en
Feedback
Benishangul Gumuz Education Bureau

Benishangul Gumuz Education Bureau

Open in Telegram

ይህ ቻናል የቤኒሻንጉል-ጉሙዝ ክልል ትምህርት ቢሮ የቴሌግራም ቻናል ሲሆን ከክልል እስከ ትምህርት ቤቶች ድረስ የተከናወኑ እንዲሁም ሀገራዊ ፣ አህጉራዊ እና አለማቀፋዊ የትምህርት መረጃዎች ተደራሽ የሚደረጉበት ነው፡፡

Show more
7 042
Subscribers
-724 hours
+517 days
+1 11230 days
Attracting Subscribers
September '26
September '26
+17
in 0 channels
August '26
+1 270
in 4 channels
Get PRO
July '26
+443
in 1 channels
Get PRO
June '26
+98
in 2 channels
Get PRO
May '26
+56
in 0 channels
Get PRO
April '26
+90
in 0 channels
Get PRO
March '26
+182
in 0 channels
Get PRO
February '26
+51
in 1 channels
Get PRO
January '26
+50
in 0 channels
Get PRO
December '25
+277
in 2 channels
Get PRO
November '25
+200
in 2 channels
Get PRO
October '25
+313
in 4 channels
Get PRO
September '25
+437
in 2 channels
Get PRO
August '25
+126
in 2 channels
Get PRO
July '25
+139
in 2 channels
Get PRO
June '25
+119
in 2 channels
Get PRO
May '25
+152
in 1 channels
Get PRO
April '25
+128
in 1 channels
Get PRO
March '25
+118
in 0 channels
Get PRO
February '25
+72
in 2 channels
Get PRO
January '25
+136
in 4 channels
Get PRO
December '24
+154
in 2 channels
Get PRO
November '24
+183
in 1 channels
Get PRO
October '24
+278
in 1 channels
Get PRO
September '24
+154
in 2 channels
Get PRO
August '24
+157
in 2 channels
Get PRO
July '24
+182
in 3 channels
Get PRO
June '24
+204
in 2 channels
Get PRO
May '24
+411
in 3 channels
Get PRO
April '24
+173
in 2 channels
Get PRO
March '24
+114
in 1 channels
Get PRO
February '24
+138
in 1 channels
Get PRO
January '24
+173
in 2 channels
Get PRO
December '23
+148
in 2 channels
Get PRO
November '23
+151
in 2 channels
Get PRO
October '23
+245
in 2 channels
Get PRO
September '23
+135
in 0 channels
Get PRO
August '23
+119
in 0 channels
Get PRO
July '23
+91
in 0 channels
Get PRO
June '23
+73
in 0 channels
Get PRO
May '23
+89
in 0 channels
Get PRO
April '23
+109
in 0 channels
Get PRO
March '23
+236
in 0 channels
Get PRO
February '23
+1 539
in 0 channels
Date
Subscriber Growth
Mentions
Channels
03 September+4
02 September+3
01 September+10
Channel Posts
