Ministry of Irrigation and Lowlands- Ethiopia
Open in Telegram
7 239
Subscribers
No data24 hours
+237 days
+14030 days
Posts Archive
ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አሕመድ በ60 ሄክታር መሬት ላይ የተገነባውን ዘመናዊ የሎጂስቲክስ ማዕከል ማስፋፍያ የመጀመሪያ ምዕራፍ መረቀው ከፈቱ
ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አሕመድ በሞጆ ተገኝተው ለኢትዮጵያ ብሎም ለአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጣና ስኬት ትልቅ ሚና የሚጫወተውን እና በ60 ሄክታር መሬት ላይ የተገነባውን ዘመናዊ የሎጂስቲክስ ማዕከል ማስፋፊያ የመጀመሪያ ምዕራፍ መርቀው ክፍት አድርገዋል።
በምረቃው ወቅት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) እንደገለጹት፣ ይህ ግዙፍ ፕሮጀክት በዓመት እስከ 1 ሚሊዮን ባለ 20 ጫማ ኮንቴነሮች የማስተናገድ አቅም ያላቸው ጣቢያዎችና ዘመናዊ መጋዘኖች ያሉት ነው።
ማዕከሉ የደረቅ ብትን ጭነቶችን በሀገር ውስጥ ማሸግ ማስቻሉ ከፍተኛ የውጭ ምንዛሬን ከመቆጠብ ባለፈ ለብዙ ዜጎች ሰፊ የሥራ ዕድል ይፈጥራል።
የማዕከሉን የአሰራር ፍጥነት ለማሳደግ በሀገራችን ለመጀመሪያ ጊዜ የተተከለው የባቡር ላይ ክሬን ከባቡር መስመር የሚደረገውን የኮንቴነር ዝውውር በከፍተኛ ፍጥነት እንደሚያከናውንም ጠቅላይ ሚኒስትሩ አብራርተዋል።
ሙሉ አሰራሩ በዘመናዊ ዲጂታል መሰረተ ልማት የተሳሰረ በመሆኑ፣ ለተገልጋዮች ፈጣን እና አስተማማኝ አገልግሎት ይሰጣል።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) አክለውም፣ ይህ ማዕከል ከኢትዮ-ጅቡቲ መስመር ባሻገር ኢትዮጵያን፣ ደቡብ ሱዳንን እና ዩጋንዳን የሚያስተሳስረው የ‘ደሱ’ ኮሪደር አካል መሆኑን ገልጸው፤ ይህም ሀገራችን በዓለም አቀፍ የሎጂስቲክስ ደረጃ ላይ ያላትን ስፍራ የሚያሻሽልና የቀጣናዊ የኢኮኖሚ ትስስራችንን ወደ አዲስ የዕድገት ምዕራፍ የሚያሸጋግር ትልቅ ድል እንደሆነ አስታውቀዋል።
+1
ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አሕመድ የእመርታ ቀንን (ጳጉሜ 1ን) አስመልክቶ ያስተላለፉት መልዕክት
አባቶቻችን የኢትዮጵያን ዳር ድንበር በደምና በአጥንታቸው አስከብረው ታላቅ ሀገር አውርሰውናል፤ ዛሬ ደግሞ እውነተኛ ሉዓላዊነትን እያረጋገጥን ያለነው ከልመናና ከጥገኝነት በተላቀቀው አዲሱና ታሪካዊው መንገዳችን ነው! በሚሊዮን በሚቆጠር ዶላር ስንዴ ከማስገባት ተነስተን ዛሬ የአፍሪካ ቀዳሚ ስንዴ አምራች በመሆን የሚሊዮን ዶላሮችን ወጪ ማስቀረት ችለናል። በ«ሌማት ትሩፋት» የምግብ ዋስትናን በተግባር እያረጋገጥን፣ በ«ኢትዮጵያ ታምርት» ንቅናቄም አዳዲስ ኢንዱስትሪዎችን በማስፋፋትና የሥራ ዕድል በመፍጠር ሉዓላዊነታችንን እያረጋገጥን እንገኛለን። ከዚህ ቀደም የማይደፈሩና አይነኬ ይባልላቸው የነበሩ ከባድ የማክሮ-ኢኮኖሚ ሪፎርም ውሳኔዎችን በቁርጠኝነት በመተግበር፤ የሀገራችንን ኢኮኖሚ በፅኑ መሠረት ላይ እየገነባን እንገኛለን። እነዚህ ሁሉ ታላላቅ ድሎች ኢትዮጵያ በሚያጋጥሟት ውስጣዊና ውጫዊ ፈተናዎች ሸብረክ ሳትል በፅናት መጓዝ መቻሏን የሚያረጋግጡ ህያው ምስክሮች ናቸው፤ ይህ የእመርታ ጉዟችን ለመጪው ዓመት የሰነቀው ተስፋ እጅግ ግዙፍ ነው!
