en
Feedback
Addis መረጃ™

Addis መረጃ™

Open in Telegram

@Addis_Mereja ቀዳሚ የመረጃ ምንጭ 🇪🇹 🇪🇹 . ⏬ምርት እና አገልግሎቶን ለማስተዋወቅ ከፈለጉ⏬ ⏬ ꜰᴏʀ ᴘᴀɪᴅ ᴘʀᴏᴍᴏᴛɪᴏɴ ⏬ መረጃዎችን ለመላክ @Adis_Merejaa_bot

Show more

📈 Analytical overview of Telegram channel Addis መረጃ™

Channel Addis መረጃ™ (@addis_mereja) in the Amharic language segment is an active participant. Currently, the community unites 41 888 subscribers, ranking 6 308 in the News & Media category and 800 in the Ethiopia region.

📊 Audience metrics and dynamics

Since its creation on невідомо, the project has demonstrated rapid growth, gathering an audience of 41 888 subscribers.

According to the latest data from 02 February, 2026, the channel demonstrates stable activity. Although there has been a change in the number of participants by -500 over the last 30 days and by 0 over the last 24 hours, overall reach remains high.

  • Verification status: Not verified
  • Engagement rate (ER): The average audience engagement rate is 0%. Within the first 24 hours after publication, content typically collects N/A% reactions from the total number of subscribers.
  • Post reach: On average, each post receives 0 views. Within the first day, a publication typically gains 0 views.
  • Reactions and interaction: The audience actively supports content: the average number of reactions per post is 0.

📝 Description and content policy

The author describes the resource as a platform for expressing subjective opinions:
@Addis_Mereja ቀዳሚ የመረጃ ምንጭ 🇪🇹 🇪🇹 . ⏬ምርት እና አገልግሎቶን ለማስተዋወቅ ከፈለጉ⏬ ⏬ ꜰᴏʀ ᴘᴀɪᴅ ᴘʀᴏᴍᴏᴛɪᴏɴ ⏬ መረጃዎችን ለመላክ @Adis_Merejaa_bot

Thanks to the high frequency of updates (latest data received on 03 February, 2026), the channel maintains relevance and a high level of publication reach. Analytics show that the audience actively interacts with content, making it an important point of influence in the News & Media category.

Buy Ad
41 888
Subscribers
No data24 hours
-987 days
-50030 days
Posts Archive
ኢራን አሜሪካን ኢላማ ካደረገች መዘዙ እንደሚከፋ የአሜሪካ ባለስልጣን አስጠነቀቀቁ አሜሪካ ይህንን ያለችው ኢራን፤ አሜሪካ፣ ፈረንሳይ እና ዩኬ እስራኤልን የሚረዱ ከሆነ አጸፋውን እንደምትመልስ ማስጠን
ኢራን አሜሪካን ኢላማ ካደረገች መዘዙ እንደሚከፋ የአሜሪካ ባለስልጣን አስጠነቀቀቁ አሜሪካ ይህንን ያለችው  ኢራን፤ አሜሪካ፣ ፈረንሳይ እና ዩኬ እስራኤልን የሚረዱ ከሆነ አጸፋውን እንደምትመልስ ማስጠንቀቋን ተከትሎ ነው። እስራኤል በኢራን ላይ የፈጸመችውን ጥቃት በተመለከተ ከጥቃቱ በፊት አሜሪካ “ምክር ተጠይቃ” በምላሹ “ራሷን ለመከላከል መሰረታዊ ነው” የሚል ምላሽ እንደተሰጣት የአሜሪካ ባለስልጣን ተናግረዋል ። “አሜሪካ ስለ ጥቃቱ ቀድሞ ቢነገራትም በነዚህ ጥቃቶች ላይ ወታደራዊ ተሳትፎ አልነበራትም” ሲሉ የአገሪቱ የአለም አቀፍ ድርጅት ጉዳዮች ቢሮ ከፍተኛ ባለስልጣን ማኮይ ፒት ለተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የጸጥታው ምክር ቤት ተናግረዋል። "ዋነኛው ቅድሚያ የምንሰጠው በቀጣናው ውስጥ ያሉ የአሜሪካ ዜጎች፣ ሰራተኞች እና ኃይሎችን ጥበቃ ነው።" ብለዋል። ኢራን በቀጣናው ያሉ የአሜሪካ ዜጎች፣ የጦር ሰፈሮችን ወይም መሰረተ ልማቶችን ዒላማ ካደረገች “የሚከተላት መዘዝ አስከፊ ነው” ሲሉ ተናግረዋል። የአሜሪካ አቋም ኢራን ስምምነት ማድረግ አለባት የሚል እንደሆኑ ገልጸው አገራቸው “ዲፕሎማሲያዊ መፍትሄ” ትሻለች ብለዋል። “የኢራን አመራሮች በዚህ ወቅት መደራደራቸው ብልህነት ነው” ብለዋል። ኢራን በእስራኤል ላይ እየወሰደች ያለችን አጸፋዊ እርምጃ ለማስቆም አሜሪካ፣ ፈረንሳይ እና ዩናይትድ ኪንግደም እስራኤልን የሚረዱ ከሆነ ምላሹን እንደምትሰጥ ማስጠንቀቋን የኢራን መንግሥታዊ ሚዲያ ዘግቧል። ሶስቱ አገራት ለእስራኤል ድጋፋቸውን ከሰጡ ኢራን በቀጣናው የሚገኙ የጦር ሰፈሮቻቸውን እና መርከቦችን ኢላማ እንደምታደርግ ዘገባዎች ወጥተዋል። @Addis_Mereja

