Gelila kindergarton and Primary school
Open in Telegram
318
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days
Posts Archive
የተሻለ ውጤት የሚያመጡ ተማሪዎች የአጠናን ልምዳቸው ምን ይመስላል❓
📢 12 ወሳኝ ነጥቦች
📖1 ጥናት ከመጀመራቸው በፊት ለምን ዓላማ እንደሚያጠኑ ቀድመው ዓላማ ያስቀምጣሉ።
ይህ ማለት ምን ለማወቅ እንደሚያጠኑ ቀድመው ያቅዳሉ።
📖 2 መፅኃፍ ገልጠው ጥናት ከመጀመራቸው በፊት ስለሚያጠኑት ርዕሰ ጉዳይ የራሳቸውን ግምት ያስቀምጣሉ። መፅሀፍ ገልጠው ጥናት ከጀመሩ በኃላ የነበራቸውን ግምት እያጠናከሩ...የተሳሳተው
ን እያስተካከሉ ይጓዛሉ።
📖3 ሲያጠኑ ያገኙትን አንኳር ነጥብ አጠር አድርገው ማስታወሻቸው ላይ ያሰፍራሉ።
📖4 አንብበው ለ መረዳት ያስቸገራቸውን ነጥብ /ሀሳብ/ ደጋግመው ያነባሉ....
📖 5 ጥናት ከ መጀመራቸው በፊት ማጥናት ስለ ፈለጉት ርእሰ ጉዳይ ጥያቄዎች ይፋጥራሉ። መፅኃፍ ገልጠው ጥናት ከጀመሩ በሃላ ለጥያቄዎቻቸው መልስ ይፈልጋሉ እንጂ ሁሉም ነገር በ ማንበብ ጊዜያቼውን አያጠፉም።
📖6 ሲያነቡ ያገኙትን አዲስ ሀሳብ ወይም መረጃ ከ አሁን በፊት ከሚያወቁት ጋር አብሮ ሊሄድ የሚችል መሆኑን እና አለመሆኑን ይመረምራሉ::
📖7 በ አንድ ጊዜ ብዙ ነገር ለ ማጥናት አይሞክሩም፡፡ በ አንድ ጊዜ ብዙ ነገር ለ ማጥናት መሞከር ትርፉ ድካም መሆኑን ተረድተውታል፡፡
📖8 ሁልጊዜም ቢሆን ለትምህርት ጉዳዮች የሚጠቀሙበት የተለየ ጊዜ አላቸው፡፡
📖9 ያሰቡትን ነገር ተግባራዊ ለማድረግ ቁርጠኝነት አላቸው...አያፈገፍጉም፣ አያቅማሙም፡፡
📖10 ሲያጠኑ የሚከብዳቸውን ክፍል ቅድሚያ ሰጥተው ያነባሉ፡፡
📖11 ተባብሮ በመስራት ያምናሉ፡፡ ያግዛሉ፣ ይጠይቃሉ፡፡
📖12 እራሳቸው ይገመግማሉ፡፡ ደካማ ጎናቸዉ በፍጥነት ያስተካክላሉ፡፡
Repost from Gelila primary school
የ6ኛ ክፍል ሞደል ጥያቄ
📘 አዘጋጅ ለሚ ኩራ ፅ/ቤት
📘 2ኛ መንፈቅ አመት 2016
📘 የትምህርት አይነት
👉 አካባቢ ሳይንስ
👉 አማርኛ
👉 ሒሳብ
👉 እንግሊዝኛ
የ8ኛ ክፍል መለማመጃ ጥያቄ
📘 አዘጋጅ ኤቨረስት ዩዝ አካዳሚ
📘 2ኛ መንፈቅ አመት 2016
📘 የትምህርት አይነት
👉 አጠቃላይ ሳይንስ
👉 አማርኛ
👉 ሒሳብ
👉 እንግሊዝኛ
👉 ሲቲዚንሽፕ
ሶሻል
በ2016 ዓ/ም በአዲስ ከተማ ክፍል ከተማ በወረዳ 3 ት/ጽ/ቤት በተደረገው ትምህርታዊ አውደ ዕርዪ የገሊላ የመጀመሪያ ደረጃ ት/ቤት ከወረዳው ካሉ ትምህርትቤቶች አንደኛ በመውጣት የዋንጫ ተሸላሚ ሆኑዋል!!!
#ለመላው የገሊላ ማህበረሰብ እንኳአን ደስ አላችሁ!!!
