3 765
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days
Posts Archive
3 765
Repost from Ibnu Munewor (ኢብኑ ሙነወር)
የሚጮሁትን የማይኖሩ ጉዶች!
ክፍል - 4
~
ያያያዝኩት የባህሩ ተካ ንግግር ነው። የውሸት እርከኑን በዚህ መጠን ከፍ አድርጎታል። ውሸቱን ሲለማመደው ጊዜ "አንባቢ ይታዘበኛል" የሚለውንም ትቶታል። እንዲያው አንድ ሰው መስሎት ተሳስቶ ቢናገር ይሁን። ይሄ ሐያእ የቀለለው ፍጡር ግን በምን መልኩ ሰው ላይ እንደሚዋሽ ተመልከቱ። ሳዳት ነው ወደነዚህ አካላት የሚጣራው? በሐዲሥ እንደመጣው ከሙናፊቅ ምልክቶች ውስጥ ሁለቱ ሲያወሩ መዋሸት እና በሙግት ላይ አመፀኝነት ወይም ገልብጦ መወንጀል ነው። በነዚህ አጥፊዎች ላይ ረድ መስጠት ነው ወደነሱ መጣራት ተብሎ የሚገለፀው? ጥላቻ አናቱ ላይ ወጥቶ በትክክል ማየት እንዳይችል ጋርዶታል። በረድ ስም እየዋሸ መለጠፍ ጣፋጭ ምግብ ሆኖለታል። እጅ እጅ የሚል ፅሁፉን ውሸት ጣል ሲያደርግበት ውበትና ጥንካሬ የሚጨምር ይመስለው እንደሁ አላውቅም። "የሰካራም ግጥም ሁሌ ቅዳ ቅዳ" እንዲሉ ወጥሮ የውሸት አውቶማቲክ መተኮሱን ተያይዞታል። ረድ ማለት የጠሉት ሰው ላይ የፈለጉትን መለጠፍ ሆኗል ባህሩ ዘንድ። ሰው እንዴት በዚህ ደረጃ ውሸትን ስራዬ ብሎ አጥብቆ ይይዛል? ነብዩ ﷺ እንዲህ ብለዋል፦
وإِيَّاكُمْ والْكَذِبَ، فَإِنَّ الْكَذِبَ يَهْدِي إِلَى الْفُجُورِ، وإِنَّ الْفُجُورَ يَهْدِي إِلَى النَّارِ، ومَا يَزَالُ الرَّجُلُ يَكْذِبُ ويَتَحَرَّى الْكَذِبَ حَتَّى يُكْتَبَ عِنْدَ اللَّهِ كَذَّابًا
“አደራ ውሸትን ተጠንቀቁ! ውሸት ወደ ጥመት ይመራል፤ ጥመት ደግሞ ወደ እሳት ይመራል፡፡ አንድ ሰው ሲዋሽና ውሸትም ላይ ሲያተኩር አላህ ዘንድ ውሸታም ተብሎ ይመዘገባል።” [ቡኻሪይ እና ሙስሊም]
ሳዳትን በማጠልሸት ላይ እንቅልፍ ከምታጡ ራሳችሁን ከዚህ የውሸት ሱስ አውጡ። ሳዳት እናንተን ከነ ንዝንዛችሁ እርግፍ አድርጎ ትቶ አነሰም በዛም የራሱ ስራ ላይ ነው ያለው። ደግሞም በተለይ ተራውን ህዝብ በማንቃት ላይ ባለው አስተዋፅኦ አንዳችሁ እንኳ የሚስተካከል ቀርቶ የሚቀርብ ነገር የለውም። የራሳችሁን ድርሻ ባግባቡ እንደመወጣት ሰዎች የሱን ትምህርት እንዳይከታተሉ ጥላሸት መቀባትን ጂሃድ አድርጋችሁታል። ይሄ ነው የናንተ ስኬት።
ባህሩ ተካ እንደምታዩት ወንድማችን ሳዳትን ወደ "ቲክ – ቶክ መንደር ወርዶ ወጣቱን ወደ ዮኒ ማኛና ኢክራም አውቶሞቲቭ" ይጣራል እያለ ነው።
* ሳዳት ከአጥፊዎች ነው ያስጠነቀቀው። ባህሩ ደግሞ አጥፊዎቹን ጥሎ ሳዳትን መዝለፍ ላይ ነው የተጠመደው። ከአጥፊዎች ማስጠንቀቅ ወደነሱ መጣራት ከሆነ እንዳበደ ውሻ ሁሉን የምትናከሱት እናንተ አጥፊዎች ወደምትሏቸው እየተጣራችሁ ኖሯል ለካ? መቼም በራሳችሁ ጩኸት ስለደነቆራችሁ ሂሳባችሁ ምን እንደሚሰጥ አይገባችሁም።