#EthiopiaDelivers
የህብር ቀን!!
ሕብረ-ብሔራዊነት ማለት ልዩነቶቻችንን እንደ ውበትና ሀብት በመቁጠር፣ እኩልነትንና ፍትሕን መሠረት ያደረገ ጠንካራ አንድነት መገንባት ነው። የቋንቋ፣ የባህል፣ የታሪክና የብሔር ስብጥራችንን እንደ ትስስር ገመድ በመጠቀም የጋራ የወደፊት እድላችንን በጋራ መቅረፅን ይጠይቃል።
ልዩነታችን የመለያያ ምክንያት ሳይሆን፣ የወደፊቷን ሀገራችንን በጋራ የምንገነባበት ታላቅ ጥንካሬያችን ምንጭ ነው!
የመስኖና ቆላማ አካባቢ ሚንስቴር!!
ህዝባዊ ጽናትና የሃገር ሉዓላዊነት!!
የአንድ ሀገር ሕዝብ ጽናት እና የሀገር ሉዓላዊነት በቀጥታ የተያያዙ ናቸው። ጽናት የሕዝብ አቋም፣ አንድነት፣ በችግር ጊዜ መቆም እና የሀገርን ጥቅም ማስቀደም ሲሆን፤ ሉዓላዊነት ደግሞ አንድ ሀገር በግዛቷ፣ በፖለቲካዋ፣ በኢኮኖሚዋ እና በውሳኔዎቿ ላይ የራሷን ሥልጣን በራሷ የምትወስንበት ነፃነት ነው።
ጽናት ሉዓላዊነትን እንዴት ያጠናክራል?
አንድነትን ያጠናክራል፦ በውጫዊም ሆነ በውስጣዊ ተጽዕኖ ጊዜ አንድ ሆኖ የሚቆም ሕዝብ የሀገሩን ነፃነት ለመጠበቅ የበለጠ አቅም ይኖረዋል።
የኢኮኖሚ ነፃነትን ያሳድጋል፦ በራስ አቅም ምግብ፣ ኃይል፣ ቴክኖሎጂና አስፈላጊ ሀብቶችን ማምረት ከውጭ ጥገኝነትን ይቀንሳል።
ችግርን የመቋቋም አቅምን ያዳብራል፦ ጽኑ ሕዝብ በኢኮኖሚያዊ፣ ማኅበራዊ ወይም ሌሎች ቀውሶች ጊዜ በቀላሉ አይፈርስም።
የሀገር ጥቅምን ያስከብራል፦ የግልና የቡድን ጥቅምን ከሀገራዊ ጥቅም ጋር በማመጣጠን ሀገርን በጋራ ለማልማት ያነሳሳል።
የውጭ ጫናን ለመቋቋም ያስችላል፦ በራሱ አቅም የሚተማመንና በጋራ የሚቆም ሕዝብ የሀገሩን ውሳኔ በሌሎች እንዲወሰን አይፈቅድም።
በአጠቃላይ የሀገር ሉዓላዊነት የሕዝብ ጽናት ላይ ይቆማል፤ የሕዝብ ጽናት ደግሞ በአንድነት፣ በራስ አቅም እና በሀገራዊ ኃላፊነት ይገነባል። ስለዚህ ሉዓላዊነትን መጠበቅ የወታደራዊ አቅም ብቻ ጉዳይ ሳይሆን ጽኑ ሕዝብ፣ ጠንካራ ኢኮኖሚ፣ ማኅበራዊ አንድነት፣ የራስ አቅም እና ኃላፊነት የተሞላበት ዜግነት የሚጠይቅ ሀገራዊ ጉዳይ ነው።
የመስኖና ቆላማ አካባቢ ሚንስቴር !!