እስራኤል ሌላ ዙር ጥቃት ፈፀመች። በቴላቪቭ በርካታ ፍንዳታዎችን እና ውድመትን ያስከተለው ጥቃት በኢራን ላይ መፈፀሟ ተነገረ። በቴህራን የኢራን መንግስት ቲቪ እንደዘገበው ከሆነ ዛሬ አመሻሹ ላይ እስ
+1
እስራኤል ሌላ ዙር ጥቃት ፈፀመች። በቴላቪቭ  በርካታ ፍንዳታዎችን እና ውድመትን ያስከተለው ጥቃት በኢራን ላይ መፈፀሟ ተነገረ። በቴህራን የኢራን መንግስት ቲቪ እንደዘገበው ከሆነ ዛሬ አመሻሹ ላይ እስራኤል ከ150 በላይ ቦታዎች ላይ ጥቃት መፈፀሟን እና በተፈፀመው ጥቃትም በኢራን ደቡባዊ ቡሻህር ግዛት ውስጥ ከጋዝ ማውጫ ጨምሮ በርካታ ቦታዎች ላይ ጉዳት መድረሱን የገለፀ ሲሆን በጥቂቱም   20 ህጻናትን ጨምሮ ወደ 60 የሚጠጉ ሰዎች መገደላቸውን እና በመላ ሀገሪቱ ተጨማሪ ጥቃቶች መፈፀሙን ተዘግቧል። @Addis_Mereja

እስራኤል በመላው ዓለም የሚገኙ ኤምባሲዎቿን ዘጋች ** እስራኤል በኢራን ላይ የፈፀመችውን ጥቃት ተከትሎ በመላው ዓለም የሚገኙ ኤምባሲዎቿንና የቆንስላ ፅህፈት ቤቶቿን በጊዜያዊነት ዘግታለች። የእስራኤ
እስራኤል በመላው ዓለም የሚገኙ ኤምባሲዎቿን ዘጋች ** እስራኤል በኢራን ላይ የፈፀመችውን ጥቃት ተከትሎ በመላው ዓለም የሚገኙ ኤምባሲዎቿንና የቆንስላ ፅህፈት ቤቶቿን በጊዜያዊነት ዘግታለች። የእስራኤል የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴርን ጠቅሶ ሮይተርስ እንደዘገበው ተለዋጭ መልእክት እስኪሰጥ ድረስ በመላው ዓለም የሚገኙ የእስራኤል ኤምባሲዎችና የቆንስላ ፅ/ቤቶች ተዘግተው ይቆያሉ ተብሏል፡፡ በውጭ ሀገራት የሚገኙ እስራኤላውያን ጥንቃቄ እንዲያደርጉም ሚኒስቴሩ ማሳሰቡን ዘገባው አክሏል። የእስራኤል ጦር በኢራን ላይ በፈፀመው የአየር ጥቃት በተለያዩ አካባቢዎች የሚገኙ የኒውክሌር ጣቢያዎች እና ወታደራዊ ኢላማዎችን መምታቱ ተነግሯል፡፡ @Addis_Mereja

