237
Subscribers
-224 hours
-17 days
+430 days
Posts Archive
Repost from Yeka Education
ፈተና ከጀመርን በኋላ ማድረግ የሚገቡን ነገሮች (ፈተና ላይ እያለን)፤
👉 ወደ ፈተና ከመሄዳችን ቀደም ብለን ለፈተና የሚረዱንን መሳሪያዎች እና የመፈተኛ ቁሶችን ማዘጋጀት።
👉አብዝተን ፈተናን እና የምናመጣውን ነጥብ ስሌት አለመገመት ።
👉ፈተና ስንጨርስ የተሳሳትነውን ጥያቄ አብዝቶ ማሰብ እና ሌላ ተማሪ መጠየቅ ጭንቀት ውስጥ ስለሚከተን ከዚህ ይልቅ ቤት ሄደን እረፍት ማድረግ እና ለቀጣይ ፈተና መዘጋጀት ።
👉 በፈተና ጊዜ ድንገተኛ ጭንቀት እና ድንጋጤ ከገጠመን ወዲያው የምንሰራውን ገታ አድርገን በጥልቀት አየር በአፍንጫችን ስበን ወደ ሳንባ እያስገባን መልሰን ማስወጣት ይህንንም እስክንረጋጋ መደጋገም ። ከዚህ በመቀጠል የማረጋጊያ ቃላትን ለራስዎ መንገር::
👉 ፈተና በምንሰራ ጊዜ ግራ ያጋባንን እና እርግጠኛ ያልሆንበትን ጥያቄ በይለፍ ማቆየት እና ወደ ቀጣዩ ጥያቄ መሄድ ይህም ጊዜያችንን በአግባቡ እንድንጠቀም ይረዳናል። ነገር ግን ምልክት አድርገን ማለፍ፤
👉በተመሳሳይ እርግጠኛ ያልሆልንበትን መልስ ላይ ተደናግጠን መሰረዝ እና መደለዝን መቀነስ ይህም ስንደነግጥ እና ስንጨነቅ የምናውቀውን መልስ ትተን ወደ ሌላ መልስ እንድሰጥ ስለሚያረግ መሰረዝና መደለዝን መቀነስ ።
👉ፈተናውን ወደ ማገባደድ ስንደርስ በይለፍ ያስቀመጥናቸውን ግራ ያጋቡንን ጥያቄዎች ጥቂት አስበንበት መልስ መስጠት ፤ ካልሆነም ደግሞ ብልሀት ተጠቅመን የግመታ መልስ ሰጥተን ወደ ቀጣዩ ጥያቄ መሄድ ።
👉በተደጋጋሚ ሰአትን አለመመልከት ወይም ሰአት በቃን አልበቃን እያልን አለመጨነቅ።
👉መጭው ጊዜ የፈተና ወቅት ነውና ለተፈታኞች #ሸር በማድረግ ግንዛቤ እንፍጠር 🤲🤲🤲🤲
መልካም ቀን🥰🥰
✅ቻናላችን ይህ ነው
👇👇👇👇👇👇👇
💚💚💚💚💚💚💚
https://t.me/dam76
ሰላም ወላጆች ከመንግስት በተሰጠው አቅጣጫ መሰረት ነገ ዓርብ የከተራ በዓልን ምክንያት በማድረግ ትም/ት ቤቶች ዝግ የሚሆኑ ስለሆነ ሰኞ በ13/5/2016 በተለመደው ሰዓት ተማሪዎች በትም/ት ገበታቸው ላይ እንዲገኙ እንድታደርጉ በአክብሮት እያሳሰብን ከ15/5/2016 ጀምሮ የማጠቃለያ ፈተና የሚሰጥ ስለሆነ በበዓል ምክንያት ከጥናት እንዳይዘናጉ እንድታበረታቷቸው እናሳስባለን ።
።።።።።መልካም የጥምቀት በዓል!።።።።
ጣሳቸው ጫኔ /ር/መምህር
Repost from ABGS GRADE 9
6/5/2016
ሰላም ውድ ወላጆች
የ2016 ዓ/ም የ2ኛው ተርም ክፍያ ከጥር 1_10/5/2016 ዓ/ም መሆኑን ለማስታወስ ወደድን ። ክፍያወትን በወቅቱ በማጠናቀቅዎ ከልብ እናመሰግናለን ። በሌላ በኩል የ1ኛ ተርም ክፍያ ያልከፈላችሁ ወላጆች ተማሪዎች የማጠቃለያ ፈተና ከመቀመጣቸው በፊት ማጠናቀቅ የሚኖርባችሁ መሆኑን መግለፅ እንወዳለን ።
ሰሚት ሁለተኛ ደረጃ ቅርንጫፍ ትም/ት ቤት
