uk
Feedback
Debtera Media

Debtera Media

Відкрити в Telegram

ደብተራ ሚዲያ የእውነት ድምጽ! ሰብስክራይብ በማድረግ ቤተሰብ ይሁኑ!👇 በዩቲዩብ 👉 https://bit.ly/3bMfT8D በፌስቡክ 👉 fb.me/DebteraMedia በቴሌግራም 👉 t.me/DebteraMedia ማንኛውንም ሃሳብ አስተያየት ሆነ መረጃ በ t.me/DebteraMedia_Bot ማድረስ ትችላላችሁ።

Показати більше
3 726
Підписники
-624 години
-137 днів
-7030 день

Триває завантаження даних...

Хмара тегів
Немає даних
Виникли проблеми? Будь ласка, оновіть сторінку або зверніться до нашого support-менеджера.
Вхідні та вихідні згадування
---
---
---
---
---
---
Залучення підписників
липень '26
липень '26
+24
в 0 каналах
червень '26
+21
в 0 каналах
Get PRO
травень '26
+19
в 0 каналах
Get PRO
квітень '26
+14
в 0 каналах
Get PRO
березень '26
+9
в 1 каналах
Get PRO
лютий '26
+16
в 0 каналах
Get PRO
січень '26
+22
в 0 каналах
Get PRO
грудень '25
+15
в 0 каналах
Get PRO
листопад '25
+19
в 0 каналах
Get PRO
жовтень '25
+24
в 0 каналах
Get PRO
вересень '25
+10
в 0 каналах
Get PRO
серпень '25
+16
в 0 каналах
Get PRO
липень '25
+21
в 0 каналах
Get PRO
червень '25
+17
в 0 каналах
Get PRO
травень '25
+24
в 0 каналах
Get PRO
квітень '25
+30
в 0 каналах
Get PRO
березень '25
+42
в 0 каналах
Get PRO
лютий '25
+20
в 0 каналах
Get PRO
січень '25
+35
в 0 каналах
Get PRO
грудень '24
+32
в 0 каналах
Get PRO
листопад '24
+18
в 0 каналах
Get PRO
жовтень '24
+21
в 0 каналах
Get PRO
вересень '24
+14
в 0 каналах
Get PRO
серпень '24
+11
в 0 каналах
Get PRO
липень '24
+26
в 0 каналах
Get PRO
червень '24
+16
в 0 каналах
Get PRO
травень '24
+15
в 0 каналах
Get PRO
квітень '24
+25
в 0 каналах
Get PRO
березень '24
+26
в 0 каналах
Get PRO
лютий '24
+15
в 0 каналах
Get PRO
січень '24
+32
в 1 каналах
Get PRO
грудень '23
+68
в 4 каналах
Get PRO
листопад '23
+13
в 0 каналах
Get PRO
жовтень '23
+9
в 0 каналах
Get PRO
вересень '23
+17
в 0 каналах
Get PRO
серпень '23
+28
в 0 каналах
Get PRO
липень '23
+27
в 0 каналах
Get PRO
червень '23
+81
в 0 каналах
Get PRO
травень '23
+32
в 0 каналах
Get PRO
квітень '23
+49
в 0 каналах
Get PRO
березень '23
+28
в 0 каналах
Get PRO
лютий '23
+802
в 0 каналах
Get PRO
січень '23
+1 371
в 0 каналах
Get PRO
грудень '22
+111
в 0 каналах
Get PRO
листопад '22
+280
в 0 каналах
Get PRO
жовтень '22
+17
в 0 каналах
Get PRO
вересень '22
+212
в 0 каналах
Get PRO
серпень '22
+159
в 0 каналах
Get PRO
липень '22
+49