ጥንቃቄ❗️ በኢትዮጵያ የተገኘው የኤምፖክስ ቫይረስ ዝርያ "ከፍተኛ የሞት መጠን" እና "ሥርጭት" ያለው መሆኑ ተገለጸ ከአንድ ወር በፊት ወደ ኢትዮጵያ የገባው የኤምፖክስ (የዝንጀሮ ፈንጣጣ) ቫይረስ
ጥንቃቄ❗️ በኢትዮጵያ የተገኘው የኤምፖክስ ቫይረስ ዝርያ "ከፍተኛ የሞት መጠን" እና "ሥርጭት" ያለው መሆኑ ተገለጸ ከአንድ ወር በፊት ወደ ኢትዮጵያ የገባው የኤምፖክስ (የዝንጀሮ ፈንጣጣ) ቫይረስ ዝርያ "ከፍተኛ የሞት መጠን" የሚያስከትል እና በከፍተኛ መጠን የሚሠራጭ እንደሆነ ጤና ሚኒስቴር እና የኢትዮጵያ ሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት አስታወቁ። ከሁለት ሳምንት በፊት በበሽታው ሕይወቱ ያለፈው አንድ ወር እድሜ ያለው ሕጻን እንደሆነም ተቋማቱ ገልጸዋል። የጤና ሚኒስቴር እና ሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ይህንን ያስታወቁት ትናንት ረቡዕ ሰኔ 4/2017 ዓ.ም. ምሽት ባወጡት 'ወቅታዊ ማብራሪያ' ነው። ግንቦት 16 ቀን ለመጀመሪያ ጊዜ ወደ ኢትዮጵያ መግባቱ የተረጋገጠው ኤምፖክስ ከሁለት ሳምንት ባነሰ ጊዜ ውስጥ 18 ሰዎችን መያዙን የተቋማቱ መረጃ ያመለክታል። በበሽታው ከተያዙት ሰዎች መካከል አምስቱ "ሙሉ ለሙሉ" ማገገማቸውን መግለጫው ያስረዳል። የኤም ፖክስ ( Mpox) መተላለፊያ መንገዶቹም ፦ - የቅርብ ንክኪ፣ - በቫይረሱ ከተያዘ ሰው ጋር የሚኖር የእጅ መነካካት፣ - በቫይረሱ የተያዘ ሰው የሚጠቀምባቸው ቁሳቁሶችን መጠቀም እና የፊት ለፊት የትንፋሽ ግንኙነት ናቸው። የኤም ፓክስ በሽታ ምልክቶቹ ፦ ° ከፍተኛ ትኩሳት፣ ° ራስ ምታት፣ ° የጀርባ ሕመም፣ ° የሰውነት ዕጢ እብጠቶች፣ ° ለመተንፈስ መቸገር፣ ° በሰውነት ክፍል ጎልተው የሚታዩ ሽፍታዎች ሲሆን ምልክቶችም ህመምተኛው በቫይረሱ ከተያዘ ከ5 እስከ 21 ቀናቶች ውስጥ የሚታዩ ናቸው። መከላከያ መንገዶች ፦ ° በበሽታው ከተያዘ ሰው ጋር ግንኙነቶችን  መገደብ ፣ ° እጅን በሳሙና መታጠብ፣ ° በበሽታ የተያዘ ሰው የሚጠቀምባቸውን ቁሳቁሶች በጋራ አለመጠቀም። @Addis_Mereja