28ኛው ክልል አቀፍ የትምህርት ጉባኤ ነገ ይካሄዳል ------------ ------------- -------------- ----------------- (ነሃሴ 27/2018 ዓ.ም ፤ አሶሳ) የቤኒሻንጉል-ጉሙዝ ክልላዊ መንግስት ትምህርት ቢሮ 28ኛው ክልል አቀፍ የትምህርት ጉባኤውን ጥራትና ፍትሃዊነቱ የተረጋገጠ ትምህርት ለተሻለ የመማር ውጤት በሚል ቃል ነገ ይካሄዳል። የክልሉ ትምህርት ቢሮ ሃላፊ ተመስገን ዲሳሳ (ዶ/ር) ለኢቢሲ በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ ጉባኤው በዋናነት የ2018 ዓ.ም የትምህርት ዘርፍ ስኬቶችን በቀጣይ አጠናክሮ ማስቀጠልና በቀጠይ 2019 ዓ.ም የተማሪዎችን ውጤት ማሻሻልን ማዕከል ያደረጉ ስራዎችን ላይ በትኩረት ለመስራት ያለመ ውይይትና የስራ መመሪያ የሚሰጥበት መድረክ መሆኑን ጠቅሰዋል፡፡ በክልል አቀፍ ፈተናዎች በ2018 ዓ.ም 50 ፐርስንትና ከዚያ በላይ ውጤት መመዝገቡንና ከ2017 የትምህርት ዘመን ጋር አንጻር መሻሻል ማሳየቱን ያነሱት ሃላፊው ሀገር አቀፍ የ12ኛ ክፍል ፈተናም በተመሳሳይ በዚህ ዓመት መሻሻል ታይቷል ብለዋል፡፡ ይሄ ውጤት በትምህርት ስራ ሃላፊዎች ፣ በመምህራን ፣ በትምህርት ቤት አመራሮችና በትምህርት ባለሙያዎችና በባለድርሻ አካላት ርብርብ የተገኘ ውጤት ቢሆንም አሁንም ይበልጥ ከፊት ለፊታችን የትምህርት ጥራት ላይ መስራት በእጅጉ የሚቀረን የቤት ስራዎች አሉን ብለዋል፡፡ በ2019 የትምህርት ዘመን 320ሺ ገደማ ተማሪዎችን በትምህርት ካለንደሩ ተመዝግበው ትምህርት እንዲጀምሩና 53 ሺ የቅድመ መደበኛ ሕፃናት መመዝገብ ብቻ ሳይሆን በዋናነት በክፍል ተገኝተው እንዲማሩና በትምህርት ገበታ ላይ እንዲቆዩ ፤ ተገቢውን ዕውቀት እንዲያገኙ ማድረግ ሌላው በጉባኤው ትኩረት የሚሰጠው ጉዳይ ነው ሲሉ ቢሮ ሃላፊው አክለዋል፡፡ በዚህ መድረክ ላይ ከፍተኛ የፌደራል ፣ የክልል ፣ የዞን ፣ የወረዳና የዘርፉ ባለድርሻ አካላት ይሳተፋሉ ተብሎ ይጠበቃል፡፡ ዘገበው የቢሮው ኮሙኒኬሽን ዳሬክቶሬት ነው፡፡

2
No text...
918
3
+4
No text...
1 121
4
እናመሰግናለን ፤ ትምህርት ለትውልድ 👏👏👏 ‎የክልሉ የመንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ የተማሪዎች የትምህርት ቁሳቁስ ድጋፍ አደረገ ‎**** ‎ ‎(አሶሳ፣ ነሐሴ 26/2018 ዓ.ም) የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የመንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ የክረምት በጎ ፍቃድ አገልግሎት አካል የሆነ የተማሪዎች የትምህርት ቁሳቁስ ድጋፍ አደረገ። ‎ ‎የክልሉ የመንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ ኃላፊ አቶ መለሰ በየነ ድጋፉን ለተማሪዎች ባስረከቡበት ወቅት፣ የክረምት በጎ ፍቃድ አገልግሎት የዜጎችን የእርስበርስ ማህበራዊ መስተጋብርን እያጎለበተ ነው ብለዋል። ‎ ‎ቢሮው ማህበራዊ ኃላፊነቱን ለመወጣት በተያዘው የክረምት አገልግሎት በአሶሳ ከተማ የአንድ አቅመ ደካማ ቤት አዲስ ግንባታ ለመገንባት የቦታ ርክክብ በማድረግ ወደ ስራ መገባቱን አቶ መለሰ ተናግረዋል። ‎ ‎በዛሬው ዕለትም የተቋሙ የክረምት በጎ ፍቃድ አገልግሎት አካል የሆነ የተማሪዎች የትምህርት ቁሳቁስ ድጋፍ መደረጉን ገልጸዋል። ‎ ‎ድጋፉ ተማሪዎች በትምህርት ቁሳቁስ እጥረት ምክንያት ከትምህርት ገበታ ውጪ እንዳይሆኑ ያግዛል ያሉት አቶ መለሰ፣ በቀጣይም የአንድ አቅም ደካማ አዲስ ቤት ግንባታና የማዕድ ማጋራት መርኃ-ግብር እንደሚካሄድም ገልጸዋል። ዘገባው የክልሉ ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ ነው።
1 117
5
የፋሮ ፋዎንዴሽን የሆሞሻ የሴት ተማሪዎች አዳሪ ትምህርት ቤት የ9ኛ ክፍል ተማሪዎች ለ2019 የትምህርት ዘመን ምዝገባ ጀምሯል፡፡
1 288
6
+1
No text...