в 0 каналах
Get PRO
червень '22
+523
в 0 каналах
Get PRO
травень '22
+1 661
в 0 каналах
Get PRO
квітень '22
+2 256
в 0 каналах
Get PRO
березень '22
+177
в 0 каналах
Get PRO
лютий '22
+399
в 0 каналах
Get PRO
січень '22
+537
в 0 каналах
Get PRO
грудень '21
+17
в 0 каналах
Get PRO
листопад '21
+20
в 0 каналах
Get PRO
жовтень '21
+120
в 0 каналах
Get PRO
вересень '21
+48
в 0 каналах
Get PRO
серпень '21
+64
в 0 каналах
Get PRO
липень '21
+75
в 0 каналах
Get PRO
червень '21
+86
в 0 каналах
Get PRO
травень '21
+50
в 0 каналах
Get PRO
квітень '21
+78
в 0 каналах
Get PRO
березень '21
+139
в 0 каналах
Get PRO
лютий '21
+128
в 0 каналах
Get PRO
січень '21
+186
в 0 каналах
Get PRO
грудень '20
+6 831
в 0 каналах
Дата
Залучення підписників
Згадування
Канали
26 липня+2
25 липня+1
24 липня+1
23 липня+2
22 липня+3
21 липня+3
20 липня0
19 липня+1
18 липня0
17 липня0
16 липня0
15 липня+1
14 липня0
13 липня0
12 липня0
11 липня+1
10 липня+1
09 липня0
08 липня+3
07 липня0
06 липня+3
05 липня0
04 липня+1
03 липня0
02 липня0
01 липня+1
Дописи каналу
photo content
+3

2
ስንክሳር ሐምሌ - ፲፱ - .mp3
187
3
🕊 † እንኳን ለቅዱሳኑ ገብርኤል ሊቀ መላእክት : ቂርቆስ ወኢየሉጣ : በጥላን ጠቢብ እና ሰማዕታተ እስና ዓመታዊ በዓል በሰላም አደረሳችሁ፤ አደረሰን። † † በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን ! † † 🕊 ቅዱሳን ቂርቆስ ወኢየሉጣ: ወቅዱስ ገብርኤል ሊቀ መላእክት 🕊 † † ቅድስት ኢየሉጣ እናታችን በዘመነ ሰማዕታት ከነበሩና በዚህ ስም ከሚጠሩ ቅዱሳት አንዷ ናት:: በወቅቱ ቅዱስ ቂርቆስ የሚባል ደግ ልጅ ወልዳ ባሏ ባለመኖሩ በመበለትነት ትኖር ነበር:: የዚያ ዘመን ክርስቲያኖች ለክርስቶስ የነበራቸው ፍቅር ከመነገር በላይ ነው:: በዛው ልክ ደግሞ መከራው በጸጉራቸው ቁጥር ልክ ነበር:: ከሮም ግዛት በአንዱ ከቅዱስ ልጇ ጋር የምትኖረው ቅድስት ኢየሉጣ የስደቱ ዘመን ሲመጣ እርሷም እንደ ሌሎቹ ክርስቲያኖች ተሰደደች:: እስክንድሮስ የተባለው ከሃዲ ንጉሥ ግን ያለችበት ድረስ ተከትሎ እንድትያዝና እንድትቀርብ አደረገ:: ወዲያውም "ስምሽ ማን ይባላል?" ቢላት "ክርስቲያን እባላለሁ" አለችው:: ንጉሡ ተቆጣ:: "መዋቲ ስሜን ከፈለክ ኢየሉጣ ይባላል" አለችው:: ንጉሡ መልሶ "አሁን ለጣዖት ካልሠዋሽ ሲጀመር ስቃይ: ቀጥሎም ሞት ይጠብቅሻል" ቢላት ቅድስቲቱ መልሳ "በከተማ ውስጥ የሦስት ዓመት ሕፃን አለና እርሱን አምጣው:: ማንን ማምለክ እንዳለብን ይነግረናል" አለችው:: አስፈልጐ ቅዱስ ቂርቆስን አስመጣው:: "ስምህ ማን ይባላል?" አለ ንጉሡ:: "ከማይደፈርስ ከንጹሕ ምንጭ የተቀዳ ጥሩ ምንጭ ስሜ ክርስቲያን ይባላል:: መዋቲ ስሜን ከፈለግህ ግን ቂርቆስ ይባላል" አለው:: ንጉሡ ሊያታልለው "ደስ የተሰኘህ ሕፃን" ቢለው ቅዱሱ ሕፃን "ትክክል ተናገርክ: ለእኔ በሰማያት ደስታ ይጠብቀኛል:: አንተ ግን እውነተኛው አምላክ ይፈርድብሃል" አለው:: በሦስት ዓመት ሕፃን አንደበት ዘለፋ የገጠመው ከሃዲ ተቆጣ:: እናትና ልጅን በብዙ መክፈልተ ኩነኔ አሰቃያቸው:: ሰውነታቸውን ቸነከረ: አካላቸውን ቆራረጠ: ዓይናቸውን አወጣ:: ሌላም ሊናገሩት የሚጨንቅ ስቃይን አሰቃያቸው:: በዚህች ቀን ግን ትልቅ ድስት አሰርቶ ባሩድ: አረር: ስብና የመሳሰሉትን ጨምረውበት