👉ለ6ኛ ፣8ኛ እና 12ኛ ክፍል ተፈታኞች ተማሪዎች አጭር ማስታወሻ!
✅የ8ኛ ክፍል
👉ሞዴል ሚያዚያ 15-18/8/2016 ዓ.ም ሲሰጥ ክልል አቀፍ ፈተና ከሰኔ 4-5/10/2016 ዓ.ም ሲሰጥ
✅6ኛ ክፍል
👉ሞዴል ፈተና ከሚያዚያ 15-18/8/2016 ዓ.ም የሚሰጥ ሲሆን ክልል አቀፍ ፈተና ከሰኔ 12-14/10/2016 ዓ.ም የሚሰጥ ይሆናል!!
✅ከተማሪዎች ምን ይጠበቃል??
👉የ6ኛ ክፍል ተማሪዎች የ6ኛ ክፍል ብቻ (5ኛ ክፍል ሳይጨምር) የሁለቱን ሴሚስተር እቅድ አውጥቶ በአግባቡ ማጥናት
👉የ8ኛ ክፍል ተማሪዎች የ8ኛ ክፍል ብቻ (7ኛ ክፍል ሳይጨምር) የሁለቱን ሴሚስተር እቅድ አውጥቶ በአግባቡ ማጥናት
✅ከመምህራንና ከት/ቤቶች ምን ይጠበቃል?
👉መምህራና እና ት/ቤቶች አስፈላጊውን ትኩረት በመስጠት የይዘት የማጠናቀቅ ምጣኔ(portion coverage ) በአግባቡ እንዲጠናቀቅ ማድረግ ::
👉ለተፈታኝ ተማሪዎቻችን የስነ ልብና ምክርና አስፈላጊው እገዛ (ወርክሽት ፣ሞዴል ፈተናዎች እና ያለፋ አመታት ፈተናዎችን በማሰራት) እገዛ ማድረግ ::
✅ከተማሪ ወላጆች ምን ይጠበቃል??
👉ተማሪዎች እቅድ አውጥተው እንዲያጠኑ ማበረታታት እና አስፈላጊውን እገዛ ማድረግ::
🤲በጋራ ርብርብ የተማሪዎችን ውጤት እና ስነ ምግባር እናሻሽል🤲!
🌙🌙 ዒድ ሙባረክ 🌙🌙
عيد مبارك كل عام وانتم بخير
💫✨💫💫✨💫💫✨
تقبل الله منا ومنكم صالح الاعمال
ተቀበለላሁ ሚና ወሚንኩም
ሷሊሀል አዕማል
✨✨✨✨✨✨✨✨
⭐️ Eid Mubarek⭐️
#በስፖርት ክበብ አዘጋጅነት እየተካሄደ ያለው የተማሪዎች የእግር ኳስ ውድድር እንደቀጠለ ነው።
#በዛሬው እለት በተካሄደው 5B ከ 6A ባደረጉት ጠንካራ ፉክክር ጨዋታ
6A 5 ለ 4 በሆነ ውጤት አሸንፈዋል!!!!
23/07/18 በስፖርት ክበብ አዘጋጅነት እየተካሄደ የሚገኘው የተማሪዎች የእግር ኳስ ውድድር እንደቀጠለ ነው!!
#በዛሬው እለት 8A ከ7B ባደረጉት ጨዋታ 8A ከጨዋታ ብልጫ ጋር 10ለ2 አሸንፏል !!!!
#የጨዋታው ዳኛ መ/ር ተመስገን አስማማው!!!!
❗️❗️❗️Addis Ketema Sub-city 2015 E.C Second Semester Model Exam❗️❗️❗️
Repost from Gelila primary school
20/07/18 የሁለተኛው መንፈቅ አመት የ8ኛ ክፍል የተማሪዎች የጥያቄና መልስ ውድድር ተካሂዷል !!!
#ኤዶምያስ መኮንን ከ8A 1ኛ
#ኤርሚያስ አዲሱ ከ8A 2ኛ
#ኤደን ኩሽ ከ8B 3ኛ
የኢፌዴሪ ዴይ ኬር መመሪያ.pdf2.97 KB
Repost from Gelila primary school
#በስፖርት ክበብ አዘጋጅነት እየተካሄደ ያለው የወንዶች የእግር ኳስ ውድድር እንደቀጠለ ነው
#በዛሬው እለት 8B ከ 7A ባደረጉት ጠንካራ ፉክክር 8B 11 ለ 7 አሸንፏል
#የጨዋታው ዳኛ መ/ር ተመስገን አስማማው
#ጨዋታው ነገም ቀጥሎ ይካሄዳል
#ተተኪ ስፖርተኞችን ለማግኘት የት/ቤት የውስጥ ውድድሮች በጣም አስፈላጊ ናቸው!!!!