1 782
7
ትምህርት የዕድሜ ገደብ የለውም። 320 ነጥብ ያመጡት ቄስ ሰይፉ ተስፋይ ! " ትምህርት ፍላጎትና ተነሳሽነት ካለ ዕድሜ አይገድበውም " የሚለውን እውነታ በተግባር ያሳዩት ቄስ ሰይፉ ተስፋይ፣ በዘንድሮው የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና 320 ነጥብ በማምጣት ወደ ዩኒቨርሲቲ ለመግባት ከሚጠባበቁ ተፈታኞች መካከል ተጠቃሽ ሆነዋል። ቄስ ሰይፉ ተስፋይ በትግራይ ክልል፣ ደቡባዊ ዞን፣ ሰለዋ ወረዳ፣ ደጀን ቀበሌ፣ ግራዛፎ መንደር ነዋሪ ናቸው። የ66 ዕድሜ ባለፀጋው ቄስ ሰይፉ፣ በሰለዋ ከተማ በሚገኘው የአንበሳ ባንክ የጥበቃ ሠራተኛ በመሆን እየሰሩ ነው። ከሥራቸው ጎን ለጎን ግን ትምህርታቸውን በመቀጠል የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተናን ለመፈተን ችለዋል። በዘንድሮው የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና በትግራይ ክልል ፈተናቸውን ከወሰዱ 29 ሺህ ተፈታኞች መካከል ቄስ ሰይፉም አንዱ ሲሆኑ፣ 320 ነጥብ በማምጣት የማለፊያ ውጤት ካመጡ 3,146 ተፈታኞች መካከል አንዱ ናቸው። የቄስ ሰይፉ ውጤት በማህበራዊ ሚዲያ ትኩረት ያገኘ ሲሆን የሚሰሩበት ባንክም በተሳካላቸው ውጤት በመደሰት ማበረታቻ አበርክቶላቸዋል። ባንኩ ምን አለ ? 1. ወደ ዩንቨርስቲ ለመግባት እና ለመማር የሚያስፈልጋቸው ማንኛውም ወጪ የዩንቨርስቲ ቆይታቸው እስከሚያጠናቅቁ ድረስ ሙሉ ወጪያቸውን ባንኩ ይሸፍንላችዋል። 2. ወደ ዩንቨርስቲ ከገቡበት ወር ጀምሮ አሁን የሚከፈላቸ ወርሃዊ ደመወዝ ሙሉ በሙሉ በየወሩ ለቤተሰቦቻቸው እንዲከፈል ይደረጋል። 3. የዩንቨርስቲ ትምህርታቸው ካጠናቀቁ በኋላ ባንኩ በተገቢው የስራ ዘርፍ በመመደብ በቋሚነት ቀጥሮ የሚያሰራቸው እንደሚሆን ባንኩ አሳውቋል። የቄስ ሰይፉ ታሪክ ትምህርት ለመማር ዕድሜ፣ ሥራ ወይም ሌላ ሁኔታ እንቅፋት እንዳልሆነ፣ ፍላጎትና ተነሳሽነት ካለ ሰው የፈለገውን ግብ ለማሳካት እንደሚችል ያሳያል። ቄስ ሰይፉ ባለትዳርና የ6 ልጆች አባት ናቸው። ነሐሴ 23 ቀን 2018 ዓ/ም tikvahethiopia
1 702
8
ትምህርት ቤታቸውን ፤ ባለውለታ የቀለም ቤታቸውን እያደሱ ነው።👏👏👉 በማኦ እና ኮሞ ልዩ ወረዳ በሾሾር ቡቱጅ አንደኛና መካከለኛ ደረጃ ት/ቤት በበጎ ፍቃደኛ ወጣቶች ለ2019ዓ.ም ትምህርት ዘመን+5
ትምህርት ቤታቸውን ፤ ባለውለታ የቀለም ቤታቸውን እያደሱ ነው።👏👏👉 በማኦ እና ኮሞ ልዩ ወረዳ በሾሾር ቡቱጅ አንደኛና መካከለኛ ደረጃ ት/ቤት በበጎ ፍቃደኛ ወጣቶች ለ2019ዓ.ም ትምህርት ዘመን ለተማሪዎች ምቹ የት/ቤት አካባቢ ለመፍጠር የመማሪያ ክፍል እድሳት በማድረግ የማስዋብ ስራ ተሰርቷል። እናመሰግናለን!!