* ምናልባት አጥፊዎቹን ፊት ለፊት ተገኝቶ መምከሩን ከሆነ ወደነሱ መጣራት የምትለው ይሄ ምን ያህል በልብህ ያረገዝከው ጥላቻ ነገሮችን የመረዳት አቅምህንም እንዳሽመደመደው ነው የሚያሳየው። እንዲያው አቀራረቡ ላይ ሂስ አለኝ ብትል እንኳ እንዳንተ አይነቱ በቆሻሻ የብሄር ካባ ተጀቡኖ የጉራጌ ካፊ'ሮች ጋር አንድነት ስለማድረግ የሚሰብክ ሰው ሂስ የመሰንዘሩን ድፍረት እንዴት ነው የሚያገኘው? የጥላቻ ብቅል ይህን ያክል ያሰክራል ለካ! የሚገርመው በዚህ መልኩ አይኑን በጨው አጥቦ እየዋሸ "ውሸታም" ተባልኩ ብሎ ሲብሰው ማየት ነው። የእውነት ህሊና ካለህ ከመባልህ ይልቅ መሆንህ ያስጨንቅህ። ያለበለዚያ ነገሮችን እየገለበጥክ ማየትህን ትቀጥላለህ። ጠቢቡ ኢብኑል ቀዪም ረሒመሁላህ ምን እንደሚሉ ተመልከት:-
إياك وَالْكذب فَإِنَّهُ يفْسد عَلَيْك تصور المعلومات على مَا هِيَ عَلَيْهِ وَيفْسد عَلَيْك تصورها وَتَعْلِيمهَا للنَّاس فَإِن الْكَاذِب يصور الْمَعْدُوم مَوْجُودا وَالْمَوْجُود مَعْدُوما وَالْحق بَاطِلا وَالْبَاطِل حَقًا وَالْخَيْر شرا وَالشَّر خيرا فَيفْسد عَلَيْهِ تصَوره وَعلمه عُقُوبَة لَهُ.
"ውሸትን ተጠንቀቅ። እሱ መረጃዎችን ባሉበት ሁኔታ (በትክክለኛ ቅርፃቸው) የመረዳት አቅምህን ይበክልብሃል። በተጨባጭ መሳልና ማሳወቅንም እንዲሁ ያበላሽብሃል። ውሸታም የሌለውን እንዳለ፣ ያለውን እንደሌለ፣ እውነቱን ሃሰት፣ ሃሰቱን እውነት፣ ኸይሩን ሸር፣ ሸሩን ደግሞ ኸይር አድርጎ ገልብጦ ያቀርባል። በውሸቱ ይቅቀጣ ዘንድ የመረዳት አቅሙም እውቀቱም ይበላሽበታል።" [አልፈዋኢድ፡ 135]
ውሸትን እንደ ፅድቅ ማየት የመጣው በዚህ ምክንያት ነው። "የማይበስል ጭንቅላት መብሰሉ ላይ የሰው ማገዶ ያስጨርሳል።"
=
የቴሌግራም ቻናል
https://t.me/IbnuMunewor
3 765
Repost from Ibnu Munewor (ኢብኑ ሙነወር)
የሚጮሁትን የማይኖሩ ጉዶች!
ክፍል - 3
~
ከሶስት አመት በፊት ኮምቦልቻ ላይ በተካሄደ ደውራ ላይ ከወንድሞች ጋር ተካፍዬ ነበር። በጊዜው አንድ ሸይኽ ከሳዑዲ በስልክ እንዲያስተምር ይደረጋል። በእለቱ እኔ የተሰጠኝን ላስተምር የተገኘሁ ተጋባዥ እንግዳ እንጂ የፕሮግራም አስተባባሪ አልነበርኩም። የሰውየውን ትምህርትም አልተከታተልኩም። እነዚህ ውሸት የቀለላቸው ፍጡሮች ግን ልክ ሰውየውን እኔ እንደጋበዝኩ አድረገው ደጋግመው መክሰሳቸውን ቀጥለዋል። እኔ ስለ ሰውየው አላውቅም ብልም እምቢ ብለው እየተቀባበሉት ነው። "ሞኝ እምቢ ብሎ ይረታል" ይባላል። አይናቸውን በጨው አጥበው ቀጥለዋል። የዚህ ቅጥፈት መነሻ የሆነው ፀሐፊ ያኔውኑ መጥቶ አናግሮኝ ስለ ሸይኹ የማውቀው ነገር እንደሌለ፣ እንዲቀርብ ያደረግሁትም እኔ እንዳልሆንሁ ተናግሬ ነበር። ይህንን ከማውራታችን ጋር ነው እንግዲህ እኔ እንደጋበዝኩ አድርጎ የፃፈው። የዚህን ቀጣፊ ወሬ ነው እነ በህሩ ተካ የሚቀባበሉት።
ሰውየው ማነው? ማንስ ጋበዘው?