Repost from ETHIO-MEREJA®
ጥንቃቄ❗️ በኢትዮጵያ የተገኘው የኤምፖክስ ቫይረስ ዝርያ "ከፍተኛ የሞት መጠን" እና "ሥርጭት" ያለው መሆኑ ተገለጸ ከአንድ ወር በፊት ወደ ኢትዮጵያ የገባው የኤምፖክስ (የዝንጀሮ ፈንጣጣ) ቫይረስ
ጥንቃቄ❗️ በኢትዮጵያ የተገኘው የኤምፖክስ ቫይረስ ዝርያ "ከፍተኛ የሞት መጠን" እና "ሥርጭት" ያለው መሆኑ ተገለጸ ከአንድ ወር በፊት ወደ ኢትዮጵያ የገባው የኤምፖክስ (የዝንጀሮ ፈንጣጣ) ቫይረስ ዝርያ "ከፍተኛ የሞት መጠን" የሚያስከትል እና በከፍተኛ መጠን የሚሠራጭ እንደሆነ ጤና ሚኒስቴር እና የኢትዮጵያ ሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት አስታወቁ። ከሁለት ሳምንት በፊት በበሽታው ሕይወቱ ያለፈው አንድ ወር እድሜ ያለው ሕጻን እንደሆነም ተቋማቱ ገልጸዋል። የጤና ሚኒስቴር እና ሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ይህንን ያስታወቁት ትናንት ረቡዕ ሰኔ 4/2017 ዓ.ም. ምሽት ባወጡት 'ወቅታዊ ማብራሪያ' ነው። ግንቦት 16 ቀን ለመጀመሪያ ጊዜ ወደ ኢትዮጵያ መግባቱ የተረጋገጠው ኤምፖክስ ከሁለት ሳምንት ባነሰ ጊዜ ውስጥ 18 ሰዎችን መያዙን የተቋማቱ መረጃ ያመለክታል። በበሽታው ከተያዙት ሰዎች መካከል አምስቱ "ሙሉ ለሙሉ" ማገገማቸውን መግለጫው ያስረዳል። የኤም ፖክስ ( Mpox) መተላለፊያ መንገዶቹም ፦ - የቅርብ ንክኪ፣ - በቫይረሱ ከተያዘ ሰው ጋር የሚኖር የእጅ መነካካት፣ - በቫይረሱ የተያዘ ሰው የሚጠቀምባቸው ቁሳቁሶችን መጠቀም እና የፊት ለፊት የትንፋሽ ግንኙነት ናቸው። የኤም ፓክስ በሽታ ምልክቶቹ ፦ ° ከፍተኛ ትኩሳት፣ ° ራስ ምታት፣ ° የጀርባ ሕመም፣ ° የሰውነት ዕጢ እብጠቶች፣ ° ለመተንፈስ መቸገር፣ ° በሰውነት ክፍል ጎልተው የሚታዩ ሽፍታዎች ሲሆን ምልክቶችም ህመምተኛው በቫይረሱ ከተያዘ ከ5 እስከ 21 ቀናቶች ውስጥ የሚታዩ ናቸው። መከላከያ መንገዶች ፦ ° በበሽታው ከተያዘ ሰው ጋር ግንኙነቶችን  መገደብ ፣ ° እጅን በሳሙና መታጠብ፣ ° በበሽታ የተያዘ ሰው የሚጠቀምባቸውን ቁሳቁሶች በጋራ አለመጠቀም።   T.me/ethio_mereja         ኢትዮ-መረጃ

ለሌሊቱ ከባድ ጥቃት አፀፋ ኢራን 100 ሰው አልባ አውሮፕላኖችን ወደ እስራኤል ልካለች። @Addis_Mereja

የኢራን ጦር ሃይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ሜጀር ጀነራል መሀመድ ባገሪ ዛሬ ምሽት እስራኤል በቴህራን ላይ ባደረሰችው ጥቃት መገደላቸው ተረጋግጧል። @Addis_Mereja
የኢራን ጦር ሃይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ሜጀር ጀነራል መሀመድ ባገሪ ዛሬ ምሽት እስራኤል በቴህራን ላይ ባደረሰችው ጥቃት መገደላቸው ተረጋግጧል። @Addis_Mereja

የኢራን እስላማዊ አብዮታዊ ጥበቃ ጓድ ዋና አዛዥ ሆሴን ሳላሚ ዛሬ ምሽት እስራኤል በኢራን ዋና ከተማ ቴህራን ላይ ባካሄደችው ጥቃት መገደሉን የኢራን የዜና ምንጮች ዘግበዋል። @Addis_Mereja
የኢራን እስላማዊ አብዮታዊ ጥበቃ ጓድ ዋና አዛዥ ሆሴን ሳላሚ ዛሬ ምሽት እስራኤል በኢራን ዋና ከተማ ቴህራን ላይ ባካሄደችው ጥቃት መገደሉን የኢራን የዜና ምንጮች ዘግበዋል። @Addis_Mereja

ሰበር ዜና!! እስራኤል በኢራን ላይ ጥቃት መፈጸም ጀመረች!! የእስራኤል አየር ሃይል በኢራን የኒውክሊየር ኢላማዎች፣ ወታደራዊ ጣቢያዎች እና ጄኔራሎች ላይ ጥቃት መፈጸም ጀምሯል። @Addis_Mereja

የጤና ጥበቃ ሚኒስቴር በዝንጀሮ ፈንጣጣ (ኤምፖክስ) የተያዙ ሰዎች ቁጥር 18 መድረሱን አስታወቀ። ጤና ጥበቃ ሚኒስቴር ከኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ጋር በመሆን ባወጡት መግለጫ እስከ ሰኔ 4 2017 ዓ.ም. ድረስ ብቻ 18 በቫይረሱ መያዛቸው መረጋገጡን ገልፀዋል።በኢትዮጵያ በዝንጀሮ ፈንጣጣ (ኤምፖክስ) ለመጀመርያ ጊዜ በኢትዮጵያ መከሰቱ ይፋ የሆነው ግንቦት 17/ 2017 ዓ.ም. ሲሆን በበሽታው ከተያዙት መካከል የአንድ ወር ጨቅላ ሕይወቱ ማለፉ ይታወሳል። የጤና ጥበቃ ሚኒስቴር እስከ ትናንት ሰኔ 04/ 2017 ዓ.ም. ድረስ 102 ለሚሆኑ የላቦራቶሪ ምርመራዎች ማድረጉን እና በበሽታው የተያዙ ታማሚዎች ቁጥር 18 መድረሱን ባወጣው መግለጫ አስታውቋል።እስካሁን በበሽታዉ ከተያዙት 18 ሰዎች መካከል አምስቱ ሙሉ በሙሉ ማገገማቸው ተገልጿል።የመጀመርያው የኤምፖክስ ታማኣሚ የተገኘው ግንቦት 16/ 2017 ዓ.ም. በኦሮምያ ክልል ሞያሌ ከተማ መሆኑ ይታወሳል። እንደ ጤና ጥበቃ መረጃ ከሆነ የኤምፖክስ ቫይረስ የተለያዩ ዝርያዎች ያሉት ሲሆን በኢትዮጵያ በሕክምና ላይ ካሉ ታማሚዎች የተወሰደ ናሙና ላይ በተደረገ የዘረመል ምርመራ በተገኘው ውጤት መሰረት ክሌድ 1 ቢ (Clade 1b) የተባለው ዝርያ ዓይነት እንደሆነ ለማረጋገጥ ተችሏል።ይህ የቫይረስ ዝርያ በአንጻሩ ከፍተኛ የሚባል የስርጭት መጠን ያለውና በዚህ የቫይረስ ዝርያ ከበሽታው ጋር በተያያዘ የሚከሰት የሞት መጠን በአንፃሩ ከፍተኛ እንደሆነ በሌሎች አገራት የተገኘ ልምድ ያሳያል። ለኤምፖክስ በሽታ አጋላጭ ሁኔታዎች ተብለው ከተለዩት መንገዶች መካከል በቫይረሱ ከተያዙ ሰዎች ጋር የሚደረግ የሰውነት ንክኪ፣ የግብረ ስጋ ግንኙነት እንዲሁም ከታማሚ ሰው ጋር ንክኪ ያለውን ቁስ በጋራ መጠቀም በዋነኛነት ይጠቀሳሉ።በኢትዮጵያ በሽታው መያዛቸው ለመጀመርያ ጊዜ የተገለፀው በሞያሌ ከተማ ነዋሪ የሆኑ የ21 ቀን ዕድሜ ያለው ሕጻን እና እናቱ ነበሩ። Via Ethio FM @Addis_Mereja

አቶ ታደለ ገብረመድህን በቁጥጥር ስር ዋለ ! አትሌት ገለቴ ቡርቃ "ዘርፎኛል "በሚል በሚዲያ የከሰሰችው እና ብዙዎችን ያሳዘነው የአትሌቷ ህይወት በዛሬው እለት የአዲስ አበባ ፖሊስ የቀድሞው ባለቤቷ
+1
አቶ ታደለ ገብረመድህን በቁጥጥር ስር ዋለ ! አትሌት ገለቴ ቡርቃ "ዘርፎኛል "በሚል በሚዲያ የከሰሰችው  እና ብዙዎችን  ያሳዘነው የአትሌቷ ህይወት  በዛሬው እለት የአዲስ አበባ ፖሊስ  የቀድሞው ባለቤቷ ታደለ ገብረመድህን  በቁጥጥር ስር ታውቋል @Addis_Mereja