2 309
9
+9
No text...
2 280
10
No text...
1 748
11
የቢሮው የሴቶች ክንፍ በክረምት የበጎ ፍቃድ አገልግሎት የተለያዩ ድጋፎችን አድርጓል ----------- ----------------- ----------------- ----------- (ነሃሴ 22/2018 ዓ.ም ፤ አሶሳ) በቤኒሻንጉል-ጉሙዝ ክልል ትምህርት ቢሮ በክረምት የበጎ ፍቃድ አገልግሎት የቢሮው የሴቶች ክንፍ ለተማሪዎች የትምህርት ቁሳቀስና በቢሮው የገቢ መጠናቸው አነስተኛ ለሆኑ ሰራተኞችም የንጽህና መጠበቂያና አልባሳትን ድጋፍ አድርጓል፡፡ ወ/ሮ ሄዋን ታረቀኝ በቢሮው የንብ/አስ/ ቡድን መሪና በቢሮው የሴቶች ክንፍ አስተባባሪ ሲሆን በዛሬውም ዕለት የ2019 ዓ.ም የስራ ዕቅድ ፤ በዓመቱ የተከናወኑ ስራዎችንም ለተሳታፊዎች በሰነድ አቅርበዋል፡፡ የክልሉ የሴቶች ክንፍ አስተባባሪ ወ/ሮ አዳነች የክልሉ ትምህርት ቢሮ የሴቶች ክንፍ በክልሉ ካሉት ሴክተሮች ቀዳሚ መሆኑን ገልጸው ፤ ይህን ስራ በቀጣይ ዓመትም ተጠናክሮ መቀጠል አለበት ብለዋል፡፡ የዓመቱን ዕቅድ አስመልክቶም የቢሮው ሴት ሠራተኞች ውይይት አድርገዋል፡፡
1 676
12
ኤስ.አይ.ኤል- ኢትዮጲያ የመማሪያ ቀሳቁስ ድጋፍ አደረገ --------- ----------- ------------ --------- (ነሃሴ 22/2018 ዓ.ም ፤ አሶሳ) ኤስ.አይ.ኤል- ኢትዮጲያ መንግስ+3
ኤስ.አይ.ኤል- ኢትዮጲያ የመማሪያ ቀሳቁስ ድጋፍ አደረገ ---------   -----------   ------------  --------- (ነሃሴ 22/2018 ዓ.ም ፤ አሶሳ) ኤስ.አይ.ኤል- ኢትዮጲያ መንግስታዊ ያልሆነ ድርጅት ለተማሪዎች የትምህርት አገልግሎት የሚውል የመማሪያ ቀሳቁስ ለቢሮው አስረክቧል፡፡ የቢሮው የስርዓተ-ትምህርትና የትምህርት ተቋማት ዘርፍ ምክትል ቢሮ ሃላፊ አቶ መሀመድ ኡስማንም ድርጅቱ ላደረገው ድጋፍ አመስግነው ፤ ሌሎችም ተመሳሳይ ድጋፎችን እንዲያደርጉ ጠይቀዋል፡፡   በክልሉ የድርጅቱ ፕሮግራም አስተባባሪ አቶ ፍቃዱ ዴሬሳ ድርጅታቸው በክልሉ የአፍ መፍቻ ቋንቋዎችን ማበልጽግና መማር ማስተማሩን ላይ በዋናነት ድጋፍ እያደረገ የሚገኝ ድርጅት መሆኑን ገልጸው እንዲህ ያሉ ድጋፎችንም ሲያደርግ መቆየጡን ጠቅሰዋል፡፡   ድርጅታቸው 1000 ደብተር ፣ 1000 እርሳስና 1000 እስክሪፕቶ ለቢሮው በዛሬለው ዕለት አስረክቧል፡፡
1 610
13
የሀዘን መግለጫ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የአፍ መፍቻ ቋንቋዎችን የትምህርት ቋንቋ ለማድረግ የተለያዩ ጥናቶች በማካሄድ ብሎም ከፊደል ቀረጻ ጀምሮ አሁን ላይ ለደረሱበት ደረጃ ትልቅ አብረክቶ ያደረጉት
የሀዘን መግለጫ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የአፍ መፍቻ ቋንቋዎችን የትምህርት ቋንቋ ለማድረግ የተለያዩ ጥናቶች በማካሄድ ብሎም ከፊደል ቀረጻ ጀምሮ አሁን ላይ ለደረሱበት ደረጃ ትልቅ አብረክቶ ያደረጉትን አቶ አንድርያስ ኒውዶርፍ ህልፈተ ሕይዎት የቢሮው የስራ ሃላፊዎችና ሠራተኞች የተሰማንን ልባዊ ሀዘን እንገልጻለን፡፡ አቶ እንድሪያስ ከ1994 ዓ.ም እስከ 2008 ዓ.