en
Feedback
Mesalemiya Betel Congregation

Mesalemiya Betel Congregation

Open in Telegram

መሳለሚያ ቤቴል መካነየሱስ

Show more
259
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
-130 days
Posts Archive
ሰላም ለእናንተ ይሁን!!!      በፍፁም ልብህ “በፍጹም ልብህ በእግዚአብሔር ታመን፥ በራስህም ማስተዋል አትደገፍ፤”   — ምሳሌ 3፥5 * በእግዚአብሔር መታመን ከእግዚአብሔር ጋር ባለን ግንኙነት እጅግ አስፈላጊ ነው ። *የእግዚአብሔር ልጆች እንደመሆናችን መጠን ሰማያዊ አባታችን እንደሚወደን በሚገባ እንደሚጠነቀቅልን በትክክል እንደሚመራን ፀጋ እንደሚሰጠን የተስፋውን ቃል እንደሚፈፅምልን እርግጠኞች ሆነን መናገር እንችላለን ። * የራሳችን ማስተዋል ግን ሊሳሳት የሚችል ለስህተትም የተጋለጠ ነው ።ስለዚህ በራሳችን እስተያየት መመካት የለብንም። ሰለዚህ እኛ ደግሞ * መንገዳችንን ለእግዚአብሔር እደራ እንስጥ “መንገድህን ለእግዚአብሔር አደራ ስጥ፥ በእርሱም ታመን፥ እርሱም ያደርግልሃል።”   — መዝ 35; 5 *  በመከራ ቀን በእግዚአብሔር መታመን “እግዚአብሔር መልካም ነው፥ በመከራ ቀንም መሸሸጊያ ነው፤ በእርሱ የሚታመኑትንም ያውቃል።”   — ናሆም 1፥7 *  የተናገረይም  እንደሚፈፅመው በእግዚአብሔር እንታመን ። “ስለዚህ እናንተ ሰዎች ሆይ፥ አይዞአችሁ፤ እንደ ተናገረኝ እንዲሁ እንዲሆን እግዚአብሔርን አምናለሁና።”   — ሐዋርያት 27፥25 ስለዚህ እግዚአብሔርን በፍጹም ልባችን ልንታመንው ይገባል ። መልካም ቀን ዮሴፍ ክፍሌ

