Debtera Media
Відкрити в Telegram
ደብተራ ሚዲያ የእውነት ድምጽ! ሰብስክራይብ በማድረግ ቤተሰብ ይሁኑ!👇 በዩቲዩብ 👉 https://bit.ly/3bMfT8D በፌስቡክ 👉 fb.me/DebteraMedia በቴሌግራም 👉 t.me/DebteraMedia ማንኛውንም ሃሳብ አስተያየት ሆነ መረጃ በ t.me/DebteraMedia_Bot ማድረስ ትችላላችሁ።
Показати більше3 726
Підписники
-624 години
-137 днів
-7030 день
Триває завантаження даних...
Схожі канали
Хмара тегів
Немає даних
Виникли проблеми? Будь ласка, оновіть сторінку або зверніться до нашого support-менеджера.
Вхідні та вихідні згадування
---
---
---
---
---
---
Залучення підписників
липень '26
липень '26
+24
в 0 каналах
червень '26
+21
в 0 каналах
Get PRO
травень '26
+19
в 0 каналах
Get PRO
квітень '26
+14
в 0 каналах
Get PRO
березень '26
+9
в 1 каналах
Get PRO
лютий '26
+16
в 0 каналах
Get PRO
січень '26
+22
в 0 каналах
Get PRO
грудень '25
+15
в 0 каналах
Get PRO
листопад '25
+19
в 0 каналах
Get PRO
жовтень '25
+24
в 0 каналах
Get PRO
вересень '25
+10
в 0 каналах
Get PRO
серпень '25
+16
в 0 каналах
Get PRO
липень '25
+21
в 0 каналах
Get PRO
червень '25
+17
в 0 каналах
Get PRO
травень '25
+24
в 0 каналах
Get PRO
квітень '25
+30
в 0 каналах
Get PRO
березень '25
+42
в 0 каналах
Get PRO
лютий '25
+20
в 0 каналах
Get PRO
січень '25
+35
в 0 каналах
Get PRO
грудень '24
+32
в 0 каналах
Get PRO
листопад '24
+18
в 0 каналах
Get PRO
жовтень '24
+21
в 0 каналах
Get PRO
вересень '24
+14
в 0 каналах
Get PRO
серпень '24
+11
в 0 каналах
Get PRO
липень '24
+26
в 0 каналах
Get PRO
червень '24
+16
в 0 каналах
Get PRO
травень '24
+15
в 0 каналах
Get PRO
квітень '24
+25
в 0 каналах
Get PRO
березень '24
+26
в 0 каналах
Get PRO
лютий '24
+15
в 0 каналах
Get PRO
січень '24
+32
в 1 каналах
Get PRO
грудень '23
+68
в 4 каналах
Get PRO
листопад '23
+13
в 0 каналах
Get PRO
жовтень '23
+9
в 0 каналах
Get PRO
вересень '23
+17
в 0 каналах
Get PRO
серпень '23
+28
в 0 каналах
Get PRO
липень '23
+27
в 0 каналах
Get PRO
червень '23
+81
в 0 каналах
Get PRO
травень '23
+32
в 0 каналах
Get PRO
квітень '23
+49
в 0 каналах
Get PRO
березень '23
+28
в 0 каналах
Get PRO
лютий '23
+802
в 0 каналах
Get PRO
січень '23
+1 371