ም ድረስ በክልላችን የብዝሃ ቋንቋ ትምህርት ፕሮጀክት አስተባባሪ በመሆን በትጋት አገልግለዋል። በቆይታቸውም ፡- የቤኒሻንጉለኛ ፣ የጉሙዘኛ ፣ የሺናሽኛ ፣ የማኦኛ ፣ የኮሞኛ እና የጎማ ቋንቋዎችን ከፊደል ቀረጻ እስከ ጥናቶችን በማካሄድ የትምህርት ቋንቋ እንዲሆኑ አስችለዋል፡፡ የሙከራ መጽሐፍትን ፣ ልዩ ልዩ መዝገበ ቃላትንና አጋዥ የመማሪያ ቁሳቁሶችን አንዲሁ አዘጋጅተው ለክልሉ አበርክተዋል፡፡ ለመምህራን ሰፊ ስልጠና በመስጠትና የህጻናትን የአፍ መፍቻ ቋንቋ ትምህርት መሠረትን በማጠናከር የማይረሳ ታሪካዊ አሻራ አስቀምጠዋል ፤ ይሄንን ቢሮውና ክልሉ መቼም አይዘነጋውም፡፡ የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ትምህርት ቢሮም ለአቶ እንድሪያስ ባለቤት ፣ ለሶስቱ ልጆቻቸው ፣ ለወዳጅ ዘመዶቻቸው እንዲሁም ለመላው የትምህርት ማህበረሰብ መጽናናትን እንመኛለን፡፡ የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልላዊ መንግስት ትምህርት ቢሮ ነሃሴ 22/2018 ዓ.ም አሶሳ
1 611
14
+9
No text...
1 973
15
ትምህርት ቤቶችን ማካታትን አስመልክቶ ምክክር ተካሄደ ---------------- --------------- ------------------- (ነሃሴ 21/2018 ዓ.ም ፤ አሶሳ) ፕላን ኢንተርናሽናል ድርጅት በቤኒሻንጉል- ጉሙዝ ክልል በዑራ ወረዳ በአቁዳ የስደተኞች መጠሊያ ጣቢያና በስደተኛ ተቀባይ ህብረተሰብ የሚገኙ የትምህርት ተቋማትን ወደ መንግስት ማካታትን አስመልክቶ ባዘጋጀው መድረክ ላይ ውይይት ተካሂዷል። በዚህ መድረክ ላይ የክልሉ ትምህርት ቢሮ የስራ ሃላፊዎች ፣ RRS ተወካዮቾ ፣ UNHCR ተወካዮች ፣ የዑራ ወረዳ ትምህርት የስራ ሃላፊዎች ፣ ባለሙያዎችና መምህራን ተሳታፊ ሆነዋል። መድረኩን በይፋ የከፈቱት በክልሉ ትምህርት ቢሮ የትምህርት ፕሮግራሞች ዘርፍ ምክትል ቢሮ ሃላፊ አቶ በሺር አብዱራሂም ፕላን ኢንተርናሽናል በክልሉ በስደተኞች መጠለያ ጣቢያና ስደተኛ ተቀባይ ህብረተሰብ ከትምህርት ስራዎች ጋር በተያያዘ እያደረገ ያለውን ድጋፍ የሚበረታታና የሚደገፍ መሆኑን ጠቅሰው ፤ የትምህርት ተቋማት ወደ መንግስት በማዘዋወር ስደተኞችን ጨምሮ ሁሉንም ዜጎች እኩል አገልግሎት ለመስጠት በሚቻልበት ሂደት ቢሮው ሃላፊነቱን ይወጣል ብለዋል። በዚህም ሂደት ትምህርት ቤቶችን ወደ መንግስት በማካተትና ከተካተቱም በኋላ የትምህርት ልማት አጋሮች እንደየትኛውም ጊዜ ድጋፋቸው መቀጠል አለበት ብለዋል። አቶ ይትባረክ በድርጅቱ የትምህርት ፕሮግራም ሃላፊ ሲሆኑ ድርጅቱ በአቁዳ ስደተኞችና ስደተኛ ተቀባይ ህብረተሰብ ሲያከናውናቸው የቆየውን የትምህርት ስራዎች ለውይይት መነሻ ሰነድ አቅርበዋል። በትምህርት መሠረት ልማት ፣ የትምህርት ግብዓት አቅርቦት ፣ የመማር ማስተማር ስራዎችን የሚያሻሽሉ ስልጠናዎች ፣ የትምህርት በአደጋ ጊዜና መሠል ስራዎች ተከናውነዋል ሲሉ አቶ ይትባረክ ገልፀዋል። እነኚህንና መሠል ስራዎች በቀጣይ በድርጅቱ ድጋፍ እንደሚቀጥሉና ትምህርት ቤቶች የማካተት ፕሮግራም አስመልክቶ ከተሳታፊዎች ጋር ውይይት ተደርጓል። ዘገባው የቢሮው ኮሙኒኬሽን ክፍል ነው።
1 882
16
+6
No text...