#ስፖርት ለወዳጅነት!!!
#ስፖርት ለጤንነት!!!
የእርዳታ ተማፅኖ
#ከ2008-2013 በገሊላ የመጀመሪያ ት/ቤት የሥራ ባልደረባችን የነበረው#ቴዎድሮስ ሸዋፀጋ ወላጅ እናት ሁለቱም ኩላሌታቸው ከጥቅም ውጪ ስለሆነ በሳምንት ሦስቴ ዲያሊሲስ እያደረጉ ነው#ለሁለት አመት ያክል ለብቻው ዲያሊሲስ እንዲያደርጉ የተለያዩ ስራዎችን እየሰራ ብቸኛ ልጃቸው የሆነው #ቴዳ ሁሉንም ወጪ እራሱ እየሸፈነ እያሳከማቸው ነው#አሁን ላይ ይህን ለማድረግ አቅም ስላጣ #ከዚህ በፊት በት/ቤታችን ሶሻል ኮሜቴ አስተባባሪነት #የት/ቤታችን መምህራንና የአስተዳደር ሰራተኞችን በማስተባበር ድጋፍ አድርገንለት ነበር# አሁን ላይ ግን ቪድዮ ላይ እንደምናየው #ብቻውን ያን ማድረግ ስላቃተው #የጓደኛችን የሥራ ባልደረባችንን የሆነውን #የቴዳን እናት ከጉኑ በመሆን የቻልነው የአቅማችንን #በፀሎትም በዱአ #ወንድማችንን እናግዛው!!!
#የገሊላ ቤተሰብ ደሞ በበጎ ተግባር የማይታማ ስለሆነ #የቀድሞ የት/ቤታችንን መምህራን እንዲሁም ተማሪዎች የቻላችሁትን ድጋፍ እናድርግለት#
#ቴዳ እስካሁን እያሳለፍክ ያለሆን ነገር እኛ በደንብ ስለምንረዳ #አሁንም ከፈጣሪ ጋር የቻልነውን ነገር እናደርጋለን!!!!
#ቴዳ አይዞን !!!!ፈጣሪ አቅሙንና ብርታቱን ይስጥክ እስከቻልነው ድረስ ከጉንክ ነን!!!!!
✅የፈተና መረጃ ለ6ኛ፣8ኛ ተፈታኝ ተማሪዎች
1️⃣ የ6ኛ ክፍል በተመለከተ(ለአዲስ አበባ)
በፈተና የሚካተቱ የት/ት አይነቶች:-
👉አማርኛ
👉እንግሊዘኛ
👉ሒሳብ
👉አካ/ሳይንስ እና
👉ሞራል ሲሆኑ ለአፋን ኦሮሞ ተማሪዎች አፋን ኦሮሞ እና ገዳ ይጨምራል
✍️ሁሉም ፈተና የሚዘጋጀው ከ6ኛ ክፍል ብቻ(5ኛ ክፍልን አይጨምርም)
✅ 8ኛ ክፍል በተመለከተ(ለአዲስ አበባ)
በፈተና የሚካተቱ የት/ት አይነቶች:-
👉አማርኛ
👉እንግሊዘኛ
👉ሒሳብ
👉ሶሻል ሳይንስ
👉አጠ/ሳይንስ
👉የዜግነት ት/ት እና ለአፋን ኦሮሞ ተማሪዎች አፋን ኦሮሞ እና ገዳ ይጨምራል
✍️ሁሉም ፈተና የሚዘጋጀው ከ8ኛ ክፍል ብቻ(7ኛ ክፍልን አይጨምርም)
👉በመሆኑም የፈተና ወቅት እየተቃረበ በመሆኑ ተማሪዎች በዚህ መረጃ መሰረት በአግባቡ ማጥናት ይጠበቅባቹሀል::
👉 ት/ቤቶች እና የተማሪ ወላጆች በዚህ መረጃ መሰረት ተማሪዎቻችን አመርቂ ውጤት እንዲያመጡ የጋራ ርብርብ እናድርግ‼️
👉ሁሉም ፈተናዎች በሰኔ ወር ይሰጣሉ ተብሎ ይጠበቃል