🕌🕋እንኳን ለ1,446ኛው ዒድ አል-አደሃ (አረፋ) በዓል አደረሳችሁ! በፍቅር፣ በደስታና በአብሮነት የምታከብሩት መልካም የዒድ አል-አደሃ (አረፋ) በዓል እንዲሆንላችሁ ከልብ እንመኛለን። ✨ዒድ ሙ
🕌🕋እንኳን ለ1,446ኛው ዒድ አል-አደሃ (አረፋ) በዓል አደረሳችሁ! በፍቅር፣ በደስታና በአብሮነት የምታከብሩት መልካም የዒድ አል-አደሃ (አረፋ) በዓል እንዲሆንላችሁ ከልብ እንመኛለን። ✨ዒድ ሙባረክ! @Addis_Mereja

Repost from ETHIO-MEREJA®
🕌🕋እንኳን ለ1,446ኛው ዒድ አል-አደሃ (አረፋ) በዓል አደረሳችሁ! በፍቅር፣ በደስታና በአብሮነት የምታከብሩት መልካም የዒድ አል-አደሃ (አረፋ) በዓል እንዲሆንላችሁ ከልብ እንመኛለን። ✨ዒድ ሙ
🕌🕋እንኳን ለ1,446ኛው ዒድ አል-አደሃ (አረፋ) በዓል አደረሳችሁ! በፍቅር፣ በደስታና በአብሮነት የምታከብሩት መልካም የዒድ አል-አደሃ (አረፋ) በዓል እንዲሆንላችሁ ከልብ እንመኛለን። ✨ዒድ ሙባረክ!         ኢትዮ-መረጃ

ፕላስቲክ❗️ማንኛውም ሰው አንድ ጊዜ ብቻ ጥቅም ላይ የሚውል የፕላስቲክ ከረጢት ይዞ ከተገኘ ከ2000 እስከ 5000 ብር የሚያስቀጣው አዋጅ ፀደቀ!! ለእንጀራ፣ ለዳቦ እና ለተለያዩ የሸቀጥ እቃዎች መጠቅለያነት የሚውለውን የአንድ ብሩን ፕላስቲክ ይዞ መገኘት ከ2000 እስከ 5000 ብር የሚያስቀጣው አዋጅ ጸደቀ፡፡ ያመረተ ወይም ወደ ሀገር ውስጥ ያስገባ፣ ለገበያ ያቀረበ ወይም የሸጠ፣ ለንግድ ዓላማ ያከማቸ ወይም ይዞ የተገኘ ከ50,000 ብር በማያንስና ከ200,000 ብር በማይበልጥ የገንዘብ መቀጮ እና ከአምስት ዓመት በማይበልጥ ጽኑ እስራት  እንዲቀጣ አዋጁ ያዝዛል፡፡ የውሃ፣ መስኖ፣ ቆላማ አካባቢና አካባቢ ልማት ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ምክትል ሰብሳቢ አወቀ አምዛዬ(ዶ/ር) የአዋጁን ይዘት በንባብ ባቀረቡበት ወቅት፤ የምክር ቤት አባሉ አለሙ ጎንፋ (ዶ/ር) ህዝባችን በፕላስቲክ እቃ ይዞ ወደ ቤቱ ከገባ ይጣለው? ወይስ መልሶ ለአካባቢ ጥበቃ ያስረክበው? የሚል ጥያቄ ከጠየቁ ብኋላ የምናመርተው የፕላስቲክ ውጤት ዳግም እንድንጠቀምበት የሚያደርግ ቢሆን አይሻልም ወይ? ምክንያቱም 10 ጊዜ የምጠቀምበትን ፕላስቲክ አንድ ጊዜ ብቻ ተጠቀም ማለት ተገቢ አይደለም፣ አዋጁ ፕላስቲኩን ከተጠቀምኩበት ወዲያ የት ማስቀመጥ እንዳለበት አላስቀመጠም ብለዋል፡፡ አዋጁ ይዞ የተገኝ እንዲቀጣ ይደነግጋል ህዝባችን የዚህ ግንዛቤ ይኖረዋል ወይ? የትኛው ፕላስቲክ እንደሆነ የመለየት ግንዛቤስ አለው ወይ? ሲሉ ጠይቀዋል፡፡ ሌላ አንድ የምክር ቤት አባል በበኩላቸው ማንኛውም ሰው #ፕላስቲክ ይዞ ከተገኘ ከሁለት እስከ አምስት ሺህ ብር እንዲቀጣ ይደነግጋል፤ ይህ ከእኛ ነባራዊ ሁኔታ ጋር  እንዴት ታየ? በተለይ ዝቅተኛ ገቢ ያለው የማህበረሰብ ክፍል ሊጠቀመው ስለሚችል ጫና አይፈጥርም ወይ? ሲሉ ጠይቀዋል፡፡ ለጥያቄዎቹ ምላሽ የሰጡት የውሃ፣ መስኖ፣ ቆላማ  አካባቢ ልማት ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ምክትል ሰብሳቢ አወቀ አምዛዬ(ዶ/ር) ለአንድ ጊዜ ብቻ አገልግሎት ላይ የሚውሉ ፌስታሎችን ዝቅተኛው የማህበረሰብ ክፍልም ስለሚጠቀማቸው ቅጣቱ ያን ግንዛቤ ውስጥ ያስገባ ነው ብለዋል፡፡ ለምሳሌ «አንዲት አሮጊት ወይም ሽማግሌ የሁለት ብር ዳቦ ወይም የአስር ብር ስኳር ገዝተው ሲሄዱ 5 ሺህ ብር ክፍሉ ቢባሉ ላይኖራቸው ስለሚችል ቅጣቱ ከ5 ሺህ ወደ 2 ሺህ ዝቅ እንዲል ተደርጓል ይህም የህብረተሰቡን የመክፈልም አቅም ከግንዛቤ ያስገባ ነው ሲሉ አስረድተዋል፡፡ የፕላስቲክ ከረጢቶች ከቅጣቱ በላይ ሀገርን የሚጎዱ ናቸው እስከ መቶ ዓመት ድረስም አይበሰብሱም ያሉት ምክትል ሰብሳቢው፤ ከዚህ አንጻር ቅጣቱ ሃያም ሰላሰም ሺህ ቢሆን ሀገርን ለማትረፍ ነው ብለዋል፡፡ ለህዝቡ ግንዛቤ ለመስጠትም ከመጪው ሃሙስ ጀምሮ የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ ይካሄዳል ሲሉ አወቀ አምዛዬ (ዶ/ር) ተናግረዋል፡፡አዋጁ የፕላስቲክ ጫማዎችን፣ የውሃ ኮዳዎችን እና ወፍራም የፕላስቲክ ውጤቶችን አይጨምርም መባሉን ሰምተናል፡፡ አዋጁ ማንኛውም ሰው ከመኖሪያ ቤቱ ድንበር አንስቶ ከሃያ ሜትር በላይ አካባቢውን የማጽዳት ግዴታን ያስቀምጣል፡፡አዋጁም በነጋሪት ጋዜጣ ታትሞ ከሚወጣበት ቀን ጀምሮ በመላ ሀገሪቱ ተፈጻሚ ይሆናል፡፡ ምንጭ ፣ ሸገር ኤፍ ኤም @Addis_Mereja