2 321
17
በመንጌ ወረዳ የመንጌ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት 👏👏👏👏 በርቱልን ፤ ተማሪዎች ላይ አበክረን ከሰራን ውጤት ይመጣል።
2 064
18
ከቤኒሻንጉል-ጉሙዝ ክልል እስከአሁን ባለን መረጃ ከሆሞሻ ፋሮ ፋዎንዴሽን የሴቶች አዳሪ ትምህርት ቤት ተማሪ ረያን አሰፋ ከሴቶች 493.17 (Natural Science student from Homosha
ከቤኒሻንጉል-ጉሙዝ ክልል እስከአሁን ባለን መረጃ ከሆሞሻ ፋሮ ፋዎንዴሽን የሴቶች አዳሪ ትምህርት ቤት ተማሪ ረያን አሰፋ ከሴቶች 493.17 (Natural Science student from Homosha) ውጤት አስመዝግባለች፡፡ የክልሉ ትምህርት ቢሮም ለተማሪ ረያን አሰፋ ፣ ለወላጆቹና ለትምህርት ቤቱ የአንኳን ደስ ያላችሁ መልዕክቱን ያስተላልፋል፡፡
2 264
19
ከቤኒሻንጉል-ጉሙዝ ክልል እስከአሁን ባለን መረጃ ከወንበራ ወረዳ ደብረ-ዘይት 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ተማሪ ሙሉዓለም አምሳሉ 554.41 ውጤት አምጥቷል፡፡
ከቤኒሻንጉል-ጉሙዝ ክልል እስከአሁን ባለን መረጃ ከወንበራ ወረዳ ደብረ-ዘይት 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ተማሪ ሙሉዓለም አምሳሉ 554.41 ውጤት አምጥቷል፡፡
2 311
20
የተከተልነው ስልት ፍሬ አፍርቷል የወረዳው ት/ጽ/ቤት 👏👏👏 የማኦና ኮሞ ልዩ ወረዳ ትምህርት ጽ/ቤት በቶንጎ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ከሶስት ትምህርት ቤቶች የተሻለ ውጤት ያላቸውን ተማሪዎች ወደ አንድ ማዕከል በማምጣት በተለየ ሁኔታ በትምህርት ቤቱ በማሳደርና ተገቢውን ትምህርትና ድጋፍ ሲደረግላቸው ከነበሩት ተማሪዎች ስድስት ተማሪዎች የከፍተኛ ትምህርት ተቋም የመግቢያ ውጤት አምጥተዋል። ይሄ አብነታዊ ተግባር ውጤት ታይቶበታል ፤ ለሌሎችም ተሞክሮ ይሆናል። የወረዳው ትምህርት ጽህፈት ቤት ለዚህ ሴኬት ትልቁን ምስጋና መምህራን ቢሆኑም የወረዳው መስተዳድርና እገዛ ላደረጉ አካላት ሁሉ ምስጋና አቅርቧል። ይሄን ተግባር በቀጣይም ለማስቀጠል ይበልጥ እንደሚተጋ ጽ/ቤቱ አስታውቋል ። ያለፉ የተማሪዎች ቁጥርም ከዚህ በላይ ከፍ ሊል ይችላል ተብሏል።
2 442