Debtera Media
ደብተራ ሚዲያ የእውነት ድምጽ! ሰብስክራይብ በማድረግ ቤተሰብ ይሁኑ!👇 በዩቲዩብ 👉 https://bit.ly/3bMfT8D በፌስቡክ 👉 fb.me/DebteraMedia በቴሌግራም 👉 t.me/DebteraMedia ማንኛውንም ሃሳብ አስተያየት ሆነ መረጃ በ t.me/DebteraMedia_Bot ማድረስ ትችላላችሁ።
Більше6 136
Підписники
-524 години
-297 днів
-12030 днів
- Підписники
- Перегляди допису
- ER - коефіцієнт залучення
Триває завантаження даних...
Приріст підписників
Триває завантаження даних...
09:02
Відео недоступнеДивитись в Telegram
†
🕊
† እንኳን ለእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ዓመታዊ በዓል በሰላም አደረሳችሁ ፣ አደረሰን። † በዚሕች ቀን ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከድንግል እናቱ እግር ሥር ጠበል አፍልቋል::
🕊 † የጠበል በዓል † 🕊
[ ለእህታችን የተፈጸመ ድንቅ ተአምር ]
በአንጀት ካንሰር በሽታ በጽኑ ታማ ለስምንት ዓመታት በጽናት እግዚአብሔርን ስትማጸን ቆይታ በሸንኮራ ቅዱስ ዮሐንስ ጸበል የተፈወሰችና ተአምር የተፈጸመላት እህታችን ታሪክ
[ ክፍል - ፩ - ]
† አምላከ ቅዱሳን ከደዌ ሥጋ : ከደዌ ነፍስ በምሕረቱ ይሠውረን:: ከድንግል እመቤታችን በረከትም ያሳትፈን::
† † †
💖 🕊 💖
11.04 MB
07:16
Відео недоступнеДивитись в Telegram
†
🕊
† እንኳን ለእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ዓመታዊ በዓል በሰላም አደረሳችሁ ፣ አደረሰን። †
በዚሕች ቀን ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከድንግል እናቱ እግር ሥር ጠበል አፍልቋል::
🕊 † የጠበል በዓል † 🕊
[ ለእህታችን የተፈጸመ ድንቅ ተአምር ]
በአንጀት ካንሰር በሽታ በጽኑ ታማ ለስምንት ዓመታት በጽናት እግዚአብሔርን ስትማጸን ቆይታ በሸንኮራ ቅዱስ ዮሐንስ ጸበል የተፈወሰችና ተአምር የተፈጸመላት እህታችን ታሪክ
[ ክፍል - ፪ - ]
† አምላከ ቅዱሳን ከደዌ ሥጋ : ከደዌ ነፍስ በምሕረቱ ይሠውረን:: ከድንግል እመቤታችን በረከትም ያሳትፈን::
† † †
💖 🕊 💖
8.97 MB
Фото недоступнеДивитись в Telegram
†
🕊 † የጠበል በዓል † 🕊
🕊
† ዳግመኛ ዕለቱ የጠበል በዓል ተብሎም ይታሠባል:: ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ስለ ጠበል ፈዋሽነት ሁሌ ብታስተምርም በዚህ ቀን ግን ልዩ ትኩረቷ ታደርገዋለች::