ስሙ ዓዲል ብኑ ሙሐመድ አሱበይዒይ ይባላል። ይህንን ሸይኽ የጋበዘው ደግሞ ጠሀ ኸዲር ነው። ጠሀ ማለት የዚህ ሰካራም አንጃ አካል እንደሆ ያዙ። ስለዚህ የጠሀ ቻናል ላይ ፍንጭ እንደማገኝ በማሰብ ገባሁ። ግምቴ ልክ ነበር።
1ኛ፦ ሸይኹን የጋበዝነው እኛ ከሆንን ከባድ ወንጀል ነው አይደል? እናንተስ ከሆናችሁ? ይሄው ሸይኹን የጋበዘው ጠሀ ኸዲር ነው። ራሱ በጊዜው የፃፈውን አያይዤላችኋለሁ። አሁንስ ክሱን ወደሱ ታዞራላችሁ?
2ኛ፦ ሸይኽየው እናንተ ዘንድ የጋበዘው ሳይቀር የሚወነጀልበት ከባድ የመንሀጅ ችግር ያለበት ነው ኣ? ይሄው ጠሀ ኸዲር ዘንድ ደግሞ ሰውየው ሌላ ነው። "ፈዲለቱ ሸይኽ"፣ "ሸይኻችን"፣ "አልሙጃሂድ"፣ "አልሙረቢ"፣ "አልዋሊድ"፣ "ፈዲለቱ ሸይኽ አልኡስታዝ አልሙሐዲሥ"፣ "ሸይኹነል ከሪም" እያለ በመግለፅ ደጋግሞ ያሰራጭለታል።
በነገራችን ላይ ስለ ሸይኹ ዛሬም ድረስ ክፉም ደግም አላውቅም። እንደሚሉት ችግር ያለበት ከሆነ ግን እነ ጠሀ ስንት ፊት እንዳላቸው ተመልከቱ። ሳዑዲ ሌላ፣ ኢትዮጵያ ሌላ። ሌላው ቀርቶ ሳዑዲ ኤምባሲ ወይም የሳዑዲ የባህል ማዕከል ዘንድ ራሱ ሌላ ፊት ነው ያላቸው። እዚያ የሚያልሙት መስለሐ ስላለ የሚቀርቡበት ሌላ ጭምብል አላቸው። ከኢኽዋን ቁንጮዎች ጋር አግድም ተሰልፎ ፎቶ መነሳትም ችግር የለውም። በፊጥራ ጥሪ ላይ ድንገተኛ መገጣጠም ብቻ እንደተከሰተ አድርጎ ባህሩ ተካ ፅፎ አይቻለሁ። ከዚያ እንዳይወጡ በጥበቃ ተከልከለው ነው ኣ? ከዚያም አፈሙዝ ደቅነው አንድ ላይ ተሰልፈው ፎቶ እንዲነሱ አደረጓቸው አይደል? የፊጥራውን እንለፈው። በቅርቡ የተካሄደው ኮንፈረንስ ፊጥራ አልነበረም። የዚህ ቡድን አባል የሆነው ኡስታዝ (ነዚፍ) ራሱ ድግሱ ላይ ፕሮግራም አቅራቢ ነበር። በህሩ እንደለመደው ነው እየዋሸ ያለው። እኔ እነዚህን ነጥቦች የማነሳው ለተብዲዕ አይደለም። ጩኸታቸውና ግብራቸው የማይገናኝ እንደሆነ ለመጠቆም ያህል ብቻ ነው።
ወደ ተነሳሁበት ስመለስ ሰዎቹ ራሳቸው ባቀረቡት ሰው ሰበብ ዞረው የሚናደፉ እባቦች ናቸው። ከላይ የተጠቀሰው ሸይኽ እንደሚሉት ችግር ያለበት ከሆነ ተጠያቂው ጦሀ ኸዲር ነበር። ሰውየው ችግር ያለበት ከመሆኑ ጋር "ሸይኻችን" እያለ የሚገልፀው፣ የቴሌግራም ቻናሉን የሚያስተዋውቅለት እሱ እንጂ እኛ አይደለንም። ከሰውየው ላይ ቁጭ ብሎ የሚማረው ራሱ ነው። ቢሆንም ቡድናዊ ያለመከሰስ መብት ስላለው አይነኩትም።
አንዱ ይህንን ቅጥፈት እያሰራጨ ያለው በህሩ ተካ ነው። በህሩ ሲበዛ ውሸት የቀለለው ፍጡር ነው። እነዚህ ሰዎች ላይ እንዳጠቃላይ የማየው ችግር ስለ 'ረድ' ያላቸው ግንዛቤ በጣም የተንሻፈፈ መሆኑ ነው። የሚናገሩበትን ሰው ያጠልሽላቸው እንጂ እውነት ይናገሩ ውሸት አያስጨንቃቸውም። ችግራቸው በሚጠሉት አካል ላይ ሆነ ብለው የሚያሳድሩት ክፉ ቀስዳቸው ብቻ አይደለም። ንግግሮችን የሚረዱበት አቅምም ሲበዛ የወረደ ነው። ክፉ እሳቤ እና እጅግ የወረደ የመረዳት አቅም ከቅጥፈት ጋር ሲጣመር ውጤቱ አሁን እነሱ የሚያሳይቱን ይሰጣል።
