቹ ናቸው:: ቅዱሱ የተወለደው ቅ/ል/ክርስቶስ ስድስት መቶ ዓመት አካባቢ ሲሆን ከሚጠት [ከባቢሎን ምርኮ መልስ] ሕዝቡን ገስጿል:: ሕዝቡ ከሰባ ዓመት መከራ እንኳን ተመልሶ ኃጢአትን መሥራትን ቸል አላለም ነበር:: በተለይ የልጅነት ሚስታቸውን የሚያታልሉትን ገስጿል:: [ሚል.፪፥፲፬] (2:14) ስለ አሥራትና በኩራትም ተናግሯል:: [ሚል.፫፥፰] (3:8) እመቤታችን ድንግል ማርያምንም በንጽሕት አዳራሽ መስሎ ተናግሯል:: "ጽርሕ ንጽሕት ዘሚልክያስ" እንዳሉ አባ ሕርያቆስ:: [ቅዳሴ ማርያም] ነቢዩ ቅዱስ ሚልክያስ ፈጣሪውን አገልግሎ: ሕዝቡን መክሮ ዐርፏል:: ሚልክያስ ማለት "መልአክ: አንድም የተላከ" ማለት ነው:: ነገዱ ከነገደ ይሳኮር ነው:: † አምላከ ቅዱሳን አሥራ ሁለቱን ወራት እንደ ባረከልን አሥራ ሦስተኛዋንም ለንስሐ ቀድሶ ይስጠን:: ከቅዱሳኑም በረከትን ያካፍለን:: 🕊 [  † ነሐሴ ፴ [ 30 ] ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት  ] ፩. ቅዱስ እንድርያስ ሐዋርያ ፪. ቅዱስ ሚልክያስ ነቢይ ፫. አባ ሙሴ ዘሃገረ ፈርማ [  † ወርኀዊ በዓላት   ] ፩. ቅዱስ ማርቆስ ዘአንበሳ [ሐዋርያ] ፪. አባ ሣሉሲ ክቡር ፫. ቅዱስ ጐርጐርዮስ ነባቤ መለኮት ፬. ቅድስት ሶፍያ ሰማዕት ፭. ቅዱስ ዮሐንስ መጥምቀ መለኮት † "ስለዚህ መንፈሳችሁን ጠብቁ:: ማንም የልጅነት ሚስቱን አያታልል:: 'መፋታትን እጠላለሁ' ይላል የእሥራኤል አምላክ: የሠራዊት ጌታ እግዚአብሔር::" † [ሚል. ፪፥፲፭] † " ሰው እግዚአብሔርን ይሰርቃልን? እናንተ ግን እኔን ሰርቃቹሃል:: እናንተም 'የሰረቅንህ በምንድን ነው?' ብላቹሃል:: በአሥራትና በበኩራት ነው:: እናንተ: ይህ ሕዝብ ሁሉ እኔን ሰርቃቹሃልና በእርግማን ርጉሞች ናችሁ::" † [ሚል. ፫፥፰] † ወስብሐት ለእግዚአብሔር † † ወለወላዲቱ ድንግል † † ወለመስቀሉ ክቡር † [ ዲ/ን ዮርዳኖስ አበበ  ]          †              †               † ▬▬▬▬▬ ▬▬▬ ▬▬▬▬▬ 💖                   🕊                    💖
195
12
No text...