"ከእንግዲህ ወደኋላ አንመለስም! ኢትዮጵያ ከቃል ባለፈ በተጨባጭ ስኬት ላይ ቆማለች”፦ ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አሕመድ
ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አሕመድ ጳጉሜን 2 - የማንሠራራት ቀንን አስመልክተው ባስተላለፉት መልዕክት፣ ኢትዮጵያ ከቃል ባለፈ በተጨባጭ ስኬት ላይ መቆሟን አበክረው በመግለጽ "ከእንግዲህ ወደኋላ አንመለስም!" ብለዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማኅበራዊ ትሥሥር ገጽ ባስተላለፉት መልዕክታቸው፣ "ትናንት ‘ኢትዮጵያ ተነሥታለች’ ስንል ምኞት ሳይሆን ዛሬ በተጨባጭ ያረጋገጥነው እውነት ነው" ሲሉ ሀገራችን እያስመዘገበች ያለውን ሁለንተናዊ ለውጥ አብራርተዋል።
ለዚህም ማሳያ ከታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ማማ እስከ ዘመናዊው የኮሪደር ልማት፣ እንዲሁም ከቢሾፍቱው ሜጋ አውሮፕላን ማረፊያ ግንባታ እስከ ማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ ድረስ እየተከናወኑ ያሉ ዐበይት ሥራዎች የኢትዮጵያን መነቃቃት በተግባር ያስመሰከሩ መሆናቸውን ጠቅሰዋል።
ይህ የማንሠራራት ለውጥ በዜጎች የኑሮ ደረጃ መሻሻል፣ በከተሞች መዘመን እንዲሁም በሥራ ዕድል ፈጠራ ላይ እውነተኛ ብርሃን የፈነጠቀ መሆኑን ያነሡት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ፣ ከዚህም ባለፈ ለልጆች የነገ ብሩህ ተስፋን የሚሰንቅ ታላቅ ርዕይ መሆኑን አስገንዝበዋል።
በተጀመረው ታሪካዊ የማንሠራራት ጉዞ የልማት ኃይልን ይበልጥ በማፋጠን የኢትዮጵያን ትንሣኤ ወደ ዘላቂ ብልጽግና ከፍ እንደሚያደርጉ አረጋግጠዋል።
#Ethiopia #EBC #resurgence #Pagumen
ትላንት ነሃሴ 30/2018 ዓ.ም የመስኖና ቆላማ አከባቢ ሰራተኞች ለስራ ጉዳይ አዳማ ደርሰው ሲመለሱ በደረሰ የትራፊክ አደጋ የ 1 ባልደረባችን ህይት ያለፈ ሲሆን ሌሎች 4 ባልደረቦቻችን የአካል ጉዳት ጉዳት ደርሶባቸዋል፡፡
ሚኒስቴር መስሪያ ቤታችን በደረሰው አሳዛኝ የትራፊክ አደጋ የተሰማውን ጥልቅ ሃዘን ይገልፃል፡፡
በአደጋው ህይወቱን ላጣው አቶ አበባው ካሳ ቤተሰቦች፣ወዳጅ፣ ዘመዶች፣ እንደዚሁም ለመላው የሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ሰራተኞች መጽናናትን ይመኛል፡፡
በአደጋው ጉዳት የደገሰባቸውም ባልደረቦቻችንን የተሻለ ህክምና እንዲያገኙ ከፍተኛ ጥረት እየተደረገ ይገኛል፡፡