в 0 каналах
Get PRO
грудень '22
+111
в 0 каналах
Get PRO
листопад '22
+280
в 0 каналах
Get PRO
жовтень '22
+17
в 0 каналах
Get PRO
вересень '22
+212
в 0 каналах
Get PRO
серпень '22
+159
в 0 каналах
Get PRO
липень '22
+49
в 0 каналах
Get PRO
червень '22
+523
в 0 каналах
Get PRO
травень '22
+1 661
в 0 каналах
Get PRO
квітень '22
+2 256
в 0 каналах
Get PRO
березень '22
+177
в 0 каналах
Get PRO
лютий '22
+399
в 0 каналах
Get PRO
січень '22
+537
в 0 каналах
Get PRO
грудень '21
+17
в 0 каналах
Get PRO
листопад '21
+20
в 0 каналах
Get PRO
жовтень '21
+120
в 0 каналах
Get PRO
вересень '21
+48
в 0 каналах
Get PRO
серпень '21
+64
в 0 каналах
Get PRO
липень '21
+75
в 0 каналах
Get PRO
червень '21
+86
в 0 каналах
Get PRO
травень '21
+50
в 0 каналах
Get PRO
квітень '21
+78
в 0 каналах
Get PRO
березень '21
+139
в 0 каналах
Get PRO
лютий '21
+128
в 0 каналах
Get PRO
січень '21
+186
в 0 каналах
Get PRO
грудень '20
+6 831
в 0 каналах
| Дата | Залучення підписників | Згадування | Канали | |
| 26 липня | +2 | |||
| 25 липня | +1 | |||
| 24 липня | +1 | |||
| 23 липня | +2 | |||
| 22 липня | +3 | |||
| 21 липня | +3 | |||
| 20 липня | 0 | |||
| 19 липня | +1 | |||
| 18 липня | 0 | |||
| 17 липня | 0 | |||
| 16 липня | 0 | |||
| 15 липня | +1 | |||
| 14 липня | 0 | |||
| 13 липня | 0 | |||
| 12 липня | 0 | |||
| 11 липня | +1 | |||
| 10 липня | +1 | |||
| 09 липня | 0 | |||
| 08 липня | +3 | |||
| 07 липня | 0 | |||
| 06 липня | +3 | |||
| 05 липня | 0 | |||
| 04 липня | +1 | |||
| 03 липня | 0 | |||
| 02 липня | 0 | |||
| 01 липня | +1 |
Дописи каналу
| 2 | ስንክሳር ሐምሌ - ፲፱ - .mp3 | 187 |
| 3 | 🕊
† እንኳን ለቅዱሳኑ ገብርኤል ሊቀ መላእክት : ቂርቆስ ወኢየሉጣ : በጥላን ጠቢብ እና ሰማዕታተ እስና ዓመታዊ በዓል በሰላም አደረሳችሁ፤ አደረሰን። †
† በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን ! †
† 🕊 ቅዱሳን ቂርቆስ ወኢየሉጣ: ወቅዱስ ገብርኤል ሊቀ መላእክት 🕊 †
† ቅድስት ኢየሉጣ እናታችን በዘመነ ሰማዕታት ከነበሩና በዚህ ስም ከሚጠሩ ቅዱሳት አንዷ ናት:: በወቅቱ ቅዱስ ቂርቆስ የሚባል ደግ ልጅ ወልዳ ባሏ ባለመኖሩ በመበለትነት ትኖር ነበር:: የዚያ ዘመን ክርስቲያኖች ለክርስቶስ የነበራቸው ፍቅር ከመነገር በላይ ነው:: በዛው ልክ ደግሞ መከራው በጸጉራቸው ቁጥር ልክ ነበር::