198
13
[ ስንክሳር ነሐሴ - ፳፱ - ] .mp3
174
14
🕊 [  † እንኳን ለታላቁ ቅዱስ አባ ዮሐንስ ሐጺር ዓመታዊ የፍልሠት በዓል በሰላም አደረሳችሁ ፤ አደረሰን። †  ] † በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን ! † [ 🕊 † ቅዱስ አባ ዮሐንስ ሐጺር  † 🕊 ] † በቤተ ክርስቲያን ያሉ አበው ሊቃውንት እንደሚሉት ከቅዱሳን በቁመቱ የአባ አርሳኒን ያክል ረዥም አልነበረም:: እርሱ እንደ ዝግባ ቀጥ ያለ ነበር:: በዚያው ልክ ደግሞ የቅዱስ ዮሐንስን [ዛሬ የምናከብረውን] ያህል አጭር አልነበረም:: በዚህ ምክንያት ይሔው ለዘለዓለም " ዮሐንስ_ሐጺር- አጭሩ አባ ዮሐንስ" ሲባል ይኖራል:: ሊቃውንትም ቁመቱንና ቅድስናውን በንጽጽር ሲገልጡ :- "ሰላም ሰላም ዕብሎ በሕቁ: ለዮሐንስ ሐጺር ዘነዊኅ ሒሩተ ጽድቁ" ይላሉ:: "ቁመቱ እጅግ ያጠረ: ጽድቁ ግን ከሰማይ የደረሰ ቅዱስ ዮሐንስን ሰላም ሰላም እንለዋለን" እንደ ማለት ነው:: ቅዱሱ የተወለደው በ፬ [4]ኛው መቶ ክ/ዘመን በምድረ ግብጽ ነው:: ወላጆቹ ምንም ከሥጋዊ ሃብት ድሆች ቢሆኑም ባለ መልካም ክርስትና ነበሩና በጐውን ሕይወት አስተምረውታል:: ወደ ምናኔ የገባው ገና በ፲፰ [18] ዓመቱ ሲሆን የታላቁ አባ ባይሞይ ደቀ መዝሙር ሆኖ ተጋድሎንና ትሕርምትን ተምሯል:: ቅዱስ ዮሐንስ ሐጺር በወቅቱ ከነበሩ ቅዱሳን ከቁመቱ ባሻገር በትሕትናው: በትእግስቱና በመታዘዙ ይታወቅ ነበር:: አባ ባይሞይ ይጠራውና ያለ ምንም ምክንያት ደብድቦ ያባርረው ነበር:: እርሱ ግን "ምን አጠፋሁ?" ብሎ እንኩዋ ሳይጠይቅ "አባቴ ሆይ! ማረኝ?" እያለ ከእግሩ ሥር ይወድቅ ነበር:: ለብዙ ጊዜ በተመሳሳይ ሲደበድበው: እርሱም እርሱው ተደብድቦ: እርሱው ይቅርታን ሲጠይቅ ኖረ:: አንድ ቀን ግን እንደ ልማዱ ሊገርፈው ሲሔድ ፯ [7]ቱ ሊቃነ መላእክት ከበውት አይቶ ደንግጦ ተመልሷል:: አባ ባይሞይ ይሕንን ሁሉ የሚያደርገው ጠልቶት ወይ ክፉ ሆኖ አይደለም:: አንድ ሰው የሌላኛውን ግፍ መቀበል ካልቻለ ሰይጣንን ድል አይነሳም የሚል ትምሕርት ስለ ነበረ ነው እንጂ:: አንድ ቀን ቅዱስ ዮሐንስ ወደ መምሕሩ ቀርቦ "አባቴ ጅብ ካገኘሁ ምን ላድርግ?" ሲል ጠየቀው:: [የአካባቢው ጅብ መናጢ ነበር] አባ ባይሞይ ግን "ይዘህልኝ አምጣው" አለው:: ትዕዛዝ ነውና ቅዱሱ ወደ በርሃ ወርዶ: ጅብ አልምዶ ይዞለት መጥቷል:: ሌላ ቀን ደግሞ አባ ባይሞይ ቅዱስ ዮሐንስን ጠራውና ተፈልጦ የወደቀ ደረቅ እንጨት ሠጠው:: "ምን ላድርገው አባ?" አለው:: "ትከለውና እንዲያፈራ አድርገው:: ከዚያ አምጥተህ አብላኝ" ሲል መለሰለት:: ይህ ነገር ከተፈጥሮ ሥርዓት ውጪ መሆኑን እያወቀ ቅዱስ ዮሐንስ "እሺ" ብሎ ወስዶ ተከለው:: ከዚያም ለ፪ [2] ዓመታት ሳይታክት ውሃ አጠጣው:: ውሃውን የሚያመጣበት ቦታ ደግሞ ፲ [10] ኪሎ ሜትር ያህል ከገዳሙ ይርቅ ነበር:: ቅዱሱ ላቡን እያፈሰሰ አሁንም ማጠጣቱን ቀጠለ:: በ፫ [3]ኛው ዓመት ግን ለምልሞ አበበ: ደግሞም አፈራ:: ካፈራው በኩረ ሎሚም ወስዶ ለመምሕሩ "አባቴ! እንካ ብላ" ብሎ ሰጠው:: አባ ባይሞይ ግን ማመን አልቻለም:: እጅግ አደነቀ: አለቀሰም:: ወዲያው ያን ፍሬ ታቅፎ ወስዶ ለገዳሙ መነኮሳት አላቸው :- "ንሱ ብሉ: በረከትንም አግኙ:: ይህ የዛፍ ሳይሆን የመታዘዝ ፍሬ ነው::" ቅዱስ ዮሐንስ አባ ባይሞይ ቢታመም