በእሳት አፈሉት:: የእሳቱ ወላፈን አካባቢውን በላው:: በድስቱ ውስጥ ያለው ነገር እየፈላ ሲገላበጥ እንደ ክረምት ነጐድጓድ ይጮህ ነበር:: የስድስት ሰዓት የእግር መንገድ ድረስም ተሰምቷል:: ቅድስት ኢየሉጣ ይሔኔ ነበር ልቧ ድንግጥ ያለው:: ሕፃኑ ቂርቆስ የእናቱን ፍርሃት ሲመለከት ጸለየ:: "ፈጣሪዬ! ፍሬው ያለ ግንዱ አይቆምምና እኔን እንዳጸናሕ እናቴንም አጽናት" ሲል ለመነ:: "እግዚኦ ትፈቅድኑ ለፍሬሁ ተአልዶ: እንዘ በእሳት ታውኢ ጉንዶ" እንዲል:: በዚያች ሰዓት ቅድስት ኢየሉጣ ዓይኖቿ ተከፍተው ሰማያዊ ክብርን ተመለከቱና ልቧ ወደ ድፍረቱ ተመለሰ:: ልጇንም "አንተ አባቴ ነህ: አንተን የተሸከመች ማኅጸኔ የተባረከች ናት" አለችው:: ከዚያም ሁለቱንም ወደ ፈላው ድስት ውስጥ ቢጨምሯቸው ፍጡነ ረድኤት ቅዱስ ገብርኤል ከሰማይ ወረደላቸው:: በበትረ መስቀሉ ባርኮ የፈላውን አቀዘቀዘው:: የነደደውን ውኃ አደረገው:: ቅዱሳኑ ቂርቆስና ኢየሉጣ ከብዙ መከራ በኋላ በሰማዕትነት አልፈዋል:: † 🕊 ቅዱስ በጥላን ጠቢብ 🕊 † † ቅዱሱ ከአሕዛብ ወላጆቹ ተወልዶ: ያደገውም በጣዖት አምልኮ ነው:: በሙያው እጅግ የተመሠከረለት ሐኪም ነበር:: የሃገሩ ሰዎች "ጠቢብ" እያሉም ይጠሩታል:: በጥላን ምንም ጣዖት አምላኪ ቢሆን በተፈጥሮው ተመራማሪና ቅን ነበር:: አንድ ካህንም በጐረቤቱ ነበርና ዘወትር ስለ ሃይማኖት ይከራከሩ ነበር:: ካህኑ ሌሊት ሌሊት ስለ በጥላን ተግቶ ይጸልይ ነበርና ተሳክቶለት አሳመነው:: አንድ ቀን በጥላን መንገድ ሲሔድ እባብ ሰው ነድፎ ለሞት ደርሶ አየውና ጸሎት አድርሶ ስመ ክርስቶስን ቢጠራ የተነደፈው ድኖ እባቡ ሞተ:: በዚህ ተዓምር ደስ ብሎት ወደ ካህኑ ሒዶ ተጠመቀ:: ከዚያም ጾም ጸሎትን ጀመረ:: በየቦታው እየዞረ ሕሙማንን እንደ ቀድሞው በመድኃኒት ሳይሆን በጸሎት ያድናቸው ነበር:: ስላዳናቸውም በርካቶቹ ወደ ክርስትና መጡ:: የአካባቢው ሰው: ወላጆቹን ጨምሮ ክርስቲያኖች ሆኑ:: በመጨረሻም ቅዱስ በጥላን: ቤተሰቦቹ: ካህኑና ከደዌ የዳኑት ወገኖቹ በአካባቢው ጣዖት አምላኪ ንጉሥ ፊት ቀርበው ክርስቶስን ሰብከው በሰማዕትነት ዐርፈዋል:: † 🕊 ቅዱሳን ሰማዕታተ እስና 🕊 † † እስና ማለት ግብጽ ውስጥ የምትገኝ የቀድሞ አውራጃ ናት:: በ3ኛው መቶ ክ/ዘመን በከተማዋ በርካታ ክርስቲያኖች ይኖሩ ነበር:: የእንዴናው መኮንን መጥቶ "ክርስቶስን ካዱ: ለጣዖት ስገዱ" አላቸው:: ሕዝቡ በአንድ ድምጽ መለሱ:- "ይሕማ ፈጽሞ ሊደረግ አይችልም::" መኮንኑ ተቆጥቶ "ሁሉንም ግደሉ" አለ:: ወታደሮቹ ሰው አልመረጡም:: ከታዘለ ሕፃን አልጋ ላይ እስካለ ሽማግሌ: ከጤነኛ እስከ ሕመምተኛ: ሁሉንም ጨፈጨፏቸው:: ከተማዋ በደም ተነከረች:: ከከተማዋ ክርስቲያኖች ወሬ ለመንገር አንድ ሰው እንኳ አልተረፈም:: ሁሉም ስለ ክርስትና ደማቸውን አፈሰሱ:: † ጌታችን ስለ ሰማዕታቱ ብሎ: ደማቸውንም አስቦ በሃይማኖታችን ያጽናን:: ከመከራም ይሰውረን:: በረከታቸውንም ያድለን:: [ † ሐምሌ ፲፱ [ 19 ] ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት ] ፩. ቅዱስ ገብርኤል ሊቀ መላእክት ፪. ቅዱስ ቂርቆስ ወእሙ ኢየሉጣ ፫. ቅዱስ በጥላን ጠቢብ ሰማዕት እና ማኅበሩ ፬. ቅዱሳን ሰማዕታተ እስና [ † ወርኀዊ በዓላት ] ፩. ቅዱስ ኤስድሮስ ሰማዕት ፪. አቡነ ዓቢየ እግዚእ ጻድቅ ፫. አቡነ ስነ ኢየሱስ ፬. አቡነ ዮሴፍ ብርሃነ ዓለም † "ከክርስቶስ ፍቅር ማን ይለየናል? መከራ: ወይስ ጭንቀት: ወይስ ስደት: ወይስ ራብ: ወይስ መራቆት: ወይስ ፍርሃት: ወይስ ሰይፍ ነውን? 'ስለ አንተ ቀኑን ሁሉ እንገደላለን:: እንደሚታረዱ በጐች ተቆጠርን::' ተብሎ እንደተጻፈው ነው:: በዚህ ሁሉ ግን በወደደን በእርሱ ከአሸናፊዎች እንበልጣለን::" † [ሮሜ. ፰፥፴፭-፴፯] † ወስብሐት ለእግዚአብሔር † † ወለወላዲቱ ድንግል † † ወለመስቀሉ ክቡር † [ ዲ/ን ዮርዳኖስ አበበ  ]          †              †               † ▬▬▬▬▬ ▬▬▬ ▬▬▬▬▬ 💖                   🕊                    💖
190
4
+1
Немає тексту...