=
የቴሌግራም ቻናል
https://t.me/IbnuMunewor
3 765
Repost from Ibnu Munewor (ኢብኑ ሙነወር)
ሸይኹል ኢስላም ኢብኑ ተይሚያህ - ረሒመሁላህ - ሲሞቱ ጊዜ ታስረውበት በነበረው ወህኒ ቤት ውስጥ በሳቸው የእጅ ፅሑፍ የተፃፉ እንዲህ የሚሉ አሳዛኝ የግጥም ስንኞች ተገኝተዋል። በግርድፉ ተርጉሜዋለሁ።
“እኔ ነኝ ደካማው ከጃይ … ከሰማያቱ ባለቤት
በሁለመናዬ ስንኩል … እኔው ነኝ ምስኪኑ ማለት።
እኔው ነኝ የራሴ ጠላት … ነፍሴ እራሷ ነች በዳዬ
ኸይር ሁሉ የሚገኘው … ከሱ ብቻ ነው ጌታዬ።
ለራሴ እንኳን የማልሆን … የማላቀርብ አንዳች ፋይዳ
መከላከል አይሆንልኝ … በክፉ እንዳልጎዳ።
ሌላ ፈጣሪም የለኝ … ከሱ ውጭ ‘ሚያስተናብር
አማላጅም አይኖረኝ … ወደ ጌታ የሚያሻግር
በሱ ፈቃድ ቢሆን እንጂ … በፈጠረኝ በረሕማኑ
የሰማያቱ ባለቤት … እንዳወሳው በቁርኣኑ
ቅንጣት የሌለኝ ከንቱ … ያለ ጌታዬ ይሁንታ
አንዳች ተጋሪም የለው … በየትኛውም ሁኔታ
አጋዥ አይፈልግ ደጋፊ … ረዳት አይሻ የኔ ጌታ
ልክ እንደሚያስፈልጋቸው … ለወልዮቹ አይነታ።
ችግር ድህነት አርማዬ … የኔ ቋሚ መገለጫ
መብቃቃቱ የጌታ ነው … የሁልጊዜ ባለብልጫ
አንጋጣጭ ነው ወደ ጌታ … ፍጡር ሲባል ጠቅላላ
ሁሉም ተዋርዶ ይቀርባል … ቢሻው ጠላ ቢሻው ደላ።
ከፈጠረው ጌታ ውጭ … ምኞት ፍላጎት የሚሻ
ቂል፣ በዳይ፣ አረመኔ … አጋሪ ነው መጨረሻ።
ይመስገነው ፈጣሪዬ … አለሙን በፀጋው የሞላ
ላለፈውም ለመጪውም … ላደረገልን በመላ።
ከዚያም ሶላቱ ይትረፍረፍ … በምርጡ ነቢያችን ላይ
የፍጡራን ቁንጮ አይነታ … የሁሉ ላይ የላይ በላይ።” [አልዑቁድ፡ 391]
=
* ቴሌግራም ቻናል፡- https://t.me/IbnuMunewor
* ፌስቡክ፦ https://www.facebook.com/Ibnu.Munewor?mibextid=ZbWKwL
* ዋትሳፕ፦ https://whatsapp.com/channel/0029VaA3X1e5kg7BlsJboa2M
* ኡማ ላይፍ፦ https://ummalife.com/IbnuMunewor
3 765
Repost from የቡታጅራ አህለሱና ቂራኣትና ዳዕዋ ቻናል
السلام عليكم ورحمة الله وبركاته
ያ ጀማዓ እንዴት ናቹህ በመቀጠል ይህ ግሩፕ የተከፈተዉ የእህታችን ነፊሳ አህመድን ህይወት ለመታደግ ነዉ እህታችን ለረዥም ጌዜ በልብ ህመም ምክንያት ስትሰቃይ የቆየች ሲሆን ከዛሬ ነገ ይሻላታል በሚል ተስፋ ለአራት አመታት ህክምናዋ የቡታጀራ አንደኛ ደረጃ ሆስፒታል ስትከታተል ቆይታለች ።
ሆኖም ግን ህመምዋ ከጌዜ ወደጌዜእየተባባሰ በመሂዱ ምክንያት የህመምዋ ሁኔታ በጣም አስጊ ሆናል።
