Dire Soccer
Open in Telegram
የኢትዮዽያ ኘሪምየር ሊግ አዳዲስ መረጃዎች Join Us :- @DireSoccer ሀሳብና አስተያየት:- @direDire የሐሳብ መድረክ :- @Diresoccerfamily የፌስቡክ ድረ ገፅ :- https://m.facebook.com/diresoccer
Show more1 289
Subscribers
-224 hours
-87 days
-3330 days
Posts Archive
1 289
🇪🇹 መልካም ጨዋታ 🇪🇹
ድሬሶከር የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ከቡርኪናፋሶው አቻው ጋር በሚያደርጉት የዓለም ዋንጫ ማጣሪያ ሁለተኛ ጨዋታ መልካም ዕድል እንዲገጥማቸው ይመኛል።
💪 ድል ለኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን 💪
🏆 ድል ለዋልያዎቹ 🏆
@diresoccer
1 289
Repost from Soccer Ethiopia
የዓለም ዋንጫ ማጣሪያ የምድብ የመጀመሪያ ጨዋታ
ሁለተኛው አጋማሽ ተጀምሯል!
🇪🇹 ኢትዮጵያ 0-0 🇸🇱 ሴራሊዮን
*የኢትዮጵያ እና የሴራሊዮን ብሔራዊ ቡድኖች የዓለም ዋንጫ ማጣሪያ የመጀመሪያ ጨዋታ ሞሮኮ የክረምት ወቅት መግቢያ ላይ በመሆኗ በተከሰተው የዐየር ሁኔታ ምክንያት ሜዳው በጉም በመሸፈኑ ዘለግ ላሉ ደቂቃዎች ተቋርጦ የነበረ ቢሆንም አሁን ሁለተኛው አጋማሽ ተጀምሯል።
1 289
Repost from Soccer Ethiopia
የኢትዮጵያ እና ሴራሊዮን ጨዋታ ሁለተኛው አጋማሽ በስታዲየሙ ባለው ጭጋጋማ የዐየር ሁኔታ እስካሁን አልተጀመረም
* ጨዋታው መቀጠል እና አለመቀጠሉ እስካሁን አልታወቀም
1 289
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን የዓለም ዋንጫ ማጣርያ የሀገር ቤት ዝግጅቱ የመጨረሻ ምዕራፍ ላይ የደረሰ ሲሆን የብሔራዊ ቡድኑ አዲሱ አሰልጣኝ ገብረመድህን ኃይሌ ከሴራሊዮን እና ቡርኪና ፋሶ ጋር ለሚያደርጉት ጨዋታ የሚጠቀሙባቸውን 23 ተጫዋቾችን ለይተዋል።
⚽️ ግብ ጠባቂዎች
1. ሰዒድ ሀብታሙ
2. አቡበከር ኑራ
3. ቢንያም ገነቱ
⚽️ ተከላካዮች
4.ሄኖክ አዱኛ
5. ዓለምብርሃን ይግዛው
6. ያሬድ ባዬ
7. ሚሊዮን ሰለሞ
8. ምኞት ደበበ
9.ፈቱዲን ጀማል
10.ረመዳን የሱፍ
11.ያሬድ ካሳዬ
⚽️ አማካዮች
12. ጋቶች ፓኖም
13. ናትናኤል ዘለቀ
14. ሱራፌል ዳኛቸው
15. ከነዓን ማርክነህ
16. ወገኔ ገዛኸኝ
17. የአብሥራ ተስፋዬ
⚽️ አጥቂዎች
18. አቤል ያለው
19. አማኑኤል ገ/ሚካኤል
20. በረከት ደስታ
21. ሀብታሙ ታደሰ
22. ቸርነት ጉግሳ
23. ፍፁም ጥላሁን
@diresoccer
@diresoccer
1 289
Repost from Soccer Ethiopia
አንጋፋው የድሬደዋ ኢንተርናሽናል ስታዲየም የመጫወቻ ሜዳ ለውጥ ተደርጎበታል
ታሪካዊው የድሬደዋ ስታዲየም ከዛሬ ሃምሳ ዓመት በፊት ለአስረኛ የአፍሪካ ዋንጫ ለማዘጋጀት ሲባል ተገንብቶ አህጉር አቀፍም ሆነ የውስጥ የተለያዩ ውድድሮችን እያስተናገደ
በጊዜ ሂደት የተለያዩ ለውጦች እየተደረጉለት አሁን ያለንበት ጊዜ ደርሷል።
ያለፉትን ሦስት ዓመታት የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ጨዋታዎችን በመቀበል ከተማዋ ስታስደናግድ ቆይታለች። ሆኖም ከተፈጥሮ ጋር በተያያዘ በዝናብ ምክንያት የመጫወቻ ሜዳው ምቹ አለመሆኑን ተከትሎ ውድድሮችን በማስተጓጎሉ ትችት ሲቀርብበት መቆየቱ የቅርብ ጊዜ ትውስታ ነው።