ከሮም ግዛት በአንዱ ከቅዱስ ልጇ ጋር የምትኖረው ቅድስት ኢየሉጣ የስደቱ ዘመን ሲመጣ እርሷም እንደ ሌሎቹ ክርስቲያኖች ተሰደደች:: እስክንድሮስ የተባለው ከሃዲ ንጉሥ ግን ያለችበት ድረስ ተከትሎ እንድትያዝና እንድትቀርብ አደረገ::
ወዲያውም "ስምሽ ማን ይባላል?" ቢላት "ክርስቲያን እባላለሁ" አለችው:: ንጉሡ ተቆጣ:: "መዋቲ ስሜን ከፈለክ ኢየሉጣ ይባላል" አለችው:: ንጉሡ መልሶ "አሁን ለጣዖት ካልሠዋሽ ሲጀመር ስቃይ: ቀጥሎም ሞት ይጠብቅሻል" ቢላት ቅድስቲቱ መልሳ "በከተማ ውስጥ የሦስት ዓመት ሕፃን አለና እርሱን አምጣው:: ማንን ማምለክ እንዳለብን ይነግረናል" አለችው::
አስፈልጐ ቅዱስ ቂርቆስን አስመጣው:: "ስምህ ማን ይባላል?" አለ ንጉሡ:: "ከማይደፈርስ ከንጹሕ ምንጭ የተቀዳ ጥሩ ምንጭ ስሜ ክርስቲያን ይባላል:: መዋቲ ስሜን ከፈለግህ ግን ቂርቆስ ይባላል" አለው::
ንጉሡ ሊያታልለው "ደስ የተሰኘህ ሕፃን" ቢለው ቅዱሱ ሕፃን "ትክክል ተናገርክ: ለእኔ በሰማያት ደስታ ይጠብቀኛል:: አንተ ግን እውነተኛው አምላክ ይፈርድብሃል" አለው:: በሦስት ዓመት ሕፃን አንደበት ዘለፋ የገጠመው ከሃዲ ተቆጣ::
እናትና ልጅን በብዙ መክፈልተ ኩነኔ አሰቃያቸው::
ሰውነታቸውን ቸነከረ: አካላቸውን ቆራረጠ: ዓይናቸውን አወጣ:: ሌላም ሊናገሩት የሚጨንቅ ስቃይን አሰቃያቸው:: በዚህች ቀን ግን ትልቅ ድስት አሰርቶ ባሩድ: አረር: ስብና የመሳሰሉትን ጨምረውበት በእሳት አፈሉት::
የእሳቱ ወላፈን አካባቢውን በላው:: በድስቱ ውስጥ ያለው ነገር እየፈላ ሲገላበጥ እንደ ክረምት ነጐድጓድ ይጮህ ነበር:: የስድስት ሰዓት የእግር መንገድ ድረስም ተሰምቷል:: ቅድስት ኢየሉጣ ይሔኔ ነበር ልቧ ድንግጥ ያለው:: ሕፃኑ ቂርቆስ የእናቱን ፍርሃት ሲመለከት ጸለየ::
"ፈጣሪዬ! ፍሬው ያለ ግንዱ አይቆምምና እኔን እንዳጸናሕ እናቴንም አጽናት" ሲል ለመነ::
"እግዚኦ ትፈቅድኑ ለፍሬሁ ተአልዶ:
እንዘ በእሳት ታውኢ ጉንዶ" እንዲል::
በዚያች ሰዓት ቅድስት ኢየሉጣ ዓይኖቿ ተከፍተው ሰማያዊ ክብርን ተመለከቱና ልቧ ወደ ድፍረቱ ተመለሰ::
ልጇንም "አንተ አባቴ ነህ: አንተን የተሸከመች ማኅጸኔ የተባረከች ናት" አለችው:: ከዚያም ሁለቱንም ወደ ፈላው ድስት ውስጥ ቢጨምሯቸው ፍጡነ ረድኤት ቅዱስ ገብርኤል ከሰማይ ወረደላቸው:: በበትረ መስቀሉ ባርኮ የፈላውን አቀዘቀዘው:: የነደደውን ውኃ አደረገው:: ቅዱሳኑ ቂርቆስና ኢየሉጣ ከብዙ መከራ በኋላ በሰማዕትነት አልፈዋል::
† 🕊 ቅዱስ በጥላን ጠቢብ 🕊 †
† ቅዱሱ ከአሕዛብ ወላጆቹ ተወልዶ: ያደገውም በጣዖት አምልኮ ነው:: በሙያው እጅግ የተመሠከረለት ሐኪም ነበር:: የሃገሩ ሰዎች "ጠቢብ" እያሉም ይጠሩታል:: በጥላን ምንም ጣዖት አምላኪ ቢሆን በተፈጥሮው ተመራማሪና ቅን ነበር::
አንድ ካህንም በጐረቤቱ ነበርና ዘወትር ስለ ሃይማኖት ይከራከሩ ነበር:: ካህኑ ሌሊት ሌሊት ስለ በጥላን ተግቶ ይጸልይ ነበርና ተሳክቶለት አሳመነው::
አንድ ቀን በጥላን መንገድ ሲሔድ እባብ ሰው ነድፎ ለሞት ደርሶ አየውና ጸሎት አድርሶ ስመ ክርስቶስን ቢጠራ የተነደፈው ድኖ እባቡ ሞተ::
በዚህ ተዓምር ደስ ብሎት ወደ ካህኑ ሒዶ ተጠመቀ:: ከዚያም ጾም ጸሎትን ጀመረ:: በየቦታው እየዞረ ሕሙማንን እንደ ቀድሞው በመድኃኒት ሳይሆን በጸሎት ያድናቸው ነበር:: ስላዳናቸውም በርካቶቹ ወደ ክርስትና መጡ::
የአካባቢው ሰው: ወላጆቹን ጨምሮ ክርስቲያኖች ሆኑ:: በመጨረሻም ቅዱስ በጥላን: ቤተሰቦቹ: ካህኑና ከደዌ የዳኑት ወገኖቹ በአካባቢው ጣዖት አምላኪ ንጉሥ ፊት ቀርበው ክርስቶስን ሰብከው በሰማዕትነት ዐርፈዋል::
† 🕊 ቅዱሳን ሰማዕታተ እስና 🕊 †
† እስና ማለት ግብጽ ውስጥ የምትገኝ የቀድሞ አውራጃ ናት:: በ3ኛው መቶ ክ/ዘመን በከተማዋ በርካታ ክርስቲያኖች ይኖሩ ነበር:: የእንዴናው መኮንን መጥቶ "ክርስቶስን ካዱ: ለጣዖት ስገዱ" አላቸው:: ሕዝቡ በአንድ ድምጽ መለሱ:- "ይሕማ ፈጽሞ ሊደረግ አይችልም::" መኮንኑ ተቆጥቶ "ሁሉንም ግደሉ" አለ::