እግዚአብሔር በምክንያትም አለምክንያትም መፈወስ ይችላል:: ያለ ምክንያት በቃሉና በወዳጆቹ ቃል አድሮ "ዳን" ይላል:: ወይም ደግሞ በምክንያት በእመት [እምነት] : በጠበል : ቅዱስ ቃሉን በመስማት : በመስቀሉና በመጻሕፍት በመባረክ [በመታሸት] : በቅዱሳን አካል [በልብሳቸው : በበትራቸው : በጥላቸው በአጽማቸው . . .] ይፈውሳል::
እርሱ እግዚአብሔር ነውና በወደደውና በመረጠው አድሮ ያድናል [ይፈውሳል]:: [፪ነገ.፭፥፲ (5:10) , ሐዋ.፫፥፮ (3:6) , ፭፥፲፭ (5:15) , ፲፱፥፲፩ (19:11)]
† ዛሬ ግን የጠበል ፈዋሽነት በጉልህ ይነገራል:: [ዮሐ.፭፥፩ (5:1) , ፱፥፯ (9:7) ]
† አምላከ ቅዱሳን ከደዌ ሥጋ : ከደዌ ነፍስ በምሕረቱ ይሠውረን:: ከድንግል እመቤታችን በረከትም ያሳትፈን::
† † †
💖 🕊 💖
👍 2
Фото недоступнеДивитись в Telegram
†
🕊 💖 ሰ ላ ም ታ 💖 🕊
❝ ክርስቶስ ተንስአ እሙታን
▸ በዐቢይ ኃይል ወስልጣን ፤
አሠሮ ለሰጣን
▸ አግዐዞ ለአዳም ፤
ሰላም
▸ እምይእዜሰ ፤
ኮነ
▸ ፍስሐ ወሰላም ❞
🕊
❝ ክርስቶስ በታላቅ ኃይልና ስልጣን ከሙታን ተነሳ ፤ ሰይጣንን አሰረው ፤ አዳምንም ነጻ አወጣው ፤ ስለዚህም ከእንግዲህ ወዲህ ፍፁም ሰላም እና ደስታ ሆነ። ❞
▬▬▬▬▬▬ † ▬▬▬▬▬▬
[ 🕊 እነሆ ሁሉም አዲስ ሆነ ! 🕊 ]
† † †
💖 🕊 💖
❝ እግዚኦ መኑ ከማከ ሙታነ አንሣእከ በቃልከ እግዚኦ መኑ ከሚከ ሕይወተ ወሀብከ ሰላመ ለነ ጸጎከ እግዚኦ መኑ ከማከ ንግበር በዓለ ፋሲካ ኵልነ ምስለ ጻድቃኒከ ኅቡረ ፤ ❞
ትርጉም ፦
[ ጌታ ሆይ እንዳንተ ማነው ! ? በቃልህ ሙታንን አነሣህ ፣ ጌታ ሆይ እንዳንተ ማነው ! ? ሕይወትን ሰጠህ ለኛም ሰላም አደልህ ጌታ ሆይ እንዳንተ ማን ነው ! ? የፋሲካን በዐል ከጻድቃንህ ጋር በጋራ በመሆን ሁላችን እናከብራለን። ]
[ ድጓ ዘፋሲካ ]
† † †
💖 🕊 💖
🕊
[ † እንኳን ለእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ዓመታዊ በዓል በሰላም አደረሳችሁ ፣ አደረሰን። † ]
† በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን! †
† በዓሉ ከሰላሳ ሦስቱ ዓበይት የእመቤታችን በዓላት አንዱ ሲሆን በዚሕች ቀን ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከድንግል እናቱ እግር ሥር ጠበል አፍልቋል::
† ጥንተ ነገሩስ እንደ ምን ነው ቢሉ :-
ድንግል ማርያም አምላክ ልጇን አዝላ ስደት ወጥታ ምድረ ግብጽ ትደርሳለች:: በወቅቱ ከደረሱባት ችግሮች አንዱ ደግሞ ረሃብና ጽሙ ነበር:: እንኳን ለስደተኛ በቤቱ ላለም ረሃብና ጥም እንዴት እንደሚከብድ የደረሰበት ያውቀዋል::
† ለዛም ነው ሊቁ በቅዳሴው :-
"አዘክሪ ድንግል ረሃበ ወጽምዐ : ምንዳቤ ወኀዘነ : ወኩሎ ዐጸባ ዘበጽሐኪ ምስሌሁ" ያለው::
ታዲያ አንድ ቀን የበርሃው ፀሐይ አቃጥሏቸው ባረፉበት ድንግል እመቤታችን ውኃ ልመና ወጣች:: ብዙ ለመነች : ግን ጥርኝ እንኳ የሚሠጣት አጥታ በሐዘን ተመለሰች:: ስትመለስ ግን ይባስ ብሎ የልጇን ጫማ ሽፍቶች ወስደውት ደረሰች::
ያን ጊዜ ልጇን ታቅፋ "ውኃ ሳላገኝልሕ : ጫማሕንም አሰረቅኩብህ" ብላ ምርር ብላ አልቅሳለች::