ትራምፕ በአለም አቀፍ ንግድ ላይ አዲስ ታሪፍ ጣሉ፤ ኢትዮጵያም 10 በመቶ ታሪፍ ተጥሎባታል የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ በአለም አቀፍ ንግድ ላይ አዲስ የታሪፍ እርምጃ ወሰዱ። ረቡዕ ዕለት
+1
ትራምፕ በአለም አቀፍ ንግድ ላይ አዲስ ታሪፍ ጣሉ፤ ኢትዮጵያም 10 በመቶ ታሪፍ ተጥሎባታል የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ በአለም አቀፍ ንግድ ላይ አዲስ የታሪፍ እርምጃ ወሰዱ። ረቡዕ ዕለት በዋይት ሀውስ በሰጡት መግለጫ፣ አሜሪካ ከሌሎች ሀገራት ጋር በምታደርገው የንግድ ልውውጥ ላይ አዲስ የታሪፍ መጠኖችን መጣላቸውን አስታውቀዋል። ትራምፕ እንደገለጹት፣ ይህ እርምጃ አሜሪካን ቀዳሚ ለማድረግ እና የንግድ ጉድለትን ለመቀነስ ያለመ ነው። በአብዛኛዎቹ ሀገራት ላይ የተጣለው ታሪፍ ከ10% እስከ 49% የሚደርስ ሲሆን፣ ኢትዮጵያም 10% ታሪፍ ተጥሎባታል። አሜሪካ የንግድ ጉድለቷን ለመቀነስ እና የአሜሪካን ኢኮኖሚ ለመጠበቅ ይህን እርምጃ እንደወሰደች የገለፁት ፕሬዝዳንቱ ከ20 በላይ ሀገራት ላይ የታሪፍ ጭማሪ የተደረገ ሲሆን፣ ኢትዮጵያም ከነዚህ ሀገራት አንዷ መሆኗ ተዘግቧል ። ካፒታል ጋዜጣ @Addis_Mereja