እህታችን በከፍተኛ ህመም ውስጥ ነው ምትገኘው በዶክተሮች መረጃ መሰረት ልቧ በጣም እንደተጎዳና አንዱ ጎን እንደሌለ እንዲሁም አርቴፊሻል የደም መረጫ በአፋጣኝ እንዲገባላት አያይዘው ገልፀዋል አርቴፊሻል የደም መረጫው ለመግዛትና ሌሎች ፕሮሰሶችም ጭምር ለ ሙሉ ህክምናዋ ለመሸፈን 1.1 ሚሊን ብር እንደሚያስፈልጋት ገልፀዋል ።
ቤተሰቦቿ ደግሞ ይህንን ወጪ የመሸፈን አቅም የላቸውም ። እስካሁንም ለ4 አመታት አቅማቸው በቻለው ሲያሳክሟት ቆይተዋል አሁን ግን ከአቅማቸው በላይ ስለሆነ ከአላህ በታች የእኛን እርዳታ ፈልገው ፊታችን ቆመዋል ።
እህታችን ነፊሳ አህመድ ገና ለጋ ወጣትና የ 10ኛ ክፍል ተማሪ ናት አሁን ላይ ግን በህመሟ ምክንያት የምትወደው ትምህርቷ አቋርጣ ለህይወቷ አስጊ በሆነ ከፍተኛ ህመም ውስጥ ትገኛለች። ያጀማዓ 5 10 ሳንል ያለንን አቅማችን በቻለው እንተባበራት
ለበለጠ መረጃ በሚከተሉት ስልኮች ደውለው ማረጋገጥ ይችላሉ:-
የአባቷ ስልክ :- 0916698816
የወንድሟ ስልክ :- 0926612043
ለእህታችን ነፊሳ የእርዳታ ገቢ ማሰባሰቢያ አካዎንት :- 👇👇
((1000585445952)) ንግድ ባንክ
ተጨማሪ:-(( 7000050832347 )) ንብ ባንክ
አካዎንቶቹ የተከፈተባቸው ስም ዝርዝሮች:- 👇
አህመድ ኢድሪስ , ሉባባ አህመድ & አንዋር አህመድ
〰〰〰〰〰〰〰〰〰〰〰〰〰
¶https://t.me/ehtachin_nefisan_enrda
¶https://t.me/ehtachin_nefisan_enrda
3 765
Repost from Ibnu Munewor (ኢብኑ ሙነወር)
"እኛ ለአላህ ነን። እኛም ወደርሱ ተመላሾች ነን!"
{إِنَّا لِلَّهِ وَإِنَّاۤ إِلَیۡهِ رَ ٰجِعُونَ }
የወንድማችን ኡስታዝ ሙሐመድ ሲራጅ ልጅ ዛሬ ከሰዓት በኋላ ሞቷል። ቀብር ላይ መገኘት ለምትፈልጉ ቦታው የት እንደሚሆን ሲወሰን እናሳውቃለን፣ ኢንሻአላህ።
3 765
Repost from Fuad Mohammed
فائدة:
قال الشيخ صالح الفوزان -متعه الله بالصحة والعافية، آمين-:
نحنُ لا نهملُ قضايا المسلمين؛ بل نهتم بها، ونناصرهم ونحاول كف الأذى عنهم بكل وسيلة، وليس من السهل علينا أن المسلمين يقتَّلون ويشردون. ولكن ليس الاهتمام بقضايا المسلمين أننا نبكي ونتباكى، ونملأ الدنيا بالكلام والكتابة، والصياح والعويل؛ فإن هذا لا يجدي شيئا. لكن العلاج الصحيح لقضايا المسلمين: أن نبحث أولا عن الأسباب التي أوجبت هذه العقوبات التي حلَّت بالمسلمين، وسلطت عليهم عدوهم... وأهم هذه الأسباب... هو إهمالهم للتوحيد).