239
5
[ ስንክሳር ሐምሌ - ፲፰ - ] .mp3
222
6
🕊 [ † እንኳን ለሐዋርያው ቅዱስ ያዕቆብ ዓመታዊ የዕረፍት በዓል በሰላም አደረሳችሁ ፤ አደረሰን። † ] † በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን ! † [ 🕊 †  ቅዱስ ያዕቆብ ሐዋርያ †  🕊 ] † ይህ ቅዱስ ሐዋርያ በአባቶቻችን ሐዋርያት መካከል ትልቅ ሞገስ የነበረውና "የጌታችን ወንድም" ተብሎ የተጠራ ነው:: ቅዱስ ያዕቆብ ወላጅ አባቱ አረጋዊው ቅዱስ ዮሴፍ [የእመቤታችን ጠባቂ] ሲሆን በልጅነቱ የሞተችው እናቱ ደግሞ ማርያም ትባላለች:: በቤት ውስጥም ስምዖን: ዮሳና ይሁዳ የተባሉ ወንድሞችና ሰሎሜ የምትባል እህትም ነበረችው:: እናቱ ማርያም ከሞተች በኋላ ዕጓለ-ማውታ [ደሃ አደግ] ሆኖ ነበር:: ነገር ግን በፈቃደ እግዚአብሔር አረጋዊ ዮሴፍ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያምን ከቤተ መቅደስ ሊጠብቃት [ሊያገለግላት] ተቀብሎ ሲመጣ ያ ቤተሰብ ተቀየረ:: የበረከት: የምሕረትና የሰላም እመቤት የአምላክ እናቱ ገብታለችና ያ የሐዘን ቤት ደስታ ሞላው:: እመ ብርሃን ግን ገና ወደ ዮሴፍ ልጆች ስትደርስ አለቀሰች:: የአክስቷ ልጆች የሚንከባከባቸው አጥተው ቆሽሸው ነበር:: በተለይ ደግሞ ትንሹ ቅዱስ ያዕቆብ ያሳዝን ነበር:: እመ ብርሃን ማረፍ አልፈለገችም:: ወዲያው ማድጋ አንስታ ወደ ምንጭ ወርዳ ውኃ አምጥታ የሕፃኑን ገላ አጠበችው:: [በአምላክ እናት የታጠበ ሰውነት ምስጋና በጸጋ ይገባዋል::] እመቤታችን ጌታ ከመወለዱ በፊት ለዘጠኝ ወራት: ከተወለደ በኋላ ደግሞ ለሁለት ዓመታት ሕፃኑን ያዕቆብን ተንከባከበችው:: ለሦስት ዓመት ከስድስት ወር ግን ድንግል ማርያም አምላክ ልጇን ይዛ ተሰዳለችና ተለያዩ:: ከስደት መልስ ግን ለሃያ አምስት ዓመታት ቅዱስ ያዕቆብ ከጌታችን ጋር ሲያድግ ወላጅ እናቱ ትዝ ብላው አታውቅም:: አማናዊቷ እናት ከጐኑ ነበረችና:: ሊቃውንት እንደ ነገሩን እመቤታችን ለቅዱስ ያዕቆብ ያልሰጠችው ነገር ቢኖር ሐሊበ ድንግልናዌ [የድንግልና ወተትን] ብቻ ነው:: ስለዚህም :- "እመ ያዕቆብ በጸጋ ማርያም ንግሥተ ኩሉ" ይላል መጽሐፍ:: [መልክዐ ስዕል] † ቅዱስ ያዕቆብ "የጌታ ወንድም" ተብሎ በተደጋጋሚ በሐዲስ ኪዳን ተጠርቷል:: ለዚህ ምክንያቱ ፩. ለሰላሳ ዓመታት ሳይነጣጠሉ አብረው በማደጋቸው ፪. የጌታችን የሥጋ አያቱ [የቅድስት ሐና] የእህት ልጅ በመሆኑ ፫. በዮሴፍ በኩልም የአንድ ቅድመ አያት ልጆች በመሆናቸው ፬. ጌታችን ከትህትናው የተነሳ ደቀ መዛሙርቱን "ወንድሞች" ይላቸው ስለ ነበር ነው:: [ሥጋቸውን ተዋሕዶ ተገኝቷልና::] ራሱ ቅዱስ ያዕቆብ ግን "የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ባሪያ ነኝ" ብሎ በፈጣሪና በፍጡር መካከል ያለውን ልዩነት ገልጧል:: [ያዕ.፩፥፩] ቅዱስ ያዕቆብ ጌታችን ሲያስተምር ተከተለው:: - ከሰባ ሁለቱ አርድእት ተቆጠረ - ሦስት ዓመት ከሦስት ወር ወንጌልን ተማረ - ለመጀመሪያ ጊዜ ከድንግል ማርያምና ከቅዱስ ዮሐንስ ጋር ሆኖ "የጌታን ትንሣኤ ሳላይ እህል አልቀምስም" ብሎ ማክፈልን አስተማረ - መንፈስ ቅዱስን ተሞልቶ ወንጌልን አስተማረ - የኢየሩሳሌም የመጀመሪያው ሊቀ ጳጳስ ሆኖ አገለገለ - በመጀመሪያዎቹ የክርስትና ዘመናት የሐዋርያት ሲኖዶሶችን በሊቀ መንበርነት መራ - ሙታንን አስንስቶ - ድውያንን ፈውሶ - የመካኖችን ማኅጸን ከፍቶ: አጋንንትንም አስወጥቶ ብዙ ተዓምራትን ሠራ:: እጅግ ብዙ አይሁዳውያንን ወደ አሚነ ክርስቶስ መልሶ መልካሙን ገድል ተጋደለ:: በመጨረሻ ዘመኑ ያላመኑ የአይሁድ አለቆች ወደ ቤቱ ተሰብስበው "የናዝሬቱ ኢየሱስ ማነው? የማንስ ልጅ ነው?" ሲሉ ጠየቁት:: እነርሱ ሰይጣን በሰለጠነበት ልቡናቸው "የዮሴፍ ልጅ ነው: የእኔም ወንድሜ ነው" እንዲላቸው ጠብቀው ነበር:: [ሎቱ ስብሐት ወአኮቴት] † በልቡናቸው ያሰቡትን ተንኮል የተረዳው ሐዋርያ ወደ ቤቱ ጣራ ወጥቶ መናገር ጀመረ:: "ለስም አጠራሩ ጌትነት ይሁንና ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ :- አምላክ : ወልደ አምላክ : ወልደ አብ : ወልደ ማርያም : ሥግው ቃል : እግዚአብሔር ነው:: እኔም ፍጡሩና ባሪያው እንጂ እንደምታስቡት ወንድሙ አይደለሁም" አላቸው:: ንዴታቸውን መቆጣጠር ያልቻሉት አይሁድ ከላይ ወጥተው ወደ መሬት ወረወሩት:: በገድል