ወታደሮቹ ሰው አልመረጡም:: ከታዘለ ሕፃን አልጋ ላይ እስካለ ሽማግሌ: ከጤነኛ እስከ ሕመምተኛ: ሁሉንም ጨፈጨፏቸው:: ከተማዋ በደም ተነከረች:: ከከተማዋ ክርስቲያኖች ወሬ ለመንገር አንድ ሰው እንኳ አልተረፈም:: ሁሉም ስለ ክርስትና ደማቸውን አፈሰሱ::
† ጌታችን ስለ ሰማዕታቱ ብሎ: ደማቸውንም አስቦ በሃይማኖታችን ያጽናን:: ከመከራም ይሰውረን:: በረከታቸውንም ያድለን::
[ † ሐምሌ ፲፱ [ 19 ] ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት ]
፩. ቅዱስ ገብርኤል ሊቀ መላእክት
፪. ቅዱስ ቂርቆስ ወእሙ ኢየሉጣ
፫. ቅዱስ በጥላን ጠቢብ ሰማዕት እና ማኅበሩ
፬. ቅዱሳን ሰማዕታተ እስና
[ † ወርኀዊ በዓላት ]
፩. ቅዱስ ኤስድሮስ ሰማዕት
፪. አቡነ ዓቢየ እግዚእ ጻድቅ
፫. አቡነ ስነ ኢየሱስ
፬. አቡነ ዮሴፍ ብርሃነ ዓለም
† "ከክርስቶስ ፍቅር ማን ይለየናል? መከራ: ወይስ ጭንቀት: ወይስ ስደት: ወይስ ራብ: ወይስ መራቆት: ወይስ ፍርሃት: ወይስ ሰይፍ ነውን? 'ስለ አንተ ቀኑን ሁሉ እንገደላለን:: እንደሚታረዱ በጐች ተቆጠርን::' ተብሎ እንደተጻፈው ነው::
በዚህ ሁሉ ግን በወደደን በእርሱ ከአሸናፊዎች እንበልጣለን::" † [ሮሜ. ፰፥፴፭-፴፯]
† ወስብሐት ለእግዚአብሔር †
† ወለወላዲቱ ድንግል †
† ወለመስቀሉ ክቡር †
[ ዲ/ን ዮርዳኖስ አበበ ]
† † †
▬▬▬▬▬ ▬▬▬ ▬▬▬▬▬
💖 🕊 💖 | 190 |
| 4 | Немає тексту... | 239 |
| 5 | [ ስንክሳር ሐምሌ - ፲፰ - ] .mp3 | 222 |
| 6 | 🕊
[ † እንኳን ለሐዋርያው ቅዱስ ያዕቆብ ዓመታዊ የዕረፍት በዓል በሰላም አደረሳችሁ ፤ አደረሰን። † ]
† በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን ! †
[ 🕊 † ቅዱስ ያዕቆብ ሐዋርያ † 🕊 ]
† ይህ ቅዱስ ሐዋርያ በአባቶቻችን ሐዋርያት መካከል ትልቅ ሞገስ የነበረውና "የጌታችን ወንድም" ተብሎ የተጠራ ነው:: ቅዱስ ያዕቆብ ወላጅ አባቱ አረጋዊው ቅዱስ ዮሴፍ [የእመቤታችን ጠባቂ] ሲሆን በልጅነቱ የሞተችው እናቱ ደግሞ ማርያም ትባላለች:: በቤት ውስጥም ስምዖን: ዮሳና ይሁዳ የተባሉ ወንድሞችና ሰሎሜ የምትባል እህትም ነበረችው::
እናቱ ማርያም ከሞተች በኋላ ዕጓለ-ማውታ [ደሃ አደግ] ሆኖ ነበር:: ነገር ግን በፈቃደ እግዚአብሔር አረጋዊ ዮሴፍ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያምን ከቤተ መቅደስ ሊጠብቃት [ሊያገለግላት] ተቀብሎ ሲመጣ ያ ቤተሰብ ተቀየረ:: የበረከት: የምሕረትና የሰላም እመቤት የአምላክ እናቱ ገብታለችና ያ የሐዘን ቤት ደስታ ሞላው::
እመ ብርሃን ግን ገና ወደ ዮሴፍ ልጆች ስትደርስ አለቀሰች:: የአክስቷ ልጆች የሚንከባከባቸው አጥተው ቆሽሸው ነበር:: በተለይ ደግሞ ትንሹ ቅዱስ ያዕቆብ ያሳዝን ነበር:: እመ ብርሃን ማረፍ አልፈለገችም:: ወዲያው ማድጋ አንስታ ወደ ምንጭ ወርዳ ውኃ አምጥታ የሕፃኑን ገላ አጠበችው:: [በአምላክ እናት የታጠበ ሰውነት ምስጋና በጸጋ ይገባዋል::]
እመቤታችን ጌታ ከመወለዱ በፊት ለዘጠኝ ወራት: ከተወለደ በኋላ ደግሞ ለሁለት ዓመታት ሕፃኑን ያዕቆብን ተንከባከበችው:: ለሦስት ዓመት ከስድስት ወር ግን ድንግል ማርያም አምላክ ልጇን ይዛ ተሰዳለችና ተለያዩ:: ከስደት መልስ ግን ለሃያ አምስት ዓመታት ቅዱስ ያዕቆብ ከጌታችን ጋር ሲያድግ ወላጅ እናቱ ትዝ ብላው አታውቅም:: አማናዊቷ እናት ከጐኑ ነበረችና::