በደረሰው ድንገተኛ የትራፊክ አደጋ ህይወታቸው ያለፈው የሚኒስቴር መ/ቤታችን ባልደረባ የነበሩት አቶ አበባው ካሳ የተወለዱት ጥር 24/1981 አመተ ምህረት በደቡብ ጎንደር ዞን ታች ጋይንት ወረዳ ሲሆን እድሜያቸው ለትምህርት እንደደረሰ የመጀመሪያና ሁለተኛ ደረጃ ትምህርታቸውን በታች ጋይንትና በላይ ጋይንት ንፋስ መውጫ ተከታትለዋል።
ወደ ባህርዳር ዩኒቨርስቲ አቅንተውም በስነልቦና የመጀመሪያ ዲግሪያቸውን፣ የሁለተኛ ዲግሪያቸውን በፐብሊክ ፖሊሲ አግኝተዋል።
አቶ አበባው ካሳ የአንድ ሴትና የአንድ ወንድ ልጅ አባት ሲሆኑ:- ከ2005 ዓ.ም ጀምሮ በተለያዩ ተቋማት በተለያዩ የስራ መደቦች ያገለገሉ ሲሆን -ከ2014 ዓ.ም ጀምሮ ህይወታቸው እስካለፈበት ነሐሴ 30/2018 ዓ.ም ድረስ በመስኖና ቆላማ አካባቢ ሚኒስቴር የወጣቶች ጉዳይ ከፍተኛ ባለምያ እንዲሁም ከ2018 ዓ.ም ሐምሌ 1 ጀምሮ የአየር ንብረት ለውጥ ባለሞያ ሆነው ሃገራቸውንና ህዝባቸውን አገልግለዋል።
የመስኖና ቆላማ አካባቢ ሚኒስቴር በባልደረባችን አቶ አበባው ካሳ ድንገተኛ የትራፊክ አደጋ ህይወታቸው በማለፉ የተሰማውን ጥልቅ ሃዘን እየገለጸ፣ ለቤተሰቦቹና ወዳጆቹ እንዲሁም ለመላው የተቋሙ ሠራተኞች በድጋሚ መጽናናትን ይመኛል።
ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አሕመድ የእመርታ ቀንን (ጳጉሜ 1ን) አስመልክቶ ያስተላለፉት መልዕክት
አባቶቻችን የኢትዮጵያን ዳር ድንበር በደምና በአጥንታቸው አስከብረው ታላቅ ሀገር አውርሰውናል፤ ዛሬ ደግሞ እውነተኛ ሉዓላዊነትን እያረጋገጥን ያለነው ከልመናና ከጥገኝነት በተላቀቀው አዲሱና ታሪካዊው መንገዳችን ነው! በሚሊዮን በሚቆጠር ዶላር ስንዴ ከማስገባት ተነስተን ዛሬ የአፍሪካ ቀዳሚ ስንዴ አምራች በመሆን የሚሊዮን ዶላሮችን ወጪ ማስቀረት ችለናል። በ«ሌማት ትሩፋት» የምግብ ዋስትናን በተግባር እያረጋገጥን፣ በ«ኢትዮጵያ ታምርት» ንቅናቄም አዳዲስ ኢንዱስትሪዎችን በማስፋፋትና የሥራ ዕድል በመፍጠር ሉዓላዊነታችንን እያረጋገጥን እንገኛለን። ከዚህ ቀደም የማይደፈሩና አይነኬ ይባልላቸው የነበሩ ከባድ የማክሮ-ኢኮኖሚ ሪፎርም ውሳኔዎችን በቁርጠኝነት በመተግበር፤ የሀገራችንን ኢኮኖሚ በፅኑ መሠረት ላይ እየገነባን እንገኛለን። እነዚህ ሁሉ ታላላቅ ድሎች ኢትዮጵያ በሚያጋጥሟት ውስጣዊና ውጫዊ ፈተናዎች ሸብረክ ሳትል በፅናት መጓዝ መቻሏን የሚያረጋግጡ ህያው ምስክሮች ናቸው፤ ይህ የእመርታ ጉዟችን ለመጪው ዓመት የሰነቀው ተስፋ እጅግ ግዙፍ ነው!