انتهى باختصار من ((دروس من القرآن الكريم)).
3 765
Repost from Ibnu Munewor (ኢብኑ ሙነወር)
አንድ የኛን ነባራዊ ሁኔታ ገላጭ የሆነ እንዲህ የሚል ግጥም አለ:-
"ዝም ያለው ዘመዴ - እኔ ሳጣጥር፣
ሞተ ቢሉት መጣ - አልቅሶ ሊቀብር።"
.
በቅርቡ አንድ ዳዒያ ለህክምና ወደ ቱርክ በሄደበት የሞቱ ዜና ሲዘዋወር ነበር፣ አላህ ይማረውና። በርግጥ ይህንን ወንድም ቀድሜ ከነ ጭራሹ አላውቀውም። ግን ረዘም ላለ ጊዜ በህመም ላይ እንደቆየና ማንም ከጎኑ እንዳልነበረ አሁን ከሞተ በኋላ ሲወራ ሰማሁ። በጣም የሚያሳዝን ነው። ለምንድነው ግን በዚህ መጠን ሰው በቁሙ እያለ ከመጠየቅ ይልቅ ሩጫችን ብዙም በማይጠቅምበት ባለቀ ሰዓት መዋከብ ወይም ሞቱ ሲሰማ ጊዜ መጯጯህ የሚቀናን? ያሳዝናል።
ለማንኛውም አሁንም ከምናውቃቸው መሻይኾችና ኡስታዞች ውስጥ ጤናቸውና ኑሯቸው ፈተና ውስጥ የሆኑ ይኖራሉና ቀረብ ብሎ መጠየቅ ይልመድብን። በርግጥ እንዲሁ ሰሞንኛ ስሜቴን ለመግለፅ ያህል እንጂ ዞረን እዚያው እንደሆንን ይገባኛል። ብቻ ባለቀ ሰዓት መሯሯጥ ወይም ሞታቸውን ጠብቆ ከንፈር መምጠጥ ትርጉም የለውምና ሊበቃን ይገባል። ይሄ አካሄድ ከሞቱት ባልተናነሰ ያሉትንም ጭምር ሞራላቸውን በመጉዳት፣ ተስፋቸውን በማደብዘዝ፣ ልባቸውን በሃዘን በመስበር የሚገድል ነው። አላህ ልብ ይስጠን!
Ibnu Munewor
=
የቴሌግራም ቻናል፡-
https://t.me/IbnuMunewor
3 765
فضيلة الشيخ سليمان الرحيلي - حفظه الله -
عن شبهة أن بعض المحدثين رووا عن أهل البدع في الحديث، فما المانع أنْ نتعلم على يد المبتدع ؟
https://t.me/Abulbuhari
3 765
Repost from فوائد ومقالات منتقاة ــ عادل المشوري
قال شيخنا الكبير عبد الكريم الخضير حفظه الله :
الختمة الواحدة لا تكلف الإنسان حمل أثقال أو نحو ذلك، ولو أنَّ شخصاً اعتاد على القراءة بعد صلاة الصبح في المسجد إلى أن تنتشر الشمس، لقرأ القرآن في سبع، كما قال الرسول صلى الله عليه وسلم لابن عمرو رضي الله عنهما: "فاقرأه في سبعٍ، ولا تزد على ذلك" ، وبهذا يحصل في كل أسبوع على ثلاثة ملايين حسنة، وهذه الملايين مضبوطة ومحفوظة في سجل لا يغادر صغيرة ولا كبيرة إلا أحصاها .
3 765
من طرائف ما ترجم به الإمام الذهبي -رحمه الله- قوله في ترجمة يوسف بن أحمد الإسرائيلي المسلم:
“هو من بيت طب وفلسفة، وأجداده من فضلاء اليهود وأخيارهم؛ لعنهم الله”.
- تاريخ الإسلام ( ٥٢٥/١١ ).