የተቀጠቀጠ አካሉንም እየተፈራረቁ ደበደቡት:: አንዱ ግን ከእንጨት የተሠራ ትልቅ ገንዳ አምጥቶ የቅዱሱን ራስ ደጋግሞ መታው:: ጭንቅላቱም እንዳልነበር ሆነ:: ሰማዕቱ ሐዋርያ ቅዱስ ያዕቆብ ወደ ወደደው ክርስቶስ በዚህች ቀን ሔደ:: ቅዱሱ ሐዋርያ ያዕቆብ ቤቱን እንደ ቤተ መቅደስ አበው ሐዋርያት ይጠቀሙባት ነበር:: በመላ ዘመኑ የሚያገድፍ ነገር [ጥሉላት] ቀምሶ : ጸጉሩን ተላጭቶ : ገላውን ታጥቦና ልብሱን ቀይሮ አያውቅም:: "ወዝንቱ ጻድቅ እኅወ እግዚእነ:: ኢያብአ ውስተ አፉሁ ሥጋ ወወይነ:: ወኢገብረ ሎቱ ክልኤተ ክዳነ" እንዲል:: † ከጾም : ከጸሎትና ከመቆሙ ብዛትም እግሩ አብጦ አላራምድህ ብሎት ነበር:: ስለዚህም አበው "ጻድቁ [ገዳማዊው] ሐዋርያ" ይሉታል:: † ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ወንድሙ ይባል ዘንድ ካደለው ሐዋርያ በረከትን ያድለን:: በምልጃውም ምሕረትን ይላክልን:: [ † ሐምሌ ፲፰ [ 18 ] ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት ] ፩. ቅዱስ ያዕቆብ ሐዋርያ [ ከሰባ ሁለቱ አርድእት-የመጀመሪያው የኢየሩሳሌም ሊቀ ጳጳሳት ] ፪. ቅዱስ አትናቴዎስ ሰማዕት ፫. ቅዱስ እንድራኒቆስ ሰማዕት ፬. ዘጠኝ ሺህ ሰማዕታት [የቅዱስ ኤስድሮስ ማኅበር] [  † ወርኀዊ በዓላት  ] ፩. ቅዱስ ፊልጶስ ሐዋርያ ፪. አቡነ ኤዎስጣቴዎስ ሰባኬ ሃይማኖት [ ረባን ] ፫. አቡነ አኖሬዎስ ዘደብረ ጽጋጋ ፬. ማር ያዕቆብ ግብጻዊ † "የእግዚአብሔርና የጌታ የኢየሱስ ክርስቶስ ባሪያ ያዕቆብ: ለተበተኑ ለአሥራ ሁለቱ ወገኖች:: ሰላም ለእናንተ ይሁን:: ወንድሞቼ ሆይ! የእምነታችሁ መፈተን ትዕግስትን እንዲያደርግላችሁ አውቃችሁ ልዩ ልዩ ፈተና ሲደርስባችሁ እንደ ሙሉ ደስታ ቁጠሩት:: ትዕግስትም ምንም የሚጐድላችሁ ሳይኖር ፍጹማንና ምሉዓን ትሆኑ ዘንድ ሥራውን ይፈጽም::" † [ ያዕ. ፩፥፩ ] † ወስብሐት ለእግዚአብሔር † † ወለወላዲቱ ድንግል † † ወለመስቀሉ ክቡር † [ ዲ/ን ዮርዳኖስ አበበ  ]          †              †               † ▬▬▬▬▬ ▬▬▬ ▬▬▬▬▬ 💖                   🕊                    💖
214
7
Немає тексту...
146
8
Ye TSADIKAN KETEMA.mp3
138
9
🩵 † 🩵 🌸 ❝ ቅዱስ ያዕቆብ ሐዋርያዊ ! ❞ 🌸 💛 💛 † እንኳን ለሐዋርያው ቅዱስ ያዕቆብ ዓመታዊ የዕረፍት በዓል በሰላም አደረሳችሁ ፤ አደረሰን። † 🕊 🕊 ❝ ከሐዋርያት ጵጵስናን የተ
🩵                         †                         🩵 🌸  ❝ ቅዱስ   ያዕቆብ ሐዋርያዊ ! ❞  🌸 💛                                                    💛 † እንኳን ለሐዋርያው ቅዱስ ያዕቆብ ዓመታዊ የዕረፍት በዓል በሰላም አደረሳችሁ ፤ አደረሰን። † 🕊                                                 🕊 ❝ ከሐዋርያት ጵጵስናን የተቀበለ በአብያተ ክርስቲያናት ውስጥ መሾሙ የቀደመ በሥጋ ዝምድና የጌታችን ወንድም ለኾነ ለያዕቆብ ሰላምታ ይገባል። ❞ [ አቤቱ የሐዋርያት ተከታዮቻቸው ስለኾኑ ስለ ሰባ ኹለቱ አርድእት ብለኽ በምሕረትኽ ዐስበኝ። ... ስለ እነርሱ ማረኝ ፤ እኔን አገልጋይኽንም በሀገራቸው ውስጥ ከነርሱ ጋር ዕድል ፈንታዬን ጽዋ ተርታዬን አድርግ ፤ አሜን። ] [  ተአምኆ ቅዱሳን  ] ▬▬▬▬▬▬  ♱  ▬▬▬▬▬▬ [        ከመልዕክቱ       ] ❝ ወንድሞቼ ሆይ ፥ እምነት አለኝ የሚል ፥ ሥራ ግን የሌለው ሰው ቢኖር ምን ይጠቅመዋል ? እምነቱስ ሊያድነው ይችላልን ? . . . እግዚአብሔር አንድ እንደ ሆነ አንተ ታምናለህ ፤ መልካም ታደርጋለህ ፤ አጋንንት ደግሞ ያምናሉ ይንቀጠቀጡማል። አንተ ከንቱ ሰው ፥ እምነት ከሥራ ተለይቶ የሞተ መሆኑን ልታውቅ ትወዳለህን ? ❞ [ ያዕ.፪፥፲፬ ]  🕊 [  † ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ወንድሙ ይባል ዘንድ ካደለው ሐዋርያ በረከትን ያድለን:: በምልጃውም ምሕረትን ይላክልን:: †  ] ════════════════                            †††                ✟𝐎𝐑𝐓𝐇𝐎𝐃𝐎𝐗Y✟ 🕊                         💖                        🕊
140
10
Немає тексту...