ይህን ችግር በዘላቂነት ለመቅረፍ በማሰብ በከተማ አስተዳደሩ ከንቲባ ክቡር ከድር ጁሀር ትዕዛዝ የገንዘብ ድጋፍ እና የቅርብ ክትትል ደረጃውን የጠበቀ የፊፋን መስፈርት ያሟላ ዘመናዊ አርቲፊሻል ሳር የማንጠፍ ስራ ተጀምሮ ወደ መጠናቀቁ ደርሷል።
በዛሬው ዕለት ከንቲባ ከድር ጁሀር፣ የስፖርት ኮሚሽነር ፍራኦል ፣ የከተማው ሌሎች ከፍተኛ አመራሮች እና ግንባታውን በመውሰድ እየሰራ የሚገኘው ታን ኢንጂነሪንግ ባለቤት የቀድሞ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ተጫዋች ፉአድ ኢብራሂም እንዲሁም የመገናኛ ቡዙኀን ባለሙያዎች በተገኙበት የሜዳውን አጠቃላይ የስራ እንቅስቃሴ ምልከታ ተደርጓል።
በምንያህል ጥራት ሜዳው ተከላን ተካሂዷል የሚለውን እና ሌሎች ዝርዝር ጉዳዮችን አስመልክቶ የተሰጠውን ጋዜጣዊ መግለጫን ከቆይታ በኋላ ይዘን የምንመለስ ይሆናል።
1 289
ንግድ ባንክ የመጀመሪያ ድሉን አሳክቷል !
የ2016 የኢትዮጵያ ፕርሚየር ሊግ የሁለተኛ ሳምንት መርሐ ግብር ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ከሀድያ ሆሳዕና ጋር ያደረጉትን ጨዋታ 1 ለ 0 በሆነ ውጤት አሸንፈዋል።
ለአዲስ አዳጊው ክለብ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የማሸነፊያ ግቧን ከድር ኩሊባሊ በራሱ ግብ ላይ ከመረብ አሳርፏል።
ሀድያ ሆሳዕና በዚህ የውድድር ዘመን ያደረጋቸውን ሁለት የመጀመሪያ የሊግ ጨዋታዎች ተሸንፏል።
ቀጣይ ጨዋታ ምን ይመስላል ?
አርብ ጥቅምት 9 - ሀድያ ሆሳዕና ከ ወልቂጤ ከተማ
ቅዳሜ ጥቅምት 10 - መቻል ከ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ
@diresoccer
1 289
ቡናማዎቹ ተከታታይ ድል አስመዝግበዋል !
የሁለተኛ ሳምንት የ 2016 የኢትዮጵያ ፕርሚየር ሊግ ጨዋታቸውን ከድሬዳዋ ከተማ ጋር ያደረጉት ኢትዮጵያ ቡናዎች 1 ለ 0 በሆነ ውጤት በማሸነፍ ተከታታይ ድላቸውን ማስመዝገብ ችለዋል።
የቡናማዎቹን ብቸኛ የማሸነፊያ ግብ በፍቃዱ አለማየሁ ከመረብ ማሳረፍ ችሏል።
የመጀመሪያ ሁለት የሊግ ጨዋታዎችን በድል የተወጣው ኢትዮጵያ ቡና በስድስት ነጥቦች ሊጉን በመምራት ላይ ይገኛል።
ቀጣይ ጨዋታ ምን ይመስላል ?
ቅዳሜ ጥቅምት 10 - ሀዋሳ ከተማ ከ ድሬዳዋ ከተማ
እሁድ ጥቅምት 11 - ኢትዮጵያ ቡና ከ ባህር ዳር ከተማ
@diresoccer
1 289
የ2016 የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ሁለተኛ ሳምንት ጨዋታዎች
ነገ በአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ስታድየም መካሄድ ይጀምራሉ!!
#ድሬዳዋ_ከተማ 🆚 የኢትዮጵያ ቡና
1 289
የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ አንደኛ ሳምንት የሁለተኛ ቀን ጨዋታዎች ዛሬ ይከናወናሉ !
በጨዋታዎቹ ላይ ያልዎትን አስተያየት ያጋሩን!
@diresoccer
@diresoccerfamily
1 289
#EthPL 🇪🇹
የ2016ዓ.ም የኢትዮጵያ ፕርሚየር ሊግ በዛሬው ዕለት በሚደረጉ ሁለት ጨዋታዎች በይፋ ውድድሩን ይጀምራል።
አዘጋጅ ከተማዋ አዳማ ከተማ ከአዲስ አዳጊው ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ጋር በሚያደርጉት ጨዋታ የአመቱ ውድድር የሚጀምር ይሆናል።
ምሽት 12:00 ላይ ኢትዮጵያ ቡና ከ ሲዳማ ቡና ጋር ጨዋታቸውን ያደርጋሉ።
tikvahethsport
@diresoccer
@diresoccer