منقول
3 765
👉 [ ልብ ያለው ልብ ይበል ]
- ነብዩ (ሶለሏሁ ዐለይሂ ወሰለም) ፈገግ አሉ። (ቡኻሪ : 1021)
-ነብዩ (ሶለሏሁ ዐለይሂ ወሰለም) ሳቁ። (ቡኻሪ : 1936)
- ነብዩ (ሶለሏሁ ዐለይሂ ወሰለም) ጥቂት ዝም አሉ። (ቡኻሪ : 3695)
- ነብዩ (ሶለሏሁ ዐለይሂ ወሰለም) አዘኑ። (ቡኻሪ : 6982)
- ነብዩ (ሶለሏሁ ዐለይሂ ወሰለም) አለቀሱ። (ቡኻሪ : 1304)
"የነብዩ (ሶለሏሁ ዐለይሂ ወሰለም) ባልደረባዎች (መልካም ስራቸውን አላህ ይውደድላቸውና) የነብያችንን (ሶለሏሁ ዐለይሂ ወሰለም) ፈገግታቸውን : ሳቃቸውን : ዝምታቸውን : ሀዘናቸውን : ለቅሷቸውን ወ.ዘ. ተ. ዘግበው አስተላልፈውልናል። ለምንድን ነው? ስለ መውሊዳቸው አንድ ነገር እንኳን ዘግበው ያላስተላለፉልን ???!!!"
https://t.me/Abulbuhari
3 765
▪️رأى سعيد بن المسيب - رحمه الله - رجلا يصلي في وقت النهي ركعات كثيرة فنهاه !
فقال : «يا أبا محمد، يعذبني الله على الصلاة ؟ !!»
قال : «لا، ولكن يعذبك على خلاف السنة»
▪️قال الشيخ الألباني - رحمه الله -
« وهذا من بدائع أجوبة سعيد بن المسيب ، وهو سلاح قوي على المبتدعة الذين يستحسنون كثيرًا من البدع ، ويتهمون أهل السنة بأنهم ينكرون الذكر والصلاة ، وهم إنما ينكرون عليهم مخالفتهم للسنة في الذكر والصلاة ونحو ذلك».
[ إرواء الغليل ، ج٢ ، ص٢٣٦].
https://t.me/Abulbuhari
3 765
Repost from MuhammedSirage M.Noor
እንኳን ያንተ አይነቱ
ውሻ ቢባል ሽልማቱ
ጀግና ‘ሚባል ተሰብስቦ
ሊያከስማቸው ጥልቅ አስቦ
አንዴ ሲዘልፍ ሙሐመድን
ሌላ ግዜ ሊገላቸው ጦር ሰብስቦ አገር ቢያድን
አልሆን ብሎት አፈር በልቷል
ከነ ጀሌው ጉድጓድ ገብቷል !
የዛሬውም ከንቱ ውሻ …,
ምግባር ሆኖ ለከረፋው ማንነትህ
ባፍ ብትጮህ ብታላዝን እንዳባትህ …
በዋልጌ አምደበትህ እምነቱን አትገታም
አለም ቢደግፍህ በባዶ ራስ ቅልህ እኛን ከቶ አትረታም !!!
https://t.me/Muhammedsirage
3 765
Repost from Ibnu Munewor (ኢብኑ ሙነወር)
"የውሻ ጩኸት ደመናን አይጎዳም!"
~
በነብያችን ﷺ ላይ የሚሳለቅ እራሱን እንጂ እሳቸውን ምንም ሊያደርጋቸው አይችልም። የላካቸው አምላክ "መወሳትህን/ዝናህን ከፍ አደረግንልህ" ብሏቸዋል። ይሄው የዝናቸው ከፍ ማለትም ነው ዛሬ በርካታ ውሾችን እያስጮኻቸው ያለው። ትላንትም የዛሬዎቹ ውሾች አያቶች የመልእክተኛውን ክብር ሊያንቋሽሹ ሞክረው ነበር። አላህ ግን እራሱ ለመልእክተኛው ﷺ ተከላካይ ጠበቃ ይሆንና መልእክተኛው ግን ነገሩን ንቀው እንዲተውት እንዲህ ይጠቁማቸዋል፡-