ለ፲፪ [12] ዓመት አስታሞታል:: መምሕሩ ከማረፉ በፊትም መነኮሳቱን ሰብስቦ የቅዱስ ዮሐንስን እጅ አስጨበጣቸው:: "ይህ የያዛችሁት እጅ የሰው ሳይሆን የመልአክ እጅ ነው" ብሏቸው ዐርፏል:: ቅዱስ ዮሐንስም ከዓመታት ቆይታ በሁዋላ የገዳሙ አበ ምኔት ሆኖ አገልግሏል:: ብዙ ነፍሳትንም ለቅድስና ማርኩዋል:: መላእክት ንጽሕናው ደስ ስለሚያሰኛቸው አብረውት ይውሉ ነበር:: ሲተኛም በተራ በተራ ክንፋቸውን ያለብሱት ነበር:: ምጽዋትን በጣም ስለሚወድ ሰፌድ እየሰፋ ይሸጥና ገንዘቡን ለነዳያን ያን ያካፍል ነበር:: አንድ ቀን እንደ ልማዱ ወደ ገበያ ወጥቶ ሳለ ተደሞ [ተመስጦ] መጣበት:: ሰማያት ተከፍተው: ቅዱሳን ሊቃነ መላእክት ሚካኤል እና ገብርኤል በግርማ በጌታ ፊት ቆመው ተመለከተ:: "እጹብ: እጹብ" እያለ ሲያደንቅ አንድ ገዢ መጥቶ "ባለ እንቅብ ዋጋው ስንት ነው?" ቢለው "እኁየ ሚካኤልኑ የዓቢ ወሚመ ገብርኤል - ከሚካኤልና ከገብርኤል ማን ይበልጣል?" ብሎታል:: ገዢውም ደንግጦ "እብድ መነኩሴ" ብሎት ሔዷል:: ቅዱስ ዮሐንስ ሐጺር ወደ ባቢሎን [የአሁኗ ኢራቅ] ሒዶ ከተመለሰ በሁዋላ በበርበሮች ምክንያት ከአስቄጥስ ወደ ቁልዝም ተሰዷል:: በዚያም በአባ እንጦንስ በዓት ውስጥ ዐርፏል:: ለ፬፻ [400] ዓመታት በዚያው ቆይቷል:: በ፰፻፳፭ [825] ዓ/ም ግን በአባ ዮሐንስ ፓትርያርክ ዘመን ክቡር ሥጋው ወደ ገዳመ_አስቄጥስ ተመልሷል:: ቅዱሱ ያረፈው ጥቅምት ፳ [20] ቀን ሲሆን ዛሬ ሥጋው የፈለሠበት ነው:: በዚህ ዕለትም የቅዱስ ዮሐንስ ሐጺርና የታላቁ ቅዱስ_መቃርስ ሥጋ በተገናኙ ጊዜ ግሩም ተአምር ተደርጉዋል:: ወደ ቤተ ክርስቲያኑ ሲገባም ታላቅ የብርሃን ጐርፍ ሲፈስ ታይቷል:: ሰማያዊ መዓዛም አካባቢውን ሞልቶታል:: ከዻዻሳቱ አንዱ እባረካለሁ ብሎ የቅዱስ ዮሐንስን ሥጋ ቢገልጠው አካባቢው ተናወጠ:: መባርቅትም [መብረቆች] ተብለጨለጩ:: ደንግጠው ቶሎ ቢያለብሱት ጸጥታ ሆኗል:: በዚህ ሁሉ ደስ ያላቸው አበው ቅዱሱን በዝማሬ ሲያወድሱት ውለዋል:: † አምላከ ቅዱሳን የሐጺር ቅዱስ ዮሐንስን መታዘዙን: ትሕትናውን: ትእግስቱንና ቅንነቱን ያድለን:: በበረከቱም ይባርከን:: 🕊 [  † ነሐሴ ፳፱ [ 29 ] ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት  ] ፩. ቅዱስ አባ ዮሐንስ ሐጺር [ፍልሠቱ] ፪. ቅዱስ አትናቴዎስ ሰማዕት ፫. ቅዱሳን ገርሲሞስና ቴዎዶጦስ [ሰማዕታት] ፬. አባ ባስልዮስ ጻድቅ [ዘትግራይ] [  † ወርኀዊ በዓላት   ] ፩. የፈጣሪያችንና ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በዓለ ልደት ፪. ቅድስት አርሴማ ድንግል ፫. ቅዱስ ዼጥሮስ ተፍጻሜተ ሰማዕት ፬. ቅዱስ ማርቆስ ዘቶርማቅ ፭. ቅድስት ፍቅርተ ክርስቶስ ኢትዮዽያዊት ፮. ቅዱስ ዘርዐ ክርስቶስ [ጻድቅና ሰማዕት] † " እናንተ ደግሞ የታዘዛችሁትን ሁሉ ባደረጋችሁ ጊዜ 'የማንጠቅም ባሪያዎች ነን: ልናደርገው የሚገባንን አድርገናል' በሉ::" † [ሉቃ.፲፯፥፲] (17:10) † ወስብሐት ለእግዚአብሔር † † ወለወላዲቱ ድንግል † † ወለመስቀሉ ክቡር † [ ዲ/ን ዮርዳኖስ አበበ  ]          †              †               † ▬▬▬▬▬ ▬▬▬ ▬▬▬▬▬ 💖                   🕊                    💖
181
15
+2
No text...