"በከየት ወትቤ ማርያም ማዕነቅ::
እምሰብአ ሃገር አልቦ ዘየአምራ ለጽድቅ::
ሰአልክዎሙ ማየ ኢወሀሐቡኒ በሕቅ::
ወአሕጎልኩ ለወልድየ አሳእኖ ዘወርቅ::" እንዳለ ደራሲ::
ይሕንን የተመለከተ ልጇ የቆመችበትን መሬት ቢባርከው ሕይወትነት ያለው ማይ [ጠበል] ፈለቀ:: ጌታችን : እመቤታችን: ዮሴፍና ሰሎሜ ከውኃው ጠጥተዋል::
ሲሔዱ ግን ለእንግዶች ጣፋጭ [መድኃኒት] : ለአካባቢው ሰዎች ግን መራራ ሁኗል::
"ከመ ኢይስተይዋ ሰብአ ሐገር ለይእቲ ማይ አምረራ::
ወለርኁቃንሰ ፈውሰ ወጥዕምተ ገብራ::" እንዳለ መጽሐፍ:: [ሰቆቃወ ድንግል]
ከመቶዎች ዓመታት በኋላም ጌታ ጠበል ያፈለቀበት : ድንግል እመቤታችን የቆመችበት ቦታ ላይ በእመ ብርሃን ስም ቤተ ክርስቲያን ታንጿል:: ቅዳሴ ቤቱም ተከብሯል:: ጠበሉም ሲባርክና ሲፈውስ ይኖራል::
† 🕊 የጠበል በዓል 🕊 †
† ዳግመኛ ዕለቱ የጠበል በዓል ተብሎም ይታሠባል:: ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ስለ ጠበል ፈዋሽነት ሁሌ ብታስተምርም በዚህ ቀን ግን ልዩ ትኩረቷ ታደርገዋለች::
እግዚአብሔር በምክንያትም አለምክንያትም መፈወስ ይችላል:: ያለ ምክንያት በቃሉና በወዳጆቹ ቃል አድሮ "ዳን" ይላል:: ወይም ደግሞ በምክንያት በእመት [እምነት] : በጠበል : ቅዱስ ቃሉን በመስማት : በመስቀሉና በመጻሕፍት በመባረክ [በመታሸት] : በቅዱሳን አካል [በልብሳቸው : በበትራቸው : በጥላቸው በአጽማቸው . . .] ይፈውሳል::
እርሱ እግዚአብሔር ነውና በወደደውና በመረጠው አድሮ ያድናል [ይፈውሳል]:: [፪ነገ.፭፥፲ (5:10) , ሐዋ.፫፥፮ (3:6) , ፭፥፲፭ (5:15) , ፲፱፥፲፩ (19:11)]
† ዛሬ ግን የጠበል ፈዋሽነት በጉልህ ይነገራል:: [ዮሐ.፭፥፩ (5:1) , ፱፥፯ (9:7) ]
† አምላከ ቅዱሳን ከደዌ ሥጋ : ከደዌ ነፍስ በምሕረቱ ይሠውረን:: ከድንግል እመቤታችን በረከትም ያሳትፈን::
🕊
[ † ሰኔ ፰ [ 8 ] ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት ]
፩. የእመቤታችን ድንግል ማርያም ቅዳሴ ቤት
፪. የቅዱስ ውኃ (ጠበል) መታሠቢያ
፫. ቅድስት ትምዳ እናታችን
፬. ቅዱስ አውሎጊስ
፭. አባ አትካሮን
[ † ወርኀዊ በዓላት ]
፩. ቅዱስ ሙሴ ሊቀ ነቢያት
፪. ኪሩቤል [ አርባዕቱ እንስሳ ]
፫. አባ ብሶይ [ ቢሾይ ]
፬. አቡነ ኪሮስ
፭. አባ ሳሙኤል ዘደብረ ቀልሞን
፮. ቅዱስ ማትያስ ሐዋርያ [ከአሥራ ሁለቱ ሐዋርያት]
† " ለእግዚአብሔር ክብርን ስጡ:: ግርማው በእሥራኤል ላይ: ኃይሉም በደመናት ላይ ነው:: እግዚአብሔር በቅዱሳኑ ላይ ድንቅ ነው:: የእሥራኤል አምላክ እርሱ ኃይልን: ብርታትንም ለሕዝቡ ይሰጣል:: እግዚአብሔርም ይመስገን:: " † [መዝ. ፷፯፥፴፬]
† ወስብሐት ለእግዚአብሔር †
† ወለወላዲቱ ድንግል †
† ወለመስቀሉ ክቡር †
[ ዲ/ን ዮርዳኖስ አበበ ]
† † †
▬▬▬▬▬ ▬▬▬ ▬▬▬▬▬
💖 🕊 💖
👍 1