(فَٱصۡدَعۡ بِمَا تُؤۡمَرُ وَأَعۡرِضۡ عَنِ ٱلۡمُشۡرِكِینَ إِنَّا كَفَیۡنَـٰكَ ٱلۡمُسۡتَهۡزِءِینَ ٱلَّذِینَ یَجۡعَلُونَ مَعَ ٱللَّهِ إِلَـٰهًا ءَاخَرَۚ فَسَوۡفَ یَعۡلَمُونَ وَلَقَدۡ نَعۡلَمُ أَنَّكَ یَضِیقُ صَدۡرُكَ بِمَا یَقُولُونَ فَسَبِّحۡ بِحَمۡدِ رَبِّكَ وَكُن مِّنَ ٱلسَّـٰجِدِینَ وَٱعۡبُدۡ رَبَّكَ حَتَّىٰ یَأۡتِیَكَ ٱلۡیَقِینُ)
"የታዘዝክበትንም ነገር በይፋ ግለፅ፤ አጋሪዎችንም ተዋቸው። እኛ ተሳላቂዎችን ሁሉ በቅተነሃል። (እነሱም) እነዚያ ከአላህ ጋር ሌላ አምላክን ያደረጉ ናቸው፤ በርግጥም (የስራቸውን ዋጋ) ወደፊት ያውቃሉ። አንተም በሚሉት ነገር ልብህ የሚጠብ መሆኑን በርግጥም እናውቃለን። ጌታህንም ከማመስገን ጋር አጥራው፤ ከሰጋጆቹም ሁን። እውነቱም (ሞት) እስከሚመጣህ ድረስ ጌታህን አምልክ።" [አልሒጅር፡ 94-99]
ስለዚህ ተሳላቂዎቹ ውሾች ቢሳለቁም የነብያችን ﷺ ዝና የበለጠ ይገናል። የውሾቹ ስም ይከስማል። ውሻ ደግሞ ምን ታሪክ አለውና?!! እስኪ የነብያችንና የትላንት ጠላቶቻቸውን ዝና አወዳድሩ። ሲጀመር መወዳደር ይችላሉ? በጭራሽ!! “የሰማይና የመሬት ያክል ነው” ብንል እንኳ በትክክል አይገልፀውም።
ግን የነብያችንን ﷺ ክብር ለማጉደፍ ተፍ ተፍ የሚሉ ሰዎች አላማቸው ምን ይሆን? መልሱ ግልፅ ነው።
1. አንዳንዶቹ በነብዩ ﷺ እውቅና ሂሳብ እውቅና መሸመት የሚፈልጉ ናቸው። “አንዳንዶች ታዋቂዎችን በመተቸት ታዋቂ መሆን ይፈልጋሉ” ሲባል አልሰማችሁም?
2. ሌሎቹ ደግሞ የኢስላም ውበቱና ሁለንተናዊነቱ የሚያስቀናቸው፤ ከፍተኛ ግስጋሴው የሚያስበረግጋቸው ናቸው። ስለሆነም ሙሐመድን ﷺ ሲያንቋሽሹ የኢስላም ውበቱ የሚደበዝዝ፣ ግስጋሴው የሚገታ ይመስላቸዋል። እውነታው ግን ተቃራኒው ነው። ኢስላም ዛሬ ጠላቶቹን እንቅልፍ በሚነሳ መልኩ በከፍተኛ ፍጥነት እየገሰገሰ ነው። ስለዚህ ውሾቹ አመል ሆኖባቸው ይጮሃሉ እንጂ የኢስላምን ግስጋሴ ሊገቱት አይችሉም!! ውሾቹ ይጮሃሉ፣ ዋው! ዋው!....። ግመሉ ግን ጉዞውን ቀጥሏል። ውሻ ግመልን ማስቆም ከቻለች ትሞክር።
ባይሆን ከኛ አንድ ነገር ይጠበቃል። ከሃዲዎችን የነብያችንን ﷺ ስም ለመዘለፍ ያበቃቸው ለነብዩ አስተምሮ ያላቸው ጥላቻ መሆኑ ይታወቃል። አዎ የነቢዩ ﷺ ሱና እጅጉን ያስቆጫቸዋል!! እውነቱ ይህ ከሆነ ከሃዲዎችን የበለጠ ለማስቆጨት የሚጓጓ፤ ለሙሐመድ ﷺ እውነተኛ ወዳጅነቱን ማንፀባረቅ የሚፈልግ፣ ብሎም የአላህን ውዴታ ማትረፍ የሚሻ የበለጠ ወደ መልእክተኛው ሱና ይቅረብ፤ ትእዛዛቸውንም ይፈፅም፤ ከከለከሉትም ይራቅ። ይህን የሚያደርግ ጠላቱን የበለጠ ያስቆጫል። የአላህንና የመልክተኛውንም ﷺ ውዴታ ያፍሳል። ያ ሱብሓላህ! የአላህና የመልክተኛውን ውዴታ ያገኘ ምን የቀረበት ነገር አለ?! ያ ወሃ፞ቡ አንተ ወፍቀን! ኣሚን
(ኢብኑ ሙነወር፣ መስከረም 08/2005)
የቴሌግራም ቻናል
https://t.me/IbnuMunewor
3 765
المولد شبهات وردود
فضيلة الشيخ الدكتور حسن أحمد حسن الهواري - حفظه الله - .