256
16
[ ስንክሳር ነሐሴ - ፳፰ - ] .mp3
221
17
[ 🕊 † ቅዱስ ያዕቆብ ርዕሰ አበው † 🕊 ] † የአባቶች አለቃ የተሰኘ ቅዱስ ያዕቆብ ለሁለቱ ታላላቅ አባቶቹ እርሱ ሦስተኛቸው ነው:: እነርሱን መስሎ: እነርሱንም አህሎ በጐዳናቸው ተጉዟል:: በፈቃደ እግዚአብሔር ብኩርናን ከኤሳው ተቀብሎ ወደ ሶርያ ሲሸሽ ቤቴል [ፍኖተ ሎዛ] ላይ ድንጋይ ተንተርሶ በተኛበት ግሩም ራዕይን አይቷል::ይህችውም የወርቅ መሰላል የድንግል ማርያም ምሳሌ ናት:: "አንቲ ውዕቱ ሰዋስው ዘርእየ ያዕቆብ" እንዳለ ቅዱስ ኤፍሬም [ውዳሴ ማርያም ዘሠሉስ] ተነስቶም "ዛቲ ይእቲ ኈኅታ ለሰማይ: ዝየ ይትሐነጽ ቤተ እግዚአብሔር - ይህች የሰማይ ደጅ ናት: ቤተ እግዚአብሔርም ይታነጽባታል::" ብሎ ትንቢት ተናግሯል:: ይህ ቅዱስ አባት ለድንግል ማርያም ቅድመ አያት ከመሆኑ ባሻገር ነቢያትን: ካህናትን: ነገሥታትንና መሣፍንትን ወልዷል:: ከሁለቱ ሚስቶቹ [ልያና ራሔል] : ከሁለቱ ደንገጥሮች አሥራ ሁለት ልጆችን ወልዷል:: ከአጐቱ ከላባ ዘንድ ለሃያ አንድ ዓመታት አገልግሎ: ሃብት ንብረቱን ጠቅልሎ ወደ ርስቱ ከነዓን ሲመለስ ለብቻው ራቅ ብሎ ይጸልይ ገባ:: በዚያም እግዚአብሔር ሲታገለው አደረ:: [ይኸውም የፍቅርና የምሥጢር ነው::] ለጊዜው ጌታ ያዕቆብን "ልቀቀኝ?" ቢለው "ካልባረከኝ አለቅህም?" አለው:: ጌታም ስሙን "እሥራኤል" ብሎ ባርኮታል:: ቅዱስ ያዕቆብ በስተእርጅና ብዙ መከራ አግኝቶታል:: ልጁን ዮሴፍን ወንድሞቹ ሽጠው "አውሬ በላው" ብለውታልና በለቅሶ ዓይኑ ጠፋ:: በረሃብ ምክንያትም በመቶ ሰላሳ ዓመቱ ከሰባ አምስት ያህል ቤተሰቦቹ ጋር ወደ ግብጽ ወረደ:: በዚያም ለሰባት ዓመታት ኑሮ በመቶ ሰላሳ ሰባት ዓመቱ ዐርፏል:: ልጆቹም ቀብረውታል:: † በሰማይና በምድር ከሞላው ከአባቶቻችን በረከት ፈጣሪያቸው አብዝቶ: አትርፎ: አትረፍርፎም ያድለን:: 🕊 [  † ነሐሴ ፳፰ [ 28 ] ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት  ] ፩. ቅዱስ አብርሃም [ የአባቶች አለቃ ] ፪. ቅዱስ ይስሐቅ [ የአባቶች አለቃ ] ፫. ቅዱስ ያዕቆብ [ የአባቶች አለቃ ] [  † ወርኀዊ በዓላት  ] ፩. አማኑኤል ቸር አምላካችን ፪. ቅድስት ዓመተ ክርስቶስ ፫. ቅዱስ ቴዎድሮስ ሮማዊ ፬. ቅዱሳን እንድራኒቆስና አትናስያ † " አብርሃምንና ይስሐቅን: ያዕቆብንም: ነቢያትንም ሁሉ በእግዚአብሔር መንግስት ባያችሁ ጊዜ: እናንተ ግን ወደ ውጭ ተጥላችሁ ስትቀሩ በዚያ ልቅሶና ጥርስ ማፋጨት ይሆናል::" † [ሉቃ. ፲፫፥፳፰] † ወስብሐት ለእግዚአብሔር † † ወለወላዲቱ ድንግል † † ወለመስቀሉ ክቡር † [ ዲ/ን ዮርዳኖስ አበበ  ]          †              †               † ▬▬▬▬▬ ▬▬▬ ▬▬▬▬▬ 💖                   🕊                    💖
227
18
🕊 [  † እንኳን ለአበው ቅዱሳን አብርሃም: ይስሐቅ እና ያዕቆብ ዓመታዊ የዕረፍት በዓል በሰላም አደረሳችሁ ፤ አደረሰን። †   ] † በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን ! † [ 🕊 † አበው ቅዱሳን አብርሃም: ይስሐቅ እና ያዕቆብ  † 🕊 ] † እኒህ ቅዱሳን ከሰው ወገን እጅግ ክቡራን ከመሆናቸው የተነሳ መንግስተ ሰማያት በእነርሱ ስም ተጠርታለች:: ጽድቃቸውና ክብራቸው እንደ ሰማይ ከዋክብት የበዛ ነውና ጽፈንም: ተናግረንም አንፈጽመውም:: እንዲሁ "ዕጹብ! ዕጹብ!" እያልን ፈጣሪያቸውን ከማመስገን በቀር:: [ 🕊 † ቅዱስ አብርሃም ርዕሰ አበው † 🕊 ] † የሃይማኖት: የደግነት: የምጽዋት: የፍቅር አባት የሆነው አብርሃም በቤተ ክርስቲያን ትውፊት መሠረት አባቱ ታራ ጣዖትን ይጠርብና ይሸጥ ነበር:: ሽጦ ገንዘብ የሚያመጣለት ደግሞ ልጁ አብርሃም ነበር:: በዚያ ወራት አብርሃም እውነተኛውን አምላክ ፍለጋ ገብቶ ነበር:: አንድ ቀን ጣዖቱን ሊሸጥ ወደ ገበያ እየሔደ የተሸከመውን እንጨት ይመራመረው ገባ:: "አሁን ይሔ ምኑ ነው አምላክ!" እያለም ያደንቅ ገባ:: መንገድ ላይም ደክሞት ካረፈበት "ለምን አልጠይቀውም?" በሚል አናገረው:: "እርቦኛል አብላኝ?" አለው:: መልስ የለም:: "እሺ አጠጣኝ?" አለው:: አሁንም ያው ነው:: "ባይሆን እሺ አጫውተኝ?" አለው:: ጣዖቱ ተራ እንጨት ነውና መልሱ ዝምታ ነበር:: ከዚያ ተነስቶ ወደ ገበያው ሲደርስ "ዓይን እያለው የማያይ: ጆሮ እያለው የማይሰማ አምላክ የሚገዛ?" እያለ ይጮህ ጀመር:: ይህን ሲሰሙ አንዳንዶቹ "የታራ ልጅ አብዶ" ሲሉ ሌሎቹ ደግሞ "እሱ ያቀለለውን ማን ይገዛዋል::" ብለውት ሔደዋል:: ሲመለስም ጣዖቱን ተመልክቶ አብርሃም እንዲህ አለ:: "አንተ ቀድሞውን በዕለተ ሠሉስ የተፈጠርክ ዕፅ ነህ::" ብሎ ሰባበረው:: ወደ ቤቱ ሲመለስም ሁሉንም ጣዖታት ሠባበራቸው:: የመንግስተ ሰማያት አበጋዝ: የእግዚአብሔር ወዳጅ አባታችን አብርሃም የሕዝብና የአሕዛብ አባት የሆነው አብርሃም እግዚአብሔርን አምልኮ: ጣዖታትን ሰብሮ ወደ ከነዓን ከወጣ በኋላ ብዙ ችግርን አሳልፏል:: በረሃብ ምክንያት ከአንድም ሁለት ጊዜ ወደ ግብጽና ፍልስጥኤም ተሰዷል:: በዚያ ግን ፈጣሪው አክብሮታል:: ሁለቱ ነገሥታት [ፈርኦንና አቤሜሌክ] ሣራን እንነካለን ቢሉ ተግሣጽ ደርሶባቸዋል:: ነቢይ ነውና በአብርሃም ጸሎት ተፈውሰዋል:: ቅዱስ አብርሃም ከደግነቱ የተነሳ በኬብሮን (በተመሳቀለ መንገድ) ላይ ድንኳን ሠርቶ እንግዳ ይቀበል ነበር:: ምሥክር ሳይዝም እህል አይቀምስም ነበር:: ሰይጣን ከፍቶ እንግዳ ቢያስቀርበት ያለ ምግብ ለሦስት ቀናት ቆይቷል:: በፍጻሜውም ሥላሴ በእንግድነት መጥተውለት በክብር ላይ ክብር: በጸጋ ላይ ጸጋ: በጣዕም ላይ ጣዕም ተጨምሮለታል:: እርሱ የሥላሴን እግር ያጥብ ዘንድ: በጀርባውም ይሸከማቸው ዘንድ አድሎታልና:: ሥላሴም በቤቱ ተስተናግደው: ልደተ ይስሐቅን አብሥረውታል:: ጻድቁ ሰውም በፈጣሪው ፊት ስለ ሰዶምና ገሞራ ለምኗል:: አብርሃም በአምልኮው ፍጹም ነውና የሚወደውን ልጁን ይስሐቅን ለመስዋዕት አቅርቧል:: በዚህም የነቢያት: የሐዋርያት: የነገሥታት: የካህናት አባት: ሥርወ ሃይማኖት [የሃይማኖት ሥር] ተብሏል:: ለጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በሥጋ አያቱም ተብሏል:: አንድ ቀን እግዚአብሔር መላእክቱን "ብየ አርክ አብርሃም በዲበ ምድር - በምድር ላይ ወዳጄ አብርሃም አለ::" አላቸው:: ያን ጊዜ ዘጠና ዘጠኙ ነገደ መላእክት ፈጣሪያቸውን አመሰገኑ :- ◉ "አብርሃም አርከ እግዚአብሔር [አብርሃም የእግዚአብሔር ወዳጅ]" ◉ "አብርሃም ብእሴ እግዚአብሔር [አብርሃም የእግዚአብሔር ሰው]" ◉ "አብርሃም ገብረ እግዚአብሔር [አብርሃም የእግዚአብሔር አገልጋይ]" ◉ "አብርሃም ምዕመነ እግዚአብሔር [አብርሃም የእግዚአብሔር ታማኝ] ◉ "አብርሃም ፍቁረ እግዚአብሔር [አብርሃም የእግዚአብሔር ተወዳጁ ነው::] እያሉ አሰምተው ተናግረዋል:: አባታችን አብርሃም በክብር: በቅድስናና በሞገስ ከዘፍጥረት እስከ ዮሐንስ ራእይ ድረስ ተጠቅሷል:: ፈጣሪ በስሙ ለቅዱሳን ተለምኗል:: ስለ ክብሩም በሲዖል ውስጥ እንኳ ማረፊያን ሠርቶለታል:: አጋንንትም ሊቀርቡት አልተቻላቸውም:: ያረፈውም ከክርስቶስ ልደት አንድ ሺ ዘጠኝ መቶ ዓመታት በፊት ነው:: እድሜውም መቶ ሰባ አምስት ዓመት ነበር:: ◉ ፍቅሩን የተረዱ ሊቃውንት ድንግል ማርያምን "ሐይመቱ [ድንኳኑ] : ተናግዶቱ [እንግድነቱ] ለአብርሃም" ሲሉ አመስግነዋታል:: ሊቁም :- † "አብርሃም ፍጹም በሒሩት ወበአምልኮ: እግዚአብሔር አዕበየከ ወባረከከ ባርኮ: እስከ ሰመየከ ዲበ ምድር አርኮ::" ብሎ በምሥጢር ገልጾታል:: [ 🕊 † ቅዱስ ይስሐቅ ርዕሰ አበው † 🕊 ] † የደግ ዛፍ ፍሬ: የአብርሃም ልጅ ደጉ ይስሐቅ እጅግ ንጹሕ በመሆኑ የወልድ ክርስቶስ ምሳሌ ተብሏል:: የይስሐቅ ልደት እጅግ የተጠበቀ ከመሆኑ ባሻገር የተፈጸመውም በብሥራተ አምላክ ነው:: ስሙንም ያወጡለት ሥላሴ ናቸው:: ቡሩክ ይስሐቅ በብዙ ነገሩ ድንቅ ነው:: ለእርሱ ሃያ ዓመት ለአባቱ መቶ ሃያ ዓመት በሆናቸው ጊዜ ጭንቅ ትዕዛዝ ከፈጣሪ ዘንድ ተሰማ:: አብርሃም ይሰዋው ዘንድ ወደ ደብረ ምሥጢር ይዞት ከወጣ በኋላ መስዋዕቱ እርሱ እንደ ሆነ አወቀ:: ለፈጣሪውና ለአባቱ ይታዘዝ ዘንድ "እሺ" አለ:: በዚያውም ላይ አባቱን "አባ ስንፈራገጥ እንዳልጐዳህ እሠረኝ:: ዓይኔን አይተህ እንዳትራራ በሆዴ አስተኛኝ::" አለው:: አቤት ትሕትና! አቤት መታዘዝ! ወዮ አባታችን ይስሐቅ! ቅንነትህ ምን ይደንቅ! ለዚህ አነጋገርህ አንክሮ ይገባል! † "ሰላም ለይስሐቅ ዘኢያግዘፈ ክሳዶ: ለደኒን ወለተሐርዶ" እንዲል:: ቸር ፈጣሪ ግን የአብርሃምን አምልኮ: የይስሐቅን ንጹሕ መታዘዝ ለዓለም ገለጠ እንጂ እንዲሞት አላደረገም:: ቅዱስ ይስሐቅ በዚህች ዓለም ለመቶ ሰማንያ ዓመታት: በትዳር ደግሞ ለመቶ ሃያ ዓመታት ቆይቷል:: ከቅድስናው የተነሳ በእነዚህ ጊዜያት ከአንድ ቀን በቀር ከሚስቱ ርብቃ ጋር አልተኛም:: በዚህቺው ዕለትም ያዕቆብና ኤሳው ተጸንሰዋል:: እግዚአብሔር በመቶ ሰማንያ ዓመቱ ወደ ሰማይ ይዞት ወጣ:: በዚያም ግሩም ምሥጢርን ተመለከተ:: በእሳት መጋረጃ መካከል አብርሃምን አየው:: ከአምላክ ዙፋንም እንዲህ የሚል ቃል ወጣ:: † 🕊 "ወዳጄን ይስሐቅን የሚያከብረውን አከብረዋለሁ:: † 🕊 ልጁን አምኖ "ይስሐቅ" ብሎ የሚጠራውን † 🕊 በስሙ ለነዳያን የሚራራውን † 🕊 ለቤቱ እጣን ያመጣውን † 🕊 በዚህች ሌሊት በጸሎት የተጋውን † 🕊 'አምላከ ይስሐቅ' እያለ መቶ [ ፻ ] ጊዜ የሰገደውን † 🕊 ዜና ይስሐቅን የጻፈውን: ያነበበውን ሁሉ በመንግስተ ሰማያት ዋጋውን እከፍለዋለሁ:: ይህንንም ልጁ [አባታችን ያዕቆብ] ተመልክቶ ከትቦታል:: ቅዱስ ይስሐቅም ከንጽሕናው ሳይጐድል በበረከት እንዳጌጠ ዐርፏል:: † ወገኖቼ ! ከላይ ካነበባችሁት መርጣችሁ አንዷን በእምነት እንድትፈጽሙ አደራ እላለሁ !
177
19
+1
No text...
298
20
[ ስንክሳር ነሐሴ - ፳፯ - ] .mp3
254