ሊቃውንት እንደ ነገሩን እመቤታችን ለቅዱስ ያዕቆብ ያልሰጠችው ነገር ቢኖር ሐሊበ ድንግልናዌ [የድንግልና ወተትን] ብቻ ነው:: ስለዚህም :-
"እመ ያዕቆብ በጸጋ ማርያም ንግሥተ ኩሉ" ይላል መጽሐፍ:: [መልክዐ ስዕል]
† ቅዱስ ያዕቆብ "የጌታ ወንድም" ተብሎ በተደጋጋሚ በሐዲስ ኪዳን ተጠርቷል:: ለዚህ ምክንያቱ
፩. ለሰላሳ ዓመታት ሳይነጣጠሉ አብረው በማደጋቸው
፪. የጌታችን የሥጋ አያቱ [የቅድስት ሐና] የእህት ልጅ በመሆኑ
፫. በዮሴፍ በኩልም የአንድ ቅድመ አያት ልጆች በመሆናቸው
፬. ጌታችን ከትህትናው የተነሳ ደቀ መዛሙርቱን "ወንድሞች" ይላቸው ስለ ነበር ነው:: [ሥጋቸውን ተዋሕዶ ተገኝቷልና::]
ራሱ ቅዱስ ያዕቆብ ግን "የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ባሪያ ነኝ" ብሎ በፈጣሪና በፍጡር መካከል ያለውን ልዩነት ገልጧል:: [ያዕ.፩፥፩] ቅዱስ ያዕቆብ ጌታችን ሲያስተምር ተከተለው::
- ከሰባ ሁለቱ አርድእት ተቆጠረ
- ሦስት ዓመት ከሦስት ወር ወንጌልን ተማረ
- ለመጀመሪያ ጊዜ ከድንግል ማርያምና ከቅዱስ ዮሐንስ ጋር ሆኖ "የጌታን ትንሣኤ ሳላይ እህል አልቀምስም" ብሎ ማክፈልን አስተማረ
- መንፈስ ቅዱስን ተሞልቶ ወንጌልን አስተማረ
- የኢየሩሳሌም የመጀመሪያው ሊቀ ጳጳስ ሆኖ አገለገለ
- በመጀመሪያዎቹ የክርስትና ዘመናት የሐዋርያት ሲኖዶሶችን በሊቀ መንበርነት መራ
- ሙታንን አስንስቶ
- ድውያንን ፈውሶ
- የመካኖችን ማኅጸን ከፍቶ: አጋንንትንም አስወጥቶ ብዙ ተዓምራትን ሠራ:: እጅግ ብዙ አይሁዳውያንን ወደ አሚነ ክርስቶስ መልሶ መልካሙን ገድል ተጋደለ::
በመጨረሻ ዘመኑ ያላመኑ የአይሁድ አለቆች ወደ ቤቱ ተሰብስበው "የናዝሬቱ ኢየሱስ ማነው? የማንስ ልጅ ነው?" ሲሉ ጠየቁት:: እነርሱ ሰይጣን በሰለጠነበት ልቡናቸው "የዮሴፍ ልጅ ነው: የእኔም ወንድሜ ነው" እንዲላቸው ጠብቀው ነበር:: [ሎቱ ስብሐት ወአኮቴት]
† በልቡናቸው ያሰቡትን ተንኮል የተረዳው ሐዋርያ ወደ ቤቱ ጣራ ወጥቶ መናገር ጀመረ:: "ለስም አጠራሩ ጌትነት ይሁንና ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ :-
አምላክ :
ወልደ አምላክ :
ወልደ አብ :
ወልደ ማርያም :
ሥግው ቃል :
እግዚአብሔር ነው:: እኔም ፍጡሩና ባሪያው እንጂ እንደምታስቡት ወንድሙ አይደለሁም" አላቸው::
ንዴታቸውን መቆጣጠር ያልቻሉት አይሁድ ከላይ ወጥተው ወደ መሬት ወረወሩት:: በገድል የተቀጠቀጠ አካሉንም እየተፈራረቁ ደበደቡት:: አንዱ ግን ከእንጨት የተሠራ ትልቅ ገንዳ አምጥቶ የቅዱሱን ራስ ደጋግሞ መታው:: ጭንቅላቱም እንዳልነበር ሆነ:: ሰማዕቱ ሐዋርያ ቅዱስ ያዕቆብ ወደ ወደደው ክርስቶስ በዚህች ቀን ሔደ::
ቅዱሱ ሐዋርያ ያዕቆብ ቤቱን እንደ ቤተ መቅደስ አበው ሐዋርያት ይጠቀሙባት ነበር:: በመላ ዘመኑ የሚያገድፍ ነገር [ጥሉላት] ቀምሶ : ጸጉሩን ተላጭቶ : ገላውን ታጥቦና ልብሱን ቀይሮ አያውቅም::
"ወዝንቱ ጻድቅ እኅወ እግዚእነ::
ኢያብአ ውስተ አፉሁ ሥጋ ወወይነ::
ወኢገብረ ሎቱ ክልኤተ ክዳነ" እንዲል::
† ከጾም : ከጸሎትና ከመቆሙ ብዛትም እግሩ አብጦ አላራምድህ ብሎት ነበር:: ስለዚህም አበው "ጻድቁ [ገዳማዊው] ሐዋርያ" ይሉታል::
† ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ወንድሙ ይባል ዘንድ ካደለው ሐዋርያ በረከትን ያድለን:: በምልጃውም ምሕረትን ይላክልን::
[ † ሐምሌ ፲፰ [ 18 ] ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት ]
፩. ቅዱስ ያዕቆብ ሐዋርያ [ ከሰባ ሁለቱ አርድእት-የመጀመሪያው የኢየሩሳሌም ሊቀ ጳጳሳት ]
፪. ቅዱስ አትናቴዎስ ሰማዕት
፫. ቅዱስ እንድራኒቆስ ሰማዕት
