Mesalemiya Betel Congregation
Ir al canal en Telegram
259
Suscriptores
Sin datos24 horas
Sin datos7 días
-130 días
Archivo de publicaciones
ሰላም ለእናንተ ይሁን!!!
በፍፁም ልብህ
“በፍጹም ልብህ በእግዚአብሔር ታመን፥ በራስህም ማስተዋል አትደገፍ፤”
— ምሳሌ 3፥5
* በእግዚአብሔር መታመን ከእግዚአብሔር ጋር ባለን ግንኙነት እጅግ አስፈላጊ ነው ።
*የእግዚአብሔር ልጆች እንደመሆናችን መጠን ሰማያዊ አባታችን እንደሚወደን በሚገባ እንደሚጠነቀቅልን በትክክል እንደሚመራን ፀጋ እንደሚሰጠን የተስፋውን ቃል እንደሚፈፅምልን እርግጠኞች ሆነን መናገር እንችላለን ።
* የራሳችን ማስተዋል ግን ሊሳሳት የሚችል ለስህተትም የተጋለጠ ነው ።ስለዚህ በራሳችን እስተያየት መመካት የለብንም።
ሰለዚህ እኛ ደግሞ
* መንገዳችንን ለእግዚአብሔር እደራ እንስጥ
“መንገድህን ለእግዚአብሔር አደራ ስጥ፥ በእርሱም ታመን፥ እርሱም ያደርግልሃል።”
— መዝ 35; 5
* በመከራ ቀን በእግዚአብሔር መታመን
“እግዚአብሔር መልካም ነው፥ በመከራ ቀንም መሸሸጊያ ነው፤ በእርሱ የሚታመኑትንም ያውቃል።”
— ናሆም 1፥7
* የተናገረይም እንደሚፈፅመው በእግዚአብሔር እንታመን ።
“ስለዚህ እናንተ ሰዎች ሆይ፥ አይዞአችሁ፤ እንደ ተናገረኝ እንዲሁ እንዲሆን እግዚአብሔርን አምናለሁና።”
— ሐዋርያት 27፥25
ስለዚህ እግዚአብሔርን በፍጹም ልባችን ልንታመንው ይገባል ።
መልካም ቀን
ዮሴፍ ክፍሌ
_የተያዝሁበትን_ያን_ደግሞ_እይዛለሁ_ከአገልጋይ_ዮሐንስ_አባተ_ጋር_ክፍል_1_Sermon_with_Yohannes.m4a22.30 MB
ሰላም ለእናንተ ይሁን!!!
የ ሕይወት መንገድ
"በበጎ ሥራ በመጽናት ምስጋናንና ክብርን የማይጠፋንም ሕይወት ለሚፈልጉ የዘላለምን ሕይወት ይሰጣቸዋል፤"
ሮሜ 2:7
በዚህ ጥቅስ ሐዋርያው ጳውሎስ ለሮሜ ሰዎች በጻፈው መልእክት ውስጥ፣ በፊት ለፊታችን ስላሉ ሁለት መንገዶች ይናገራል -
📖 አንዱ ወደ ሕይወት የሚያመራ፣
📖 ሌላኛው ደግሞ ወደ ጥፋት የሚያመራ ነው ። እነዚህ በዓለም ውስጥ ከፍተኛ ስፍራን የያዙ የሰውን ልጅ የመጨረሻ ግብ ለመድረስ በሚጓዝበት መስመር ላይ የተዘረጉ በግዴታ ሳይሆን በምርጫ የምንራመድባቸው መስመሮች ናቸው ። ጳውሎስ ሲጽፍ ምርጫችን ይህ ይሁን ከማለቱ በፊት በክፍሉ ሦስት ቁልፍ ነገሮችን አስቀምጧል፦
በበጎ ሥራ መጽናት
ምስጋናንና ክብርን መፈለግ
የማይጠፋ ሕይወት መፈለግ የሚሉትን ሲያስቀምጥ እነዚህ ሦስቱ ለዘላለምን ሕይወት መሠረታዊ ነገሮች ናቸው። ይህ ለእኔና ለእናንተ የመጨረሻ ግባችን ነው። እዚህ ግብ ላይ ለመድረስ ቃሉ እነደሚለን ፦ በበጎ ሥራ በመጽናት አለብን።
⏭ በምድር ላይ ስንኖር ትግል አለ። ሕይወት መራራም ፣ ጣፋጭም ናት። አንዱ ሲደሰት ከጎን ያለው ያለቅሳል። ሰውን የተለያዩ ሁኔታዎች ያስጨንቁታል፤ ደስታውን ያጨልማሉ ፤ 👉ይሁን እንጂ በሚገጥመን ክፉ ነገር ውስጥ ሁሉ ጸንቶ መቆም ፦ ⏭ መታገስ ⏭ ተስፋ አለመቁረጥ፣
⏭ ፈተናን መቋቋም እነዚህን ስናደርግ አለመሸነፋችን ጽናታችንን ይገልጻል ።
👉ታዲያ ምንም ከባድ ቢሆንም በዚህ ሁሉ ውስጥ እያለፍን በጎ ማድረግን አለመተው፦
·⏭ በጎነትን በቀጣይነት መፈጸም፤
⏭ ቢያስቸግርም በጎነትን አለመተው፤
⏭ የእግዚአብሔርን ትእዛዝ በታማኝነት መጠበቅ፤
·⏭ ለሌሎች በፍቅር ማገልገል፤
👉 ይህን በማድረጋችን የምንፈልገውን ምስጋናና ክብር እናገኛለን። የሰው ልጅ እነዚህን ከሰው ይፈልጋል። ጳውሎስ እየነገረን ያለው የእግዚአብሔርን ምስጋና ነው። ከሰው ሳይሆን ከእግዚአብሔር ምሥጋናና ክብር ከማግኘታችን ባሻገር የዘላለምን ሕይወት እንቀበላለን። መጽሐፍ ቅዱስ
📖 ስለ ማይጠፋ ሕይወት ሲነግረን...
"ሕይወታችሁ ምንድር ነው? ጥቂት ጊዜ ታይቶ ኋላ እንደሚጠፋ እንፍዋለት ናችሁና። " — የያዕቆብ 4:14
· ሀብትና ክብር ያልፋል
· ምድራዊ ምስጋና ይጠፋል ይለናል።
📖 ከእግዚአብሔር ጋር የምንኖረው ዘላለማዊ ሕይወት
· ⏭ ሞት የሌለበት ሕይወት ⏭ ሥቃይ፣ ሀዘን፣ ጩኸት የሌለበት ፥👉ፍጹም ደስታና ሰላም እናገኛለን።(ራእይ 21:4)
📖 "የዘላለምን ሕይወት ይሰጣቸዋል" ይህ ስጦታ ነው እንጂ ደመወዝ አይደለም
· የዘላለም ሕይወት የእግዚአብሔር ስጦታ ነው (ሮሜ 6:23)
እንደዚሁም ሥራ የሌለው እምነት ቢኖር በራሱ የሞተ ነው። — የያዕቆብ መልዕክት 2:17 (አማርኛ 1954)
ወገኖቼ፦
· እምነት ወደ በጎ ሥራ ይመራል
· በጎ ሥራ እምነታችንን ያረጋግጣል
· ሁለቱም ለዘላለም ሕይወት ያስፈልጉናል። "በበጎ ሥራ በመጽናት የዘላለምን ሕይወት ለመቀበል እግዚአብሔር ይርዳን። አሜን።
ተባረኩ
ወንድም አባይነህ ሽፈራው