_የተያዝሁበትን_ያን_ደግሞ_እይዛለሁ_ከአገልጋይ_ዮሐንስ_አባተ_ጋር_ክፍል_1_Sermon_with_Yohannes.m4a22.30 MB

የተያዝንበትን መያዝ በሚል ርዕስ በፓስተር ዮሐንስ አባተ የቀረበ መልዕክት

Voice message13:01

ዝማሬ   በሀ መዘምራን

Voice message09:34

ዝማሬ   በሀ መዘምራን

Voice message21:30

ዝማሬ በሀ መዘምራን

Voice message19:06

ትላንት እሁድ በነበረው አምልኮ ፕሮግራም በእህት ናርዶስ ህሩይ የቀረበ መልዕክት

ሰላም ለእናንተ ይሁን!!! የ ሕይወት መንገድ "በበጎ ሥራ በመጽናት ምስጋናንና ክብርን የማይጠፋንም ሕይወት ለሚፈልጉ የዘላለምን ሕይወት ይሰጣቸዋል፤" ሮሜ  2:7 በዚህ ጥቅስ  ሐዋርያው ጳውሎስ ለሮሜ ሰዎች በጻፈው መልእክት ውስጥ፣ በፊት ለፊታችን ስላሉ  ሁለት መንገዶች ይናገራል - 📖  አንዱ ወደ ሕይወት የሚያመራ፣ 📖 ሌላኛው ደግሞ ወደ ጥፋት የሚያመራ ነው ። እነዚህ በዓለም ውስጥ ከፍተኛ ስፍራን የያዙ   የሰውን ልጅ የመጨረሻ ግብ ለመድረስ በሚጓዝበት መስመር ላይ የተዘረጉ  በግዴታ ሳይሆን በምርጫ   የምንራመድባቸው መስመሮች ናቸው ። ጳውሎስ ሲጽፍ ምርጫችን ይህ ይሁን ከማለቱ በፊት በክፍሉ ሦስት ቁልፍ ነገሮችን አስቀምጧል፦ ​በበጎ ሥራ መጽናት ​ምስጋናንና ክብርን መፈለግ ​የማይጠፋ ሕይወት መፈለግ የሚሉትን ሲያስቀምጥ እነዚህ ሦስቱ   ለዘላለምን ሕይወት  መሠረታዊ ነገሮች  ናቸው።  ይህ ለእኔና ለእናንተ የመጨረሻ ግባችን ነው።  እዚህ ግብ ላይ ለመድረስ ቃሉ እነደሚለን ፦ በበጎ ሥራ በመጽናት  አለብን።  ⏭  በምድር ላይ ስንኖር  ትግል አለ። ሕይወት መራራም ፣ ጣፋጭም ናት። አንዱ ሲደሰት ከጎን ያለው ያለቅሳል። ሰውን የተለያዩ ሁኔታዎች ያስጨንቁታል፤  ደስታውን ያጨልማሉ ፤ 👉ይሁን እንጂ በሚገጥመን ክፉ ነገር ውስጥ ሁሉ ጸንቶ መቆም ፦     ⏭ መታገስ       ⏭ ተስፋ አለመቁረጥ፣ ⏭ ፈተናን መቋቋም  እነዚህን ስናደርግ  አለመሸነፋችን ጽናታችንን ይገልጻል ። 👉ታዲያ ምንም ከባድ ቢሆንም በዚህ ሁሉ ውስጥ እያለፍን   በጎ ማድረግን አለመተው፦ ·⏭ በጎነትን በቀጣይነት መፈጸም፤ ⏭ ቢያስቸግርም በጎነትን አለመተው፤  ⏭ የእግዚአብሔርን ትእዛዝ በታማኝነት መጠበቅ፤ ·⏭ ለሌሎች በፍቅር ማገልገል፤ 👉 ይህን በማድረጋችን የምንፈልገውን ምስጋናና ክብር  እናገኛለን። የሰው ልጅ እነዚህን ከሰው ይፈልጋል። ጳውሎስ  እየነገረን ያለው  የእግዚአብሔርን ምስጋና  ነው። ከሰው ሳይሆን ከእግዚአብሔር  ምሥጋናና ክብር ከማግኘታችን ባሻገር   የዘላለምን ሕይወት እንቀበላለን። መጽሐፍ ቅዱስ 📖  ​ስለ ማይጠፋ ሕይወት ሲነግረን... "ሕይወታችሁ ምንድር ነው? ጥቂት ጊዜ ታይቶ ኋላ እንደሚጠፋ እንፍዋለት ናችሁና። " — የያዕቆብ  4:14 · ሀብትና ክብር ያልፋል · ምድራዊ ምስጋና ይጠፋል ይለናል። 📖 ከእግዚአብሔር ጋር የምንኖረው ዘላለማዊ ሕይወት · ⏭ ሞት የሌለበት ሕይወት  ⏭ ሥቃይ፣ ሀዘን፣ ጩኸት የሌለበት ፥👉ፍጹም ደስታና ሰላም እናገኛለን።(ራእይ 21:4) 📖 "የዘላለምን ሕይወት ይሰጣቸዋል" ይህ  ስጦታ ነው እንጂ ደመወዝ አይደለም · የዘላለም ሕይወት የእግዚአብሔር ስጦታ ነው (ሮሜ 6:23) እንደዚሁም ሥራ የሌለው እምነት ቢኖር በራሱ የሞተ ነው። — የያዕቆብ መልዕክት 2:17 (አማርኛ 1954) ወገኖቼ፦ · እምነት ወደ በጎ ሥራ ይመራል · በጎ ሥራ እምነታችንን ያረጋግጣል · ሁለቱም ለዘላለም ሕይወት ያስፈልጉናል። "በበጎ ሥራ በመጽናት የዘላለምን ሕይወት ለመቀበል እግዚአብሔር ይርዳን። አሜን። ተባረኩ ወንድም አባይነህ ሽፈራው  

Voice message06:40

ዝማሬ በምስክር መዘምራን

Voice message18:07

ዝማሬ በምስክር መዘምራን

Voice message13:57

ከቃሉ ቦኃላ የነበረው ፀሎት

Voice message30:33

ትላንት አርብ በነበረው የፈውስ ፕሮግራም በቄስ ሙሉቀን ከተማ የቀረበ መልዕክት