፬. ዘጠኝ ሺህ ሰማዕታት [የቅዱስ ኤስድሮስ ማኅበር]
[ † ወርኀዊ በዓላት ]
፩. ቅዱስ ፊልጶስ ሐዋርያ
፪. አቡነ ኤዎስጣቴዎስ ሰባኬ ሃይማኖት [ ረባን ]
፫. አቡነ አኖሬዎስ ዘደብረ ጽጋጋ
፬. ማር ያዕቆብ ግብጻዊ
† "የእግዚአብሔርና የጌታ የኢየሱስ ክርስቶስ ባሪያ ያዕቆብ: ለተበተኑ ለአሥራ ሁለቱ ወገኖች:: ሰላም ለእናንተ ይሁን:: ወንድሞቼ ሆይ! የእምነታችሁ መፈተን ትዕግስትን እንዲያደርግላችሁ አውቃችሁ ልዩ ልዩ ፈተና ሲደርስባችሁ እንደ ሙሉ ደስታ ቁጠሩት:: ትዕግስትም ምንም የሚጐድላችሁ ሳይኖር ፍጹማንና ምሉዓን ትሆኑ ዘንድ ሥራውን ይፈጽም::" † [ ያዕ. ፩፥፩ ]
† ወስብሐት ለእግዚአብሔር †
† ወለወላዲቱ ድንግል †
† ወለመስቀሉ ክቡር †
[ ዲ/ን ዮርዳኖስ አበበ ]
† † †
▬▬▬▬▬ ▬▬▬ ▬▬▬▬▬
💖 🕊 💖 | 214 |
| 7 | Немає тексту... | 146 |
| 8 | Ye TSADIKAN KETEMA.mp3 | 138 |
| 9 | 🩵 † 🩵
🌸 ❝ ቅዱስ ያዕቆብ ሐዋርያዊ ! ❞ 🌸
💛 💛
† እንኳን ለሐዋርያው ቅዱስ ያዕቆብ ዓመታዊ የዕረፍት በዓል በሰላም አደረሳችሁ ፤ አደረሰን። †
🕊 🕊
❝ ከሐዋርያት ጵጵስናን የተቀበለ በአብያተ ክርስቲያናት ውስጥ መሾሙ የቀደመ በሥጋ ዝምድና የጌታችን ወንድም ለኾነ ለያዕቆብ ሰላምታ ይገባል። ❞
[ አቤቱ የሐዋርያት ተከታዮቻቸው ስለኾኑ ስለ ሰባ ኹለቱ አርድእት ብለኽ በምሕረትኽ ዐስበኝ። ... ስለ እነርሱ ማረኝ ፤ እኔን አገልጋይኽንም በሀገራቸው ውስጥ ከነርሱ ጋር ዕድል ፈንታዬን ጽዋ ተርታዬን አድርግ ፤ አሜን። ]
[ ተአምኆ ቅዱሳን ]
▬▬▬▬▬▬ ♱ ▬▬▬▬▬▬
[ ከመልዕክቱ ]
❝ ወንድሞቼ ሆይ ፥ እምነት አለኝ የሚል ፥ ሥራ ግን የሌለው ሰው ቢኖር ምን ይጠቅመዋል ? እምነቱስ ሊያድነው ይችላልን ? . . . እግዚአብሔር አንድ እንደ ሆነ አንተ ታምናለህ ፤ መልካም ታደርጋለህ ፤ አጋንንት ደግሞ ያምናሉ ይንቀጠቀጡማል።
አንተ ከንቱ ሰው ፥ እምነት ከሥራ ተለይቶ የሞተ መሆኑን ልታውቅ ትወዳለህን ? ❞ [ ያዕ.፪፥፲፬ ]
🕊
[ † ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ወንድሙ ይባል ዘንድ ካደለው ሐዋርያ በረከትን ያድለን:: በምልጃውም ምሕረትን ይላክልን:: † ]
════════════════
†††
✟𝐎𝐑𝐓𝐇𝐎𝐃𝐎𝐗Y✟
🕊 💖 🕊 | 140 |
| 10 | Немає тексту... | 129 |
| 11 | [ + የነፍስ ነጻነት + ] .mp3 | 130 |
| 12 | 🍒 🍒
🕊 ም ክ ረ ቅ ዱ ሳ ን 🕊
═══════════════
▷ ❝ የ ነ ፍ ስ ነ ፃ ነ ት ! ! ❞
[ 💛 በብፁዕ አቡነ ሺኖዳ ሣልሳዊ 💛 ]
🕊 🍒 🕊
❝ አሁን ግን ከኃጢአት አርነት ወጥታችሁ ለእግዚአብሔርም ተገዝታችሁ ፥ ልትቀደሱ ፍሬ አላችሁ ፤ መጨረሻውም የዘላለም ሕይወት ነው። ❞ [ ሮሜ.፮፥፳፪ ]
════════════════
†††
✟𝐎𝐑𝐓𝐇𝐎𝐃𝐎𝐗Y✟
🕊 💖 🕊
👇 | 149 |
| 13 | 🕊
[ ማረሚያ ! ]
አስቀድሞ ቀርቦ የነበረው የሐዋርያው ቅዱስ ያዕቆብ ዓመታዊ የዕረፍት በዓሉን የተመለከተ ፖስት በስህተት በመሆኑ የቅዱሱ ዓመታዊ የዕረፍት በዓሉ ሐምሌ 17 [ ፲፯ ] ሳይሆን ከነገ ወዲያ ሐምሌ 18 [ ፲፰ ] እንደሆነ እንረዳ።
▬▬▬▬▬▬ ♱ ▬▬▬▬▬▬ | 199 |
| 14 | Немає тексту... | 213 |
| 15 | [ ስንክሳር ሐምሌ - ፲፯ - ] .mp3 | 196 |
| 16 | 🕊
በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ ፡፡ አሜን ፡፡
[ † እንኩዋን ለነቢዩ ቅዱስ ዮናስ እና ለእናታችን ቅድስት አውፎምያ ዓመታዊ የዕረፍት በዓል በሰላም አደረሳችሁ † ]
🕊 † ቅዱስ ዮናስ ነቢይ † 🕊