129
11
[ + የነፍስ ነጻነት + ] .mp3
130
12
🍒 🍒 🕊 ም ክ ረ ቅ ዱ ሳ ን 🕊 ═══════════════ ▷ ❝ የ ነ ፍ ስ ነ ፃ ነ ት ! ! ❞ [ 💛 በብፁዕ አቡነ ሺኖዳ ሣልሳዊ 💛 ] 🕊 🍒 🕊 ❝ አሁን ግን ከኃጢአት አርነት
🍒                                               🍒      🕊     ም ክ ረ     ቅ ዱ ሳ ን     🕊 ═══════════════ ▷    ❝  የ ነ ፍ ስ   ነ ፃ ነ ት   !  !   ❞ [ 💛  በብፁዕ አቡነ ሺኖዳ ሣልሳዊ  💛  ] 🕊                        🍒                       🕊 ❝ አሁን ግን ከኃጢአት አርነት ወጥታችሁ ለእግዚአብሔርም ተገዝታችሁ ፥ ልትቀደሱ ፍሬ አላችሁ ፤ መጨረሻውም የዘላለም ሕይወት ነው። ❞ [ ሮሜ.፮፥፳፪ ] ════════════════                            †††                ✟𝐎𝐑𝐓𝐇𝐎𝐃𝐎𝐗Y✟ 🕊                        💖                       🕊                              👇
149
13
🕊 [ ማረሚያ ! ] አስቀድሞ ቀርቦ የነበረው የሐዋርያው ቅዱስ ያዕቆብ ዓመታዊ የዕረፍት በዓሉን የተመለከተ ፖስት በስህተት በመሆኑ የቅዱሱ ዓመታዊ የዕረፍት በዓሉ ሐምሌ 17 [ ፲፯ ] ሳይሆን ከነገ ወዲያ ሐምሌ 18 [ ፲፰ ] እንደሆነ እንረዳ። ▬▬▬▬▬▬   ♱    ▬▬▬▬▬▬
199
14
+1
Немає тексту...
213
15
[ ስንክሳር ሐምሌ - ፲፯ - ] .mp3
196
16
🕊 በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ ፡፡ አሜን ፡፡ [  † እንኩዋን ለነቢዩ ቅዱስ ዮናስ እና ለእናታችን ቅድስት አውፎምያ ዓመታዊ የዕረፍት በዓል በሰላም አደረሳችሁ †  ] 🕊  †   ቅዱስ ዮናስ ነቢይ  †  🕊 በቤተ ክርስቲያን አስተምሕሮ ከ፲፪ [12] ቱ ደቂቀ ነቢያት አንዱ የሆነው ቅዱስ ዮናስ ከክርስቶስ ልደት ፰ መቶ [800] ዓመታት በፊት እንደ ነበረ ይታመናል:: ሊቃውንት እንዳስተማሩን ደግሞ እናቱ ቅዱስ ኤልያስን የመገበችው የሰራፕታዋ መበለት ናት:: ቅዱስ ዮናስ ገና ሕጻን ሳለ በእሥራኤል ምድር ዝናብ ለ፫ [3] ዓመታት ከ፮ [6] ወራት ተከልክሎ ነበር:: ይሕንንም ያደረገው ደጉ ነቢይ ኤልያስ ለአምልኮተ እግዚአብሔር ቀንቶ ነው:: በወቅቱ ኤልያስ በሰራፕታ ሳለ ሕጻኑ ዮናስ ታሞ ሞተ:: ልጇ የሞተባት መበለትም ኤልያስን ለመነችው:: ኤልያስም ወደ ፈጣሪው ማልዶ ሕጻኑን ዮናስን ከሞት አስነስቶታል:: ትንሽ ከፍ ባለ ጊዜም ከጉዋደኞቹ [ከነቢያቱ] አብድዩና ኤልሳዕ ጋር ሆነው ታላቁን ነቢይ ኤልያስን ተከትለውታል:: ኤልያስ ካረገ በሁዋላ ሁሉም በየተሰጣቸው አገልግሎት ተሠማርተዋል:: ቅዱስ ዮናስን እግዚአብሔር "ወደ ነነዌ ሒደሕ ንስሃን ስበክ" አለው:: ዮናስ ግን የፈጣሪውን መሐሪነት ጠንቅቆ ያውቃልና አልሔድም አለ:: [ተመልከቱ የየዋሕነት ብዛት] እግዚአብሔር እየደጋገመ እንዲሔድ ሲነግረው ነቢዩ "እንዲሕ የሚዘበዝበኝ ከፊቱ ብቀመጥ አይደል" ብሎ ሊኮበልል ወጣ:: ነገር ግን አልቀናውም:: በእርሱ ምክንያት ማዕበል ተነሳ:: ሕዝቡም ሊያልቁ ሆነ:: ከእንቅልፉ የነቃው ዮናስ ከመርከቡ ላሉት አሕዛብ አምልኮተ እግዚአብሔርን ሰብኮላቸው: በእርሱ ጠያቂነት ሐምሌ ፲፭ [ 15 ] ቀን ወደ ባሕር