ጨረቃ ዛሬ በመታየቷ የዒድ አል-ፈጥር በዓል ነገ ይከበራል የሸዋል ወር ጨረቃ ዛሬ ቅዳሜ በመታየቷ 1 ሺህ 446ኛው የዒድ አል-ፈጥር በዓል ነገ እሁድ መጋቢት 21 ቀን 2017 ዓ.ም እንደሚከበር ተገ
ጨረቃ ዛሬ በመታየቷ የዒድ አል-ፈጥር በዓል ነገ ይከበራል የሸዋል ወር ጨረቃ ዛሬ ቅዳሜ በመታየቷ 1 ሺህ 446ኛው የዒድ አል-ፈጥር በዓል ነገ እሁድ መጋቢት 21 ቀን 2017 ዓ.ም እንደሚከበር ተገልጿል። የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ፕሬዚዳንት ሃጂ ኢብራሂም ቱፋ 1 ሺህ 446ኛው የኢድ አል-ፈጥር በዓልን አስመልክቶ ባስተላለፉት የመልካም ምኞት መግለጫ መልዕክት፤ ሕዝበ ሙስሊሙ በዓሉን ሲያከብር አስተምኅሮቱን በመተግበር ሊሆን እንደሚገባ አሳስበዋል፡፡ @Addis_Mereja

45' | ኢትዮጵያ 🇪🇹 0-2 🇪🇬 ግብፅ 31' ሞ ሳላህ 40' ዚዞ #2026_የዓለም_ዋንጫ_ማጣርያ @Addis_Mereja

ኢትዮጵያ ከግብጽ ጋር ከ6ሰዓት ላይ የምታደርገውን ጨዋታ ለማየት ይህን አፕ ዳውን ሎድ አድርጉ። Cricfy TV በነፃ ነው። ለሌላ ጊዜም ይጠቅማችኋል። Application ለማውርድ በዚህ ገፅ ላይ ካደረግን Copyright ሊዘጋብን ሰለሚችል አዲስ ቻናል ከፍተናል ለቀናል አፕልኬሽኑን Another channel 👉 https://t.me/H

ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ ከነገ በስቲያ በፓርላማ ተገኝተው ለጥያቄዎች ምላሽ ሊሰጡ ነው! ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ ከነገ በስቲያ ሐሙስ መጋቢት 11፤ 2017 በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት
ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ ከነገ በስቲያ በፓርላማ ተገኝተው ለጥያቄዎች ምላሽ ሊሰጡ ነው! ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ ከነገ በስቲያ ሐሙስ መጋቢት 11፤ 2017 በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በመገኘት፤ ከፓርላማ አባላት ለሚቀርቡላቸው ጥያቄዎች ምላሽ እና ማብራሪያ ሊሰጡ ነው።የሐሙሱ የፓርላማ መደበኛ ስብሰባ፤ የፌደራል መንግስት የስድስት ወር የእቅድ አፈጻጸም ሪፖርቱን ለምክር ቤት አባላት መላኩን ተከትሎ የሚካሄድ ነው። በ57 ገጾች የቀረበው እና “ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” የተመለከተችው ይህ ሪፖርት፤ በዘንድሮው በጀት ዓመት የመንፈቅ ጊዜ ውስጥ የፌደራል መንግስት ያከናወናቸውን ዋና ዋና ስራዎች የሚዘረዝር ነው።ሪፖርቱ በኢኮኖሚ፣ በማህበራዊ ልማት፣ በሰላም እና ደህንነት ግንባታ፣ በውጭ ግንኙነት እና ዲፕሎማሲ እንዲሁም በፍትህ እና አስተዳደር ዘርፎች የነበሩ አፈጻጸሞችን ዳስሷል። ተጠሪነቱ ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የሆነው የሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን የስራ አፈጻጸምም በሪፖርቱ ላይ ተካትቷል።የተወካዮች ምክር ቤት አባላት በሪፖርቱ ላይ ያላቸውን ጥያቄ በጽሁፍ አስገብተው ያጠናቀቁት ባለፈው ሳምንት ሐሙስ እንደሆነ የ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” የፓርላማ ምንጮች ገልጸዋል። Via Ethiopia Insider @Addis_Mereja