በቤተ ክርስቲያን አስተምሕሮ ከ፲፪ [12] ቱ ደቂቀ ነቢያት አንዱ የሆነው ቅዱስ ዮናስ ከክርስቶስ ልደት ፰ መቶ [800] ዓመታት በፊት እንደ ነበረ ይታመናል:: ሊቃውንት እንዳስተማሩን ደግሞ እናቱ ቅዱስ ኤልያስን የመገበችው የሰራፕታዋ መበለት ናት:: ቅዱስ ዮናስ ገና ሕጻን ሳለ በእሥራኤል ምድር ዝናብ ለ፫ [3] ዓመታት ከ፮ [6] ወራት ተከልክሎ ነበር::
ይሕንንም ያደረገው ደጉ ነቢይ ኤልያስ ለአምልኮተ እግዚአብሔር ቀንቶ ነው:: በወቅቱ ኤልያስ በሰራፕታ ሳለ ሕጻኑ ዮናስ ታሞ ሞተ:: ልጇ የሞተባት መበለትም ኤልያስን ለመነችው:: ኤልያስም ወደ ፈጣሪው ማልዶ ሕጻኑን ዮናስን ከሞት አስነስቶታል:: ትንሽ ከፍ ባለ ጊዜም ከጉዋደኞቹ [ከነቢያቱ] አብድዩና ኤልሳዕ ጋር ሆነው ታላቁን ነቢይ ኤልያስን ተከትለውታል::
ኤልያስ ካረገ በሁዋላ ሁሉም በየተሰጣቸው አገልግሎት ተሠማርተዋል:: ቅዱስ ዮናስን እግዚአብሔር "ወደ ነነዌ ሒደሕ ንስሃን ስበክ" አለው:: ዮናስ ግን የፈጣሪውን መሐሪነት ጠንቅቆ ያውቃልና አልሔድም አለ:: [ተመልከቱ የየዋሕነት ብዛት]
እግዚአብሔር እየደጋገመ እንዲሔድ ሲነግረው ነቢዩ "እንዲሕ የሚዘበዝበኝ ከፊቱ ብቀመጥ አይደል" ብሎ ሊኮበልል ወጣ:: ነገር ግን አልቀናውም:: በእርሱ ምክንያት ማዕበል ተነሳ:: ሕዝቡም ሊያልቁ ሆነ:: ከእንቅልፉ የነቃው ዮናስ ከመርከቡ ላሉት አሕዛብ አምልኮተ እግዚአብሔርን ሰብኮላቸው: በእርሱ ጠያቂነት ሐምሌ ፲፭ [ 15 ] ቀን ወደ ባሕር ጥለውታል::
አሣ አንበሪም ተቀብሎታል:: በግዙፉ አሣ ውስጥም ያለ እንቅልፍ በጾም: በጸሎትና በምስጋና ፫ [3] ለቀን ቆይቷል:: ሙስና ሳያገኘውም በዚህች ቀን አሣ አንበሪው ነነዌ ዳር ላይ ተፍቶታል:: ቅዱስ ዮናስ እግዚአብሔር እንዳዘዘው "እስከ ሠሉስ ዕለት ትትገፈታእ ነነዌ ዓባይ ሃገር" [እስከ ሦስት ቀን ድረስ ነነዌ ትገለበጣለች [ዮናስ ፫፥፬ [3:4] ብሎ አሰምቶ ሰበከ::
የነነዌ ሰዎችም በስብከተ ዮናስ አምነው: ንስሃም ገብተው ድነዋል:: በዚህም ጌታችን በወንጌል ላይ አመስግኗቸዋል:: ቅዱስ ዮናስ መኮብለሉ በሐዲስ ኪዳን ለሚደረገው ምስጢረ ትንሳኤ ጥላ [ምሳሌ] ነውና ይደነቃል:: [ማቴ.፲፪፥፴፰] [12:38] ነቢዩ ግን በተረፈ ሕይወቱ ሕዝቡን ሲያስተምር: ፈጣሪውን ሲያገለግል ኑሮ በመልካም ሽምግልና ዐርፏል::
† 🕊 ቅድስት አውፎምያ ሰማዕት 🕊 †
እናታችን ቅድስት አውፎምያ [ስሟ አፎምያ አይደለም:: በስሕተት "ው" መካከል ላይ የገባች እንዳይመስልዎ:: እስመ ከመዝ ስማ-ስሟ እንዲሁ ነው የሚጠራው] በ፫ [3]ኛው መቶ ክ/ዘመን ከነበሩ ወጣት ክርስቲያኖች አንዷ ናት:: ገና ከልጅነቷ ልቧ በፍቅረ ክርስቶስ የተነደፈ ነበር::
በዚህም ምክንያት ራሷን በጾምና በጸሎት ወስና ትኖር ነበር:: እድሜዋ ገና በአሥራዎቹ ቢሆንም በመንኖ ጥሪት መኖር ምርጫዋ ነበር:: ሊቃውንት አበው ከሰማዕትነቷ ደርበው "ጻድቅት አውፎምያ" እያሉም ይጠሯታል::
አንድ ቀን ግን መንገድ ወጥታ ነበርና ክርስቲያኖች ሲሰቃዩ ተመለከተች:: ምንም ጥፋት ሳይገኝባቸው ክርስቶስን ስላመለኩ ብቻ ይሙት በቃ ተፈርዶባቸው ሊገደሉ እየተወሰዱ ነበር:: አሕዛብ ግብራቸው የአውሬ ነውና ርሕራሔ የላቸውም:: ሰማዕታቱ ደማቸው በየመንገዱ እየፈሰሰ ጥቁር ሰንሰለት በአንገታቸው: በእጃቸውና በእግራቸው ላይ አድርገው ይጐትቷቸው ነበር::
ቅድስት አውፎምያ የተደረገውን ሁሉ ተመልክታ አምርራ አለቀሰች:: ፈጠን ብላም ወደ መኮንኑ ቀርባ ገሰጸችው::
"አንተ አእምሮ የጎደለህ ! እንዴት ክርስቲያኖችን እንዲህ ታሰቃያለህ? አምላካቸው ጌታ ክርስቶስ ታጋሽ ባይሆን ኑሮ በቅጽበት ከገጸ ምድር ባጠፋህ ነበር" አለችው::