ጥለውታል:: አሣ አንበሪም ተቀብሎታል:: በግዙፉ አሣ ውስጥም ያለ እንቅልፍ በጾም: በጸሎትና በምስጋና ፫ [3] ለቀን ቆይቷል:: ሙስና ሳያገኘውም በዚህች ቀን አሣ አንበሪው ነነዌ ዳር ላይ ተፍቶታል:: ቅዱስ ዮናስ እግዚአብሔር እንዳዘዘው "እስከ ሠሉስ ዕለት ትትገፈታእ ነነዌ ዓባይ ሃገር" [እስከ ሦስት ቀን ድረስ ነነዌ ትገለበጣለች [ዮናስ ፫፥፬ [3:4] ብሎ አሰምቶ ሰበከ:: የነነዌ ሰዎችም በስብከተ ዮናስ አምነው: ንስሃም ገብተው ድነዋል:: በዚህም ጌታችን በወንጌል ላይ አመስግኗቸዋል:: ቅዱስ ዮናስ መኮብለሉ በሐዲስ ኪዳን ለሚደረገው ምስጢረ ትንሳኤ ጥላ [ምሳሌ] ነውና ይደነቃል:: [ማቴ.፲፪፥፴፰] [12:38] ነቢዩ ግን በተረፈ ሕይወቱ ሕዝቡን ሲያስተምር: ፈጣሪውን ሲያገለግል ኑሮ በመልካም ሽምግልና ዐርፏል:: † 🕊 ቅድስት አውፎምያ ሰማዕት 🕊 †  እናታችን ቅድስት አውፎምያ [ስሟ አፎምያ አይደለም:: በስሕተት "ው" መካከል ላይ የገባች እንዳይመስልዎ:: እስመ ከመዝ ስማ-ስሟ እንዲሁ ነው የሚጠራው] በ፫ [3]ኛው መቶ ክ/ዘመን ከነበሩ ወጣት ክርስቲያኖች አንዷ ናት:: ገና ከልጅነቷ ልቧ በፍቅረ ክርስቶስ የተነደፈ ነበር:: በዚህም ምክንያት ራሷን በጾምና በጸሎት ወስና ትኖር ነበር:: እድሜዋ ገና በአሥራዎቹ ቢሆንም በመንኖ ጥሪት መኖር ምርጫዋ ነበር:: ሊቃውንት አበው ከሰማዕትነቷ ደርበው "ጻድቅት አውፎምያ" እያሉም ይጠሯታል:: አንድ ቀን ግን መንገድ ወጥታ ነበርና ክርስቲያኖች ሲሰቃዩ ተመለከተች:: ምንም ጥፋት ሳይገኝባቸው ክርስቶስን ስላመለኩ ብቻ ይሙት በቃ ተፈርዶባቸው ሊገደሉ እየተወሰዱ ነበር:: አሕዛብ ግብራቸው የአውሬ ነውና ርሕራሔ የላቸውም:: ሰማዕታቱ ደማቸው በየመንገዱ እየፈሰሰ ጥቁር ሰንሰለት በአንገታቸው: በእጃቸውና በእግራቸው ላይ አድርገው ይጐትቷቸው ነበር:: ቅድስት አውፎምያ የተደረገውን ሁሉ ተመልክታ አምርራ አለቀሰች:: ፈጠን ብላም ወደ መኮንኑ ቀርባ ገሰጸችው:: "አንተ አእምሮ የጎደለህ ! እንዴት ክርስቲያኖችን እንዲህ ታሰቃያለህ? አምላካቸው ጌታ ክርስቶስ ታጋሽ ባይሆን ኑሮ በቅጽበት ከገጸ ምድር ባጠፋህ ነበር" አለችው:: በድፍረቷ የተገረመው መኮንኑ "አንቺስ ማንን ታመልኪያለሽ?" ሲል ጠየቃት:: እርሷም "ሰማይና ምድርን የፈጠረውን: ስለ እኛ ሲል በቀራንዮ አንባ የተሠዋውን ኢየሱስ ክርስቶስን አመልካለሁ" ስትል መለሰችለት:: በዚያች ሰዓት የመኮንኑ ቁጣ በቅድስቷ ላይ ነደደ:: ነገር ግን ቁጣውን ከቁም ነገር አልቆጠረችውምና እንዲያሰቃዩዋት አዘዘ:: ወታደሮቹ ሥጋዋን በብዙ አሰቃዩ:: ብላቴናዋ አውፎምያ ግን ጽንዕት ናትና አልቻሏትም:: በመጨረሻ በእሳት ተቃጥላ ትሞት ዘንድ ተፈረደባት:: እሳቱ ከመሬት ከፍ ባለ ጊዜ ወደ ውስጥ ወረወሯት:: በእሳቱ መካከል ቁማ ለረዥም ጊዜ ጸለየች:: ከዚያም ነፍሷን አሳልፋ ሰጠች:: ምዕመናን በክብር ገንዘው ቀብረዋታል:: አምላካችን ከነቢዩና ከሰማዕቷ ወዳጆቹ በረከት ይክፈለን:: [  † ሐምሌ ፲፯ [ 17 ] ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት †  ] ፩. ቅዱስ ዮናስ ነቢይ [ ከአሣ አንበሪ ሆድ የወጣበት ] ፪. ቅድስት አውፎምያ [ ጻድቅትና ሰማዕት ] ፫. ቅዱስ ዮስጦስ ሰማዕት [ ታላቁ ] ፬. ቅዱስ ዘካርያስ [   †  ወርኀዊ በዓላት  ] ፩. ቅዱስ እስጢፋኖስ ሊቀ ዲያቆናት [ቀዳሜ ሰማዕት ] ፪. ቅዱስ ያዕቆብ ሐዋርያ [ወልደ ዘብዴዎስ] ፫. ቅዱሳን አበው መክሲሞስና ዱማቴዎስ ፬. አባ ገሪማ ዘመደራ ፭. አባ ዸላሞን ፈላሢ ፮. አባ ለትጹን የዋህ ፯. ቅዱስ ኤዺፋንዮስ ሊቅ [ዘደሴተ ቆዽሮስ] " በዚያን ጊዜ ከጻፎችና ከፈሪሳውያን አንዳንዶቹ መለሱና:- 'መምሕር ሆይ! ከአንተ ምልክት እንድናይ እንወዳለን' አሉት:: እርሱ ግን መልሶ እንዲህ አላቸው:- 'ክፉና አመንዝራ ትውልድ ምልክት ይሻል:: ከነቢዩም ከዮናስ ምልክት በቀር ምልክት አይሰጠውም:: ዮናስ በአሣ አንበሪ ሆድ ሦስት ቀንና ሦስት ሌሊት እንደ ነበረ እንዲሁ የሰው ልጅ በምድር ልብ ሦስት ቀንና ሦስት ሌሊት ይኖራል:: የነነዌ ሰዎች በፍርድ ቀን ከዚህ ትውልድ ጋር ተነስተው ይፈርዱበታል:: በዮናስ ስብከት ንስሃ ገብተዋልና:: እነሆም ከዮናስ የሚበልጥ ከዚህ አለ::" [ማቴ.፲፪፥፴፰] † ወስብሐት ለእግዚአብሔር † † ወለወላዲቱ ድንግል † † ወለመስቀሉ ክቡር † [ ዲ/ን ዮርዳኖስ አበበ  ]          †              †               † ▬▬▬▬▬ ▬▬▬ ▬▬▬▬▬ 💖                   🕊                    💖
184
17
Немає тексту...
134
18
Ye TSADIKAN KETEMA.mp3
131
19
🩵 † 🩵 🌸 ❝ ቅዱስ ያዕቆብ ሐዋርያዊ ! ❞ 🌸 💛 💛 † እንኳን ለሐዋርያው ቅዱስ ያዕቆብ ዓመታዊ የዕረፍት በዓል በሰላም አደረሳችሁ ፤ አደረሰን። † 🕊 🕊 ❝ ከሐዋርያት ጵጵስናን የተ
🩵                         †                         🩵 🌸  ❝ ቅዱስ   ያዕቆብ ሐዋርያዊ ! ❞  🌸 💛                                                    💛 † እንኳን ለሐዋርያው ቅዱስ ያዕቆብ ዓመታዊ የዕረፍት በዓል በሰላም አደረሳችሁ ፤ አደረሰን። † 🕊                                                 🕊 ❝ ከሐዋርያት ጵጵስናን የተቀበለ በአብያተ ክርስቲያናት ውስጥ መሾሙ የቀደመ በሥጋ ዝምድና የጌታችን ወንድም ለኾነ ለያዕቆብ ሰላምታ ይገባል። ❞ [ አቤቱ የሐዋርያት ተከታዮቻቸው ስለኾኑ ስለ ሰባ ኹለቱ አርድእት ብለኽ በምሕረትኽ ዐስበኝ። ... ስለ እነርሱ ማረኝ ፤ እኔን አገልጋይኽንም በሀገራቸው ውስጥ ከነርሱ ጋር ዕድል ፈንታዬን ጽዋ ተርታዬን አድርግ ፤ አሜን። ] [  ተአምኆ ቅዱሳን  ] ▬▬▬▬▬▬  ♱  ▬▬▬▬▬▬ [        ከመልዕክቱ       ] ❝ ወንድሞቼ ሆይ ፥ እምነት አለኝ የሚል ፥ ሥራ ግን የሌለው ሰው ቢኖር ምን ይጠቅመዋል ? እምነቱስ ሊያድነው ይችላልን ? . . . እግዚአብሔር አንድ እንደ ሆነ አንተ ታምናለህ ፤ መልካም ታደርጋለህ ፤ አጋንንት ደግሞ ያምናሉ ይንቀጠቀጡማል። አንተ ከንቱ ሰው ፥ እምነት ከሥራ ተለይቶ የሞተ መሆኑን ልታውቅ ትወዳለህን ? ❞ [ ያዕ.፪፥፲፬ ]  🕊 [  † ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ወንድሙ ይባል ዘንድ ካደለው ሐዋርያ በረከትን ያድለን:: በምልጃውም ምሕረትን ይላክልን:: †  ] ════════════════                            †††                ✟𝐎𝐑𝐓𝐇𝐎𝐃𝐎𝐗Y✟ 🕊                         💖                        🕊
134
20
Немає тексту...
108