#EthiopiaDelivers
መገጭ የመስኖ ግድብ 33 ሚሊዮን ሜትሪክ ኪዩብ ውሃ ይዟል!!
አጠቃላይ የፕሮጀክቱ ግንባታ ስራ 94 በመቶ ተጠናቅቋል!!
# የዋናው ግድብ ሙሌት 9.4 ሚሊዮን ሜትር ኪዩብ ሲሆን አሁን ላይ 8.25 ሚሊዮን ሜትር ኪዩብ ተሞልቷል፤ ቀሪው የ 1.15 ሚሊየን ሜትር ኪዩብ የግድብ ሙሌት በቅርቡ የሚጠናቀቅ ይሆናል!!
# የግድቡ ትርፍ ውሃ ማስወጫ spillway ሙሉ በሙሉ ተጠናቋል
# የመስኖ ውሃ መቆጣጠሪያ (intake tower) ሲቪል ስራ መቶ በመቶ ተጠናቋል ኤሌክትሮ መካኒካል ስራው አጭር ጊዜ የሚጠናቀቅ ይሆናል
# የመስኖ ውሃ ማስወጫ፡ መጠንና ሃይል መቆጣጠሪያ (Howell-Bunger Valve)ተገጥሟል
# ለጎንደር ከተማ ለመጠጥ ውሃ አቅርቦት የሚሆን ውሃ ማስወጫ ቱቦ እና መቆጣጠሪያ (valve) ገጠማ ተጠናቋል
# የሎት 2 የወንዝ መቀልበሻ የአናት ስራው (wier) ሙሉ በሙሉ ተጠናቋል
# የሎት 2 የዋና ቦይ 3 ኪሎ ሜትር ግንባታ ሙሉ በሙሉ ተጠናቋል፤ ቀሪ የዋና መስኖ ቦይ እና ሁለተኛ የመስኖ ቦይ ግንባታ ስራው እየተፋጠነ ይገኛል!!
የመስኖና ቆላማ አካባቢ ሚንስቴር በቆላማ አከባቢ ኑሮ ማሻሻያ ፕሮጀክት 232 ሞተር ሳይክሎች ለክልሎች አስረከበ።
ሞተር ሳይክሎቹ የቆላማ አከባቢ ኑሮ ማሻሻያ ፕሮጀክት ተግባራዊ በሚደረግባቸው ድሬዳዋ አስተዳደርን ጨምሮ 7 ክልሎች ለሚገኙ 116 ወረዳዎች የሚከፋፈል ነው ።
በርክክብ መርሃ ግብሩ ላይ ንግግር ያደረጉት ክቡር አቶ ተስፋዬ ይገዙ የመስኖና ቆላማ አካባቢ ሚንስቴር ሚኒስትር ዴኤታ የኢትዮጵያን ቆላማ አካባቢዎችን ለማልማት ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ የተለያዩ ፕሮጀክቶችን ተግባራዊ እያደረገ መሆኑን ገልጸው የፕሮጀክቶቹን ስራ ለማሳለጥ የሞተር ሳይክሎቹ ድጋፍ መደረጉን አሳውቀዋል።
አቶ ሰኢድ ኡመር የቆላማ አከባቢ ኑ ሮ ማሻሻያ ፕሮጀክት (LLRP) አስተባባሪ ፕሮጀክቶቹ ተግባራዊ የሚደረጉት ገጠራማ በሆኑ አካባቢዎች በመሆኑ ፕሮጀክቱ የሚሰጣቸውን አገልግሎቶች እንደዚሁም የሚገነቡ መሰረተ ልማቶችን ለመከታተል ተሽከርካሪዎቹ ከፍተኛ አስተዋጽኦ አላቸው ብለዋል።