በድፍረቷ የተገረመው መኮንኑ "አንቺስ ማንን ታመልኪያለሽ?" ሲል ጠየቃት:: እርሷም "ሰማይና ምድርን የፈጠረውን: ስለ እኛ ሲል በቀራንዮ አንባ የተሠዋውን ኢየሱስ ክርስቶስን አመልካለሁ" ስትል መለሰችለት:: በዚያች ሰዓት የመኮንኑ ቁጣ በቅድስቷ ላይ ነደደ::
ነገር ግን ቁጣውን ከቁም ነገር አልቆጠረችውምና እንዲያሰቃዩዋት አዘዘ:: ወታደሮቹ ሥጋዋን በብዙ አሰቃዩ:: ብላቴናዋ አውፎምያ ግን ጽንዕት ናትና አልቻሏትም:: በመጨረሻ በእሳት ተቃጥላ ትሞት ዘንድ ተፈረደባት::
እሳቱ ከመሬት ከፍ ባለ ጊዜ ወደ ውስጥ ወረወሯት:: በእሳቱ መካከል ቁማ ለረዥም ጊዜ ጸለየች:: ከዚያም ነፍሷን አሳልፋ ሰጠች:: ምዕመናን በክብር ገንዘው ቀብረዋታል::
አምላካችን ከነቢዩና ከሰማዕቷ ወዳጆቹ በረከት ይክፈለን::
[ † ሐምሌ ፲፯ [ 17 ] ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት † ]
፩. ቅዱስ ዮናስ ነቢይ [ ከአሣ አንበሪ ሆድ የወጣበት ]
፪. ቅድስት አውፎምያ [ ጻድቅትና ሰማዕት ]
፫. ቅዱስ ዮስጦስ ሰማዕት [ ታላቁ ]
፬. ቅዱስ ዘካርያስ
[ † ወርኀዊ በዓላት ]
፩. ቅዱስ እስጢፋኖስ ሊቀ ዲያቆናት [ቀዳሜ ሰማዕት ]
፪. ቅዱስ ያዕቆብ ሐዋርያ [ወልደ ዘብዴዎስ]
፫. ቅዱሳን አበው መክሲሞስና ዱማቴዎስ
፬. አባ ገሪማ ዘመደራ
፭. አባ ዸላሞን ፈላሢ
፮. አባ ለትጹን የዋህ
፯. ቅዱስ ኤዺፋንዮስ ሊቅ [ዘደሴተ ቆዽሮስ]
" በዚያን ጊዜ ከጻፎችና ከፈሪሳውያን አንዳንዶቹ መለሱና:- 'መምሕር ሆይ! ከአንተ ምልክት እንድናይ እንወዳለን' አሉት:: እርሱ ግን መልሶ እንዲህ አላቸው:- 'ክፉና አመንዝራ ትውልድ ምልክት ይሻል:: ከነቢዩም ከዮናስ ምልክት በቀር ምልክት አይሰጠውም:: ዮናስ በአሣ አንበሪ ሆድ ሦስት ቀንና ሦስት ሌሊት እንደ ነበረ እንዲሁ የሰው ልጅ በምድር ልብ ሦስት ቀንና ሦስት ሌሊት ይኖራል:: የነነዌ ሰዎች በፍርድ ቀን ከዚህ ትውልድ ጋር ተነስተው ይፈርዱበታል:: በዮናስ ስብከት ንስሃ ገብተዋልና:: እነሆም ከዮናስ የሚበልጥ ከዚህ አለ::" [ማቴ.፲፪፥፴፰]
† ወስብሐት ለእግዚአብሔር †
† ወለወላዲቱ ድንግል †
† ወለመስቀሉ ክቡር †
[ ዲ/ን ዮርዳኖስ አበበ ]
† † †
▬▬▬▬▬ ▬▬▬ ▬▬▬▬▬
💖 🕊 💖 | 184 |
| 17 | Немає тексту... | 134 |
| 18 | Ye TSADIKAN KETEMA.mp3 | 131 |
| 19 | 🩵 † 🩵
🌸 ❝ ቅዱስ ያዕቆብ ሐዋርያዊ ! ❞ 🌸
💛 💛
† እንኳን ለሐዋርያው ቅዱስ ያዕቆብ ዓመታዊ የዕረፍት በዓል በሰላም አደረሳችሁ ፤ አደረሰን። †
🕊 🕊
❝ ከሐዋርያት ጵጵስናን የተቀበለ በአብያተ ክርስቲያናት ውስጥ መሾሙ የቀደመ በሥጋ ዝምድና የጌታችን ወንድም ለኾነ ለያዕቆብ ሰላምታ ይገባል። ❞
[ አቤቱ የሐዋርያት ተከታዮቻቸው ስለኾኑ ስለ ሰባ ኹለቱ አርድእት ብለኽ በምሕረትኽ ዐስበኝ። ... ስለ እነርሱ ማረኝ ፤ እኔን አገልጋይኽንም በሀገራቸው ውስጥ ከነርሱ ጋር ዕድል ፈንታዬን ጽዋ ተርታዬን አድርግ ፤ አሜን። ]
[ ተአምኆ ቅዱሳን ]
▬▬▬▬▬▬ ♱ ▬▬▬▬▬▬
[ ከመልዕክቱ ]
❝ ወንድሞቼ ሆይ ፥ እምነት አለኝ የሚል ፥ ሥራ ግን የሌለው ሰው ቢኖር ምን ይጠቅመዋል ? እምነቱስ ሊያድነው ይችላልን ? . . . እግዚአብሔር አንድ እንደ ሆነ አንተ ታምናለህ ፤ መልካም ታደርጋለህ ፤ አጋንንት ደግሞ ያምናሉ ይንቀጠቀጡማል።
አንተ ከንቱ ሰው ፥ እምነት ከሥራ ተለይቶ የሞተ መሆኑን ልታውቅ ትወዳለህን ? ❞ [ ያዕ.፪፥፲፬ ]
🕊
[ † ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ወንድሙ ይባል ዘንድ ካደለው ሐዋርያ በረከትን ያድለን:: በምልጃውም ምሕረትን ይላክልን:: † ]
════════════════
†††
✟𝐎𝐑𝐓𝐇𝐎𝐃𝐎𝐗Y✟
🕊 💖 🕊 | 134 |
| 20 | Немає тексту... | 108 |
